en
Feedback
ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Open in Telegram

እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sistu

Show more
Ethiopia2 732The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች (@riyit) is an active participant. Currently, the community unites 10 338 subscribers, ranking in the Other category and 2 732 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 338 subscribers.

According to the latest data from 04 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 285 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sist...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

10 338
Subscribers
+524 hours
+637 days
+28530 days
Posts Archive
#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_21 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መቅደላዊት ጋ የተዋወቅነው አንድ ናሆም የሚባልን ልጅ ትክክል ያልሆነ አረዳዱን ለመቀየር ጥሩ የሆነ አስተሳሰብ እንዲኖረው ለማድረግ ........." እያለ ሁሉንም ነገር እንዴት እንደተፈጠረ እንዴት እንደተግባቡና እንደወደደቸው አንድ በአንድ አስረድቶት ወደ ውጪ ለመሄድም ምክንያት የሆነኝ እሱ ነው! ግን ከእሷ ጋር ይቅርታ አውርጀ ከልቤ መልካም ነገርን ተመኝቼላት ነው የተለያየነው ።አሁን ላይ ለሷ ምንም አይነት ጥላቻ የለኝም። ቅሬታየን ሁሉ ያኔ ትቼው ነው የመጣሁት። አሁን ላይ የማስበው በዚህ በመጣሁበት ትምህርት ሀገሬን እንዴት ልጠቅም እንደምችል ማሰብ ራሴን ለተሻለ ነገር መዳረግ ነው። ይህን ብቻ ነው የማስበው ። ለመቅደላዊትም ቢሆን መልካም ነገር እንዲገጥማት ደስተኛ እንድትሆን ነው የምፈልግ ብዙ ጥሩ ነገሮች ይገባታል። ንፁህ ልብ ነው ያላት ሲበዛ ደግሞ ጠንካራ ነች ብዙ ነገሮችን ተቋቁማ ነው ያለችው ውበቷ መስመሯን ሊያስታት ያልቻለ የብዙወች አድናቆትና ወጀብ ያላናወጣት ጀልባ ናት። ከእርሷ ብዙ ነገሮችን ተምሪያለሁ!! ከዚህ ውጪ ምን ላስብ እችላለሁ " ብሎ ዝም አለ። " ጥሩ ነገር ግን አሁን ዋናው አንተን ማውራት የፈለኩበት ትልቁ ጉዳይ እና ሳታውቀው እንዳትቀር የፈለኩት በአሁኑ ስአት መቅደላዊት በትዝታ በፍቅር በፀፀት እየተሰቃየች መሆኑን ነው። ልጅቱ ምንም ራሷን ልትሆን አልቻለችም በትምህርቷም ቀንሳለች አእምሮዋም ልክ አይደለም በምንም ታዕምር ልናስተካክለው አልቻልንም ቤተሰቦቿም ስጋትና ጭንቀት ላይ ናቸው! የሆነ ነገር ባየችና በሰማች ቁጥር ወደ ራሷ ሕይወት እያስገባች ተቸግረናል። እና ይሄ ሁኔታዋ አስፈሪ ነው በዚሁ ከቀጠለች መቅደላዊትን እናጣታለን!! ስለዚህ ራሷን እንድትመልስ እርዳን " አለ ዶክተር ባሩክ አንገቱን ለትንሽ ሰከንዶች ያህል አቀረቀረና ከአንደገና ቀና በሎ " የሆነውን ነገር አላውቅም በእውነት መቅደላዊትን እዚህ እስክትደርስ አላያትም ነበር። ችግር የለውም አሁን ሁሉንም ማስተካከል እንችላለን እኔ በምችለው ነገር ሁሉ አለሁ! የፈለገ ምንም ብታደርግብኝ እንኳ ይሄ ለእርሷ አይገባትም!! ** የመርዕድና የናታኔም አንድ መሆን ግራ ያጋባቸው ተማሪወች ስጋ ያለበት ቦታን ለማግኘት እንደሚያነፈንፍ ጥንብ አንሳ ወሬ በማነፍነፍ ላይ ናቸው። " ቆይ እንዴት ? ምን አገናኝቷቸው ናሆም ምንስ አድርጓቸው? የጋራ ጠላታቸው ይሆናል? እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን እየተጠያየቁ ሁሉም በየፊናቸው የጥያቄወቻቸውን መልስ ለማግኘት ይባክኑ ጀመር። " አንዳንዴ ምንም ሳትሆን ምንም ሳይደርስብህ እንደዚህ አይነት ነገሮችን ለማድረግ አትደፍረም ናሆምም እነሱ ልክ በሆኑበትም ይሁን ባልሆኑበት መንገድ አግኝተውት ይሆናል። እንጅ ማንም ሰው ደርሶ ከመሬት ተነስቶ ጠላትህ አይሆንም። በእርግጠኝነት ናሆምም የሁለታቸው መንገድ ላይ ገብቷል ባይገባ ኖር በጠላትነት አይፈርጁትም ነበር።" አለ አንደኛው ወጣት " አይ እኔ ግን አይመስለኝም ናሆም በጭራሽ የሰው መንገድ ላይ ዝም ብሎ አይቆምም ምን አልባት የሚሄዱበት መንገድ እሱን ካልነካው በቀር እነሱ ጅ ደርሶ የሰው መንገድ ላይ የሚቆም ተራ እብድ አይደለም። ቢሆንም ግን ሁሉም የራሳቸው እውነት ይኖራቸዋል። " አለ ሌላኛው " ቢሆንም ይህ ለናሆም አይገባውም በራሱ ሕይወት ሲሰቃይ የኖረ ልጅ ነው እድሜ ለባሩክ ከዛ የጨለማ ሕይወት አስወጣው ። አሁን አጠገቡ ፍቅረኛው ብቻ ነች ያለችው። ምፅፅፅፅ ያሳዝናል የነ ናታኔም እጣ ደግሞ መታሰር አለዚያም ከጊቢ መባረር ነው።" አለ **** ዮርዳኖስ በተፈጠረው ነገር በጣም አዝና ተቀምጣለች እንዳትሄድ ሜላትን ፈራቻት እንዳትቀር ደግሞ ናሆም የሚታዘባት መሰላት። በዚህ ግራ በተጋባ ሁኔታ ላይ ሆና ስለ መቅደላዊት አሰበች። ስለ ባሩክም " ባሩክ እዛ ምን አልባት ሌላ ሕይወት ጀምሮ ቢሆንስ? ማን ያውቃል ጎበዝ ነው ቆንጆ ነው በዛ ላይ ከመቅደላዊት ጋር ተጣልቶ ነው የሄደው ስለዚህ ፍቅረኛ የማይዝበት ምንም ምክንያት አይኖርም ግን ይዞ ከሆነ መቅዲ በጣም ታዝናለች ያኔ ነው በጣም የምትጎዳው አታገግምም ጌታ ሆይ አደራህን አስተምረህ አስታርቃቸው!" አለችና እጆቿን በሀዘኔታና በልመና ወደላይ ዘረጋቻቸው! " ፍቅር ለሁሉም ነገር መፍትሔ ያበጃል። መጨረሻ ሳያዘጋጅ መጀመሪያ አያስቀጥልም! ዮርዳኖስ ስልኳን አንስታ እያወላወለች ስልኳን ታሽከረክራታለች። በዚህ ስሜት መሀል እያለች ኤሊያና ደወለችላት። ዮርዲ ስልኳን ስታየው ደነገጠች ።ፈራ ተባ እያለች አነሳችውና " አቤት ኤሊያ " ሰላም ዮርዳኖስ እንዴት ነሽ?" " ደህና እግዚአብሔር ይመስገን አንቺ እንዴት ነሽ" አለች ዮርዳኖስ አፀፋዋን ለመመለስ ያህል " እኔ ደህና ነኝ ትምህርት እንዴት ነው!" " ጥሩ ነው በጣም አንቺጋስ " አለች ዮርዳኖስ የዛሬው የኤሊያና ሁኔታ ባልተለመደ መልኩ አወራሯ ተቀይሮባት ከንፈሯን እየለጠጠች።" እኔ የደወልኩልሽ እንኳ አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነው!" አለች " እሽ ምን ችግር አለው ጠይቂኛ የምመልስልሽ ከሆነ ምን ችግር አለው " አለች ዮርዳኖስ አይኗን እያርገበገበች " እኔ ልጠይቅሽ የምፈልገው በ መቅደላዊት ዙሪያ ነው! ማለቴ መቅደላዊት አሁን ከማን ጋ ናት ?" አለች ዮርዳኖስ የጥያቄዋ ሁኔታ ስለገባት ፈጥና " ከማንም ጋ አይደለችም " አለች " ናታኔም ከሚባል ልጅ ጋር አልነበረችም ? " አለች ኤሊያና " እሱማ ነበረች ግን ባሩክ እያለ ነውኮ የተጣሉት!" አለች ዮርዳኖስ " እና በምን ሁኔታ ነች ሌላ ሰው ጋ ጀምራለች ?" የአሁኑ የኤሊያና ጥያቄ የመደወሏን ምክንያት ፍንትው አድርጎ ገለጠላት ለዮርዳኖስ ፈገግ አለችና " ኧረ በጭራሽ ለራሷ በባሩክ ናፍቆትና ፍቅር እየማቀቀች እንኳን ሌላ ሰው ልትለምድ" አለች ግን በሰላም ነው ይሄን ሁሉ የጠየቅሽኝ?" አለች መልሳ ዮርዳኖስ አንዳች ነገር እየጠረጠረች! " አይ ባሩክ.. Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 22♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_20 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ስካይፑ ላይ ያለውን ቁጥር አያቀውም ።ለማንሳትና ላለማንሳት ካመነታ በኋላ አንስቶ ሄድሴቱን ጆሮው ላይ ገጥሞ ቪዲዮ ላይ አደረገው። ባሩክ እጁን አፉ ላይ ጭኖ " ዶክ " አለ አቤት ባሩክ እንዴት ነህ?" አለ ዶክተር ፍፁም በሆነ ፈገግታ " ደህና ነኝ ዶክ " አለ አሁንም ድንጋጤው ሳይለቀው። " ጥሩ ትምህርቱስ እንዴት ነው? ነው ትተኸው ጥገኝነት ጠየክ?" ብሎ ሳቅ አለ። በአሁኑ የዶክተር አነጋገር ባሩክም ሳቅ አለና " ምን ጥገኝነት የሚጠይቁት እኮ ራሳቸው ነው ጥሩ ጥሩ ተማሪወቻችንን በግድ አሜሪካዊ ካልሆንክ የሚል ጥያቄ ያቀርባሉ በእኛ ጎበዞች ሀሳብ ጥገኛ ይሆናሉ። " አለ ባሩክ አሜሪካ ከሄደ በኋላ የታዘበውን በትንሹም ቢሆን እየተናገረ። " በእርግጥ ልክ ነህ እኔ እሽ ብየ ቢሆን አንዱ ሰለባ ነበርኹ ነገር ግን ግዴታየን አልተወጣሁም ብየ ተመልሸ ወደ አድዋ ዩኒቨርስቲ እንዳየኸኝ ተመልሼ በማገልገል ላይ እገኛለሁ!! " አለ ዶክተር " እውነት መልካም ነገርን እኮ ያደረከው ዶክ ለብዙዎች ምሳሌ መሆን የሚችል ላስተማረች ሀገር ውለታዋን መክፈል ማለት ይሄ ነው በዛ ላይ የመማር ትክክለኛ ትርጉሙ እንዲህ አይነት ውሳኔ ለመወሰን በጣም ይጠቅማል። እና በእርሰወ አሁን ሀገራችን ብዙ ታተርፋለች ኤርሰዎ ባያተርፉም በገንዘብ በኩል ያው እዚህ ሊከፈለዎት ከሚገባው በላይ ሳይሆን በታች በመሆኑ" አለ ባሩክ ይበልጥ በዶክተር ስብዕናና ድርጊያ ከልቡ ሀሴት እየተሰማው። " አወ ባሩክ አሁን ኢትዮጵያ ጥሩ ሀገር ሆናለች እኛ እየተማርን በነበረበት ወቅት ግን እጅግ አስቸጋሪ ነበር ቤተሰቦቻችን በሰላም ወደቤት እንድንመጣ ቤተክርስቲያን መስጅድ ተንበርክከው ነበር የሚፀልዩት። እጅግ መከራ ነበር ነገር ግን ይሄው ያሁሉ አልፎ ታሪክ ሆኖ እኛም እያወራነው ነው ለእናንተ።" አለ ዶክተር " እውነት የሚገርም ነው በዛ ጊዜ ጭራሽ የውጭ እድል ተገኝቶ ወደ ሀገር ቤት መመለስ የማይታለም ነው ግን ዶክ ሀገሬ ውለታዎን ትክፈለዎት ከማለት ውጪ ምንም ልል አልችልም " አለ ባሩክ ለዶክተሩ አድናቆትንና ክብርን እየለገሰ! " አዎ ውለታ ያለብን እኛ ነን ይቺ ሀገር እኛ ነዋሪወቿ ህዝቦቿ ካልተንከባከብናት ባዶ ትሆናለች። ምክንያቱም ሀገር ማለት ሰው ነው!" አለ ዶክተር ። ባሩክ ራሱን እንደመነቅነቅ አደረገና " ይቅርታ ዶክ እኔ ግን ሀገር ሰው ነው ብየ አላምንም ሀገር ሰው ቢሆን ኖሮ ሰው ለሀገር ባልሞተ ነበር። ለዚህ ደግሞ የአድዋ ጀግኖችን ሞት እንደ ትልቅ ምሳሌ መውሰድ እንችላለን። ታዲያ ሀገር ሰው ቢሆን ለምንድነው ተዋግተው ሞቱ??? አይደለም ሀገር ማለት ዳር ድንበር ነው። ሌላው ደግሞ የአሁኗ እስራኤል እንዴት እንደተመሰረተች መቼም ግልፅ ነው የተበታተኑት እስራኤላውያን ባሉበት ለምን ሀገር አልሆኑም ለምን አንድ ላይ ሆነው ሀገር መመስረት ፈለጉ? ይሄ ትልቅ መልስ ይመስለኛል። እኔም ሀገር ሰው ሳይሆን ሀገር ላይ የሚገኝ ልክ ምድሯ ላይ እንደበቀሉት እፀዋቶች እንደ አንደኛው ነው! አሁን እኛ አሜሪካ እየኖርን ነው በጣም ብዙ ግዛቶች ላይ ብዙ ኢትዮጵያዊያን አለን ነገር ግን ሀገራችን አይደለም።አሜሪካ ና ህዝቦቿም ይሄ ሀገራችን ነው ብንል አይሰሙንም። የሀገር ትርጉሙ ከሰው መሆንም በላይ ነው። ነገር ግን ሀገር በሰውም እንደምትመሰረትና እንደምትተዳደር አውቃለሁ። ከዛ ውጪ ባለ ትርጉም አልስማማም!" ብሎ የዶክተርን ምላሽ መጠበቅ ጀመረ። ዶክተር እጆቹን አገጩ ላይ አስደግፎ በጥሞና ሲያዳምጠው ከቆየ በኋላ ራሱን ነቀነቀና " እይታህ ሁልጊዜም ያስገርመኛል ሀሳቦችህ የሚዘገኑ ናቸው። የተሻልክ ያደርጉሀል እናም አንተ ከሁላችንም በላይ ትሆናለህ በርታ "" አለ ዶክተር በባሩክ የተራቀቀ ዕይታ አንገቱን በአድናቆት እያወዛወዘ።" እሽ ዶክ በጣም አመሰግናለሁ! " አለ " እሽ ስለ ፍቅርስ ምን አይነት እይታ አለህ?" አለ ዶክተር ባሩክ ፊቱ ባንዴ ቅይር አለ ደነገጠ። ዝም አለ፡ ዶክተር የጠየቀውን ያልሰማው መስሎት በድጋሚ ጠየቀው። ባሩክ ፊቱን እንደመጥረግ እያደረገ "ለእኔ ፍቅር ማለት እስካሁን በትክክል ልደርስበት ሊገባኝ ያልቻለ ትርጉም አልባ ምስጢር ነው። ፍቅር ስንፈልግ የምናገኘው ወይም የምንቀበለው ሳንፈልግ ደግሞ የምንተወው ተራ ስሜት አይደለም! ፍቅር ኢ አመክንዮ ነው! መቀበልን ሳይሆን መስጠትን ብቻ! ልክ ክርስቶስ በመስቀሉ ላይ እየተቸነከረ ይቅር በላቸው እንዳለው እየጠሉህ መውደድ እያሳደዱህ ማፍቅር መቻል ነው! በንፁህ ልብ መቀበል መቻል ማለት ነው። ነገር ግን እኛ አብዝሐኛውን ጊዜ አረዳዳችን ተዛንፎ ተንሸዋሮ ይታየኛል!! የወደደህን መውደድ የፈለግነውን ሰው ስላፈቀርን የፍቅር ትርጉም ገብቶናል ማለት አይደለም! ሳጠቃልለው ፍቅር ትልቅ ሀይል ነው!...." ልክ እንዳልከው ፍቅር ይቅርታ ማድረግ የሚችል ልብ መኖር የሚችል ኃይል ነው!" አለ ዶክተር " " በትክክል ዶክ ይቅርታ የማያደርግ ልብ በጭራሽ ፍቅር ሊኖረው አይችልም!" አለ ዶክተር ራሱን በአወንታዊ ከነቀነቀ ኋላ " መቼም ጨዋታን ጨዋታ ይወልዳል የሚባለው እውነት ነው! መቼም ተማሪየ ብቻ አይደለህም እንደ ወንድምህ ልታየኝ ይገባልና ስለ መቅደላዊት የሚሰማህን ንገረኝ!!! ምክንያቱም በአሁኑ ጊዜ እንዴት አየሆነች እንዳለች እያየሁ ነውና ጉዳዩን ከአንተ ደግሞ በይበልጥ ብሰማው" አለ ዶክተር " ባሩክ ስለ መቅደላዊት ከዶክተር ጋር ለማውራት እንደማፈር እያለ ተሽኮረመመ " አይዞህ እንደ ምክትል ፕሬዚዳንት ሳይሆን እንደ ትልቅ ወንድምህ የልብህን እንደምታማክረው ጓደኛ ልታየኝ ትችላለህ አትጨናነቅ " አለ ምቾት እንዲሰማው ። ባሩክም ሳቅ እያለ "እንደ ትልቅ ወንድሜ ልቆጥርህማ እንዴት እችላለሁ እሱማ ከባድ ነው በአንድ ጊዜ ነገር ግን ምንም ሳልሳቀቅ የተፈጠረውን እነግርሀለሁ!" አለ " አወ እኔም እሱን ነው የምፈልገው አየህ አንዳንዴ በመሀላችን ያለው የኃላፊነት ና የእድሜ ተራራ ይመስለኛል እንዳንግባባ የሚያደርገን ነገር ግን እሱ ከማፈራራት ባሻገር ችግሮችን ወርዶ አንድ ሆኖ ለመፍታት ያስቸግራል። እሱ እንዲሆን ደግሞ አልፈልግም! ለዛ ነው እንደ ወንድምህ ቁጠረኝ ያልኩህ " አለ ዶክተር " ገብቶኛል ዶክ ችግር የለውም እ ም መቅደላዊት ጋ......... Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 21♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_19 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ በአምባዬ ጌታነህ "ግን ፈጣሪ ምን አድርጌው ነው እንደዚህ የሚያሰቃየኝ " አለች መቅደላዊት የተኛውን ናሆም እያየች። " መቅዲ በአንች ስህተት አይደለምኮ ለምንድነው እንዲህ የምትሆኚው የተፈጠሩትን ነገሮች ወደራስሽ እያዞርሽማ እንዲህ አትሁኝ የኔ ቆንጆ ሁሉም በእኔ ጥፋት ነው የሆነው በአጉል ቅናት ነው በማይረባ ስሜት ነው ለዚህ የዳረኩት" አለች ሜላት። ናሆም ህመሙ በጣም ያደከመው ይመስላል። ከወደ ግራ ጎኑ ህመም በጣም ይሰማዋል! ለመገላበጥ አስቸግሮታል። ከእርሱ የህመም ስሜት እኩል አይኖቻቸውን በህመም ስሜት ይጨፈግጋሉ መቅደላዊት እና ሜላት። " እንግዲህ አንዳንዴ እንደዚህ መቅመስም አለ!" አለ ናሆም ፈገግ ለማለት እየሞከረ። ሁለቱም ግን አፀፋውን አልመለሱም። በሀዘኔታ ይተያያሉ " በቃ እርሱት ያለፈው ዘና በሉ እንጅ እንዴ እዝን የተቀመጣችሁ እኮ ነው የምትመስሉት አንዴ ያለፈው አልፏል የሆነውም ሆኗል። አሁን የሚያሳስብ ነገር የለም ። ከሚገርማችሁ አንድም ቀን ሰው የሚመታኝ አይመስለኝም ነበር። ነገር ግን ይሄው በተቃራኒው ለወጌሻ እንኳ እንዳልሆን ሆኜ ታሸሁ! " በማለት በድጋሚ ለመቅለድ ሞከረ። በዚህን ጊዜ ሜላት ዝም ብላ በስስት ስትመለከተው ከቆየች በኋላ " ሁሉም ነገር የኔ ጥፋት ነው። ልሰማህ ይገባ ነበር ላምንህ ይገባ ነበር። " አለች፡ ናሆም በደንብ ሲመለከታት የጥፋተኝነት ስሜት እንዳለባት አወቀና ። ሳቅ እያለ " አሁን ያልሻትን ቢሮ ስገባ በማመልከቻ ፅፈሽ ታስገቢልኛለሽ " አለ፡ ሜላት ገብቷታል መቅደላዊትም ምቾት እንዲሰማቸው እና እንዳይጨናነቁ ፈልጎ እያደረገ እነደሆነ ገብቷታል !! ሜላት ተነስታ ጉንጩን ሳመችው። ናሆም አይኖቹን እንደመጨፈን አደረጎ " እህ ይሄን ሁሉ ሀገር አቋርጠሽ መጥተሽ ምነው ጉንጨን ስመሽ ተመለሽ? ትንሽ አለፍ አትይም ነበር!" አለ ፡ ሜላት ሳትፈልግ ሳቀችና " ያማ ለበሽተኛ አይመከርም " አለች። " ኤጭ አሁን ገና በሽታየ አስጠላኝ መቼ እንደምነቃ ጓጓሁ" አለ፡ መቅደላዊት ከት ብላ ሳቀች ሜላትም ተከተለቻት ናሆምም አጀባቸው። በራሱ ጥረት ምንም እንዳልሆነና እንዳመመው ላለማሳወቅ እንዳይጨናነቁ ያደረገው ጥረት ከብዙ በጥቂቱ ተሳክቶለታል ናሆም! ** በብዙ አጀብና ግርምታ አለም ላይ ስሟ የገነነችው ልዕለ ሀያል ሀገሯ አሜሪካ በሰማይ ጠቀስ ህንፃወቿ ታጅባ የስልጣኔዋን መዳረሻ ለፈጣሪ እያሳየች ትመስላለች። አሜሪካ አሁን ለደረሰችበት ስልጣኔ የነ ፕሬዚዳንት ጆኖፍ ኬኔዲ የነ ፕሬዚዳንት ቴወዶ ሩዝቤልት የወቅቱ ዲፕሎማት በተለይ በኢትዮጵያ በኩል የነበረውን ግንኙነት በጥሩ ወዳጅነት እንዲቀጥልና ከወቅቱ ከኢትዮጵያ ንጉስ ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ጋር ጥሩ ወዳጅነት ለመመስረት የኳተነው ሮበርት ስኪነር አሻራ ጎልቶ ይታያል። ነገር ግን ከሁሉም የስፓኒሽን ጦርነት ድል ማደረጓና ነፃነቷን ማወጇ ነው። ይህን ሁሉ ለራሱ እያወራ በኒዮርክ 42 street ጎደና ሞቅ ያለ ጃኬቱን ለብሶ እጆቹን ኪሱ ላይ አስገብቶ ቀስ ብሎ እየተንቆራጠጠ ግራ ቀኙን እያማተረ ትዝታና ናፍቆት እንደ ሊቢያ በረሃ ፅጌሬዳ ያጠነዘለው የሀበሻ መልከ-ገፅ ያለው ወጣት ቀስ እያለ ይራመዳል። አይኖቹ በአስተውሎትና በንቃት በየ ደቂቃው በመንገዱ ህዳግ ባሉ ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ላይ እየላከ ይመልሳል።በየመንገድ ዳሩ የሚርመሰመሰው ነጭ መኪና ድንገት ፊት ለፊቱ ከአንድ ጥቁር ጋ ተገጣጠመ ! ጥቁሩ ሰውም ባሩክን በአርምሞ ከተመለከተ በኋላ " ኢትዮጵያ ነህ አይደል?" አለ። ባሩክ ሰውየው በተናገረው የአማርኛ ሰዋሰው ስህተት እንደመሳቅ እያለ " አወ ኢትዮጵያዊ ነኝ " አለ! ። "of course! Defnetly ma predict is right !" አለ ጥቁሩ ፍፁም በሆነ ኩራት ባሩክ እንደመገረም ብሎ " how you predict am ethiopian ? is there any indication ?" አለ ። ጥቁሩ ተቀበለና " because all Ethiopian has the same appearance and the same psychologycal. your walking your talking freedom will also same other Ethiopian .any way am sengus " ብሎ እጁን ወደ ባሩክ ዘረጋ " baruk " አለው ባሩክ የሰውየው ሁኔታ እያስደነቀው። " nice meet you baruk!" አለና ትቶት እብስ አለ። " ምን አይነት እብድ የሆነ ሰው ነው "ብሎ ሳቅ አለና ባሩክ አግራሞቱንም መደነቁንም ተወና " ለነገሩ በአድዋ የአርበኞች ድል ፋና ወጊነት መላው ጥቁር አይደለም መላው ነጭ ባያወቀን ነበር የሚገርመው! አያቶቻችን ድል ባደረጓቸው ነጮች የልጅ ልጅ እንድንለይ ደማቅ የቀለም ማህተብ አስረው አትመውብናልና እኛን በቀላሉ አለመለየት አይችሉም! " አለና የእጅ ስአቱን ተመለከተ በአሜሪካ የስአት አቆጣጠር አመሻሽ 11:30 ይላል። የእርምጃውን ፍጥነት እየጨመረ! ከራሱ ጋር እንዲህ በማለት አወራ " time is the best arbiter ፣ ጊዜ የማያዳላ ዳኛ ነው " ብሏል ፊዮዲዬር ዶስቶቭስኪ። " እውነት ነው ጊዜ ለሁሉም እኩል እንጅ ለአንደኛው በዝቶ ለአንደኛው አያንስም።አያዳላም አያሳንስም!!!! በፍጥነት እየገሰገሰ ቤቱ ሲገባ ስካይፑ ላይ ሰው እየደወለ እንደሆነ ሰምቶ ወደ ማውሪያ ክፍሉ አመራ!! ይቀጥላል ............... አሁን ከዚህ በኋላ እናንተ ሼር በማድረግ እኔ ደግሞ " መቅደላዊትን ባለማቋረጥ " ቃል ተገባብተን ቻናሏን ትልቅና ተደራሽነቷ ሰፋ ያለ እንድትሆን የበኩላችንን እንወጣ ካነበባችሁ በኋላ ኮንታክታችሁ ላሉ ጓደኛኞቻችሁ ቤተሰቦቻችሁ አጋሩ Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 20♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_18 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ፊትለፊቷ የሚመጣባትን ችግር እያሰበች መፍትሔውን ማብሰልሰል ያዘችና ስለ ባሩክ እንዲህ አለች። " ባሩክ ግን የት ነው ያለኸው? ምን እያደረክ ነው? ቆይ ግን አልናፈኩህም? " አለች በስስት መቅደላዊት ባሩክ አጠገቧ መጥቶ እያወራት እንዳለ እስኪመስላት ድረስ! በምናቧ ከአጠገቧ ባሩክን አስቀምጣ እየሄደች ታወራዋለች። ልታቅፈውም ትፈልጋለች! ግን ደግሞ ተናዳበታለችም በንደዚህ አይነት ስሜት ኤየሄደች ወደ ብሎክ አካባቢ ስትደርስ። የናሆምን መመታት ሁሉም ተማሪ እያወራበት ሴቶች ብሎክም እንደጉድ ተዛምቶ የሷም ጀሮ ላይ በሌሎች የመወያያ ርዕስ መልክ ደረሳት " ምንም አላስተረፈውም እኮ " " ኧረ ጭራሽ ደምም እየፈሰሰው ነበር!" " ኧረ እንጃ መነሳት እኮ አልቻለም " " ለሁለት ነው አሉ ደግሞ የደበደቡት " " ሲያሰጠሉ እንዴት ሁለት ሆነው ይመቱታል " ናሆም ግን ጅግና ነው እሱም መትቷቸዋል አሉ " " አይ ቢሆንም ግን ናሆም ብቻውን መሄድ አልነበረበትም " " እህ እሱ በምን ያውቃል ለሁለት እንደሚደበድቡት!' " ግን ናታኔም አልመታውም ይባላል " " አወ እሱማ አልመታውም እንደውም መርዕድን ገልግሎታል እንጅማ ይሄኔ ሆስፒታልማ ባልደረሰ ነበር።" " ግን አያሳዝንም ናሆም ይሄ ሁሉ የደረሰበት ለመቅደላዊት ሲል እኮ ነው " " ኧረ አይደለም ለራሱ ነው በሜላት መጥተውበት " " እንጃ አይመስለኝም ግን ሜላትን በአሁን ስአት ማፍቀሩ ከባለፈው ሂወቱ የተማረና የተቀየረ ለመሆኑ ምስክር ነው!" " ቢሆንም አሁንም ገና አልተቀየረም አንዳንድ ነገሮቹ እንደበፊቱ ናቸው" " ኧረ ያ ችግር የለውም አሁን በዳነ እንጅ የባህሪው ነገር እንኳ ችግር የለም ይደርሳል።" " እሽ አሁን በምን ሁኔታ ላይ ነው የሚገኘው?" " እንጃ ብቻ ግን ትንሽ ራሱን ሳይስት አይቀርም!" " እንደው ሜላት ምን ሆና ይሆን የምታሳዝነው እሷ ናት በእሱ ጉዳይ በጣም ተሰቃየች! " እየተባባሉ አንድ ጊዜ መልካሙን አንድ ጊዜ መጥፎውን እተነጋገሩ ውጭ ላይ ሆነዋል ይህን ሁሉ ስትሰማ የነበረችው መቅደላዊት ራሷን ይዛ የተወሰነ ተቀመጠችና እየዞረባት ተነስታ ቀስ ብላ ወደ ሆስፒታል ሄደች። ውጭ ላይ ከተረኞች ዶክተሮች በቀር ማንም የለም። ዶክተሮቹ ብቻ ናቸው ከአንደኛው ክፍል ወደ አንደኛው ክፍል እየተዘዋወሩ ያሉት ራሷን በሁለት እጇ ይዛ ቀስ እያለች ወደ ድንገተኛ ክፍል ስትገባ ሜላትን መግቢያ በሩ ላይ አገኛቻት። መቅደላዊት ምንም ሳትል የሜላትን አንገት አቅፋ ማልቀስ ጀመረች ። ሜላትም እንባዋ ኩልል ብሎ በጉንጮቿ እየወረደ ይበልጥ መቅደላዊት እንዳታለቅስና እንዳትረበሽ በሚያባብል መልኩ " አይዞሽ ደህና ነው ብዙም አልጎዱትም እግዚአብሔር ሲረዳው " አለች ሜላት ።መቅደላዊት አልመለሰችላትም ዝም ብላ ታለቅሳለች። የምታለቅሰው ግን በናሆም ጉዳት ምስል የሚናፍቃትን ባሩክን አስታውሳ ነው! ** የተማሪ ተወካዮች መርዕድን ተከታትለው ያዙት ናታኔምንም ከዶርሙ አስወጥተው በፅህፈት ቤታቸው እያነጋገሯቸው ነው።" ለምንድነው የደበደባችሁት? ምክንያታችሁ ምንድነው? " አለ እስክርቢቶውን እያነሳ " ሊመታኝ ሲል ነው የተከላከልኩት " አለ መርዕድ " ማክዶም በመርዕድ መልስ ፈገግ አለና " እሽ ናታኔምስ ?" አለ " እኔ እኮ ምንም ያደረኩት ነገር የለም " አለ " ሁለታችሁም ያደረጋችሁት ነገር የለም ልመናችሁ?" አላቸውና " አሁን የሰራችሁት ስራ በጣም ከባድ ቅጣት እንደሚያስቀጣ አታውቁም ? እሽ ናታኔምስ ፍሬሽ ስለሆንክ አታውቅም እንበል አንተ ስ ተመርቀህ ማስተሬስ ጀምረሀል የዚህን ዩኒቨርስቲ ህግ አታውቅም ? " አለ መርዕድ አልመለሰለትም! ማክዶም የተለያዩ ጥያቄወችን ከጠየቃቸው በኋላ ጥበቃ አስጠርቶ ሁለቱንም ዩኒቨርስቲው ውስጥ ካለ ማቆያ ክፍል እንዲወሰዱ አደረገ! **** ናሆም ካሸለበው የድካም እንቅልፍ ቀና ሲል ሜላትን አያት ፍዝዝ ብላ ስትመለከተው በናፍቆትና በስስት በርህራሄ ና በሃዘኔታ ።ፈገግ አለላት አጠገቧ አንገቷን ያቀረቀረች ልጅ አየ ነገርግን ገጿን ስላላየው ማንነቷ ሊገለፅለት አልቻለም። ሜላት ወደ ናሆም ለመጠጋት እንቅስቃሴ ስትጀምር መቅደላዊት ካቀረቀረችበት ቀና አለች። ናሆም ነቅቷልአይኖቿ ላይ የተቋጠሩት እንባወቿ በሳቀው ፈገግታዋ ጎን በጎንጮቿ ተንከባለሉ። ናሆም ጋር አይን ለአይን ተጋጩ። ናሆም መቅደላዊትን ሲያያት ተረበሸ ፊቱ በአንዴ ተቀየረ ፊቱን ወደ ግራ በኩል አዞረና አለቀሰ! መቅደላዊት ግራ ተጋባች " ለምንድነው የዞረው መምጣት አልነበረብኝ ይሆን እንዴ ? በእኔ ስለተመታ እኔን አኩርፎኝ ይሆን ?" ራሷን መጠየቅ ጀመረች ።ናሆም አይኑን ከጠራረጋ በኋላ መቅደላዊትን ወደ አጠገቡ እንድትመጣ በእጁ ምልክት ሰጣት ሜላትም የእጁን ምልክት ተከትላ መቅደላዊትን በአይኗ እንድትመጣ ጋበዘቻት ። ሄደች መቅደላዊትን አቀፋት " እንደ እውነቱ ለመናገር ለአንቺ እንዲህ ሆኜ መታየት ስለማልፈልግ እንድትመጭ አልፈለኩም ነበር። ምክንያቱም እንድታዝኝ አልፈልግም የምታዝኝበት ብቻ ይበቃሻል። አንድ የምነግርሽ ነገር እንዲህ የሆንኩት በአንቺ ምክንያት እንዳልሆነ ነው እኔ እንደ አንቺ እና እንደ ባሩክ ለሌላ ሰው መስዋዕት መሆን አልችልም እንደዛ እንድሆን አልተፈጠርኩም። እናም በፍጹም የጥፋተኝነት ስሜት እንዳይሰማሽ በሜሊ መጥተውብኝ ነው እሷን ሊነጥቁኝ ስለሞከሩ ነው። በቃ ግን ችግር የለም አንድ ቀን ዋጋውን እመልስለታለሁ " አለ ናሆም የመቅደላዊትን እጅ እያሻሸ " በቃ ተዋቸው ናሆም ለእኔ ስትል ናታኔም ያለበት ነገር ከችግር ውጪ ሌላ ነገር አየተርፍም እባክህ ተዋቸው " መቅደላዊት ተማፀነችው " እባክሽ ሜሊ ተው በይው " እሷንም ለመነቻት " እሽ እኮ አይለኝም መቅዲ " አለች ሜላት ። " ቃል እገባላችኋለሁ ከዚህ በኋላ ምንመ አይነት ችግር አልፈጥርም " አለ ናሆም የመቅደላዊትነና የሜላትን እጅ ጨብጦ Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 19♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_17 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መርዕድ የሚያየውን ማመን አቃተው ። ናታኔም መርዕድን በሀፍረት እየተሸማቀቀ ተመለከተው! ናሆም ናታኔምን በንቀት አየውና ፊት ለፊቱ ላይ ካለ መሬት ተፋበት። መርዕድ ደንግጧል ግን ድንጋጤውን ላለማሳወቅ በኩራት ተጀብኖ የናሆምን እንቅስቃሴ በጥሞና ይከታተላል። ናሆም ስልኩን ቀስ አድርጎ ከኪሱ አወጣና ደወለ። ሜላት ስልኩን አነሳችውና " ምን ልትለኝ ነው ምን እንዳምንህ ፈልገህ ? እንዳታስበው ከዚህ በኋላ አላምንህም .... ናሆም አቋርጣት " አትመኝኝ ግን አሁን ለሁሉም ነገር መልስ የምታገኝበት አጋጣሚ ነው ስለዚህ አሁኑኑ ገብርየ ዋርካ ነይ ለተናገርሽኝ ነገር በቂ ምላሽ ታገኝበታለሽ አሁኑኑ " ብሎ ስልኩን ጆሮዋ ላይ ዘጋው " ወንድሜ መርዕድ እንደ ሴት ልጅ እንደዚህ ዙሪያውን ነገር ከምትተበትብና ነገር ከምትሸርብ ፊት ለፊት ብትጋፈጠኝ ምን ያህል ደስ ብሎኝ በተፋለምኩህ! ለስሙ ተምረህ ተመርቀሀል ነገር ግን አስተሳሰብህ ካልተማሩትም በታች ነው የተማርከውን ጊዜ ሳስብ ይበልጥ አሳዘንከኝ። እኔ ወንድነህ ብየ ልጣላህ ነበር ሀሳቤ ነገር ግን ወንድ እንዳልሆንክ አረጋገጥኩ። በጣም ሲበዛ ቀሽም ነህ ስላላወክ ነው እንጅ በሰው ሀዘን ደስታ አይመሰረትም ሰዋዊ ባህሪ ካለህ " በቃህ! አለና ዘሎ በቦክስ ነረተው! ደገመው " አንተ ነህ እኔን አፍህን ሞልተህ የምትናገረኝ " አለና ደግሞ መታው ናሆምን መሬት ላይ ዘረረው። ናታኔም በድንጋጤ የሚሆነው ነገር በህልሙ የሚሆን እስኪመስለው ድረስ ደንዝዞ ቆመ። ናሆምን እታች አድርጎ መርዕድ አጣደፈው " አንተ ነህ እኮ በስሜቷ ላይ ስትቀልድ የነበረው ደግሞ ከአንተ ብሶ እኔን ስለጭካኔ ልትናገረኝ ትፈልጋለህ? አንተ እረኛ ከመቼ ወዲህ ነው ከየት ያለህን ለሴት ልጅ ክብር እንዳለህ የምታስመስለው? ደደብ !" ናታኔም ሁኔታውን ሲመለከት ከቆየ በኋላ መንተፍረቱን ደመነፍሱን ተከመረበት መርዕድ ናታኔምን " ወደዛ ሂድ "ከለና አሸቀንጥሮ ጣለው ናሆም ትንፋሽ ያጠረው ይመስላል። ናታኔም ከወደቀበት ከእንደገና ተነስቶ መርዕድን ገላገለው "ያምሀል? " አለው " ተወኝ ናቲ ልግደለው "ብሎ ተገለገለ። ናሆም ከተኛበት አልተነሳም አፉ ላይ ደም ይተፋል። በዚህን ጊዜ ሜላት ደረሰች ። ራሷን ይዞ ወደ ተኛው ናሆም ተንደረደረችና ከአንገቱ ቀና አደረገችው አንገቱ ተዝለፈለፈባት። መርዕድንና ናታኔምን ቃኘቻቸው። ሁለቱም ትተዋት ሄዱ " ኧረ እርዱኝ " ሜላት በለቅሶ ጮኸች እነ መርዕድ የሜላትን ጩኸትና ተማፅኖ እንደገደል ማሚቶ ከማስተጋባት በቀር ሊረዷት አልፈቀዱም። ናሆም የተከደኑ አይኖቹን እንደምንም ከፈታየው ከአፋ ያለውን ደም ተፋውና ለመቃናት ሞከረ ነገር ግን እምቢ አለው ። ሜላት አቀፈችው " ምንድን ነው የሆንክብኝ ምንድን ነው ያደረጉህ የኔ ፍቅር እባክህን ቀና በል" አለች እያለቀሰች ። የማይታወቁ ልጆች ደረሱላትና ናሆምን ደግፈው ወደ ዩኒቨርስቲው ሆስፒታል ሄዱ ። ሜላት አለቀሰች " እኔ እኮ ምንም አልተቀየምኩህም ከፍቶኝ እኮ ነው አምንሀለሁ እኮ ለምን እስከዚህ ድረስ ትሆናለህ እኔ ሳትመታ እኮ አምንሀለሁ " ከዚህም ከዚያም ቀባጠረች። በምን ቁጭቷን መግለፅ እንዳለባት ጠፋባት። ብቻ ዝም ብላ ታለቅሳለች ሊሞት አፋፍ ላይ ያለ ቅድም የደወለላት የስንብት ንግግሩ መሰላት። ከእንደገና ታማትባለች ለቅሶዋን አታቆምም ከትንሽ ቆይታ በኋላ የናሆም መመታት እና ሆስፒታል መግባት ጊቢውን አዳረሰው ናሆምን የሚያውቁት ልጆች የክላሱ ተማሪዎች ወዲያው መጡ። ግማሾቹ የናሆም አኳኋን እና የሠደገበት ተፅዕኖ እንዳለበት የሚያምኑና የሚያሳዝናቸው። በደበደበው ልጅ በጣም ተበሳጩ " እንዴት ሊደበድበው ይችላል ምን አድርጎት ምን አይነት የሚያሳዝን ልጅ ነው! " እየተባባሉ ትንሽ ቆዩ ወዲያው የተማሪ ተወካዮች በመምጣታቸው የተሰበሰቡት ተማሪዎች ወደየ ማደሪያ ህንፃወቻቸው እንዲመለሱ አስተባበሩ። " ለማዘንና ለማልቀስ የተፈጠረች ልጅ ምን ይሻላታል ገና ገና ለመደሰት ስትጀምር እንደዚህ አይነት ነገር ተፈጠረባት" አለ አንድ ልጅ የሜላትን ሁኔታ በአርምሞ የተመለከተ ልጅ " ማነው ከናሆም ጋ ያለው?" ብሎ አይኑን ከተደረደሩት ተማሪዎች ላይ ላከ ሁሉም ወደ ሜላት ፊታቸውን አዞሩ። ዶክተሩ እንደሚጠራት ነገራት አጠገቧ የተቀመጠ ልጅ። በፍጥነት ተነሳችና ከሩጫ ባልተናነሰ ርምጃ ዶክተሩ ጋ ደረሰችና ተስገብግባ " ምን ሆነ ዶክተር ደሆና ነው አይደል ?" አለች " አይዞሽ ተረጋጊ አሁን በጥሩ ጤንነት ላይ ነው። ትንሽ ተሽሎታል! ትንሽ የተማታው ቦታ ላይ እብጠት አለ እንጅ ከዛ ውጪ ምንም ነገር የተለየ ከባድ ነገር የለውም አብረሽኝ መግባት ትችያለሽ" አለ " ኡፍፍፍ ፈጣሪየ ሆይ ተመስገን " አለችና ፈጥና ተከተለችው ። *** መቅደላዊት ላይብረሪ በጥሩ ሙድ ካነበበች በኋላ ወደ ሌሊት ስድስት ስአት ሊይ ከላይብረሪ ወጥታ ወደ ዶርም እየሄደች በየመንገዱ ባሩክን እያሰበችው ትሄዳለች ። እርጋታውንና አወራሩን እያቀያየረች እያንዳንዱን ድርጊቶች እያመላለሰች ከሄደች በኋላ ፊትለፊቷ........ Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 18♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_16 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ አይኖቹ ተርገበገቡ እግሮቹ ተንቀጠቀጡ ። ልቡ በፍርሀት ራደ የሆነ ነገር ሊናገር ፈልጎ ነገር ግን ምን መናገር እንዳለበት ግራ ገባው። አፉ ተርበተበተ። " ጀግና ነህ ጥሩ ስራ ነዋ የምታቅደው! " አለና ናሆም ራሱን ነቀነቀ አፉን እጨራመመ ወደ ናታኔም ተራመደ። ሃሃሃሃሃ በረጅሙ ሳቀና " እሽ ናቲ በል ማንን ነበር እንዲህ በጥሩ ምስጢር የምታወራው ማን ጋር ነበር በእኔ ሕይወት ስትደራደር የነበረው? አንተ በቃ ስራህ ሁሉ ተንኮል ነው የሰው ሕይወት ማበላሸት ነው ይሄው የሌላ ሕይወት ልታበላሽ ነው ደግሞ ያንተ ደስታ ይሄ ነው? ንገረኝ እስኪ ወንድሜ ናቲ ከመቼ ወዲህ ነው እስኪ እንደዚህ ስብዕና የለሽ የሆንከው ምን ሆነህ ነው እንደዚህ ... ማ ማለቴ አል. አልገባኝም እኔ እኮ ግራ ገባኝ " አለ ናሆም በአግራሞት እየተመለከተው ። ናታኔም ዝም " አናግረኝ እንጅ ቢያንስኮ ጓደኛህ ነበርኩ አሁን ለምን እንደዚህ ልትሆን ቻልክ ?" ናታኔም አፉን ብቻ እያንቀሳቀሰ ዝም አለ። ናሆም ይበልጥ በዝምታው ተናደደ። ናሆም " በል አሁን አብሮህ ማን እንዳለ ብቻ ንገረኝ ካልነገርከኝ እመነኝ አሁንስ ማንም አያስጥልህም አንቅሀለሁ " አለ አሁንም ዝም!" መልስልኝ! አለና ዘሎ ሲከመርበት " በቃ መርዕድ ነው " አለ " ምን ?" አለ ናሆም ከናታኔም ራሱን እያላቀቀ " መርዕድ "በድጋሚ ተናገረ በሚያሳዝን ድምፅ " እኮ መርዕድ ይሄ አብሮህ የሚሄደው የአንተ ጓደኛ ?" አለ ናሆም " አዎ " አለ ናታኔም " ቆይ እሱ ከእኔ ምንድን ፈልጎ ነው? ከአንተ ጋር የሚሰራው?" አለ ናሆም " አላውቅም !" ናታኔም መለሰለት " አላውቅም አትበለኝ! በደንብ ነው የምታውቀው ናታኔም እልኬን አታስጨርሰኝ " ናሆም ጮኸ። " በናትህ ልለምንህ በቃ በደንብ አትጠይቀኝ ናሆም ከዚህ በኋላ አልደርስብህም !" አለ ናታኔም " ኧረ ባክህ ልመንህ አትደርስብኝም አትቀልድ አሁን ዝም ብለህ ለጠየኩህ ጥያቄ ብቻ መልስ ስጠኝ!!!" አለ " እሽ እነግርሃለሁ " ሲል የናታኔም ስልክ ጠራ አየው የመርዕድ ስልክ ነው ባለየ ዝም ብሎ ቀና ሲል " ለምንድን ነው ማታነሳው? በቃ እኔ ላንሳልህ እንዴ " ብሎ እጁን ሲልክ " ኧረ አነሳዋለሁ " አለና አነሳው ናሆም በእጅ ምልክት ላውድ እንዲያደርገው ነገረው። ላውድ አደረገው " እሽ ልመጣ ነው የት አካባቢ እንገናኝ?" አለ መርዕድ ናታኔም እ እ ተንተባተበ ናሆም በአፉ እንቅስቃሴ የት እንደሚገናኙ ነገረው " እ በቃ የተለመደው ቦታ ዋርካው ጋ " አለ ናታኔም " እሽ እመጣለሁ ግን ደህና ነሃ?" አለ መርዕድ ነገር ግን አወራሩ በሰላም እንዳልሆነ ስለተረዳ ደግሞ ደጋግሞ ስለ ደህንነቱ ጠየቀው የናታኔም ምላሽ ግን አንድ ነው " ደህና ነኝ " ናሆምና ናታኔም ህንፃውን ፊትና ኋላ ሌባ ና ፖሊስ ሆነው ወረዱ ። *** እንደተቆረጠች ጨረቃ ለምሽቱ ውበት አንደኛውን ቦታ ብች በውበቷ አድምቃዋለች የለበሰችው ሀገር በቀል ጥልፍ ቀሚስ የውበቷን ድብቅ ድካ ገልጦታል። አካሄዷ ትርጉም አለው እርምጃወቿ ሌላ የተመልካች የጥያቄና የአድናቆት መልዕክትን ይዟል። ከቀሚሷ አፈትልኮ የወጣው ባቷ ሎሚ መስሎ ተመልካችን አፉን አስከድኗ በአርምሞ አስደምሞታል። አይኖቿ ጥርት ያሉ ሆነው ቦግ ቦግ ሲሉ ሌላ አጥቢያ ኮከብ ለመግባት የሚታገል ይመስላል። ፀጉሯን እነደነገሩ ለቃዋለች። " ዋው!" አለ አንደኛው ጨበሬ ልጅ ሜራቁን እየዋጠ ። " ቆይ ይቺ መቅደላዊት አይደለች?" አለ ሌላኛው በግርምት ለረጅም ስአት አብረውት ሲመለከቱ ከነበሩ ጓደኞቹ ጋር ሲያያት ቆይቶ " አዎ " ሌላኛው " እኮ ምን አግኝታ ነው አሁን እንደዚህ ደግሞ ሆና የመጣችብን? " አለ " ለምን ራሷን አጠይቃትም ነፍሴ ያው እንደዛ ያስነፈረቃት ባሏ ፈላስፋው ድንገት ከፍልስፍናው የእንቅልፍ አለም ሲነቃ እስኪ ደግሞ እሽ ልበላትና ልፈላሰፍ 'ብሎ ለመፈላሰፍ እሽ ብሏት ይሆናላ" አለ " ኧረ አይመስለኝም ዲዮጋን እኮ የሆነ ግትር ነገር ነው ሲበዛ በጣም ችግር ያለበት ሰው ነው። በዛ ላይ እስካሁን ምንም እንዳለወሩ ነው የሰማሁት!" አለ ሌላኛው " ወይኔ ግን እንደዚህ ቆንጆ ናት ወይስ አይኔ ነው ቆንጆ ያደረጋት " አለ በመጀመሪያ ዋው ብሎ ምራቁን የዋጠው ጨበሬ ልጅ " ባክህ አንተ ደግሞ ችግር አለብህ ምን እንደ አዲስ ትሆናለህ ስንት ጊዜ ነው የምታደንቃት ?" አለው አጠገቡ ያለው ጓደኛው " ከምር ገርሞኝ እኮ ነው የሌለ እኮ ነው የምትከይፈው ፈረሰኛውን!" አለ ጨበሬው ልጅ ፀጉረን እያፍተለተለ ።በዚህን ጊዜ መቅደላዊት ከአይናቸው እየራቀች ወደ ምንሊክ ቤተመፅሀፍት በኩል ሄደች " አሚገርም ነው ትምህርት ትታ ማሰብ ትታ መብላት ትታ ብቻ ሁሉን ነገር ትታኮ በቃ ስራዋ ባሩክን ማሰብና ማልቀስ ብቻ ነበርኮ " አለ እነሱ ሲያወሩ ዝም ብሎ ሲሰማቸው የነበረ ሌላኛው የቡድኑ አካል። እንዲህ ተማሪውን እያስገረመችና እያስተዛዘበች መቅደላዊት እንደስከዚህ ቀደሙ ውብና ቆንጆ ሆና ለማንበብ ሁሌም ወደ ምታነብበት ላይብረሪ ገባች። ተማሪዎች ስለመቅደላዊት ድንገተኛ ድርጊት እያወሩ አመሹ። መቅደላዊት ፍፁም በሆነ ፈገግታ ና ደስታ የምታነበውን መፅሐፏን ገለጠች። መፅሐፉን ስትገልፀው ድንገት አእምሮዋ አቃጨለ " ባሩክ " ብላም ተጣራች። ከዛ በመጣራቷ እንደመሸማቀቅ ብላ ከእንደገና በድንጋጤ የዘጋችውን መፅሐፏን ገለጠች **** መርዕድ ገብርየ ዋርካ ቀድሞ ተገኝቶ ናታኔምን እየጠበቀ ነው። በናታኔም አነጋገር ግን የሆነ ያልነገረው ነገር እንዳለ በጥርጣሬ ና ግራ በተጋባ አረዳድ እያብሰለሰለው ነው። ናታኔም አልፎ አልፎ ዘወር እያለ ናሆም እንደሚከተለውና እንደማይከተለው ያረጋግጣል። ናሆም ደግሞ በኤልህና በፍጥነት ናታኔምን እየተከተለው ነው! Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 17♥️ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_15 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናሆም ከተቀመጠበት ተነስቶ ሜላትን ተከተላትና ሊያስቆማት ፈለገ ሊተዋትም ፈለገ ብቻ ልቡ ከሁለት ሆነ። እንዳያስቆማት አናደደችው እሱን ባለማመኗ በጣም ተሰምቶታል። እንዳይተዋት ደግሞ በጣም ይወዳታል።አይኖቹን ጨፈነና በዝግታ ተራመደ። ድንገት መንገድ ላይ የነበረ ድንጋይ መታውና ዳር ይዞ ተቀመጠ የእግሩን አውራ ጣት አደማው። ሜላት ወደ ኋላ ሳትዞር ዝም ብላ ሄደች። "ምን አይነት ግራ የገባው አለም ላይ ነው ያለሁት።" አለና ስልኩን አውጥቶ ለሜላት ፎቶውን የላከላትን ሰው ስልክ ወደ ስልኩ አሰፈረና ደወለ። ስልኩ ጥሪ አይቀበልም " ሺት ሲያስጠላ" አለና ሴቭ አድርጎ ፕሮፋይሉን ሲያይ ምንም አይነት ፎቶውም ሆነ ሌላ ነገር የለም። " ችግር የለም እደርስብሀለሁ እንዴት እንደምደርስብህ እኔ አውቃለሁ አለና ቀጥታ ወደ ናታኔም ዶርም ሄደ ናታኔም ዶርም አልነበረም ከናታኔም ጋር ሁለተኛ ሲሚስተር ዶርም ተለያይተዋል። በዶርም አባሎቹ አስደወለለትና አስጠራው ናታኔም ብዙም ሳይቆይ መጣ። ናታኔም ዶርሙን ክፍት እንዳደረገ ናሆም ተነሳ " ምነው ችግር አለ ናሆም " አለ ናሆም የናታኔምን ጥያቄ ባልሰማ አለፈውና ስልኩን አውጥቶ " ይሄን ስልክ ታቀዋለህ?" አለ ናሆም ናታኔም የሚያሳየውን ስልክ ቁጥር በደንብ ከተመለከተው በኋላ " አላውቀውም " አለ ናታኔም ናሆም ራሱን መቆጣጠር አቃተው ዘሎ አንገቱን አነቀው እጁንም ጠበቅ አደረገና " በደንብ ታውቀዋለህ የዚህን ስልክ ባለቤት ማንነት ከነገርከኝ ብቻ ነው እጄን አንገትህ ላይ የማነሳው ።እስካሁን ባደረክልኝ መልካም ነገር ምክንያት ብዙ ስራወችን ስትሰራ ባላየ አልፌህ ነበር አንተ ግን አልበቃህ አለ እመነኝ ዛሬ እውነቱን ካልነገርከኝ አንገትህን አንቄ ነው የምገልህ" አለ የናሆምን ሀይለ ቃልና የናታኔምን ፃር የበዛበትን ድምፅ ሲሰማ ከተኛበት የተነሳው የዶርም አባል ከአልጋው በፍጥነት ተነስቶ የናሆምን እጅ ከናታኔም አንገት አላቀቀውና " እንዴ ያምሀል እንዴ አባቱ ልትገለው ነው?" አለ ናሆም ለልጁ አልመለሰለትም ስለገለገለው በጣም ተናዷል። " እየውልህ ናታኔም የዚህን ስልክ ማንነት ካልነገርከኝ እመነኝ አጠፋሀለሁ አንተ ተንኮለኛ ሰይጣን እንኳን ለእኔ ለምትወዳት ልጅ እንኳ የማትተኛ እንደሆንክ አውቃለሁ። ስለዚህ ካልገገርከኝ በግድ እንድትነግረኝ አደርግሀለሁ ከዛሬ ጀምሮ እከተልሀለሁ በምትሄድበት ሁሉ" አለና ናሆም በሩን በሀይል ዘግቶት ወጣ ። ናታኔም አንገቱን እየነካካ ወደ ኋላና ወደፊት ወደጎን ና ወደጎን እያነቃነቀ " ያመዋል እንዴ በሽተኛ ሆኗል ዝም ብሎ በማላውቀው ነገር ይከሰኛል እንዴ ቆይ የማደርግህን እኔ ነኝ የማውቀው " አለና ጣቱን አፉ ላይ ጭኖ " አሃሃሃሃሃ በርግጠኝነት መርዕድ ሌላ ስልክ ቁጥር አውጥቷል በዚያ ስልክም ከሜላት ጋር የሆነ ነገር አድርጓል ወይም መቅደላዊት ጋር አንድ ነገር አድርጓል። ሃሃሃ ለካ ያለ ነገር ዘጋ ዘጋ አላደረገኝም የሆነ ነገር እንደያዘ አሁን ትዝ አለኝ በዛ ላይ ስለኩ ዝግ ነበር አሁን ነው ሁሉም ነገር እየተገለጠልኝ የመጣው የሚገርም ነው ።እኔ ላይ መጫወትም ፈለክ ሃሃሃሃ እኔ ባመጣሁት ጥይትማ አትመታኝም እንዴት እንደምመታህ አውቃለሁ!!!" አለና ለመርዕድ ደወለ አላነሳለትም ደግሞ ደወለ አላነሳለትም መጨረሻ ላይ " በአዲሱ ስልክ ቁጥርህ ላይ የምታደርገውን ነገር ደርሼበታለሁ ወይ ስለምታደርገው ነገር በደንብ አስረዳኝና እኔም ልጠቀምበት አንተንም ልከላከልልህ ኧረ ካልክ ደግሞ ሁሉንም እንድትጋፈጥ የማውቀውንና ለማወቅ ትንሽ የቀረውን ለናሆም አስረዳዋለሁ። ናና እናውራበት ኧረ ካልክና ከኔ ጀርባ የምታሴር ከሆነ ያልቅልሀል። " የሚል መልዕክት ላከለት መርዕድ መልክቱን እንዳነበበ ወዲያው ለናታኔም ደወለለት " ምንድን ነው የምትለው እኔ ከአንተ ተደብቄ ምን እሰራለሁ እኔ ሰርፕራይዝ ላደርግህ ነበር ሁሉንም ነገር ሳደርግ የነበረው ላንተም ለኔም ነው " አለ መርዕድ " እና ምን አዲስ ነገር አለ ብየ ስጠይቅህ ለምን ምንም ነገር የለም አልከኝ ቢያንስ ባትነግረኝ እንኳ ለምን የሆነ ነገር እየሰራህ እንደሆነ ፍንጭ አልሰጠኸኝም በጣም እኮ ነው የምትገርመው ህ እንዴት ላምንህ እችላለሁ ። አሁን በዛሬው የናሆም ሁኔታ ያላጋፈጥኩህ እኔ ሆኜ ነው። እሽ እንጅማ እንደስራህ መጋፈጥ ያለብህ ልጅ ነበርክ በል አሁንም ምን እየሰራህ እንደሆነ ማወቅ ስላለብኝ በደንብ አስረዳኝ በል ፍጠን " አለ ናታኔም " እሽ ወንድሜ አሁኑኑ መጣሁ " አለ መርዕድ " አፍጥነው ናሆም ገና ሳትጀምር ደርሶብሀል " ብሎት ። ስልኩን ዘግቶ ቀና ብሎ ሲያይ የሚያየውን ማመን አቃተው ስልኩን በድንጋጤ መሬት ላይ ጣለው። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 16♥️ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_14 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜላት ለናሆም ሁለት ጊዜ ደወለችለት ነገር ግን አያነሳም በሶስተኛው አንስቶ " የኔ ፍቅር ትንሽ ጠብቂኝ ቆይቼ እደውልልሻለሁ " ብሎ ሊዘጋው ሲል " እንዳትዘጋው " አለችና አንባረቀችበት ናሆም ድንግጥ አለና " ምነው ምን ሆነሽ ነው?" አለ ግራ በተጋባ አነጋገር " አሁን የት እንዳለህና ከማንጋር እንደሆንክ ንገረኝ " አለች " ከዮርዳኖስ ጋር ከዋርካው አጠገብ ካለው ህንፃ ዘረአይ ፓርክ " አለ " አሁኑኑ መጣሁ " አለችና ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጋችበት። እየተፈጠረ ባለው ነገር ደንግጦ የተዘጋውን ስልኩን ማየት ጀመረ። ሁኔታውን አይታ " ምነው የተፈጠረ ነገር አለ ? ናሆም " አለች ዮርዳኖስ " ትከሻውን ወደላይ ሰበቀና " አላውቅም ተናዳለች የተናደደችው ደግሞ በእኔ ነው። ለምን ትናደድብኛለች አብረን ነበርን ምን የተለየ ነገር አድርጌ ነው ከሷ በኋላ ደግሞ አንችን ነው ያገኘሁት ግራ አገባችኝ " አለ ናሆም " ምን አልባት እኔ መሄድ ሳይኖርብኝ አይቀርም " ብላ ዮርዳኖስ ልትነሳ ስትል " አይሆንም ለምን ትሄጃለሽ መቼ ጨረስን ቁምነገራችንን " ብሎ እጇን ስቦ አስቀመጣት " ማለቴ ያው ሁለታችሁ ማውራት ያለባችሁ ነገር ያለ ነገር ይኖራል ብየ ስላሰብኩ ነው" አለችና ተደላድላ ተቀመጠች። " ምን አጋጥሟት ነው?" አለ ናሆም እጁን አፉ ላይ ጭኖ ። ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ሜላት እሳት ለብሳ እሳት ጎርሳ መጣች። አኳኋኗን ተመልክቶ ናሆም ከተቀመጠበት ብድግ አለ ናሆምን አለፈችና የዮርዳኖስን አንገት አነቀች ናሆም ተስፈነጠረና " ምን እያደረግሽ ነው ያምሻል እንዴ " ብሎ እጇን ከአንገቷ አላቀቀውና ለብቻዋ ገፍቶ አቆማት። ዮርዳኖስ ደንግጣ ባለችበት ቆመች ። እጆቿ ተንቀጠቀጡ አፏ ተርበተበተ ደንዝዛ ተቀመጠች ።" ምን አደረገችሽ ምን ሆንኩ ብለሽ ነው ያምሻል " አለ ናሆም ተናዶ " ምንድን ነው ያደረጋችሁት ይባስ ብለህ ደግሞ እኔን ትጠይቀኛለህ አንተ ራስህ ምንድነው ያደረከው መልስልኛ?" አለች ሜላትም በናሆም ላይ የተናደዱ አይኖቿን እየወረወረችና እጇን ወደደረቱ እየጠቆመች " አሁን ምን ተፈጥሯል ብለሽ እንደመጣሽ ብቻ ንገሪኝ ካልሆነ ግን እንጣላለን " አለ ናሆም " ተጣላኛ ደግሞ በላይ እንደገዳይ እኔ ላይ ልትናደድና ለመጣላት እንደምትፈልግ ልታስፈራራኝ ትፈልጋለህ አላበዛኸውም? እንጣላ እኔ እንኳ ያን ሁሉ ነገር አድርገኸኝ እንጣላ አላልኩም ጨምላቃ ውሸታም እውነቱ ሲገለጥብህ በዚህ ልታስፈራራኝ ትፈልጋለህ ?" አለች ሜላት ደረቱን እየገፋች " ናሆም ግራ ተጋባ ምን ሆነሽ ነው ምን አደረኩ እሽ ቆይ ለምን አትነግሪኝም?" አለ " ምኑን ልንገርህ ልድገምልህ? እዚህ ከሷ ጋር ምን እያደረክ ነበር። እኔ እኮ በመቅደላዊት ጉዳይ እና ስለባሩክ የምታወሩ መስሎኝ ነበር እስከዛሬ ማመኔ ለካ በእኔ ላይ ድራማ ትሰሩብኛላችሁ እስከመቼ ነበር ልትደብቁት የፈለጋችሁት እ? ንገረኛ እኔን እንደማፈቅርህ ስለምታውቅ የፈለከውን ታደርጋለህ ስትመጣም ስትሄድም በአወንታና በይሁንታ ስለምቀበልህ ትፈነጭላለህ? ቆይ ግን የምታስመስለው እስከመቼ ነው ?" ያለ እረፍት ወረደችበት። ናሆም ይበልጥ ግራ ገባው። በምንም በኩል ሜላትን ሊቋቋማት አልቻለም። ጥያቄውንም ልትመልስለት ቀርቶ ልታዳምጠውም አልፈቀደችለትም። ራሱን ያዘና ወደ ዮርዳኖስ ዞሮ " ዮርዲ በጣም ይቅርታ እደውልልሻለሁ አሁን ሁለታችን ማውራት ያለብን ጉዳይ ሳይኖር አይቀርም " አላት ዮርዳኖስ በፍርሀት አይን ሁለታቸውንም እየተመለከተቻቸው ምንም ሳትመልስለት ብድግ ብላ ሄደች። ትንሽ በአይኑ ከሸኛት በኋላ ወደሜላት ዞረና " አሁን በምትናገሪው ነገር ግራ ተጋብቻለሁ በምን ምክንያት እኔና ዮርዲን አንድ ላይ አድርገሽን እንዳወራሽ እንደሆንሽ አልገባኝም ።ስለዚህ እኔ ለመጨረሻም ጊዜ የምለምንሽና የእውነት እስካሁን ስለምትወጅኝ አብረሽኝ ከነበርሽ እንደዚህ በቅርብ ስአት ይሄን ሀሳብና ጥርጣሬ ያስገባሽን ነገር ንገሪኝ ከዛ በኋላ የእኔን ምላሽ አትጠብቂ የፈለግሽውን ወስኝ። እኔ አሁን እድሜ ለባሩክ ቀይሮኛል አመለካከቴንም ጭምር እሱ ብቻም ሳይሆን መቅደላዊትም አሁን ለያዝኩት ስብእና ራሷን ሰጥታኛለች። ስለዚህ አንቺን የምጎዳበት ታዕምር የለም አንቺ ግን እንደምጎዳሽ ካሰብሽና እንደጎዳሁሽ እንደከዳሁሽ ከተሰማሽ ቢያንስ ንገሪኝና ውሳኔሽን ልቀበለው ኧረ ዝም ብኝ እጮሀለሁ ካልሽ እንደፈለግሽ " አለ ና ዝም አለ። " ምንም ብትል አላምንህም ከድተኸኛል ዮርዳኖስን ስመሀታል ይሄው ከዚህ በላይ ምንም ልታስረዳኝ አትችልም ። አለችና ቴሌግራሟን ከፍታ አሳየችው ስልኳን ተቀበላትና ቀጥታ የላከላትን ስልክ ቁጥር በአይኑ ከተመለከተ በኋላ ሸምድዶ ፎቶውን አየ ። " እና አመንሽው ይሄን ፎቶ የላከልሽን " አለ " ሰውየውን አላምነውም ፎቶውን ግን አምነዋለሁ " አለች። "እሽ እና በከንቱ ነዋ የምደክመው እሽ ለማንኛውም እውነቱን ልንገርሽ ከፈለግሽ እመኝ ካልፈለግሽ ደግሞ አትመኝ ዮርዳኖስን የሳምኳት ግንባሯን ነው የሳምኳትም ከአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ጋ ሄዳ ለዶክተሩ መቅደላዊት ያለችበትን ሁኔታ በማስረዳት ከባሩክ እህት ጋ አስደውላ የባሩክን አድራሻ እንደተቀበለች ስለነገረችኝ ነው ደስ ብሎኝ ልሳምሽ ብየ የሳምኳት ትክክለኛው እና የሆነው ይሄ ነው። " አለ " አላምንህም" አለች ሜላት " አለማመን መብትሽ ነው እኔ ግን እውነቱን ነግሬሻለሁ እወድሻለሁ በዚህ ጊዜ አንችን የማስቀይምበትም ሆነ የማሳዝንበትም ወቅት አይደለም። እባክሽ እምነትሽን ስጭኝና በኔና የአንቺ መሀል ክፍተት አይፈጠር እመኝኝ" አለ ናሆም እጁን እየሰጣት " አላምንህም ከአንድ ጊዜ በላይ ብዙ ጊዜ ተጫውተኸብኛል አሁንም ዋሽተኸኛል። በጣም ሲበዛ ስቃየ እንደሚያዝናናህ እያሳየኸኝ ነው" አለችና ተነስታ ትታው ሄደች ። ናሆም ራሱን ይዞ አቀረቀረ ሳያስበው የእምባው ዘለላወች በጉንጮቹ ወረዱ። መሬቱን በቡጢ ነረተውና ተነስቶ ሜላትን ተከተላት። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 15♥️ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_13 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜላት አይኖቿን ከድና ዳግም ከፈተችና ያየችውን ለማረጋገጥ ከፈተችው። የተለወጠ ነገር አልነበረም። ናሆም የዮርዳኖስን ግንባር እየሳማት ነው። እንደ አዲስ እንደተወለደች ያደረጋት የምታፈቅረው የሚያፈቅረኝ ብላ የምታስበው ናሆም ሌላ ሴት የሌላ ወዝና ገላ ሊለመድ እንደሆነ ተሰማት። የሌላ ሆኖ የታያትም መሰላት። በእርግጥ ዮርዳኖስ በቅርብ ጊዜ በባሩክ ጉዳይ ሊያማክሯት የቀረቧት ልጅ እንደሆነች ታውቃለች ነገር ግን አሁን በምታየው ነገር በጥርጣሬ አይንና በድንጋጤ ፎቶውን አየችው ከት ብላ ሳቀች። እየሳቀች እንባዋ ይወርዳል ያለማቋረጥ ትስቅ ጀመር። ተነሳችና ወንበሩ ላይ እየተቀመጠች ቆይ እኔ ግን ማነኝ? ለምንድነው እንዲህ የምሆነው እንዴ ናሆም ኮ ያፈቅረኛል ግን እኮ ደግሞ አሁን ሌላ ሴት አቅፏል ለምን ይስማታል?" መልስ የሌላቸውን ጥያቄዎች ማዥጎድጎድ ጀመረች።ህይወት ፊቷን እያዞረችባት እንደሆነ ተሰማት። የኔየ ግን ምንድነው ?" አለችና ፎቶውን ወደላከላት ሰው ስልክ ደወለች። ስልኩ አይነሳም ።" አንተ ማንነህ?" የሚል መልዕክት ፃፈችለት። " እኔን አታውቂኝም እኔ ግን አውቅሻለሁ ሁልጊዜም ታሳዝኝኛለሽ የናሆምን ሁኔታና ተግባሮች ለአንቺ ያለውን አመለካከት ሳይ ይበልጥ ታሳዝኝኛለሽ" ብሎ ወዲያው መልዕክት ፃፈላት። " እሽ ለእኔ የምታዝን ከሆነ በዚህ ስአት የት እንዳለ ንገረኝ " በማለት መለሰችለት " እንደዚህማ መሆን የለብሽም አሁን መረጋጋትና በደንብ ማሰብ አለብሽ እሱን ነው ማድሰግ ያለብሽ በስሜትማ የሆነ ነገር ለማድረግ መነሳት የለብሽም አሁን ማድረግ ያለብሽ ስለዛሬው ሁኔታ ነገ ስታገኝው አንድ በአንድ መጠየቅ የዚህን ፎቶ እውነት ከደበቀሽ ያኔ አሳይተሽው መወሰን ትችያለሽ አሁን ግን መረጋጋት ና በደንብ ማሰብ አለብሽ" በማለት መለሰላት " ቆይ እንዲህ አይነት የክህደት ምስል እየተመለከትሁ እንዴት ነው የምረጋጋው ወንድሜ ስታስበው እንቅልፍ የሚወስደኝ ይመስልሀል ነገ ድረስ የምትደርስ ይመስልሀል እንዴት ነው እንቅልፍ የሚወስደኝ እንዴት ነው ያለ ሀሳብ እንዴት ነው ምንም እንዳልተፈጠረ የማስመስለው?" አለች " እኔ እንግዲደድ የተየኝንና ለአንቺ የሚሻለውን ነገር ነው የመረጥኩልሽና የነገርኩሽ ቀሪውን ለአንቺ " አለና ከቴሌግራም ወጥቶ መርዕድ ፈገግ አለ ።ወዲያው ደወለችለት ስልኳን እየተመለከተ ገና ሽህ ጊዜ ትደውይልኛለሽ እንዳሰቃየሽኝ ደስታየን እንዳጨለምሽው የአንችንም ምስቅልቅሉን ነው የማወጣው ያኔ መሀል መንግድ ላይ እኔን ብቻ እንድትመርጭ አደርግሻለሁ ። " አለና ስልኩን ጣለው ከትንሽ ሰከንዶች በኋላ በመልዕክት ማስቀመጫ " በናትህ ስልክህን አንሳና አውራኝ የእውነት ለእኔ ካዘንክ የምልህን አድርግልኝ እኔም በምላሹ የቻልኩትን ፌቨር ልሰራልህ እችላለሁ " የሚል መልዕክት ደረሰው። አነበበውና " ባክሽ አትቅለስለሽብኝ ለራስሽ ጉዳይ ስለሆነ ነው እንዲህ ጎንበስ ቀና የምትይው " አለና ስልኩን አጥፍቶ ያኛውን የስልክ ቁጥር ስልክ አበራው። ብዙ ያልተሳካ ጥሪ ደረሶታል። ሁሉም ያልተሳኩት ጥሪወች መልዕክት የናታኔም ስለክ ነበር። መርዕድ እሽ ተማሪ ናታኔም አለና ደወለለት ።በመጀመሪያው ጥሪ ናታኔም አነሳውና ስልኩን " ወንድሜ መርዕድ ምንድነው ስልክህን የዘጋኸው " አለ " አይ እንዲሁ መዝጋት ስለፈለኩ ነው ደብሮኝ " አለ መርዕድ እያፌዘ " እንዴ ምን ሆነህ የደበረህ በዚህ ስአት እኮ ደበረኝ ተብሎ የሚቆምበት ስአት አይደለም ለምንድነው እንደዚህ የምትሆነው? አይዞህ እንጅ ወንድሜ " አለ ናታኔም " እሽ ልክ ነህ በቃ እንደዛ አስባለሁ እንደዛ አደርጋለሁ ታዲያ ምን አዲስ ነገር አለ?" አለ መርዕድ " ኧሰ እኔስ ጋር ምንም የለም አንተ ጋር ከሌለ በቀር መርዕድ ከአንተ ጋ እንዳለ ብየ ነበር እንደዚህ ብዙ ጊዜ የደወልኩልህ " አለ ናታኔም " እኔም ጋ ምንም የለም ባክህ ሁሉም እንደነበረውና እንደታቀደ ብቻ ነው እየሄደ ያለው አባቴ አንተ ጋ እንዴት እስካሁን ምንም ነገር የለም። " አለ መርዕድ እየሳቀ " አንተ ጋር ነበራ መስራት ያሰብኩት ለማንኛውም ተገናኝተን ብናወራ " አለ ናታኔም " አልችልም ብዙ ስራ አለብኝ ታይትልም ስለማስመረጥ ትኝሽ ማንበብና መዘጋጀትም አለብኝ " አለ መርዕድ " እሽ በቃ እንዳልክ ለማንኛውም ግን አትጥፋ ይህኛውን ቸል አትበለው ቶሎ መስራት አለብን እኔ አሁን ለባሩክ እፅፍለታለሁ ከዛ ቀጣዩን ስቴፕ ደግሞ አብረን እየተነጋገርን ብናደርግ የተሻለ ነው" አለ ናታኔም የመርዕድ ሁኔታ ግራ እያጋባው። " እሽ እናወራለን ግን ደግሞ ትምህርትህንም መዘንጋት የለብህም ማንበብ አለብህ በዚህ ነገር ብቻ ተመርዘህ ያነኛውን ና ዋነኛውን እንዳትረሳ " አለ መርዕድ "እሽ አታስብ እሱንማ ካልያዝኩ በምን ምክንያት እዚል ጊቢ እቆያለሁ " አለ ናታኔም " መልካም እንደዛ ካደረክ በቃ እኝደዋወላለን አአለና መርዕድ ስልኩን ዘግቶ " ከዚህ በኋላ ከአንተም ጋር ግንኙነታችን በመስመር መሆን አለበት ብዙ ጊዜ ከአንተ ጋር ማሳለፍ የለብኝም ኧረ እንደውም መገናኘትም የለብንም " አለ **** ሜላት ለናሆም ሁለት ጊዜ ደወለችለት ነገር ግን አያነሳም በሶስተኛው አንስቶ...... ይቀጥላል ....... Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 14♥️ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_12 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " እሽ ምን አዲስ ነገር አለ ዮርዲ ?" አለ ናሆም " አዲስ ነገር ብዙ አለ ምን መሰለህ አዲሱ ነገር ለአካዳሚክ ጉዳዮች ፕሬዚዳንት ለ ለዶክተር ወንድማገኝ ይመር ስለመቅደላዊት ሁኔታ ነገርኩት ከዛ የባሩክ እህት ጋ ደውልን የባሩክን አድራሻ እንድትሰጠን ጠየቅናት አቅማምታ ነበር ነገር ግን ከዩኒቨርስቲው ነው ስላትና ዶክተር አለ ስላት ነበር የሰጠችኝ ዶክተርም የባሩክን ስልክ ወስዶ እኔ እደውልለታለሁ ለመቅደላዊትም የስነልቦና ባለሞያ እንቀጥራለን በጣም ከተጎዳች ብሏል። በቃ በእኔ በኩል ያለው አዲስ ነገር ይሄ ነው ለዚህ ነው ላገኝህ የፈለኩት።" አለች ዮርዳኖስ ። ናሆም ራሱን ወዘወዘ " የእውነት የሚገርም ስራ ነው የሰራሽው አኩርተሽኛል። በጣም ብዙ ነገሮችን ገድለሻል ምንም ያስተረፍሽው ነገር እኮ የለም ፐ ፐ ፐ ፐ ምን ታዲያ በርቀት ትመለከችኛለሽ ነይ ልቀፍሽ እንጅ" አለና ግራ እጁን እንደክንፍ ዘረጋው።እየሳቀችና እየተቅለሰለሰች መጥታ ተወሸቀች። አቀፋትና ግንባሯን ሳም አደረጋት ። **** ግንባሯን ሲስም ፊትለፊት ሲከታተላቸው የነበረው ልጅ ፎቶ አነሳቸውና በፍጥነት ከአካባቢው ተሰወረ። ናሆምና ዮርዳኖስ ፎቶ ያነሳቸውን ልጅ ምንነት ና ማንነት አላወቁም እንደውም ፎቶ እንደተነሱም የሚያውቁት ነገር የለም ልጁ በፍጥነት ሄደና አሳፓልት ዳር ላይ ሆኖ እየጠበቀው ላለው ልጅ ስልኩን ሰጠ። ልጁ መርዕድ ነበር። የልጁ የፎቶ ጋላሪ ገብቶ ፎቶውን አየና " ጎበዝ አንተ ጥሩ ካሜራ ማን ነህ በጣም በሚገርም ሁኔታና ፍጥነት ነው ያነሳኸው በዛ ላይ ፎቶው ራሱ ያምራል።" የተቀመጡበት ቦታ በግማሹ ብርሀንን የተላበሰ በመሆኑ ፎቶው እንዲህ እንዲሆን አስተዋጽኦ አበርክቷል። " አለ ልጁ " አይ ብርሀኑ ብቻ አይደለም ያንተ ከብርሀን የላቀ እይታም ጭምር ነው። በጣም የሚገርም ፎቶ ነው እንደመጀመሪያ እጅግ ደስ ይላል አለና ፎቶወቹን በደንብ ቀረብ እያደረገ ከተመለከተ በኋላ ወደ ራሱ ስልክ ላከና " በጣም ከልቤ አመሰግናለሁ ወደፊት በጣም ጥሩ ጥሩ ፎቶወች እንደምታመጣልኝ እጠብቃለሁ። ለአሁኑ ደግሞ ከልቤ አመሰግናለሁ። ለዛች ምስኪን ሴትም የወደፊት እጣዋን በማውጣትህ እንዲሁ በእውነት ፍቅር ይዟት አላምን ብላ አስቸግራኝ ነበር። አሁን ግን አይኗን ማመን ካቃታት ምንም ልናደርግ አንችልም ።እና ወንድሜ በእሷም ስም በእኔም ስም አመሰግናለሁ ።እንካ ይቺን ደግሞ ለሻይ አለና 20 ብር ሰጠው። ልጁ ስላመሰገነው ሳይሆን በሰጠው ሀያ ብር እየፈነደቀ ወዲያው ከመርዕድ ተሰወረ ። መርዕድ ከእንደገና ፎቶውን ገብቶ እያየ " ናሆም ሰራሁልህ እሰራልሀለሁም ።ደስታየ ላይ እንደቀለድህብኝ ፍቅሬን እንደወሰድክብኝ ፍቅሬን እንደቀማኸኝ አትቀርም ነበር ይሄው ቀን ጠብቄ አገኘውህ። አሁን የሜላት ፍቅር ሲገባህ ከሜላት መሸሽ መለየት ሲከብድህ ጠረኗን ማሽተት ሲያምርህ አይኖቿን በፍቅር መመልከት ከንፈሯን መሳም ሲያምርህ ሜላትን እወስድብሀለሁ እቀማሀለሁ። መልሼ ወደነበርክበት ህይወት እመልስሀለሁ። አለና " ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ " ብሎ በረጅሙ ሳቀ። የሜላትን ፎቶ ደግሞ በሌላኛው የፎቶ ማህደር አወጣና አንችም ሜላት በእኔ ፍቅር እንደተሳለቅሽ እንደቀለድሽ አትቀሪም አሁን ያለ ምርጫ እንድታፈቅሪኝ አደርግሻለሁ ።ሁለታችሁንም አገኘኋችሁ። ያገኘሽውን ደስታ በውል ሳታጣጥሚው ይሄው ደረስኩብሽ እኔ የሌለኝን እኔ ያጣሁትን ደስታ አንች አይኖርሽም። አለና ፈገግ ብሎ ወደ ማስተርስ ብሎክ የሚወስደውን መንገድ ይዞ ሄደ። ** " እውነት ዮርዲ ትልቅ ስራ ነው የሰራሽው እኔ ማድረግ ያልቻልኩትን በዛ ላይ የመቅደላዊት ጉዳይ አሳስቦሽ እንዲህ ጊዜሽን ሰውተሽ ስላደረግሽ በጣም እናመሰግናለን " አለ ናሆም " ተው እንጅ ናሆም ምስጋና አታብዛብኝ መቅደላዊት እኮ በጣም ታሳዝናለች። ሁኔታዋን እያየሁ እንዴት ይሄን አላማድረግ እችላለሁ በዛ ላይ ምስኪንና ሩህረህ ናታ ከራሷ በላይ ለሰው ማድረግ የምትችል መሆኗን አውቃለሁ። በዛ ላይ ለባሩክም ጭምር ብየ ነው በእርግጠኝነት ባሩክ መቅደላዊት እንደዚህ ሆና ቢያያት ይጎዳል። ምክንያቱም ጥሩ ልብ አለው ሲበዛ በጣም ነዋህ ነው። ሲቀጥል ደግሞ እንዲህ ያደረገኝ የናታኔም ብልግና ነው። ብቻ ግን ከሁሉም ከሁሉም ትልቋ ምክንያቴ ሴቷ መቅደላዊት ናት " አለች ዮርዳኖስ " እሽ ዮርዲ ልክ ነሽ ስለቅንነቷ ይሄ ይገባታል።ታዲያ ቀጣይ ምን ማድረግ አለብን?" አለ ናሆም ስለቀጣዩ ሁኔታ ከዮርዳኖስ ጋር ይበልጥ ለማውራት ። ** ሜላት አልጋዋ ላይ ተኝታ አይኖቿን እያርገበገበች ሳቅ አለችና ስሌሊቱ አዳሯ አሰበች ለመጀመሪያ በፍቅርና በውዴታ ከናሆም ጋር የወጣችበት ሌሊት ትዝ አላት ከእንደገና አልጋዋ ላይ ተንከባለለችና ስልኳን አውጥታ ፎቶወቿን አየች አልጋ ላይ ሆነው ራቁታቸውን አብረው ከናሆም ጋር የተነሳቻቸውን ፎቶወች ተመለከተች። ወደደረቷ አቀፈችውና ፎቶውን አይኖቿን ጨፈነች። የልብ ትረታዋ ያለ ለከት መምታት ጀመረ መፍጠኑን ቀጠለ። ከዛ ከፎቶው ማህደር ወጣችና የቴሌግራም አካውንቷን ከፈተች እንደከፈተች ብዙ መልዕክቶች ደርሰዋታል። እነሱን በየተራ እየገባች እየተመለከተች ቀጥላ በአንድ በማታውቀው ስልክ ቁጥር የተላከው ፎቶ ላይ ደርቃ ቀረች። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 13♥️ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_11 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " አንተ የኔ ድክመት የፍቅሬ ምልክት አላልቅልሽ አለኝ ቢመዘዝ ሰበዙ፣ እንደ አባይ ዳር በለስ ሆነህብኝ ወንዙ። ትመጣለህ ብየ ባይ ማዶ ባይ ማዶ አለቀልህ ልቤ ተንዶ ተንዶ። " አንገቷን ሰበር አድርጋ መቅደላዊት ለራሷ አንጎራጎረች። አይኖቿ ላይ ትዝታና የማይመጠን ፍቅር ይታያል። ጠንካራ ለመሆን እየሞከረች ትመስላለች። ነገር ግን ፍቅሩ አድክሟታል። አይኖቿ ማዶ በጉም ብዛት ከተሸፈነው ሰማይ ተሰክተዋል። ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ሰማዩን ያስጌጠችው ቀስተደመና ደግሞ ሰማዩን በግማሽ በኩል አካለለች ። አሁንም አይኖቿ እንዳቀረዘዙ ናቸው። ቀስተደመናው እየደመቀ ጉሙ እየሳሳ ሰማዩ ደግሞ ወደ ውሀ ቀለም እየተቀየረ ሄደ። መቅደላዊት ግን ማየት እንጅ አልተመለከተችውም። በራሷ የምናብ ምድርና ሰማይ ሆና የራሷን ከዋክብቶች እየቆጠረች ነው። " እንደዚህ አትሁኝ እመኝኝ አንድ ነገር አደርጋለሁ። ባሩክን ታገኝዋለሽ ደስተኛም ትሆኛለሽ " አለና ናሆም የጥሞና ቀልቧን አስበረገጋት። " እ ናሆም በየት ተገኝህ " አለይና ፈገግ ብላ ለሰላምታ እጇን ሰጠችው። ተቀበላትና አቀፋት ። " እንዴት ነሽ " " አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን ደህና ነኝ " አለች መቅደላዊት ። " እና ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ ?" አለ ናሆም ። " ናሆም ባሩክን ለመርሳት ወስኛለሁ!" አለችና ዝም አለች። ናሆም ደነገጠ ዞሮ ተመለከታት ከወትሮው በተለየ አይን ማዶ አድማስ ስትመለከት አያት። ግራ ተጋባ ደነገጦ የሚለው ጠፋበት። " ምነው ዝም አልክ ?" አለች መቅደላዊት ። አ አ አይ ምን ማለት እንዳለብኝ ጠፍቶኝ በዚህ አጭር ጊዜ ትረሽዋለሽ የሚል እምነት ስላልነበረኝ ነው። እንደዛ ከወሰንሽና ውሳኔሽ የሚያስደስትሽና አንቺን ሰላም የሚሰጥሽ ከሆነ ለእኔ ምንም ችግር የለውም ብቻ አንቺ ደስተኛ ሁኝ እንጅ።" አለ " አንዳንድ ጊዜ ደስተኛ ለመሆን ሳይሆን መውን ስላለብህ ወይም ሌላ የምትወስነው ነገር ምርጫ ካልቀረበልህ የግድ የምትወስነው ነገር ይኖራል።" አለች ። " እሽ ብቻ በዚህም አለ በዚያ በዚህ ውሳኔ ደስተኛ ከሆንሽና ምርጫ ካደረግሽው ጥሩ አድርገሻል። ምን አልባት አንድ እርምጃ ወደፊት ያስጉዝሻል ነገሮችን በተለየ መንገድ እንድታይ ይረዳሻል።" አለ " አወ እኔም ብየ ተስፋ አደርጋለሁ። ለዚህ ነው አንተንም የጠራውህ ላወራህ ልነግርህ የፈለኩት እናንተንም ከዚህ በላይ ላሰቃያችሁ አልፈልግም። ህይወታችሁን ኑሯችሁን እንድትኖሩ መልቀቅ አለብኝ እኔም ከዚህ በላይ በሰው ትከሻ መሄድ ያለብኝ መስሎ አልታየኝም።" አለች መቅደላዊት " ኧረ እኔንም ሆነ ሜሊን ምንም የተሻማሽን ጊዜም ሆነ ጉልበት የለም እኛን በምንም ነገር አልጎዳሽንም እንደውም በዚህ ታሪክ ውስጥ የተጎዳሽው አንቺና አንቺ ነሽ።ስለዚህ እንደዚህ ማሰብ የለብሽም " አለና ናሆም መቅደላዊትን አቀፋት። " አንቺኮ እዚህ ሁሉ ጣጣ የገባሽውና ባሩክም ከአገር የወጣው በእኔ ምክንያት ነው። እና አንቺ ለእኔ ራስሽን በመስጠት ካደረግሽው ነገር በላይ ማንም ያደረገ የለም የሚያደርግም አይኖርም። እኔ ግን በምንም ቢሆን ለአኔቺ የምሰጥሽ ነገር የለም።" አለ ናሆም " ተው እንደዛማ አትበል አንተም ጥፋት የለብህም ሁሉም ነገር የሆነው መሆን ስላለበት እንጅ በዚህ የታሪክ ሂደት ውስጥ ማንም ተወቃሽ ሰው የለም በቃ ሁሉም መሆን ያለበት መሆን ስላለበት ብቻ ነው። አሁን ይሄን ውሳኔ የወሰንኩት ውጤቴን ማስተካከል እና ቤተሰቦቼን ማስደሰት ስለብኝ ነው የመጀመሪያው ሁለተኛው ደግሞ ውጤቴ ስኮላር የሚያስወስደኝ ከሆነ ወደ ውጪ ለመሄድ ነው እዛ ሄጀ ባገኘው ይሻለኛል። የመጨረሻ እድሌን ያኔ ይቅርታ ጠይቄው ወይ ከነ በባሩክ ተስፋ እቆርጣለሁ አለዚያ ደግሞ ህይወቴን በደስታ ከሱ ጋር እቀጥላለሁ" አለች ። ናሆም በመቅደላዊት ሀሳብ የተስማማ ይመስላል ሳቅ ብሎ ከተመለከታት ኋላ " ደስ የሚል ሀሳብ ነው ግን እኮ እሱ የአንድ አመት ወይም የስድስት ወር ጊዜ ብቻ ይመስለኛል እኮ ቆይቶ የሚመለሰው።" አለ ናሆም በመሀል የናሆም ስለክ ጠራ ስልኩን ሲያየው ዮርዳኖስ ነች። " አንድ ጊዜ ይሄን ስለክ ላውራ መቅዲ " አለና የመቅደላዊትን ፈቃድ ጠየቀ ለማንሳት " ችግር የለውም አውራ " አለችና አንዱን እጇን ከሌላኛው እጇ አጣምራ እግሮችቿን አወዛወዘች። " አቤት ዮርዲ " አለ ናሆም " ላገኝህ ፈልጌ ነበር የማወራህ ነገር አለ " አለች ዮርዲ " አሁን ከመቅደላዊት ጋር እያወራሁኝ ነበር ወደ በኋላ ልደውልልሽ ከእሷ ጋር እንደጨረስኩ " አለ " እሽ ስትጨርስ በቃ እንገናኝ " አለች ዮርዳኖስ ። " ይቅርታ መቅዲ ያው መተው የማልችለው ስልክ ስለሆነ ነው!" አለ ናሆም ያው ለማለት ያህል እንጅ ምንም እንደማትል እያወቀ " ኧረ ችግር የለውም እና ለዚህ ነው የፈለኩህ እነ ናታኔም ደግሞ ብዙ ነገር ለማድረግ ይፈልጉ ይሆናል። ከስልክም በላይ ሊያደርጉ ይችላሉ አንተ ብቻ ተረጋጋ ስሜታዊ መሆን የለብህም። ስሜታዊ በማድረግ የሆነ ስህተት እንድትሰራ ለማድረግ ነው። " አለች " አይ የእውነት ይሄ ስልክ የናታኔም ወይም ናታኔም የላከው ሰው እንዳደረገው ካወኩማ አለቀውም ዋጋ ይከፍላል " አለ ናሆም በአንድ ጊዜ ፊቱ እየተቀየረ " እኮ በአባትህ ቃል ግባልኝ ምንም እንዳታደርግ ቢያንስ አንተ እዚህ ሁንልኝ የአንተን ወንድምነት እንዳያሳጡኝ ስለምፈራ ነው። " አለች " አታስቢ መቅዲየ ምንም አልሆንም " አለ " እሽ ካልክ ብቻ ምንም ነገር አታስብ ከዚህ በኋላ ራሴን እጠብቃለሁ።" አለች " እኔም እሱን ነው የምፈልገው የቀድሞዋን ቆንጆዋንና ሳቂታዋን መቅደላዊት ማየት ነው የምፈልገው" አለ ናሆም ። " ችግር የለም አሁን ዶርም ልሂድ የምሰራው ስራ አለ " አለች መቅደላዊት " እሽ" አለና ናሆም መቅደላዊትን ሸኝቶ ለዮርዳኖስ ደወለ። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 12♥️ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_10 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " የዛሬው ምሽት በጣም ልዩ ነበር እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ። አንተ ሁሌም የኔ ነህ። እንድትሆንም ነው የምፈልገው " አለች ሜላት የናሆምን ፂም እየነካካች።" አታስቢ የኔ ነሽ አንቺም እኔም የአንቺ ነኝ።" አለ ናሆም ። ፅሀይዋ ሳትወጣ ገና በወገግታ ላይ ነች። የናሆም ስልክ ጠራ ሜላት ፈጠን ብላ ለማንሳት እጇን ወደ ጠረምጴዛ እየላከች " በዚህ ስአት ማን ነው የሚደውለው?" አለችና ስልኩን አኔስታ ስታየው የማይታወቅ ቁጥር ነው። " የማይታወቅ ቁጥር ነው ናሆ" አለች ሜላት ፊቷን ወደ ናሆም እያዞረች " አምጭው " አለና ተቀበላት። ናሆም ከአንገቱ ሸና አለና የአልጋውን ራስ ተደግፎ " አቤት " አለ ናሆም ነገር ግን ከወዲያኛው መስመር ሊመልስልት የቻለ አንዳች ሰው አልነበረም። "ለምንድነው ስልክ ደውለው የማያዋሩት? ሄሎ አለ በድጋሚ አሁንም የተሰጠው አፀፋ ዝምታ ነው። የኔትወርክ ችግር ይመስለኛል በማለት ስልኩን ዘጋው በድጋሚ ተደወለ። አነሳውና ሄሎ አለ" ከወዲያኛው የስልክ ጫፍ " ሰላም ወንድሜ ማን ልበል? " አለ ናሆም አሁንም ወደ መጀመሪያው የስልክ ሁናቴ ተመለሰ ሄሎ ያላው የወዲያኛው ሰው በድጋሚ ፀጥ ረጭ አለ ። ናሆም ደጋግሞ ሃሎ ቢልም ሀሎውን ግን የመለሰለት ሰው አልነበረም። በንዴት ስልኩን ወረወረ " አውቆ ነው የሆነ ሰው የማላቀው እሱ ደግሞ የሚያውቀኝ "አለ ተወራጭቶ እየተነሳ ።ሜላት አብራው ብድግ አለችና " ናሆሜ ተረጋጋ ስሜታዊ አትሁን አትናደድ ደግሞ በስህተት ሊሆንም ይችላል መገጣጠምም ሊሆን ይችላል ብዙ አትናደድ" አለች ለማረጋጋት ያህል " አይ አይመስለኝም የኔ ቆንጆ ሆን ተብሎ ነው....በድጋሚ ተደወለ ናሆም በንዴት አይኖቹን አስለመለመና ብድግ አድርጎ " እየውልህ ማንም ሁን ማንም ያወኩህ እለት አለቅህም እሽ" አለ " ምነው ምን ሆነህ ነው? ችግር አለ እንዴ?" አለች መቅደላዊት ናሆም ስልኩን አየው መቅደላዊት ነበረች። " ውይ መቅዲ አንቺ ነሽ እንዴ አሁን እኮ ከአንቺ በፊት እየደወሉ በጥብጠውኝ ስለነበር ነው ይደውላሉ አያወሩም እናም ያ ስልክ መስሎኝ ነው። " አለ ናሆም " ማን ሊሆን ይችላል የናታኔምን ስልክ ታውቀዋለህ አይደል?" አለች ግራ በመጋባት ሁናቴ " አወ የሱንማ አውቀዋለሁ መቼም ለእንደዚህ አይነት ብልግናና ጭምልቅና ስራ ብሎ ስልክ እንደማያወጣ እና የነበረንን ግንኙነት ለማሻከር ይሞክራል ብየ አላስብም እንደዛም እንደማያደርግ ተስፋ አደርጋለሁ " አለ " እሱማ ላይሆን ይችላል እንዲሁ ዝም ብየ የገመትኩት ነው።"አለች መቅደላዊት የናታኔምን ስም በማንሳቷ እንደመሳቀቅና እንደመፍራት ብላ ** " ሰላም ነሽ ኤልያና ዮርዲ ነኝ አውቀሽኛል " አለች ዮርዳኖስ " እ ዮርዳኖስ እንዴት ነሽ?" አለች ኤልያና እንደመንደላቀቅ እያለች ዮርዳኖስ በኤልያና አወራር ብስጭት እየተሰማት እንደመናደድ ብላ "እየውልሽ ኤልያና ምንም ብትይ እና ምንም ብትሆኝ አክት ብታደርጊ እረዳሻለሁ ግን ደግሞ ሰውንም ለመረዳት ሞክሪ የአንቺ ስሜት ወንድምሽንም ሊጎዳው ይችላል " አለች "ምን ለማለት ፈልገሽ ነው ምን አድርጌ ነው የምረብሸው ደግሞ እኔ እንዴት ነው የምታስቢው? ደግሞ ጭራሽ ወደኔ አዞርሽው?" አለች ኤልያና በተንቀለቀለና በተናደደ ድምፅ " እሽ ለማንኛውም ከቻልሽ ለባሩክ የምታስቢ ከሆነ የባሩክን ስለክ ፈልጌ ነበር አሁን ያለሁት የአድዋ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ቢሮ ነው በሱ ትዕዛዝ መሰረት ነው የደወልኩልሽ ከፈለግሽ ዶክተርን ማዋራት ትችያለሽ " አለችና ዮርዳኖስ ሀሳቧን አሳረገችላት " ኤልያና እንደመደንገጥም እንደመጠርጠርም ብላለች ግን ደግሞ የኤልያና ፍራቻ የዮርዳኖስ እውነት ነበር ።አወራሯም ነበር እውነቷን ስለመሆኗ የጠረጠረችው ትንሽ ካቅማማች በኋላ " እሽ ጠብቂኝ አሁኑኑ እልክልሻለሁ " አለችና ኤልያና ያለምንም ማንገራገር ስለኳን ዘግታ ወዲያው ላከችላት። ዮርዳኖስም ደስ ብሏት " ይሄው ላከችልኝ " አለችና ለዶክተር ወንድማገኝ ይመር የባሩክን አድራሻ አሳየችው "መልካም ነው አሁን እኔ እደውልለታለሁ ጉዳዩን በአፅንኦት አስረዳዋለሁ። ያለውን ነገርም ማወቅ አስፈላጊ ነው። አንቺ ግን በርቺ ጥሩ ልጅ ነሽ ጉዳዩን እዚህ ድረስ ስላመጣሽው ደስ ብሎኛል። ከዚህ በኋላ ዩኒቨርስቲውም በመቅደላዊት ጉዳይ ተገቢውን እርዳታ ያደርጋል ልጅቱ በጣም ከተጎዳችም የስነልቦና ባለሞያ እኔዲቀጠር እናደርጋለን በይበልጥ ደግሞ ከባሩክ ጋር በደንብ እናወራለን " አለና ሰላምታ ሰጥቷት ተለያዩ። ዮርዳኖስ ከዶክተር ወንድማገኝ ቢሮ እንደወጣች በደስታ ዘለለች ደስ አላት አንድ ነገር ትልቅ ነገር ያደረገች ተሰማት ውስጧ በሀሴት ሲሞላ ታያት። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 11♥️ ማክሰኞ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_9 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ከባድ ነው ምን ተነግሮ አያልቅ በተለይ እንደ ባሩክ አይነት ወንድም ሲሆንማ ጭራሽ " አለች ኤልያና "አይዞሽ ቻል አድርጊው ግን አይደውልልሽም እንዴ? " አለ መርዕድ ፈገግ እያለ " ኧረ እንደዋወላለን በቅርቡም ደውሎልኝ ብዙ አውርተናል።" አለች " እኔ ጋር እኮ ከተመረቅሁ በኋላ አግኝቼው አላውቅም በጣም ጥሩ ልጅና አስተዋይ ነበር። በሱ ሀሳቦችና ምክሮች ብዙ ነገሮችን ቀይሪያለሁ እና እባክሽን ስልኩን ባገኝና ባወራው ደስ ይለኝ ነበር አትተባበሪኝም" አለ መርዕድ በልመና በሚመስል አነጋገር " " ኧረ ችግር የለውም ግን ምንም ጊዜ የለውም ለማውራት " አለች ኤልያና " አያሳስብም አንቺ ብቻ ስጭኝ እንጂ እኔ እሱ በፈለገው ጊዜ እንዲያወራኝ መልዕክት እተውለታለሁ " አለ ባሩክ ።ኤልያና በአወንታ በመስማማት ስልክ ቁጥሩን በመልዕክት ማስቀመጫ ላከችለት። መርዕድ በጉንብስ ቀና ቀረሽ ምስጋና አመሰገናት። ምስጋናው ምንም እንደማያስፈልግ እና ያደረገችው ነገር ያን ያህል የሚያስመሰግን እንዳልሆነ እየገለጠችለት ንግግራቸውን ለጠቁ። ስልኩን ከዘጋው በኋላ በሀሴት ጮቤ ረግጦ ወደላይ ዘለለ እጆቹንም ወደ ፊትና ኋላ በማደረግ ደስታውን ገለፀ። " አሁን ትልቅ ዜና አለኝ ናታኔም ቡዳ የሆነ የደስታ መርዶ ላረዳህ ይገባል በምላሹም የደስታየን ፅዋ አብረኸኝ እንድትጎነጭ እፈልጋለሁ "በማለት ስልኩን አውጥቶ ደወለለት ። ናታኔም የሱን ስልክ እየጠበቀ ያለ እስኪመስል ድረስ የመጀመሪያው ጥሪ ገና እንደጀመረ ስልኩን አንስቶ " እንዲህ በዚህ ፍጥነት ያስደወለህ አንዳች ትልቅ ነገር ትልቅ ጀብድ ፈፅመህ መሆን አለበት። " አለ ናታኔም " እርግጥ ነው ልክ ብለሀል ስልክ ቁጥሩ እጄ ገብቷል። አሁን ላከችልኝ" አለ መርዕድ " በለው ወንድሜ መርዕድ ጎብዘሀል እንጅ ትልቅ ስራ እኮ ነው የሰራኸው። የሚገርም ጅማሮ ነው ።በዚህ አካሄድማ የብዙወችን የሀዘን ጊዜ አቅርበን የኛን የደስታ ጊዜ ደግሞ እናቀርባለን። በርታልኝ ወንድሜ እኔም አሁን አሪፍ ስራ እሰራለሁ ያቺን ቀትረ ቀላል መቅደላዊት እየተከታተልኩ ነው ። ሌላው ናሆምና ሜላት ደግሞ ለእራት ወጥተዋል።" ስለዚህ እንደፈለኩ ማድረግ እችላለሁ።" አለ ናታኔም " አቃለሁ አንተ ይበልጥ ከእኔ በላይ አሪፍ ዜና እንደምታመጣ " አለ መርዕድ " ተውማ አሁን እንኳ ዘርረኸኝ እየመራኸኝ ነው" ብሎ ናታኔም ቀለደ " ለማንኛውም መልካም ጊዜ። " ብዙ አትዘኝ ለአንቺ ካለው ሄዶ ይመጣል። እንዲህ ራስሽን በጣልሽ ቁጥር ራስሽንም አጥተሽ እሱንም ታጭዋለሽ አሁን እሱ ምታገኝበትን ነገር ማመቻቸት ነው ያለብሽ። አንቺ እኮ የሁላችንም የጥንካሬ የሁሉ ነገር ምሳሌ ነሽ እንዲህማ አትሁኝ እባክሽን ቤተሰቦችሽንም አስቢ" እንጅ አለች ማኪ የመቅደላዊትን እምባ ከአይኖቿ ስር እያበሰችና እያቀፈቻት " ምን ላድርግ ማኪ ያኔ በጅልነት አስቀየምኩት የሱን ንፁህነት ማየት ተሳነኝ እውነትነቱን ማመን አቃተኝ ፍቅሬን ማወቅ አቃተኝ። እርግጠኛ ላልሆንኩበትና ለእኔ ደስታ ፍፁም ለማይጨነቅ ሰው በውሸትና በማስመሰል ለተሞላ ሰው ብየ ባሩክን የልቤን ሰው አፍቃሪየን ለእኔ ሲል ራሱን እስከማጋፈጥ የደረሰውን ባሩክን ማጣቴ እኮ ስለሚያንገበግበኝ ነው ማኪየ ይሄን ነገር የምሆነው ፈልጌው አይደለም። ሳላውቀው በጉዳት የምሆነው እንጅ" አለች መቅደላዊት " አውቃለሁ መቅዲየ ሳልረዳሽ በርቼኮ አይደለም ኤንደዚህ የምልሽ ግን እንዲህ ብዙ አትዘኝ በዛ ላይ ባሩክ መምጣቱ አይቀርም ያኔ እንደምንም ብለሽ ይቅርታ ትጠይቂዋለሽ። እሱም ምንም ነገር አይልም በእርግጠኝነት ይቀበልሻል። ሁሉንም ይረሳዋል። ደግሞ ስለሚያፈቅርሽ ይቅርታሽን ያለምንም ሽምግልና ይቀበልሻል። " አለች ማኪ " እስኪ ያድርግልኝ ጓደኛየ ግን ከዚህ በኋላ ለሁላችሁም ቃል እገባለሁ ትምህርቴን በስርአት አነባለሁ እከታተላለሁ እ ጥሩ ውጤትም አመጣለሁ" ብላ እምር አለች ማኪ ደስ አላት " እንደሱ ስትሆኝ ነው የሚያምርብሽ " ግን ጥሩ ውጤት ማምጣት የምፈልገው ባሩክ የሄደበት ዩኒቨርስቲ ስኮላር እንዲደርሰኝ ስለምፈልግ ነው እዛው ሄጄ ይቅርታ ጠይቄው ፍቅሬን ማጣጣም ነው የምፈልገው " አለች Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 10♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_8 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "የመጀመሪያው እቅዴ ተሳክቷል ። የሚገርም ነበር እንደ እብድ ነው የሆነችው ገና አሳብዳታለሁ። በእኔ እንደቀለደች አትቀርም ዋጋዋን ሳይሆን ከዋጋዋ በላይ ነው የምተምንላት ቀጣይ አንተ ከኤልያና የባሩክን ስልክ ትቀበልልኛለህ። ሃሃሃሃሃሃ ረጅም ሳቅ ሳቀና ራሱን ነቀነቀ አሁን ማንነቴን በደንብ እገልጥላታለሁ " አለ ናታኔም " እኔ ግን እንደዛ ባታደርግ ደስ ይለኛል በጣም ትጎዳለች " አለ መርዕድ " ወንድሜ መርዕድ ምንፈለኩና ሌላ ታዲያ በደንብ እንድትጎዳ እኮ ነው የምፈልገው። በደንብ እንድታለቅስ እራሷን እንድትጠላ እኮ ነው የምፈልገው ። አንተ ወደ ኋላ አትበል በዚህ ሂደት ውስጥ አንተም ህልምህን ታገኝ ይሆናል ምክንያቱም ናሆም እንዲህ ሳደርግ መገናኘታችንና መጋጨታችን አይቀርም ያኔ አንተ ወደ ሜላት ቀሚስ እጅህን ትሰዳለህ" አለ ናታኔም " እንደዛ እንኳ በቶሎ ይከብዳል ሜላት እጅግ በጣም ነው የምታፈቅረው " አለ መርዕድ " እሱን እንኳ ተወው ሴቶች በሁኔታና በጊዜ ነው የሚወሰኑት የሚንቀሳቀሱት በዛ ላይ እንድትቀና ነው የምናደርጋት " አለ ናታኔም "እንዴት አድርገን ልናስቀናት እንችላለን ?" አለ መርዕድ " አየህ አሁን ትክክለኛ ጥያቄ ጠየክ እንዴት ነው የምናስቀናት ጥሩ ጥያቄ ነው እኔ ወደ መቅደላዊት እየቀረብሁ የህመሟን ቁስል ነካ እያደረኩ አሳምማታለሁ። እንደዚህ ባደረኩ ቁጥር ናሆም ይበልጥ እየቀረባት ይሄዳል በየቀኑ ከሷ ጋር ለመሆን ያዘወትራል። ያኔ ሜላት መቅናት ትጀምራለች ለእኔ ጊዜ ለምንድነው የማትሰጠኝ ምናምን እያለች ማላዘን ትጀምራለች ይሄኔ ከናሆም ጋር መኮራረፍ ይጀምራሉ እሱ ደግሞ አንተ አንድ ስቴፕ እንድትጠጋ ያደርግሃል ከዛ በኋላ በሆነ አጋጣሚ እጅህ ላይ ካስገባህ በኋላ አጋጣሚውን መጠቀም ነው።" አለ ናታኔም በግራ አይኑ መርዕድን ጠቀሰው። " አሁን ያነሳሀት ምክንያት ገዝታኛለች።ስለዚህ ተቀብየሀለሁ አሁን የመጀመሪያው ስራየ የባሩክን ስልክ በመቀበልና እሱን የምታገኘው በኛ በኩል እንደሆነ ነግረናት ከእኛ ጋር ማቅረብ ይሆናል። ብቻ እንዴት እንደምንሰራላት እየታየኝ ነው" በማለት መርዕድ ጮቤ ረገጠ " ተው ወዳጄ በሀሳብ ገና በገና አትርካ ደስታህን በውስጥ አድርገውና ስራህን ጀምር እኔም ስራየን እጀምራለሁ ።" አለ ናታኔም መርዕድ እንደ ህፃን ልጅ ያለምንም ማስተባበያ ተቀበለና ተለያዩ። *** ናሆምና ሜላት የጊቢው በር ላይ ተገናኝተው ተቃቅፈው ወደ አድዋ ከተማ አቀኑ ። ከተማው ጋር እንደደረሱ ሶሎሜ ሆቴል ገብተው የአበባ መአት የተከመረበት ጠረንጴዛ ፈልገው ተቀመጡ። ናሆም በውስጡ " ይህን ውበት ላለማየት ብዙ ጥሪያለሁ ለማየት እድሉን አግኝቼ ያልተጠቀምኩበት ብዙ ጊዜ ነበር ያ ጊዜ ግን በዛሬ ውብ ቀን ተቀይሯል ከጥላቻ በነፃ ከበቀል በነፃ ንፁህ ልቤ ውበቷን እያየሁት ነው። ጌታየ እንዴት በዚህ ውበት ላይ በኩራት ስረማመድ ልቆይ እችላለሁ።ይገርማል አሁን ግን የእኔ አካል ናት ሳላያት ስውል ማታ ላይ ትናፍቀኝ ይዛለች ትኩስ ከንፈሯ በናፍቆትም ይገርፈኛል ወይ ጉድ አሁንም አጠገቤ ነች ተመስገን ጌታየ ከዛ ሁሉ መአት አውጥተህ ለዚህ ክብር ስላበቃኸኝ።" እንዲህ አለ። ከሀሳቡ ያነቃችው የአስተናጋጇ " ምንልታዘዝ ንግግር "እና የሜላት " ምን ሀሳብ ውስጥ ገብተህ ነው " አባባል ነበር ።ወደ ሀሳቡ ተመለሰና " አንቺ አታዥም የአንቺ ምርጫ እኮ ምርጫየ ነው። አለና ብቻ ምግቡ ጋር ወይን መምጣቱ እንዳይቀር " አለና ናሆም ፈገግ አለ " እሱማ እንዴት ይቀራል " ግማሽ ኪሎ ሸክላ ጥብስ "አዘዘችና ወይን እንዲመጣ ነግራት አስተናጋጇ ባዶ ማሳለፊያ ይዛ ተሰወረች። " ይቺ ቀን ልዩ ናት ሜሊ " አለ ናሆም " በጣም እንጅ " አለች እሷም እጁን አሻግራ ጠበቅ አድርጋ ያዘችውና " ናሆሜ በጭራሽ ላጣህ አልፈልግም በጣም ነው የማፈቅርህ ከአንተ ውጪ ሌላ መልመድ አልችልም "አለች " " ሜሊ አሁን ላይ ውስጤ የሚያስበውን ብታውቂ እንዲህ ባላልሽኝ ነበር። እኔ ከአንቺ በላይ ነው ለአንቺ ያለኝ ስሜት እኮ እኔም እኮ በጣም ነው የማፈቅርሽ። አሁን ላይ ሁለታችንም ያለን ፍቅር ለየት ያለ መሆኑ ይበልጥ ሁለታችንንም ያፋቅረናል ።ስለዚህ ከዚህ በኋላ ምንም መፍራት የለብሽም ምክንያቱም አሁን የአንችን ንፁህ ስሜት እኔም ስለምጋራ ምንም መፍራት የለብሽም " አለና እጇን ብድግ አድርጎ ሳመው። አይኖቿን ጨፈነች በደስታም ታለቅስ ነበር። *** " ሰላም ነው ኤልያና " አለ መርዕድ " ደህና እንዴት ነህ መርዕድ " አለሁልሽ ትምህርት እንዴት ነው?" " በጣም ቆንጆ ነው አንተስ ማስተርስህን ለመማር ሄድክ አይደል?" አለች ኤልያና " አዎ የወንድም ናፍቆት እንዴት እያደረገሽ ነው?" Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 9♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_7 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜላት ረዘም ያለ ስስ ተከፋች ጃኬት ከላይ ጣል አድርጋ የሰውነት ቅርጿን ለይቶ የሚያሳይ ታይት ሱሪ ለብሳ ከሸራ ጫማ ጋር ተጫምታ ከቆዳ የተሰራችውን ባጓን አንጠልጥላ ቁልቁል እየወረደች ።ስልኳን አውጥታ ለናሆም ደወለች ።ናሆምም በመጀመሪያው ጥሪ አነሳውና " ወጣሽ ?" አለ " አዎ " አለች " ጥሩ በቃ ውጪ ላይ ነኝ ነይ " አለ " እሽ መጣሁ ብላ ስልኩን ዘጋችው። * "የዘመን ጥላሸት ውስጥህ ላይ እንዳይቀር ትተጋለህ ያለፈው ትዝታህ ሲከተልህ ደግሞ ዛሬ የምታደርገውን አታውቅም በትላንት እንቅብና ቁና ልክ ተሰፍተህ ነው የምትቀረው እንጅ ከስፌቱ ልክ ወጥተህ መሳብም ሆነ መነሳት አትችልም ። ይህ የኛ የኢትዮጵያውያን እውነት ነው። " አለ አማኑኤል። አማኑኤል ይሄን ያለው የሁለተኛው ወሰነ ትምህርትን መሰረት በማድረግ 14ኛውን የአድዋ ዩኒቨርስቲ የስነፅሁፍ ዝግጅት ለማዘጋጀት ሙሉ የኪነጥበብ ቤተሰቦች በተሰባሰቡበት ነው። "ለምንድነው ከስፌቱ ወጥተን የማናስበው ?" አለ ጥግ ላይ ሆኖ የአማኑኤልን ንግግር በአርምሞ ሲያዳምጥ የነበረው ናታኔም ሁሉም ዞሩ መቅደላዊትም አብራ ስትዞር ናታኔም ነበር ።ከተነሳችበት እንደ አሞራ ከንፋ በመሄድ አንገቱን አነቀችው " አንተ ውሻ ህይወቴን በጠበጥከው ከራሴ ጋር አለያየኸኝ በአንተ ምክንያት ራሴን መሆን አቃተኝ! በአንተ ምክንያት በህይወቴ ትልቅ ነገር ያደረገልኝን ሰው የማፈቅረውን ሰው ነጠከኝ ።ባሩክን የወሰድክብኝ አንተ ነህ " እያለች አንገቱን በደንብ አነቀችው። ሁሉም ደንግጠው ፈዘው ቀሩ አማኑኤል እየሮጠ በመሄድ እጇን ከአንገቱ ላይ አላቅቆ መቅደላዊትን ወደነበረችበት ቦታ እንድትሄድ አቅፎ ይዟት ሄደ እሷ ግን ለያዥ ለገናዥ አስቸገረች ። " ይሄ ቆሻሻ እኮ ነው በእኔ ላይ የቀለደው ለምንድነው የምትገለግለኝ አማን አንቄ ብገድለው ምንኛ ደስ ባለኝ " አለች አማኑኤል ዝም ብሎ ወደ ወንበሯ እየገፋ ወሰዳት ሁሉም እርስበርሳቸው መተያየት መጠቋቆም ጀመሩ። ስለመቅደላዊት የሚያውቁ አንገታቸውን ሰብረው አዘኑ አሳዝናቸው ምፅ ይላሉ። " ለተፈጠረው ነገር እጅግ በጣም ይቅርታ እያልኩ የቲያትር ክፍሎች ወደ አዳራሽ ግቡና ቮካል ጀምሩ የስነፅሁፍ ክፍል ደግሞ ስራወቻችሁን እዚሁ ቢሮ ሆናችሁ ተገማገሙ እኔና መቅደላዊት ወጣ ብለን እንመጣለን " አለና አማኑኤል ከመቅደላዊት ጋር ወጣ " መቅዲ አውቃለሁ በዚህ ድርሰት በሚመስል ታሪክ ውስጥ የተጎዳሽው ማዕበል እንዳናወጣት ጀልባም እንደሆንሽ አውቃለሁ በዚህም ምክንያት ራስሽን እንዳልሆንሽ አውቃለሁ ዘርዘሬ የማልጨርሳቸውን ነገሮች እንደደረሱብሽም ጭምር ግን መፍትሔ የሌለው ችግር የለምና ተረጋጊ በደረስሽበት ሁሉ እንዲህ ሆነሽ አትዘልቂውም የዚህን ታሪክ ማብቂያ ቆም ብለሽ ልታስቢበትና ልታመዛዝኝ ይገባል። በዛ ላይ ራስሽን ስትሆኝ ነው ሌላውም የሚያከብርሽ ለራስሽ በምትሰጪው ቦታ ነውና መቅዲ ራስሽን እንዲህ አድርገሽ አትጣይ። በዛ ላይ ለአንቺ ደስታ የሚተጉ የሚባትሉ የሚባዝኑ የዙሪያሽን ሰወች አስቢያቸው አሁን ሀዘን ላይ ናቸው። በአንቺ ስኬት የሚሞላው አባትሽ በአንቺ የምትኮራው እናትሽ ስምሽን የሚጠሩት አድናቂወችሽ በሙሉ አሁን ምን አይነት ስሜት እንደሚሰማቸው ለማወቅ ሞክሪ እስኪ ለደቂቃስ አልመሽው ታቂያለሽ? እ? እናም አሁን የምትፈተኝበት ጊዜ ነው እሳት ውስጥ ያለሽ ወርቅ ነሽ ወይ ነጥረሽ ትወጫለሽ አለዚያ ደግሞ ቀልጠሽ ትቀሪያለሽ! ሁለቱንም የምትሆኝ አንቺ ካሰብሽና ካላሰብሽ ብቻ ነው አስቢና ተፈትነሽ ነጥረሽ ውጪ በየ ጉራንጉሩ አትርመስመሽ ይሄን ስልሽ ባሩክን ርሽው ለሱ ያለሽ ስሜት ምንም ነው ርሽው እያልኩሽም አይደለም እርሱን በልብሽ አድርገሽ ፅኚና መንገድሽን መሄድ ጀምሪ ማለቴ ነው። ወደ ቀድሞዋ አንቺነትሽ ተመለሽ። ባሩክ ሲበዛ ጠንካራ ና አስተዋይ ልጅ ነው የሱ መንፈስ ሊጋባብሽ ይገባል" በማለት አነገቷን ነካ ነካ አድርጎ ካቀረቀረችበት ቀና አደረጋት። " አየሽ ያኔ ራስሽን ስትሆኝ ባሩክን የምታገኝበትን መንገድ መሄድ ትጀምሪያለሽ በትክክልም ታገኝዋለሽ በዛ ላይ የስኮላሩ የትምህርት እድሜ አንድ አመት ነው። እዚህ ዩዝድሮዋል ስለሞላ ተመልሶ ካቆመበት ይቀጥላል ያኔም ደግሞ እሱን የማግኘት እድልሽ ሰፊ ነው። እመኝኝ ባሩክ ላይ የሚቀየረው ዘመን ብቻ ነው እሱ በራሱ ነው የሚያስበው በጊዜና በአመት አይወሰንም" አለና አማኑኤል ዝም አለ " ሞክሬ እኮ ስላልቻልሁ ነው አማን" አለች መቅደላዊት " ደግመሽ ሞክሪ ትሪያል ኤንድ ኢረርን ተምረሽ የለ ህይወት ላይም ትክክለኛ መልስና መፍትሔ እስኪገኝ መሞከር አለ ። የሙከራ ጊዜሽኮ አላለቀም ስለዚህ ቀጥይ ሞክሪ " አለና " በይ አሁን ጥሩ ስሜት ላይ ስላልሆንሽ ወደ ዶርም ልሸኝሽ " አለና ይዟት ሄደ " አሁን ግሬድሽን አስተካክይ ማንበብ ጀምሪ ውጤትሽን በፋይናል ለማስተካከል መጣር አለብሽ " በማለት ብዙ እየመከራት የብሎክ በሯ አድርሷት ሞቅ አድርጎ ሰላም ብሏት ሊመለስ ሲመለስ " አመሰግናለሁ እሽ "አለችው መቅደላዊት " ምንም አይደል " ብሏት መንገዱን ቀጠለ። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 8♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_6 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " የኔ ውድ ወንድም ሲያሳዝን በሰው ሀገር በዛ ላይ ምንም አልተመቸውም ምን ላደርግለት እችላለሁ " እያለች አጉተመተመች ኤልያና ። ኤልያና አይኖቿ ወፈር ብለው የቅንድቧ ፀጉር ሊሰራ ደርሷል። አፍንጫዋ ስልክክ ብሎ የወረደ ሲሆን ከንፈሯ አንዳች አስማት አለው። የፊት ጥርሶቿ የበለዙ ናቸው። ተክለሰውነቷ የተስተካከለና ሳቢ ነው። ኤሊያና ቶሎ ተናዳጅና ተናጋሪ ነች ከ ባሩክ ጋር ፍፁም የተለያዩ ናቸው። " መቅደላዊት ወንድሜን ከአገር አስወጣሽው አይደል ?" ከራሷ ጋር ታወራለች ውስጧን በቀል ሲንጣት ታስታውቃለች። **** ናሆም የኤልያናን ስልክ ከዮርዳኖስ እንደተቀበለ በቀጥታ ደወለ። " ሄሎ " አለች ኤልያና የተደወለውን ስልክ በድጋሚ እየተመለከተች " ሰላም ነው ኤልያና " አለ ናሆም " ደህና ማን ልበል?" አለች " ናሆም እባላለሁ የባሩክ ጓደኛ ነኝ " አለ ናሆም እንድታውቀው እና የምታየው እስኪመስለው ድረስ በእጁ ምልክት እየሰጠ " ናሆም የሚባል ጓደኛ እንዳለው አልነገረኝም አላውቅም " አለች ኤልያና " እሽ ችግር የለውም ከአድዋ ዩኒቨርስቲ ነው" አለ " እህህ አሁን ትዝ አለኝ አወኩህ ስለ አንተ ወንድሜ ባሩክ አብዝቶ ይጨነቅ ነበር ስለአንተ የወደፊት አለም ያስብ ነበር " አለች " አውቃለሁ ኤልያና ዘግይቼም ቢሆን አውቄዋለሁ አሁን አጠገቤ ባለመኖሩም እጅግ በጣም ነው የማዝነው የከፋኝም። ባሩክ ከጓደኛም አልፎ ጥሩ ወንድምም ነው። ግን ምን ታደርጊዋለሽ በደንብ ሳልጠቀምበት የሱ ጥቅም ሳይገባኝ ሄደ እናም እሱን ማግኘት ፈልጌ ነበር። ነገር ግን በምንም አድራሻ ማግኘት አልቻልኩም ። እስኪ እባክሽን የቻልሽውን እርጅኝ " ብሎ ናሆም ተማፀነ " እኔ ምን እንደማደርግልህ አላውቅም ብረዳህ ደስ ይለኝ ነበር ነገር ግን እኛም እስካሁን ልናገኘው አልቻልንም ምን አልባት የኛ ስልክ ስላለው ከደወለ ግን ልሰጥህ እችላለሁ።" አለች ኤልያና ናሆም አወራሯን ሲሰማው እንዳልደወለላቸው አመነና እሷ ያለችውን አመናት ። ናሆም ባሩክ ሲበዛ የመርህ ሰው ግትር እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል ለዛም ነው በቶሎ ያመናት።ይሄን እንደሰማና እንዳወቀ ለዮርዳኖስ የደረሰበትን ጉዳይ ሊነገራት ፈለገና ደወለላት ። ዮርዳኖስ በመጀመሪያው የስልክ ጥሪ አነሳችው " አቤት ናሆም ሰላም ነህ ?" አለች ዮርዳኖስ " ደህና ነኝ ዮርዲ " እ ምን አዲስ ነገር አለ?"አለች ዮርዳኖስ " ለኤልያና ደወልኩላት ነገር ግን አልቀናኝም" አለ " ምን አለችህ?" አለች ዮርዳኖስ "የባሩክን አድራሻ ብጠይቃት እስካሁን ደውሎላቸው እንደማያውቅና እነሱም ጰለእሱ የሚደውሉበት አድራሻ እንደሌላቸው ነግራኝ ነገር ግን ሲደውል እንደምትሰጠኝ አውርተን ተለያየን" አለ ናሆም " ኧረ በስመአብ ምን ሆና ነው እንዲህ ጨካኝ የሆነችው አሁን ቅርብ ቀን እንደደወለላትኮ ሰምቻለሁ ።" አለችና ዮርዳኖስ " ሌላ የምትቀበልበትን መንገድ አስብ ልጅቱ እየዋሸች ነው ላለመስጠት ስለፈለገች እንጅ ባሩክ አልፎ አልፎም ቢሆን እንደሚደውል መረጃ አለኝ" አለች ዮርዳኖስ " ቆይ ለምንድነው የምትዋሸው ለምንስ አለመስጠት ፈለገች?" አለና ናሆም በኤልያና ባህሪ እየተገረመ "በቃ ዮርዲ ተገናኝተን እናወራለን " አለና ስልኩን ዘግቶት ለትንሽ ደቂቃ ያህል የተቀመጠበትን ወንበር ተደግፎ ወደ ላይ ፊቱን አንጋጦ ቆየ። ከሀሳቡ ያነቃው ስልኩ በድጋሚ ሲጠራ ነበር። ደወይዋ ሜላት ነበረች " ሜሊ " አለ ናሆም ፊቱ ከመቅፅበት ፈገግ እያለ " ወይየ የኔ ፍቅር " አለች ሜላት " ጠፋሁብሽ አይደል የኔ ቆንጆ " አለ ናሆም " አወ ግን ችግር የለውም ኤረዳሀለሁ እኔ ምልህ ዛሬ ራት ውጪ እንድንበላ ፈልጌ ነበር ምን ታስባለህ?" አለች ሜላት " አንቺ ካሰብሽው ውጪ ምን ላስብ እችላለሁ በደስታ ነዋ ራት ጋባዥ ግን ማነው? እኔ ብር የለኝም ከወደእርሰዎ በኩል ፈንድ ካልተደረገ " አለ ናሆም " ረጅም ሳቅ ከሳቀች በኋላ አታስብ የዛሬውን ወጪ እኔ እሸፍናለሁ " አለች ሜላት እየሳቀች ናሆምም በሳቁ አጀባት አብሯት ሳቀ በቃ የኔ ውድ ቆንጆ ማታ ላይ ተዘጋጅተሽ ስትጨርሽ ደውይልኝ።" አለ ናሆም " እሽ እደውላለሁ " ብላው ሜላት ወሪያቸውን ቋጩ ።ናሆም ሜላትን አውርቶ እንደጨረሰ የኤልያና ንግግር ትዝ አለው " በጣም የምትገርም ልጅ ነች ፐ ከባድ ልጅ ነች ሲበዛ " አለና ራሱን በአግራሞት ወዘወዘ። ይቀጥላል ... Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 7♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_5 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ጨረቃ ገና ፅሀይ ሳትጠልቅ ከመሀለኛው የሰማይ ክፍል በግማሽ አካሏ ብቅ ብላ የብርሃን ውሏ በፅሀይ ተይዞበት በመኖርና ባለመኖር መሀል ቆማ ጊዜን ትጠብቃለች። ደራሽ አልባው ህዝብ በአደዋ ዩኒቨርስቲ ምድር ዝቅ ብሎ በተማሪ መልክ ይርመሰመሳል። ብዙ ህልም ያለው በነገ ብቻ ዛሬን የሚገፋ ትውልድ የአያቶቹ ደም በፈሰሰበት ልዩ ምድር አድዋ ላይ ሁሉንም ለአንድ የተሻለ ነገ አገናኝቷቸው ቤተሰብ ሆነው ሲማሩ ይስተዋላል። ከሀገር አልፎ ለጎረቤት ሀገራት ባዘጋጀው የስኮላርሺፕ የትምህርት ዕድል መሰረት መጥተው ያለ ምንም ስጋትና ምሬት ይማራሉ ። ምክንያቱም ይህ የሁሉም የጥቁር ልጅ ነፃ የወጣበት ምድር አድዋ ነውና። ፈረንጆቹ ብዙ ታሪክን ለማሸሽ ከኢትዮጵያ አይናቸውን ይጥላሉ ለምሳሌ የአክሱም ሀውልትን የላሊበላ መስቀልን ወሰደው ማስቀረት እንደሚመኙት ሁሉ የአድዋን ምድርንም ወስደው ከአገራቸው ቢያሰቀምጡት ይመኛሉ። ዳሩ ግን ፍላጎታቸው ህልም ሆኖ ይቀራል ። " መወደድ ፍቅር ብቻ ልቤ ደክሞልሀል፣ መንገኛው ሁሉ ወጪና ወራጁ አንተን ይመስለኛል።" እያለች ሜላት ታንጎራጉራለች ለብቻዋ ትዘፍናለች። ሜላት በአሁኑ ስአት በጣም ደስታና ተስፋ የተሞላበት ህይወት አላት።ሁልጊዜም ቢሆን በፈለገችው ጊዜና ስአት የምትወደውንና የምታፈቅረውን ናሆምን እያገኘች ፍቅሯን ትቋደሳለች። ነገር ግን የሰሞኑ የናሆም የጥፋተኝነት ስሜት ውስጡን ሲረብሸው አስተውላ እንደመጨነቅ ብላለች። የመቅደላዊት ሁኔታም ትንሽ ከበድ ብሏል።አሳዝናታለች ግን በምን መልኩ መሬዳት እንዳለባት ግን ግራ ገብቷታል። * ኤልያና በናፍቆት አይኖቿ ቀልተው ወንድሟ ጋራ ከትንሽ ወራት በኋላ ልታወራው ተዘጋጅታለች። ምንም እንዳልተረበሸችና እንዳልተከፋች ለማስመሰልና ባሩክን እንዳይረብሸው እምባዋን ጠራርጋ ላፕቶፗን ከፍታ ስካይፗን ከፈተችና ከዋይፋይ ጋር አገናኝታ ትንሽ እንደጠበቀች ባሩክ ደወለላት። ሄድሴቷን ጀሮዋ ላይ አደረገችና " ወንድሜ " አለች " አቤት እህቴ " አለ ባሩክ የፈገግታውን ጫፍ በአእምሯዋ እንዲረበብ እየላከ " ደህና ነህልኝ ናፍቀኸኝ ነበር በጣም ሲበዛ ንፍቅ አልከኝ ኮ ለምንድን ነው የማትደውልልኝ ነው እኔ አልናፍቅህም ማለት ነው? እ? " አለች የጥያቄዋን መአት እያዥጎደጎደች ። ባሩክ ጥያቄዋን ሳይመልስላት ፈገግ አለና " አንቺ ኤኮ እኔ ነሽ እኔ ደግሞ ከራሴ ጋር ነኝ ሁሌም እንቅስቃሴወቼ በሙሉ ከአንች ጋር ነው ማለት ነው ምን አልባት ይሄን ስለማታውቂ ነው እንዲህ ያልሽኝ ችጌር የለውም ይቅርታ ባትጠይቂኝም ኤረዳሻለሁ " አለና በደንብ ፈገግ አለ ። " እንዲህ እያልክ አትሸንግለኝ ህፃን መሰልኩህ እንዲህ እያልክ የምታታልለኝ? " አለች " እሽ በቃ አታኩርፊ ስለጠፋሁ ይቅርታ በጣም ከምነግርሽ በላይ ጊዜ ስላጠረኝ ነው።" አለ ባሩክ " ለእኔ የሚሆን ጊዜ አጣህ?" አለች " እንግዲህ ነገረኛ ሚስት አትሁኝ" አለ ባሩክ ሳቅ እያለ " እሽ ለዛ ነው የከሳኸው ?" አለች " ከሳሁ እንዴ ብሎ ራሱን መመልከት ጀመረ ምን አልባት የእንቅልፍ ማነስና የምግብ አለመመጣጠን ይሆናል። አየሽ የኔ እህት ነጮች እንኳን ራሳቸው የተናገሯትን ሌላ ሰው የተናገረውን በማህደር ሰድረው ያስቀምጣሉ ለየት ያሉ ሰወች ናቸው ለታሪክ ያላቸው አመለካከት በጣም ነው የሚለየው። ሲበዙ ጥንቁቆች ናቸው። እኔ በጣም ብዙ የማላቃቸው ያላነበብኋቸው ብዙ ታሪኮችን አግኝቻለሁ እና ባለኝ ጊዜ እነዚህን ታሪኮች ማወቅ ስለምፈልግ ከዚህኛው ትምህርቴ የምትተርፈኝን ጊዜና ከእንቅልፌ እየተሻማሁ ስለሆነ ነው። ትንሽ የሰውነት ክብደቴ ቀንሶ እንዲህ ስልየ በአኔቺ ፊት የተጋለጥኩት።" አለ ና አይኑን አረገበገበና ፈገግ አለ " እሽ ግን ቢያንስ ራስህን አትጉዳ " አለች " አልጎዳም እናቴ እንዴት ነች ሀገሬ ኢትዮጵያ እ ? ህዝቦቿስ በነገርሽ ላይ እዚህ ነጮች ኢትዮጵያዊ ነኝ ስትይ ከአንቺ በላይ ስለኢትዮጵያ ሲያወሩ ትሰሚያቸዋለሽ በጣም ነው የምትገረሚው እና ደግሞ ባለ ሰንሰለታማ ተራራዋ የአፍሪካዋ ሲውዘርላንድ እያሉ ነው የሚያሞካሿት ።ማንም ነጭ የእረፍት ጊዜውን ሊያሳልፍባት የሚፈልግ ሁሉ ኢትዮጵያን ቁጥር አንድ ይመርጣል። " አለ ባሩክ " እሱማ ግልፅ ነውኮ እኛ ነን እንጅ ውጪ ውጪ የምንለው። " አለች " በዛ ላይ የአሁኗ ገናና ሀገር አሜሪካ ከ150 አመት በፊት በምንሊክ ጊዜ ብዙ ነገሮችን ከኢትዮጵያ ትወስድ ነበር ። ብቻ ተይውና እሱን እና አባባ ሁሉ ሰላም ናቸው እናቴስ?" ደህና ናቸው!!" "ጥሩ በቃ ብዙ ጊዜ የለኝም አንዳንድ ጊዜ እንዲህ እያመቻቸሁ አወራሻለሁ እነ እናቴንም አወራቸዋለሁ " አለ " እሽ ደግሞ ያቺ ዮርዳኖስ መጥታ ነበር ስለ አንተ ልትጠይቀኝ " አለች " ኦ ዮርዳኖስ? ሰላም በይልኝ በድጋሚ ከመጣች በእኔ ስም ትምህርት አሪፍ ነወይ በርቺ በይልኝ " አለ ባሩክ ስልኩን ለመዝጋት እየተቻኮለ " እሽ እልሀለሁ በቃ ቸው አለች ኤልያና እሱም ቻው አላትና ተለያዩ ። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 6♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_4 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ የሚያዩትን ማመን አቃታቸው። መቅደላዊት ከናሆም ጋር ሲያይዋት በጣም የሚያስፈራ መልከገፅና ተክለ ሰውነቷ ላይ ደርቀው ቀሩ። ሁለቱም ከእንደገና ተያዩ እጅግ በጣም ነበር የምታሳዝነው።ናታኔም ተነስቶ ከአካባቢው ተሰወረ።መርዕድም ተከተለው። " ናሆም ስለ ባሩክ ማሰብ አደከመኝ ባሩክ ሰውነቴን ሁሉ አዛላቸው ከዚህ በላይ አልችልም " አለች መቅደላዊት " እሽ ይገባኛል አውቃለሁ መቅዲ አይዞሽ ጠንከር በይ እኔ አሁን ዮርዳኖስን አገኛታለሁ " አለ ናሆም " አብረን እናግኛታ እኔም ላወራት እፈልጋለሁ " አለች መቅደላዊት " እሽ " አለ ናሆም መከልከሉ አስፈላጊ ሆኖ ስላላየው ናሆም ዮርዳኖስን በቀጠራት እና በጠራት ስአት መጥታለች። ዮርዳኖስ ናሆምንም ሜላትንም መቅደላዊትንም እያፈራረቀች ተመለከተቻቸው በሁኔታቸው ግራ ተጋብታለች ።እነሱም ዝም ብለው ይመለከቷት ጀመሩ " እየውልሽ " ናሆም ሀሳቡን ጀመረ " ሜላት መቅደላዊትን ይዛት እንድትነሳ በአይኑ ምልክት ሰጣት። ሜላትም የመቅደላዊትን እጅ ይዛ ልትነሳ ስትል መቅደላዊት ላለመነሳት አቅማማች ነገር ግን ብዙም ሳታስቸግር ተነሳች። ከሜላት ጋር ተቃቅፈው ሄዱ ። ናሆም በአይኑ ከሸኛቸው በኋላ " በቅድሚያ ስለመጣሽ በጣም ነው የማመሰግነው ዮርዳኖስ " አለ " ኧረ ችግር የለውም " አለች ዮርዳኖስ " እንደምታያት መቅደላዊት በባሩክ ምክንያት እየተሰቃየች ነው። ምንም ነገር እያደረገች አይደለም ምግብም አትበላም ትምህርቱንም ትታዋለች። ውሎና አዳሯ ማልቀስ ነው የባሩክን ስም እየጠራች ባጭሩ ከምነግርሽ በላይ እየተሰቃየች ነው ለዚህም ደግሞ እኛ ልንረዳትም ልንረዳትም ይገባል።ስለዚህ በቻልሽው እርጅን " አለ ናሆም ።"በእውነት በጣም ነው የማዝነው ታስዝናለች ግን እኔ በምን መልኩ ልረዳት እችላለሁ የምረዳበትን መንገድ ንገረኝና ምንም ችግር የለውም " አለች ዮርዳኖስ " አንቺ የምትረጅን የናሆምን ትክክለኛ አድራሻ በማፈላለግ ይሆናል። እሱን ካገኘሽልን በቃ ትልቁን እግዣ ነው ያደረግሽልን" አለ ናሆም ።ዮርዳኖስ ራሷን ግራ ና ቀኝ ወዘወዘችው " ምነው?" አለ ናሆም " ይህን ባደርግ ደስ ይለኝ ነበር ግን እኔ ባለፈው ወደ ውጭ ሳላገኘው ስለሄደ በስካይፒ ላወራው ፈልጌ አዲሱን አድራሻ እህቱን ስጠይቃት አወንታዊ ምላሽ አልሰጠችኝም ነበር። ለማንም ስልክ እንደማትሰጥ ነው የተናገረቸኝ" አለች ዮርዳኖስ " የሷ ስልክ ይኖርሻል እንዴ?" አለ ናሆም " አወ ይኖረኛል ብላ ሴለኳን አውጥታ የባሩክን እህት የኤሊያናን ስልክ ሰጠችው " እስኪ ስለ ልጅቱ የተውነ ንገሪኝ ባህሪዋን በተመለከተ " አለ ናሆም " ያው ያን ያህል የተጋነነ መጥፎ ባህሪ የላትም ግን አንዳንድ ችግሮች አሉባት የሷን ጉዳይ ማስቀደም ትወዳለች ትንሽ ሰው ያለማዳመጥ ችግር አለባት ።ለባሩክ ያላት ፍቅር የተለየ ነው። በጣም ነው የምትወደው ባሩክ ወደ ውጪ ሲሄድ በጣም ነው የከፋት። እና ለስለስ አድርገህ ካወራሀት ያን ያህል የምትከብድ አይመስለኝም። እንደሚሳካልህ ተስፋ አደርጋለሁ ግን እኔ በበኩሌ የምትጠይቀኝን ከመመለስና ስለሁኔታው ከማስረዳት የዘለለ ምንም ልረዳህ አልችልም። አሁን ሁሉም ቁልፎች ያሉት እህቱ ጋ ነው። እህቱን እንደምንም ብለህ አሳምን " አለች ።ናሆም ግራ የገባው መሰለው ከሜላት ጋር ያለችውን ምስኪን ሴት አትኩሮ ተመለከታት ሕይወት ለመስጠት ስትባዝን የነበረች ጠንካራ ሴት ዝላ ታየችው አንጀቱ ተላወሰላት ግራ ግብት አለው አንገቱን አቀረቀረ ። ዮርዳኖስ ተጨነቀች እሷንም ግራ ገባት ምን ማድረግ እንዳለባት ጨነቃት " እየውልህ ናሆም ምን መሰለህ አሁን የምትቆዝምበት ጊዜ አይደለም በዛ ላይ መቅደላዊት በጣም ተጎድታለች ስለዚህ የቻልከውን ሁሉ አድርግ " አለች ዮርዳኖስ ። " የኔ የፀፀትና የበቀል ፅዋ የያዘው የግፍ ውሀ በጉሮሮው እየወረደ ያለ መሰለው ።አልቅሶ ቢወጣለት ተመኘ ራሱን እስኪጠላ ድረስ ተከፋ። ግን ደግሞ ሀዘንና መከፋት አንዳች ፋይዳ እንደሌለው አመነ።" እሽ ዮርዳኖስ ለእርዳታሽ በጣም አመሰግናለሁ እና ከቻልሽ ስልኳን ከሰጠሽኝ ይበቃኛል ከዛ በላይ ያለው ነገር ለእኔ ተይው የቻልሁትንም ያልቻልሁትንም የማልችለውን ሁሉ አድርጌ ደስታዋን እመልሳለሁ።" አለ ናሆም ዮርዳኖስም ናሆምም ተመሰጋግነው ተነሱ ። መቅደላዊት ዘወር ስትል ዮርዳኖስ ስትሄድ አየቻት እየሮጠች ሄደች ።ዮርዳኖስ ደንግጣ ስትዞር መቅደላዊት ነበረች። ለምን እንደመጣች ገብቷታል " እባክሽ እምቢ እንዳትይኝ ባሩክ ናፍቆኛል ከዚህ በላይ መሄድ አይደለም መንቀሳቀስ አልችልም እሱን የማገኝበትን መንገድ ብቻ አሳይኝ እኔ እሄዳለሁ።" አለች መቅደላዊት እምባወቿ በመንታ ጉንጮቿ ቁልቁል እየወረዱ ። ዮርዳኖስ የመቅደላዊት ስቃይ አመማት ድርጊቷ ነገራት አሳዘነቻት ። አቀፈቻትና ሁሉንም ነገር ከናሆም ጋር አውርተናል ከዚህ በኋላ አታስቢ እኔም ከጎንሽ ነኝ ምንም ቢፈጠር" አለች ዮርዳኖስ እሷም እምባዋ አይኗ ላይ እያቀረዘዘ። ናሆም መጥቶ ሁለቱንም አለያያቸውና ዮርዳኖስን ሸኝቶ መቅደላዊትን ይዞ ወደ ልዑል ራስ መኮንን አደባባይ!! ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 5♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_3 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ክፋት መጨረሻው ራስን ከራስ ጋ ማጣላት ነው! አየህ እኔ አሁን የሰራሁት መልካም ነገር ሳይሆን እኔ ላይ የሚነሳው ወይም የሚወራው የሰራሁትን መጥፎ ስራ ብቻ ነው። በሕይወትህ በጣም ከባዱ ይሄ ነው። አሁን ናሆም ልብ ላይ እኔ ምታወሰው በመጥፎ ታሪክ እንጅ በመልካም ነገር አይደለም ይሄ ደግሞ እኔን ይረብሸኛል።" አለ ናታኔም ከሰል የመሰለ ፊቱን ይበልጥ እንዲጨልም እያደረገው። " እኔ ለሷ ብዙ ዋጋ ከፍያለሁ በእሷ ከዚህ በላይ መጎዳት አይኖርብኝም የለብኝምም ሜላት የኔ ብቻ ነው መሆን ያለባት " አለ መርዕድ መሬቱን በቡጢ እየነረተ " እዚህ ላይ ነው ስህተትህ አሁን ይሄ መንገድ እኔ መቅደላዊትን ለራሴ ለማድረግ ስጠቀምበት የነበረው መንገድ ነው። እሱ ደግሞ ስህተት ነው የመንገዱን ልክ አለመሆን ከኔ በላይ ሌላ ሰው ሊያስረዳህ አይችልም። ስለዚህ አሁን ማድረግ ያለብህ ነገር ከልጅቱ ጋር ያለህን ግንኙነት ማስተካከል እሷ ለአንተ ያላትን አመለካከት እንድትቀይር ማድረግ ነው። ለምሳሌ ድሮ ሁልጊዜም እንደምታፈቅራት ትነግራት ከሆነ አሁን እሱን ትተወውና ናሆም ጋ ያላትን ነገር እንድታጠናክር ትነግራታለህ ያዘንክ በመምሰል በዚህን ጊዜ አንተን እንደ አማካሪ ሁሉ ልትጠቀምህ ትችላለች። ታዲያ የሁለታችሁ ተግባቦት በጨመረ ጊዜ ናሆም ጋ የሚጣሉበትን መንገድ እንፈጥራለን። አንተ ብቻ በጥንቃቄ ተራመድ ሌላውን ለእኔ ተወው።" አለ ናታኔም ።መርዕድ በናታኔም ሐሳብ የተስማማ ይመስላል። ራሱን በአወንታ ነቀነቀ።" ቆይ አንተስ ምን አሰብክ ስለ መቅደላዊት?" አለ መርዕድ ናታኔም እንደማቀርቀር አለና " አየ መርዕድ እኔማኮ አንዴ ነገሮች ተበላሽተውብኛል።በራሴ መንገድ ብሄድ ኖሮ እንዲህ አልደርስም ነበር ከመቅደላዊት ጋርም ሆነ ከናሆም ጋር ኮ ማውራት አልችልም ። መቅደላዊት በዚህ ስአት እንደ ነፍስ አጥፊ ነው የምትመለከተኝ ስታየኝ ትቀያየራለች የምትሆነው ይጠፋታል።እኔም ፀፀት ፣ስቃይ ፣ቁጭትና ውስጤን ገብቶታል ይበልጥ እሷን እየፈለኳት መጣሁ። ምን ያህል እንደማፈቅራት የማውቀው እኔ ነኝ አውቃለሁ ባሩክ ጋ የውለታ ፍቅር ነው የያዛት ሴት ልጅ ደግሞ በንደዚህ አይነት ስሜተ ላይ ይጠቃሉ።ስለዚህ እሷን ማፍቀር ማቆም አልችልም። የማስባቸውን በሙሉና ለኔ ይጠቅማሉ የምላቸውን አደርጋለሁ።ይበልጥ ደግሞ አሁን ራሴን አሻሽየ ልቀርባት ይገባል።" አለና ናታኔም ብድግ አለ መርዕድም አብሮት ተነሳ። " እየውልህ ናታኔም አንተ ገና ልጅ ነህ በዚህ እድሜህ ልታስብ የሚገባው በብዛት ስለትምህርትህ ነው ገባህ? እሷን ደግሞ በጣም ከወደድካት ድርቅ ባለ መልኩ አታድርገው።አረጋጋው ነገሮችን በደንብ ተመልከታቸውማ እኔና አንተ ላይ በጣም ከረውብናል። መቅደላዊት አንተን በጣም ጠልታሀለች ልታይህ ሁሉ አትፈልግም ናሆም በጣም አዝኖብሀል። ይሄን የነሱን እይታና ለአንተ ያላቸውን አመለካከት መቀየር የምትችለው ከግትርነትህ አቋም ውጣና ተለሳለስ።"አለ መርዕድ " እሽ እስኪ የቻልሁትን እሞክራለሁ ግን ከምነግርህ በላይ ሰልችቶኛል በዛ ላይ እኔ ጥሩ ስሜት የማይሰማኝ ከባሩክ ጋር ስትሆን ነበር። " አለ " እና መቅደላዊትን የማናገር ዕቅድ የለህም ማለት ነው?" አለ መርዕድ " እአእ አንተ ደግሞ እቅድማ እንዴት አይኖረኝም ግን እሽታዋን የማገኝበትን መንገድ እያሰብሁ ነው እንጅ" አለ ናታኔም " አየህ ናቲ በዚህ የፍቅር አለም ውስጥ ሁለታችንም ተመሳሳይ ታሪክ ነው ያለን ሁለታችንም የምናፈቅራቸው ሴቶች ሌላ ወንድ ወደው ለሰከንድ እንኳ ስለ እኛ አያስቡም እኛ ደግሞ በተቃራኒው ፍቅር ትርጉም የሌለው መድረሻ ነው። ማለቂያ የሌለው ስሜት እንደማትፈለግ እያወክ ስሜትህን ብቻ ማዳመጥ ይህ የፍቅር ውስብስብ የመድረሻው ጎዳና ነው። እኔ ሜላት አንተ መቅደላዊት አዎ እኛ እኛ እንጀምራለን እነሱ ደግሞ ይጨርሳሉ ።ግን እመነኝ በዚህኛው ድል የኛ ናት ድል የአይታክቴ ሰወች ናት ይል የለ። አወና በዚህ እንኳ ደስታቸውን አሳጥተንም ቢሆን ደስታችንን ማምጣት አለብን እናመጣለንም። " አለና መርዕድ ረጅም ሳቅ ሳቀ የያዛትን ማስታወሻም ዘረጋና የሜላትን ስዕል ተመለከተ። ግርጌው ላይ ደግሞ " አፈቅርሻለሁ " የሚለውን ፅሁፍ በሀሰሳ አነበበውና ሸፈነው። ናታኔም አጁን ጉልበቱ ላይ ጭኖ ቁልቁል ወደ መሬት አዘቀዘቀ መሬቱ አንዳች የሚለው ነገር ያለ ይመስል ወደ ምድሩ አይኑን ያንቀዋልላል። ዝም ጭጭ ዝም ሁለቱ እርስበርስ ተያዩ አይናቸውን ማመን አልቻሉም። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 4 ♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_2 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ፀሀይ ከወትሮው በተለየ መልኩ በቀይ ምንጣፍ ላይ ለረጅም ስአት ቆየች። ነፋሱ ከወደ ምዕራብ እየተነሳ ወደ ምስራቅ አቅጣጫ ይነፍሳል ዛፎቹም እንደ ካህናት ወረብ ሲያሸበሽቡ ምድር ላይ የወዳደቁት አበቦች ከእንደገና በነፋሱ ሲበረበሩ ሽቅብ ወደ ላይ እየተነሱ ሲወድቁ መመልከት የተፈጥሮ የምሳሌ እሽክርክሪት ነው። ናሆም ከአንዲት የዛፍ ስር የተተከለች እምነበረድ ላይ እግሩን ከእግሩ አነባብሮ እጆቹን በግራና በቀኝ ዘርግቶ አይኖቹን ሽቅብ ወደ ዛፏ ቅርጫፎች ልኮ ከንፈሩን እያሸራመጠ ይመለከታል። ከትንሽ አፍታ ምልከታ በኋላ አንደኛውን እግሩን ከሌላኛው እግር ሸክም አንስቶ ራሱን አስተካክሎ ካስቀመጠ በኋላ እጆቹን ከእንደገና ፊት ለፊት ጣቶቹን ከጣቶቹ በማስተቃቀፍና በማሰካካት አይኖቹን ቁልቁል ወደ መሬት ወረወረ ለረጅም ስአት ካቀረቀረ በኋላ ከሐሳብ አለሙ ያነቃው " ምን ሆነህ ነው እንደዚህ በጣም የተከዝከው?" የሚለው የሜላት ንግግር ነበር። ናሆም እንደመደንገጥ ብሎ አይኖቹን እያርገበገበ ከተቀመጠበት ብድግ ብሎ አቀፋት። ጉንጮቹን አገላበጠቻቸው አይኖቹም ቀልተው አየቻቸው ምን ሆነህ ነው ናሆየ? " ምን እሆናለሁ የኔ ቆንጆ የመቅደላዊት የእለት ተዕለት ሁኔታ እያሳሰብኝና እያስጨነቀኝ ነው። የዚህ ሁሉ አልፋ እኔ መሆኔ ደግሞ ከመቅደላዊት እከል ያስከፋኛል ያሳዝነኛል ።ምናልባት የእኔ አመለካከት ከመጀመሪያው የተሻለና መልካም ቢሆን ኖሮ መቅደላዊት እዚህ በማይገባት የህይወት ማዕበል ውስጥ ገብታ ባልተናወጠች ነበር። አየሽ የዚህ ሁሉ ታሪክ የሚጀምረው የእኔ የብቸኝነት አለምና ከአባቴ ውጭ ሳላውቅ ማደጌ ነው። ይሄ ምን አልባት የእኔ አስቀያሚው ጊዜየና ወቅቴ ነው። ግን የአንኔ የብሶትና የበቀል ታሪክ ምንም የማያውቁትን ሶስት ልጆች ታሪካቸውን አበላሸ።በቃ እኔ ከዚህ የመጥፎ አለም ትዝታ ላመልጥ አልችልም ብሸሸውም ይከተለኛል። ለምሳሌ ተመልከች ባሩክ በራሱ አለም ይኖር የነበረ ልጅ አሁን ግን በእኔ ምክንያት ሔደ ናታኔምም ከሁለት ያጣ ሆኖ እንደምታይው ነው። መቅደላዊትን ተመልከች ጭራሽ የሌለ አለም ነው የምትኖረው። አሁን መቅደላዊት የኔን ሕይወት ልትደግም ነው እኔን እንዳከሙኝ ለእሷም አስታማሚ ሊያሳፈልጋት ነው የአስታማሚዎቿ ታሪክ ደግሞ እንዴት እንደሚሆን አይታወቅም ብቻ ታሪክሽ እንዲህ እያለ እየተፃፈ ይቀጥላል ሳያስቡት ታሪክሽ ላይ የገቡ ሰወች ደግሞ መራራውን የታሪክሽን እንፋሎት እየቀመሱት እየተወኑት ይቀጥላሉ። " እና ይሄ አያሳዝንም?" አለና ቀና ብሎ ተመለከታት " እረዳሀለሁኮ አባ አንተኮ ያሳለፍከውን ታሪክ ወደኸው አይደለም ያሳለፍከው እነሱም አንተ ሕይወት ላይ እንዲገቡ ፈልገኸውም አይደለም ብቻ እያንዳንዱን ነገር በራስህ እያስገባህ ራስህን ከኮነንክ ምንም ወደፊት መራመድ አትችልም ።ስለዚህ እባክህ ወደ ባለፈው ሕይወትህ ጋር ሚመስል አሁን አትግባ " አለች ሜላት " አይዞሽ መግባትስ አልገባም ግን የመቅደላዊትን ጉዳይ የሆነ እልባት መስጠት አለብኝ!!!! " አለ ናሆም " አውቃለሁ በቻልከው መልኩ ትረዳታለህ ምንም ችግር የለውም እኔም በቻልኩት ሁሉ እረዳታለሁ አብረን እናደርገዋለን የመጀመሪያ ስራችን የሚሆነውም የባሩክን አድራሻ መፈለግ ይሆናል ። " አለች ሜላት " አመሰግናለሁ የኔ ቆንጆ በጣም አለና በስሱ ከንፈሯን ሳም አድርጎ አቀፋት። ሜላት ፊቷ በብርሀን ተሞሏ አይኖቿ በፍቅር የፊት ገፁ ላይ ተንከራተቱ። ልቧ ያለልክ መምታቱን ቀጠለ!!! ናሆም ግን በሀሳብ ረዝሙን የመቅደላዊት የስቃይ መንገድ ገረመመው። ራሱን ወዘወዘ አሳዘነችው።"ወንድ ልጅስ መቼም ይችለዋል እሷ ግን በጣም ይከብዳታል።" አለ በሆዱ የሜላትን እጅ ይዞ ተነሳ ። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 3 ♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።