en
Feedback
ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Open in Telegram

እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sistu

Show more
Ethiopia2 732The category is not specified

📈 Analytical overview of Telegram channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች

Channel ቆየት ቆየት ያሉ ሙዚቃዎች (@riyit) is an active participant. Currently, the community unites 10 338 subscribers, ranking in the Other category and 2 732 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 10 338 subscribers.

According to the latest data from 04 December, 2024, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 285 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
እንደኔ ኦልድ ዘፈኖች ወዳጆች ኑ ከኔጋ ዘና በሉ @Riyit Join ይበሉቻናል ላይ full ዘፈኖች ያገኛል ደስ ያሉትን ዘፈን እየተገባበዝን ዘና ፈታ እንላለን ዘፈን የፈለጋችውትን ለመምረጥ @Heluuuu_bot ውድ የቻናላችን ተከታዮች ሀሳብ አስተያየት መስጠት ከፈለጉ እንዲሁም ለቻናላችን ማጋራት ሚፈልጉት ቆየት ያለ ሙዚቃ ካለ 👉 በነኚ በኩል ያግኙን @mark_sist...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 December, 2024), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Other category.

10 338
Subscribers
+524 hours
+637 days
+28530 days
Posts Archive
#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል-41 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ መቅደላዊት " የናሆም ዝግጅት ምን ይሆን?" በሚል የውስጥ ጥያቄ ታጅባ ፈተናዋን ጨረሰች ፈተናዋን የጨርሰችው ከስአት በመሆኑ አስራ ሁለት ስአት ገደማ ለናሆም ደወለችለት። ናሆም እንደጨረሰች ያውቃል። ነገር ግን ስልኳን አላነሳውም ስራ እየሰራ ነበር። መቅደላዊት ደግማ ደወለች። አሁን ባያነሳው እንደበቀደሙ ልትረበሽ እንደምትችል ስላሰበ ስልኩን አነስቶ ማውራት ጀመረ። " እሽ ጨርሻለሁ ምንድን ነው?"አለች መቅደላዊት በመጓጓት " ጥሩ እንኳን ደስ አለሽ። በቃ ዶርም ጠብቂያት ሜላት ትመጣለች። እኔ ጊቢ ውስጥ አይደለሁም " ብሎ ከመጨረሱ የመቅደላዊት ዶርም ተንኳኳ።ስልኩን አልጋዋ ላይ አስቀምጣ ዶርሙን ከፈተች። ዮርዳኖስ ነበረች። ከዮርዳኖስ ጋ ተሳሙና " ዮርዲየ ደህና ነሻ?" አለች መቅደላዊት " ደህና ነኝ መቅዲ " አለች ዮርዲ "ደግሞ አምሮብሻል" አለች መቅዲ ዮርዳኖስን በደንብ እያየች። " አመሰግናለሁ መቅዲ " አለች።በዚህም ጊዜ በሩ ተንኳኳ ። መቅደላዊት ከፈተችው። ሜላት ነበረች። "ዋው " አለች መቅደላዊት ሜላትን አይታ ሜላት ረጅም ቀሚስ ለብሳለች። አረንጓዴ ቢጫ ቀይን ጥለት ያደረገው ቀሚሱ የሜላትን ውበት አግዝፎታል። ሜላት አሁን በለበሰችው አለባበስና ልብስ እንኳን ወንድን የሴትን አፍ የሚያስከፍት ነው። ለዚህም ነው መቅደላዊት " ዋው " ብላ አፏን የዘጋችው " ምንድን ነው ዛሬ እንዲዝ ያማረባችሁ?" ብላ መቅደላዊት አንዴ ሜላትን ሌላ ጊዜ ዮርዳኖስን እያየች ጠየቀች። " ምንም በቃ ዝም ብለን ዛሬ ወጣ ብለን እንዝናና በሚል ሀሳብ ነው። እስከ መቼ ድረስ ተጨናንቀን በፈተና በሀሳብ። " አለች ሜላት ወደ ዮርዳኖስ እያየች። " አዎ ሜሊ ልክ ነች አልፎ አልፎ እንዲህ ወጣ ብሎ ጥሩ አየር መቀበሉም ትልቅ ነገር ነው" አለች ዮርዳኖስ የሜላቴን ሀሳብ አፅንኦት በመስጠትና የራሷንም ማብራሪያ በመጨመር። " እና አንቺም ልበሺ እና ባሩክ ማለቴ ናሆም ከተማ እየጠበቀን ስለሆነ " አለች ሜላት። መቅደላዊት ሜላት የባሩክን ስም ስትጠራ እንደመደንገጥ ብላ ነበር ነግር ግን ማለቴ የናሆም ስትል ሜላት ናሆም ለማለት ባሩክ እንዳለች አምና ያላትን ልብስ እንዲሁም ቆንጆ የሚያደርጋትን ልብስ ከሻንጣዋ መበርበር ጀመረች። መቅደላዊት ሞዴል ሆና ብዙ ጊዜ ስለቆየች የተለያዩ ልብሶችና አልባሳት አሏት። " እስኪ ኑና ምረጡልኝ ጓደኞቼ " ብላ ዮርዲንና ሜላትን እርዳታ ጠየቀች። ግብዣዋን ተቀብለው አብረዋት የሚያስውባትን ልብስ ማመስ ጀመሩ ። አኔዱን ልብስ ያነሱና የእሷ ደረቴ ላይ አድርገው እያዩ ከቀየሩ በኋላ ከስንት ፍለጋና ሙከራ በኋላ አንዲት ቀሚስ ተገኘች። ቀሚሷ አሁን መቅደላዊት ያለችበትን የሰውነት ክብደት ቅጥነትና ርዝመት ያማከለች በመሆኗ ከመቅደላዊት ጋ ልክክ አለች። " ይቺ አንደኛ!" አሉ ዮርዳኖስና ሜላት በአንድ ድምፅ። ሜላቴ በምርጫቸው ተስማምታ እሷም ወዳት ነበር ለብሳ አንድ ላይ ከዶርም ወጡ። ሶስት ሆነው ሲወጡ የተመልካችን አይን ይስቡ ነበር። በየ መንገዱ ዳር ብዙ ለከፋዎች ነበሩ ። " ሶስቱ ወንዶች የት ሄደው ነው?" " ሶስቱ ወንዶች እኛ እንሁን ወይ?" "እንዲህ አምሮባችሁማ ብቻችሁን እግዜርም አይቀበለውም። ........" የሚሉ ለከፋዎች ተሰነዘሩ። እነ መቅደላዊት ምንም ባለማለት ወጡ። አንዳንዶች ደግሞ መቅደላዊትን እንደዛ አምሮባት ሲያዩ " አየሀት አሁን ባለፈው ባሩክ ናፈቀኝ ጥሎኝ ሄደ ምናምን እያለች። ስታለቅስ እነበር። ሴቶችን አትመን ይሄው ያን ሁሉ ለቅሶ ረስታ ይሄ ሌላ ወኔድ ለማግኘት ነው እንዲህ ሽክ ብላ የምትወጣው። ሴት ልጅ አንዳንዴ የአዞ እንባ ነው ያላት። በፍፁም እንዳታምናት ምንም ቢሆን አትጎዳም። አየህ እሷን ምንም አልሆነችም ባሩክ ግን ከአገር አገር ተንከራተተ እሷን ለመርሳት ለመተው ላለማየት። እሷ ግን ረሳችው አየ ሴት " አለ ለጓደኛው። ** ባሩክ የናሆምን ስልክ እየጠበቀ ሩሙ ውስጥ ተቀምጧል። ትንሽ ወደ ራሱ መለስ ሲል የምትሳልበት መቅደላዊት ናት። አድዋ ከመጣ ወደ ሶስት መፅሐፍ አንብቦ ጨረሷል። ወደ ውጪም ብዙ ጉዳዮችን ወደ ሚማርበት ዩኒቨርስቲ ኢሜል አድርጓል። ከእህቱም ጋር በየቀኑ ነው ሲያወራ የነበረው። የናሆም እናት ባሩክ አድዋ እንደመጣ ናሆም ሲነግራት በጣም ተደስታ " ልጄ ባሩክን ማግኘት እፈልጋለሁ እና እሱ ጋ ልምጣ " ብላ ስትጠይቀው ናሆምም ደስ ስላለው " እሽ እማዬ ደስ ካለሽ ነይ ግን ባትደክሚ አሪፍ ነው ወይም ቤት ይዤው እመጣለሁ " አለ ናሆም " ብዙ ጊዜ ነው እንዴ የሚቆየው? " አለች የባሩክ እናት። ናሆም ይህን ጥያቄ ስትጠይቀው ባሩክ የሚቆይበት ጊዜ አጭር እኝደሆነ ትዝ አለውና " ውይ ረስቼው እማዬ አጭር ጊዜ ነው ያለው በቃ በፕሌን ነይ " አለ " እሽ ልጄ " አለች። ናሆም ደስ ብሎት ዝግጅቱን ማዘጋጀት ጀመረ። አብረውት በርከት ያሉ ልጆች ሆቴሉን እያዘጋጁ ነው። በዚህ ጊዜ ሜላት ደወለችለት። ስለኩን አነሳውና " ሜሊ ወደ መነን ሆቴል ሂዱና እዛ ዘና በሉ ትንሽ ቆይቼ እደውላለሁ " ብሏት ወደ ስራው ተመለሰ። መቅደላዊት ዮርዲና ሜላት መነን ሆቴል ተቀምጠው ኮካቸውን እየጠጡ ያወራሉ። ናሆም አብረውት ከሚሰሩት ልጆች ጋ ሆኖ ደፋ ቀና ይላል ጠረምጴዛውን እያስተካከለ ወንበሮቹንም በደንብ እያስቀመጠ። *** ባሩክ ግራ ገባው ናሆም እደውላለሁ ብሎት እስካሁን አልደወለም።ምን አስቦ ነው? ምን እያደረገ ነው።" አለና አይኑን ወደ ሰማይ ልኮ በዝምታ ተዋጠ። ባሩክ አላስችልህ ሲለው ለናሆም ደወለ። ናሆም ግን ስልኩን አላነሳም ነበር። ናሆም ደግሞ እነ ሜላትን እያወራ ነበር ። ናሆም እነ መቅደላዊትን ሲያዘጋጀው ወደ ነበረው ሕብስት ሆቴል ጠርቷቸው ተቀምጠዋል መቅደላዊት ሆቴሉን ለአፍታ ስትቃኘው ቆየች። ሆቴሉ በተለያዩ የኢትዮጵያ ነገስታት ፎቶ ያሸበረቀ እንዲሁም ኢትዮጵያዊነትን የሚገልፁ የተለያዩ ብሔሮች ልብስ እንዲሁም አገልግሎች ሞሰቦች የተለያዩ ከለር ያላቸው ሌማቶች ተሰቅለውበታል። ከሁሉም ግን "ዓድዋ የእኛነት ምስጢር " የሚል ፅሁፍ በሆቴሉ ቢም ላይ በፍየል ቆዳ ተፅፎ ተሰቅሏል። ከፅሁፉ በታች ፊታውራሪዎቹንና እቴጌ ጣይቱን አስከትሎ ምንሊክ ከነፈረሱ በትልቅ ሸራ ላይ ሰፍሯል። ቤቱ አስገራሚ ድባብ ያለው ቤቴ ነው።ታዲያ ከቤቱ ውበት በተጨማሪ እነ ናሆም ሆቴሉን አስውበውት ነበርና። ይሄ ሁሉ ውበትና ዲኮር ያስገረማት እንዲሁም ያሰደነቃት መቅደላዊት ተደንቃ ና ተገርማ ብቻ አልቀረችም ጠየቀች " ይሄ ሁሉ ሽር ጉድ ምንድን ነው? በሆቴሉ ውበት ላይ ሌላ ውበት?" አለች ። ናሆምም ፈገግ እያለ እንግዲህ በጥያቄ የሚጀምር ምሽትና ያማረ ምሽት እንድናሳልፍ ነው!" ብሎ መልሶላት ዘወር አለ። የሚጠጣና የሚበላ አዞ አብሯቸው ተቀመጠ። " አሁን በደንብ እናውራ " አለና ናሆም ተደላድሎ ተቀመጠ። ባሩክ ከላይ ግሬይ ሸሚዝ ከታች ያልደመቀ ጥቁር ሱሪ ለብሶ ረጅም ቡትስ ጫማ ተጫምቶ አንገቱ ላይ ስካርፕ ቢጤ ጣል አድርጎ ከያዘበት አልጋ ወጥቶ ወደ ሕብስት ሆቴል የሚወስደውን መንገድ በእግሩ ተያያዘው ። እነ ናሆም ደግሞ በጨዋታ ጨዋታን እየወለዱ እየተሳሳቁ ለፍቅራቸው ለወዳጅነታቸው ፅዋቸውን እያነሱ ጨዋታቸውን ማድራቱን ተያያዙት።ባሩክ ወደ ሕብስት ሆቴል አቅራቢያ ሲደርስ ልቡ በፍርሃት ራደ ተሰምቶት የማያውቀው ስሜት ተሰማው።ቆም አለና ልቡን ደገፍ አድርጎ " እንዴ ምን ሆኜ ነው? ለምንድን ነው እንዲህ ልቤ ያለቅጥ የሚመታው? " ሲል ራሱን ጠየቀ መልስ የሌለው

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_40 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ "ለምንድን ነው እንደዚህ ያለኝ? ምን ሆኖ ነው ባሩክ? ምን ሆኖ ይሆን? ራስ ምታት ያዛት ባሩክማ የሆነ ነገር ሆኗል ለዛ ነው ይህን ሳምንት ሰውንቴን ያለቅጥ ሲሰማኝ የነበረው ። ምን ሆኖ ይሆን ራሷን በሁለት እጇ ግጥም አድርጋ ያዘችው። የታክሲው ረዳት " የመጨረሻ " የሚለውን መቅደላዊት አልሰማችውም ነበር። " ወጣቷ የመጨረሻ ነው እያልኩኮ ነው " አለ መቅደላዊት ከእንደገና ብርግግ ብላ " እሽ " አለችና ቀስ ብላ ራሷን ደግፋ ወረደች። ትንሽ ረፍት ካደረገች በኋላ በሌላኛው መስመር ወደ ዩኒቨርስቲ የሚመልሳትን ታክሲ ይዛ ተመለሰች። ጊቢ እንደደረሰች ለናሆም ደወለች። " አቤት መቅዲ " አለ " ናሆም ወደ ጊቢ ተመልሻለሁ ላገኝህ እፈሌጋለሁ!" አለች በቀዘቀዘ አነጋገር " አይ ዛሬ አይደለም የምንገናኘው ፈተና ሲያልቅ ነው!!" አለ ናሆም " በናትህ ናሆም ሳትደብቅ ንገረኝ ባሩክ የሆነው ነገር አለ? እ ምንድነው የሆነው እ? ናሆም ንገረኛ " አለች መቅደላዊት እያለቀሰች ። " ኧረ ምንም አልተፈጠረም መቅዲ ለሌላ ነገር ነው ለሌላ ዝግጅት ነው ባሩክ ምንም አልሆነም በቃ ቆይ መጣሁ ጊቢ መግቢያው በር ላይ ያለው ካፌ ጠብቂኝ " ብሎ ናሆም ደንግጦ የያዛውን ሀንድ አውት ጥሎ በፍጥነት ተነሳ። ናሆም ይሄን ስጋቷን ቀደም ብሎ አለማሰቡ አበሳጨው " ሆደ ቡቡ እንደሆነች እያወቅሁ ሌላ ዘዴ መፍጠር ነበረብኝ አሁን እሷ የሚመስላት የመሰላት ከፈተና በኋላ የምናረዳት ነገር እንዳለ ነው። ነገር ግን የምናረዳትም ነገር እንዳለ ሆኖ ግን የምናበስራት የሀዘን መርዶ ሳይሆን የደስታ ነው እኔ ያሰብኩት እሷ አሁን አስባ የተረበሸችበትን ሀሳብ ሳይሆን ከፈተና በኋላ ባሩክን እንድታገኘው ማድረግ እና በሩቅ ያሰበችውን በቅርብ እንድታገኘው ነው። ሌላ አላሰብኩም። ይሄ ያሰብኩትን ሀሳብ የምገልፅበት አንዳች ነገር ግን ሊኖር ይገባል የመጥፎ ጥርጣሬዋን ማስወገጃ መላ ግን ልዘይድ ይገባል " በማለት ከራሱ ጋር ያወራ ጀመር። ይሄን እያሰበ ናሆም የዩኒቨርስቲው መግቢያ በር ላይ ካለው ላውንች ደረሰ። መቅደላዊት ጉንጮቿ በእንባ ርሰዋል። አይኖቿ ቀልተዋል ፣ አፍንጫዋም ደም መስሏል። ናሆምን እንዳየች ተነስታ አንገቱ ስር ተወሸቀች እንዳዲስ ታለቅስ ጀመር። ናሆም በራሱ በጣም በሸቀ " ኧረ መቅዲ በማርያም አታልቅሺ አባቴ ይሙት አንቺ እነደምታስቢው አይደለም። መቼም አባቴ ይሙት ብየሽ እንደማልዋሽሽ ታውቂያለሽ። በሆነ ባልሆነውም አባቴ ይሙት አልልም። ስለዚህ በእናትሽ ተረጅኝ በቃ ምንም አልተፈጠረም ይሄ እኔ ደግሞ አትቁረጭ ያልኩሽ አንቺ የምትወጅውን ነገር ሀማድረጌ ነው የሚያስደስትሽን ነገር እኛንም የሚያስደስተንን " አለ ። መቅደላዊት ፊቷ ላይ ያለውን እንባዋን በሶፍት እያጠራረገች ለመረጋጋት ሞከረች። ናሆም በአባቱ ከማለ እውነቱን እንደሆነ ና በስህተት እንኳ ለምንም ነገር ብሎ በውሸት በአባቱ እንደማይምልም ታውቃለች። " እሽ ናሆም አምንሀለሁ። ምን ላድርግ ከመቼውም ጊዜ በላይ በዚህ ሳምንት በተደጋጋሚ ያየሁት ጊዜ የለም ይህን ሳምንት ባሩክ በጣም ቀርቦ ነው የታየኝ እና አንተ ቅድም እንደዛ ስትለኝ ምን ላስብ በጣም ደነገጥሁ ጥሩ ያልሆነ መልዕክት ወደ አእምሮየ ገባ ለዛ ነው። እኔ ባሩክ ምንም እነዲሆን አልፈልግም " አለች መቅደላዊት " አውቃለሁ መቅዲ ግን ደግሞ እንደዚህ አይነት እሳቤ መልካም አይደለም። የምትወጅው ሰው በአንቺ እጅ አይደለም የሚጠብቀው ፈጣሪ ነው። ከአንቺ ስራ በላይ በሆነ ነገር ራስሽን መጥመድ የለበትም በቃ እሱን ፈጣሪ ይጠብቀዋል። አኔቺ ይሄን ያህል መጨነቅም ሆነ ማሰብሽ ረፍት አልባ ኑሮ ያደርግብሻል። ደግሞም በፈጣሪ ስራም አይገባም ። ስለዚህ መልካም ነገር ማሰብሽ ተገቢ ሆኖ እያለ ግን ደግሞ አለፍ ያለ ሀሳብም ጥሩ አይደለም። ደግሞም እንዲህ ቢሆንስ ኤያልሽ ከምታስቢ ጥሩ ጥሩውን ብታስቢ ለአንችም በጎ ነው ለሱም መልካም እድል መመኘት ነው።" አለ ናሆም መቅደላዊትን እያባበለ አይኖቿን በመዳፉ እየጠራረገ። " እሽ ናሆም ስላስጨነኩህ በጣም ይቅርታ " አለች " አይ ይቅርታማ መጠየቅ ያለብኝ እኔ ነኝ እንደዚህ እንድታስቢ በማድረጌና ባላሰብሽው ጊዜ በማለቴ " ብሎ አቀፋት መቅደላዊትም አቀፈችው። " እ አሁን ምን ትጠጫለሽ ወይስ የሚበላ ነገር?" አለ ናሆም ፈገግ እያለ መቅደላዊትም በስሱ ፈገግ አለች። ፈገግታዋ ከፅሌመት አለም የሚያስወጣ የብርሀን ፈገግታ ይመስላል። ስቴስቅ ፅሀይ በምትወጣበት ጊዜ ምዴርም ብቻም ሳትሆን ሰማይም እንደሚፈታና እንደሚፈካዉ ሁሉ የመቅደላዊትም ፈገግታ ከማለዳዋ ፀሀይ የማይተናነስ ወገግታ ነው። የናሆም ግብዣ ምንጩ ጥፋት እንደሆነ ማሰቡ እንደሆነ ስለገባት " እሽ ስፕራይት ልጠጣ አዛዥ አንተ ብትሆንም ጋባዥ ግን እኔ ነኝ " አለች። ናሆም ሳቅ አለና " ምነው ብር አለኝ ትኬት ልቆርጥ ነበር አልሽ " አለ " አዎ እውነት ነው እኮ ታዲያ " አለች " እና እኔ ባሰብኩት እኔ ባዘዝኩት ነው አንቺ ምትከፍይው ምን አይነት ንቀት ነው። ነው አንተ ብር የለህም ነው " ብሎ ሳቀ ። " አልወጣኝም በቃ እሽ ትከፍላለህ ምን አይነት ጊዜ ነው ልክፈል ማለት ሆሆሆ " አለችና መቅደላዊት የፈገግታውን አፀፋ በፈገግታ መለሰችለት። ናሆምና መቅደላዊት እንዲህ እየተሳሳቁ ያለፈውን እኔደመርሳት አድርገው ናሆም ኮካ መቅደላዊት ደግሞ ስፕራይት ጠጥተው ናሆም ሂሳቡን ከፍሎ ወጣ። ተቃቅፈው ወደ ላይ ወጡ። ናሆምም እሷን ወደ ዶርሟ የሚያስገባው መገንጠያ መንገድ ላይ ተሰናብቶ ወደ ዶርሙ ሄደ። **** ባሩክ አድዋ ላይ ከትሞ መቅደላዊትን የሚያገኝበትን ቀን እየቆጠረ ነው። ብቻውን ስለሷ ያሰላስላል። "መቅደላዊት የፍቅር የርህራሄ ሁሉ ጥግ ናት እሷን ማፍቀር መታደል ነው። ስትስቅ ጠፈርን ታደምቃለች አእምሮዋ የዘመኑን የስነፈለክ ተመራማሪዎችን ያስንቃል። እሷ ልክ እንደ እነ ኢትዮጵያዊቷ ልዕልት አንድሮሜዳ እንደ ኢትዮጵያዊ ንጉስ ሴፊወስ እንደ ኢትዮጵያዊቷ ንግስት ካሴዮፕያ ኮከብ ሊመራላት ይገባል። ስታወራ አንጀትህን ታርሰዋለች የውስጥህኔ ትረዳዋች ቀፈገግታህ በአይኖችህ በዝምታህ ውስጥህ ላይ ያለውን አለም ትረዳዋለች። ምንም ሳትናገር አይኖችህን ብቻ አይታ መፅሀፍ ሙሉ ስለ አንተ ትፅፋለች። እሷ ከሁሉም የዘመናቼኔ ሴቶች ትለያለች። እሷ ብቻዋን የፍቅር ከተማ ናት ልክ እንደ ፓሪስ። አሁን ላይ ግን ደስታዋን ሸርሽሬዋለሁ። ግን እኔ ምን ላድርግ መቅደላዊት የደስታዋን ጠርዝ ያገኘች መስሎኝ ነበር። በናታኔም የምትደሰት መስሎኝ ነበር። እኔን ከመጤፍም አትቆጥረኝም ብየ ነበር። እኔን ድልድይ ለማድረግ ያሰበች መስሎኝ ነበር ከሷ የራኩት ። በእኔ ምክንያት እንደዚህ ትሆናለች የሚል እሳቤም አልነበረኝም። እኔ ሁሉንም ሳሌናገራት በዝምታ ያለፍኳት ዝምታየን እንድትሰማው እና እንድትረዳው እንጅ እንድትጎዳበት አልነበረም። ቢሆንም ግን እሷ የኔ ልክ ናት አሁን ያለፈው የትዝታ ሀይቅ ውስጥ ከማይታይ ከማልገልጠው ብራና ላይ አስቀምጨዋለሁ። አሁን እስከፈለገችኝ ድረስ አለሁ። እስከምትፈልገኝ ርዝመት ድረስ። የምሄደው በሷፍላጎት ብቻ ነው። እኔ የራሴ ፍላጎት የለኝም ፍላጎቴ ፍላጎቷን መሰረት ያደረገ ነው። አሁንም ያለፈውን እንደማትደግመው አሜናለሁ። ምክንያቱም ከችግርህ ለመዳንና ከስጋትህ ለመራቅ ያለህ ብቸኛ አማራጭ ማመን ብቻ ነው። ማፍቀር መውደድ ማመን ነው። ከተጠራጠርክማ ከሰርክ ሳትጠራጠር ከምትከስረው ተጠራጥረህ የምትከስረው

📚መቅደላዊት📚 ዛሬ ይጠናቀቃል😊😊😊😊😊😊😊 ሁለት ክፍል ብቻ ቀርቶናል ምን የሚፈጠር ይመስላቹሃል? 3:30 ለይ ይለቀቃል የትም እንዳትሄዱ አብራችሁን ናችሁ?

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_39 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ አውሮፕላኑ አሉላ አባነጋ አየር ማረፊያ ለማረፍ ወደ ሰማይ ሲቀዝፍ ያስገባቸውን ጎማወቹን አውጥቶ ፍጥነቱን በመቀነስ አኮበኮበ። ከብዙ ዝግጅትና ጥንቃቄ በኋላ አውሮፕላኑ ምድር ላይ አረፈ። መቐለ ውቧ ከተማ ከነባህርዳር ናዝሬት ሐዋሳ ጋር በጥራትም በንፅህናመም የተስተካከለች ድንቅ ከተማ። ነዋሪዎቿ እንግዳ ተቀባይ ናቸው።ብዙውን ጊዜ ወደ ተለያዩ የትግራይ ክፍለሀገሮች ለመሄድ በመቀለ ናቸው መቀሌን ሳይደረስ አይሄድም። ምን አልባት በሀገር አቋራጭ ከሆነ ነው እንጅ በፕሌን መቀሌን ሳይነካ የሚሄድ የለም። የመቀሌ ነዋሪ ልክ እንደሌላኛው የኢትዮጵያ ክፍል ህዝብ አኗኗር አበላል እንግዳ ተቀባይነት ያየለበት ህዝብ ነው። ባሩክ መቀሌን እጅግ በጣም ይወዳታል። መሸሌን ሳይነካ ወደ አድዋ መሄድ አይፈልግም። መቀሌ ላይ የተወሰኑ ቀናትን ወስዶ ተዘዋውሮ ከተመለከታት በኋላ ነው ወደ ዓድዋ የሚሄደው።የያዛትን አነስተኛ ሻንጣ ጀርባው ላይ አዘለና በቀስታ ከፕሌኑ ወረደ። አጠገቡ የነበረችው ልጅ ተከተለችውና " እባክህ ወንድሜ ባሩክ ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ስላልሆነ አንድ ነገር እንዳደርግ ያሰብኩትን ነገር እንዳደርግ እርዳኝ " አለች።ባሩክ ቆም ብሎ እንደማሰብ አደረገና " መጀመሪያ የምትይውን ልስማ?" አለ " ራት " ልጋብዝህ? " አለች ። ባሩክ ዝም አለ ለአንድ ደቂቃ ያህል " እ በቃ ራሴ ላይ ቅሬታ ስላለብኝ መካሻ እንዲሆን ብየ ነው " አለች። ባሩክ ፈገግ አለና " ግን ስለ እራት ግብዣ ምንነት ታውቂያለሽ? " አላት። ድንግጥ አለችና " ምን በቃ የተለየ ነገር የለውም ራት መብላት ነዋ!" አለች " አዎ እኔም በዚህ አስተሳሰብሽ እንደሆነ ራት ልጋብዝህ እንዳልሽኝ የገባኝ ለዛም ነው የጠየኩሽ፡ ለማንኛውም ራት ስትጋብዥ በጣም አስበሽ መሆን አለበት። አንድን ወንድ ራት ልጋብዝህ ስትይው ከእራት በኋላም ስላለው ነገር አስበሽ መሆን አለበት። ብዙ ወንዶችም ሆነ ሴቶች ስለ ራት ግብዣ ይጨነቃሉ ከአለባበስ ጀምሮ ከምንም ጀምሮ ያ ጭንቀታቸው ደግሞ አንዳች ቴርጉም ይሰጠናል። ትርጉሙም ከእራት በኋላ የሚኖረው ምሽትና አዳር ነው። ስለዚህ ግብዣሽን አስተካክይ እኔ ለእራት ግብዣ ለየት ያለ አመለካከትና ፍቅር ነው ያለኝ። እራት ሌላኛው የደስታየ መለኪያ መስፈሪያ እንቅብ ነው። ፍቅርን የምቋደስበት ከጨረቃዬ ጋ ከዋክብትን የምናሳጅብበት። አእዋፋትን የምንሰማበትን ዜማዎችን የምንቀዳበት። ትርጉም ያላቸውን ሹክሹክታችንን የምንሰማበት፤ በትንፋሽ የምንግባባበት፤ በፍቅር የምንሳሳምበት፤ ጊዜ ቢኖር ያ ነው። በዚህም መሠረት እራት ግብዣሽን ሳልቀበለው ቀርቻለሁ። እራትሽን እራት ለሚገባው ለእኔ ግን ፍላጎትሽ ብቻ አጥግቧኛል የይቅርታሽን ልክ ለክቼበታለሁ አመሰግናለሁ " አለና ፈጠን ፈጠን ብሎ ትቷት ወደ ታክሲዎች መቆሚያ አመራ። ልጅቷ እንደ ፀሀይ በሚያብረቀርቁት አይኖቿ ባሩክን ተከተለችው። ባሩክ ለመጨረሻ ጊዜ እንኳ ወደ ኋላ ሳይመለከታት መንገዱን ወደ ሰማዕታት ሀውልት አቅጣጫ ሄደ። **** ጥሩ ያልሆነውን ውስጧን በሙዚቃ ለማረሳሳትና ለማዝናናት የሙዚቃ ፋይሏን ስትጎረጉር የጂጂን ሙዚቃ አገኘች። የጂጂ ሙዚቃ ላይ ለደቂቃ ቆም አለችና ብዙ አሰበች። ከአሰበች በኋላ ከፈተቻት። በእርግጥ የከፈተችው ሙዚቃ ከትዝታዋ የሚያነቃት የሚያስወጣት ሳይሆን መልሶ የሚዘፍቃት ነበር። ጁጁን እንደ ባሩክ ሆና ለማዳመጥ ሞከረች። የምትለው ነገር ትንሽ ይከብዳታል። "ጂጂን ሊረዳት እና ሊያዳምጣት ሊሰማት የሚችለው ባሩክ ብቻ ነው። እሷን ከሱ ውጭ ምንም ነው " ብላ ታምናለች ትከራከራለችም። መቅደላዊት ። የጂጂ አቦሸማኔን፣ ገራገሩን፣ ሳላየው አላድርምን ሁሉንም በየተራ ካዳመጠች በኋላ የጀሯ ማዳማጫዋን ከስልኳ ነቅላ ወደ ኪሷ አስገባችው። " ፍቅር ግን ምን አይነት ሀይል ነው? እየወደድከው መኖ፤ እንደሚመጣም እንደማይመጣም ሳታውቅ መጠበቅ፤ እሱን መናፈቅ የሚያስችል ትልቅ መግነጢሳዊ ሀይል፤ ዋውውውው ይህ በጣም ይለያል። እኔ ለፍቅር እስረኛ ነኝ ፍቅር እንደፈለገ እያደረገኝ ነው። እያወራኝ ነው ብቻየን ሲፈልግም እያፈላሰፈኝም ነው። " አለችና መቅደላዊት ትኬት ለመቁረጥ ወደ አድዋ ከተማ ተነሳች። የፈተና ጊዜ ለመጨረስ አንድ ፈተና ነበር የቀረው። እሱ እንዳለቀ ቶሎ ወደ ቤተሰቦቿ ሄዳ እነሱ ጋ የተወሰነ ጊዜ በመጫወት ከዛ በኋላ ከእንደገና ወደ አድዋ መጥታ ወደ ውጪ ነው ለመሄድ ያቀደችው በዚህ ፕሮግራም ነው ለመንቀሳቀስ ያሰበችው። * ባሩክ መቀሌ ትንሽ ሲዟዟር እና ትንሽ ሲዝናና ከቆየ በኋላ ውሎ አዳሩን አድዋ ካደረገ የተወሰኑ ቀናትን አስቆጥሯል። ለናሆም ደወለ " አቤት ባሩክ ደህና ነህ? " " እኔ ደህና ነኝ ወዳጄ አንተ እንዴት ነህ ፈተና እንዴት ነበር?" አለ ባሩከ " ቆንጆ ነበር!" " መች ነው የምትጨርሱት?" አለ ባሩክ " እኛ ከ አራት ቀን በኋላ እነ መቅደላዊት ደግሞ ነገ ይጨርሳሉ።" አለ ናሆም " ኧረ ? ጥሩ አጋጣሚ ነው። ለማንኛውም አድዋ ነኝ እሽ ፈተናችሁን እንዳላዘናጋችሁ ብየ ነው እስካሁን ያልነገርኳችሁ። " አለ ናሆም ደስ አለው " እንኳን በሰላም መጣህ ወንድሜ እና የት ነው ያለኸው እንምጣ!" አለ ናሆም " አይ ፈተናህን ጨርስ ከተገናኘን ፈተና እንዳለብህም እረሳዋለሁ አንተም ትረሳዋለህ። ስለዚህ ጨርስና በሰፊው ነው ተገናኝተን ናፍቆታችንን የምንወጣው። " አለ ባሩክ " እ...ሽ እሽ ካልክ እንግዲህ " አለ ናሆም በባሩክ ሀሳብ ለጊዜውም ቢህን ተስማማ። ናሆም ባሩክን አውርቶ ከጨረሰ በኋላ ለመቅደላዊት ደወለ። መቅደላዊት በመጀመሪያ ጥሪ አነሳችው።" እጅሽ ላይ ኘበርጨስልክሽ መቅደላ?" አለ ናሆም ያነራችበትን ፍጠነት ስልኩ እጇ ላይ እንደነበር የገመተውን ግምት ልክ ለመሆን። " አዎ ጎግል እያደረኩኮ አሜሪካ ላይ የተሻለ የሚባለውን ዩኒቨርስቲ " አለች ናሆም ራሱን ነቅነቅ አድርጎ " ጥሩ አድርገሻል አሁን የት ነሽ? " አለ " እ አሁን ታክሲ ውስጥ ወደ ከተማ እየሄድኩ " አለች " እንዴ ፈተና ጨረሽ እንዴ ገና መስለሽኝ እኮ ነው?" አለ ናሆም ግራ ገብቶት ።" አይ ገና አልጨረስኩም ግን ከነገ ወዲያ ያልቃሌ ስለዚህ ትኬት ላላገኝ ስለምችል ቀድሜ ልቁረጥ ብየ ነው። ፈተና በጨረስኩ ማግስት ወደ ቤት እሄዳለሁ።" አለች " ኧረ ቆይ መቅደላዊት አትቁረጭ መጀመሪያ ከእኔ ጋር እንገናኝ የሆነ ነገር አስበናል እኔ አንቺ ሜሊና ዮርዲ እና እኛ ያሰብነው ደግሞ ከአንቺ ፈተና በኋላ ነው ያሰብነው። እና ትኬቱን አትቁረጭ በኋላ አላገኝም ይሞላል ብለሽ አስበሽ ከሆነ እኔ እቆርጥልሻለሁ። " አለ ናሆም " ማለት አልገባኝም ምን ዝግጅት ነው ያለው ነውስ ያልነገርከኝ ሌላ ነገር አለ?" አለች መቅደላዊት " ነይና እናውራ "ብሏት ስልኩ ዘጋ። መቅደላዊት ልቧ ከሁለት ተከፈለ። ይቀጥላል .... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 40♥️ ነገ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_38 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ወዲያው ሁሉም ነገር መጣላት..... እሷ 5ኛ አመት እያለች ነው። ሴቶች ስለ አንድ ሲኒየር ልጅ ያወራሉ። አንድኛዋ ተነስታ " ሴትን ልጅ በጣም ነው የሚያናንቀው። ሴት ፍጡር አትመስለውም። ስለ ሴት ሲያወራ እኮ ብታዩት ፊቱ እንዴት እንደሚቀያየር በቃ ብቻ ምን ልበላችሁ የሆንን አስፈሪ እንሰሳት ነው የምንመስለው ብቻ የሆነ ቀን ባገኘው እንጃ ብቻ ምን እንደማደርገው" አለች " ሌላኛዋ ተቀበለቻት " አዎ እሷ ልክ ናት በየ አንዳንዱ ምሽቱ ስለ ሴት ልጅ ድክመት ስለ ሴት ልጅ መጥፎነት ሳይናገር አይወርድም። ከሴት ያልተገኘ ነው የሚመስለው ። እኔም በበኩሌ ወይ ከተማ ወይ የሆነ ብታ ባገኘው አልለቀውም። " እያለች ትፎክራለች ሌላኛዋም ትቀበላትና የእራሷን የጥላቻ ረቂቅ ታረቃለች። አንድ ላይ ባሩክን ስለመደብደብ የሆነ ነገር ስለማድረግ ሴራ ይጎነጉናሉ። " ይሄ ሁሉ በምናቧ መጣባት አጠገቧ ያለው ልጅ ነው በእነዛ ሴቶች አፍ ሴትን የሚያጥላላው ተብሎ የተከሰሰው። አሁንም እነዛ ሴቶች ያሉት ነገርን በአይኗ የተወሰነ ፍንጭ እንኳ ባገኝ ብላ የምትመለከተው ይመስላል። ባሩክ በአንድ ጊዜ ስትቀየርበት ግራ ገባው ሁለት ጊዜ ጠይቋት ዝም ስትለው ትቷት ወደ ራሱ የሀሳብ አዙሪት ተመለሰ። ባሩክ ለማይሆን ነገር ጊዜ ማጥፋት አይፈልግም አንድ ሀሳብ ላይ ብቻ የሙጥኝ ብሎ አይቀመጥም። በሀሳብ ይከፋፈላል ወዲህም ወዲያም እንደ ገባር ወንዞች ተነጥሎ ያስባል ይመረመራል። "እሽ አቶ ዲዮጋን !" አለች ልጅቷ ከትውስታ አለሟ ስትነቃ ።ባሩክ አሁን ገባው ለምን በዝምታ እንደተዋጠች ለምን እንዳልመለሰችለት። ለምን በንቀት እና በጥላቻ ስትመለከተው እንደነበር።ባሩክ የሰጣት ምልሻ የድንጋጤም የፍርሃትም የምንም ሳይሆን ዝም ብሎ ፈገግ አለና " ማነሽ እህቴ አእምሮሽ ውስጥ ምን ሲመላለስ እንደነበር አላውቅም ግን በእኔ ሲመላለስ እንደነበር ለመረዳት ችያለሁ! እኔ አንቺን አላውቅሽም ስለማላውቀው ሰው ማንም ሰው ምንም ቢለኝ አልቀበልም እኔ እያንዳንዷን ነገር መርምሬና አረጋግጨ ነው የምሰራው። ዝም ብየ በአንድ አሳቢ ብቻ እንደሚመራ ስብስብ አልነዳም ። የራሴ የሆነ የሀሳብ መፍጫ መሰለቂያ መጅና ወፍጮ ያለኝ ሰው ነኝ። በምን ምክንያት እንደዚህ እንደሆንሽ አላውቅም ማወቅም አልፈልግም ማስረዳትም አይጠበቅብኝም ግን አኔቺን የምነግርሽ ለአእምሮሽ የሰጡሽን ሳይሆን ያገኘሽውን ያወቅሽውን የመረመርሽውን መግቢው። ያኔ በአመክንዮ የተሞላ በእርግጠኝነት የታጀበ አእምሮ ይኖርሻል። ከወገንተኝነት ፈቀቅ ብለሽም ስታወሪ ትደመጫለሽ። እኔ ዲዮጋን ሳልሆን የዲዮጋን አድናቂ ነኝ። ዲዮጋን በጣም ሲበዛ ግድየለሽ ለእውነቱ ብቻ የሚጨነቅ ድንቅ ፈላስፋ ነው።አንድ ነገር ልንገርሽና ሀሳቤን ልቋጭ ምክንያቱም እኔና አንቺ የተለያዬ የርዕዮተ ዓለም ስለሆነ ያለን መግባባት አንችልም። አንድ ጊዜ በታላቋ ግሪክ እንዲህ ሀሆነ የግሪክ ህዝብ ውጭ ላይ መመገብ ነውር ነው ብሎ ያምናል። ውጭ ላይ አይመገቡም ሁሉም ነገር ውስጥ እንዲሆን ነው የሚፈልጉት ነገር ግን ይሄን ህጋቸውን ዲዮጋንን ስላላሳመነው የነሱንም ህግ ይሽርና ውጭ ላይ መመገብ ያዘወትራል። የዲዮጋንን ምግባር እና የሀገሬውን ህዝብ ህግ አለማክበሩ ያበሳጫቸው ግሪካውያን አኔዴ ቀን ዲዮጋን ወደሚበላበት ቦታ በመሄድ ዲዮጋን እንደለመደው ውጪ ላይ ሲመገብ ዙሪያውን ይዞሩና በአንድ ላይ " ውሻ ውሻ ውሻ " ይሉታል። ዲዮጋንም ጩኸታቸውን ከመጤፍ ከምንም ሳይቆጥር ምግቡን በዝግታ ይበላል " ውሻ ውሻ ውሻ " የሚለው ድምፅ እየበረከተ መጣ ።ግሪካውያኖቹ ዲዮጋንን እንዲህ የሚሉት በስድባቸው ተሸማቆ ውጭ ላይ እንዳይመገብና ህጋቸውን እንዲያከብር እንዲቀበል ነበር። ነገር ዲዮጋን " ውሻ ውሻ " በሚለው ድምፃቸው ታጅቦ ምግቡን ከጨረሰ በኋላ ከተቀመጠበት ተነሳና " በሉ እናንተ ግሪካውያን አሁን እኔ በልቼ ጨርሻለሁ ወደ ቤታችሁ መሄድ ትችላላችሁ ።ውሻ የሚባለው ሰው ሲበላ የሚጮህ ነው። " ብሏቸው ትቷቸው ሄደ ።በንግግሩም በታተናቸው። ይሄን ያሌኩሽ ያለ ነገር አይደለም በሁኔታሽ ተገርሜ ነው። በእርግጠኝነት አሁን እኔ ምን አድርጌሻለሁ ብየ ብጠይቅሽ መልስሽ ምንም ነው። ወይም የተወሰኑ ልጆች ስለ እኔ ሲያወሩ የነበረውን ወሬ እንደማስረጃነት ታቀርቢልኝ ይሆናል። ግን ይሄ አኔቺነትሽን ሰውነትሽን ያሳጣሻል። እጌዜር የእህቴን ልጅ ገድሎብኝ እሱን ጠልቼ ሌላ አምኛለሁ። እንደማለት ነው የሚቆጠረው በራሱ ላይ ባልደረሰ ያልደረሰን ሰው ተጠያቂ ማድረግና መጥላት። አየሽ አንቺ በማታውቂው ነገር ባልደረሰሽ ነገር ደስታሽን አጥተሻል። ይሄኔ የጓደኞችሽን አለዚያም የዶርም ሜቶችሽን ወሬ ባትሰሚ ከእኔ ጋር በጥሩ ጨዋታ አሪፍ ጊዜ እናሳልፍ ነበር። በእርግጥ አንቺ ነሽ እንጅ እኔ ጥሩ ጊዜ እያሳለፍኩ ነው። የምወደውን ሀሳቤን እየነገርኩሽ ስለሆነ። እና አኔቺ ወጣት ነሽ ብዙ ነገር ይጠበቅብሻል የጥላቻሽን ሥንጭ አድርቂ ባልሆነ ነገር የተተበተበውን አእእምሮሽን ቀስ ብለሽ ፍቺው።" አለና ፊቱን ወደ መስኮቱ አዞረ። ኮረዳዋ ግራ በተጋባ ሁናቴ ባሩክን ትመለከተው ጀመር። ለብዙ ደቂቃዎች በሁለታቸው የነበረውን ዝምታ ለመስበር " በጣም ይቅርታ! ይሄን ያህል ካስከፋውህ?" አለች ባሩክ ፈገግ አለና " ኧረ እህቴ እኔን አላስከፋሽኝም እኔ በሰዎች ጥሩ ያልሆነ አመለካከት ወይም ጥሩ ያልሆነ አተያይ አልበሳጭም በመነፀራቸው ግን እበሳጫለሁ። የሚያዩበትን የሚያስተውሉበትን መነፅራቸውንም እተቻለሁ። አንቺም ላይ ያደረኩት ይህንኑ ነው እንጅ በአንቺ ተናድጄም ተከፍቼም አይደለም! በዛ ላይ እኔ ለእራሴ ለመናደድ ካልፈለኩ በቀር አልናደድም ማንም ሰው እኔን የማነደዱ መብትም ብቃትም የለውም" አለ። ዝም አለች በተናገረችው ነገር ሳታፍር የቀረች አትመስልም። ባሩክ መፅሀፉን ገለጥ አደረገ። ካቆመበትም ማንበቡን ቀጠለ። ይቀጥላል .... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 39♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_37 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ዶክተር ወንድማገኝ የፈተና ክፍሎችን እየተዘዋወረ ከጎበኘ በኋላ መቅደላዊትን አገኛት " ይሄ የማጠቃለያ ፈተና ሲመጣ ጥሩ ትዝታ እንደሌለሽ አውቃለሁ ቢሆንም ግን አንዳንድ ጊዜ ከነዛ መጥፎ ከሆኑ ትውስታዎች መራቅ በራሱ ራስን ማብቃት ነውና የባለፈው ፋይናል ላይ የተፈጠረውን ችግር አስታውሰሽ እንዳትረበሽ ፍፁም በተረጋጋ ሁኔታ ፈተናሽን ስሪ! በተረፈ መልካም ዕድል" ብሏት ሄደ ። "እሽ ዶክተር በጣም አድርጌ አመሰግናለሁ " አለች በፈገግታ " ምንም ችግር የለም አንቺ ብቻ አስደምሚኝ እንጅ ሌላው ነገር ቀላል ነው ። ከዛ በኋላም የምትፈልጊው ነገር እንዲደረግልሽ መጠየቅ ትችያለሽ " አለ ዶክተር " እንግዲህ የቻልኩትን አደርጋለሁ በተረፈ እግዚአብሔር ይጨመርበት! " " በይ በርቺ " ብሏት ሄደ። መቅደላዊት ውጤቱን ማምጣቷ እያጠራጠራት መጥቷል። በትክክል እያነበበች እንዳልሆነም ይሰማታል። ነገር ግን የቻለችውን እያደረገች ነው! እሷ ግን በዝግጅቷ እየረካች አይደለም። በዛ ላይ የባሩክ ናፍቆት ያናውዛታል። መቅደላዊት ከነ ብዙ ችግሯ ሆና ትምህርቷ ላይ ለማተኮር አማራጭ የሌለው ነገር እንደሆነ አስምራበታለች። መቅደላዊት የምታነበው ነገር ቶሎ ሲገባት ራሷን መጠራጠር ትጀምራለች። " እንዴት ለምን? አሁን ፈተና ላይ ይመጣል " የሚል ጥያቄ ራሷን ትጠይቅና በብዙ መልሶች ራሷን ታሻማዋለች። ይሄንን ችግሯንም ለዮርዳኖስ አማክራት የመለሰችላት መልስ " አንቺ በጣም ጎበዝ ና ፈጣን አእምሮ ስለሆነ ያለሽ ቶሎ ይገባሻል ስለዚህ ብዙ መገረም መጨነቅ የለብሽም አለቀ ፈተናው የሚመጣው አንቺ ከምታነቢውና ስታነቢው ቶሎ ከገባሽም ብዙ ቆይቶ ከገባሽም ጭምር ነው። ስለዚህ በማይሆን ጥያቄ ና ሀሳብ መስራት የሚችለውን አእምሮሽን አታጨናንቂው። ዝም ብለሽ አንብቢ በአንቺ ማንበብ ነው የውጪ እድልሽ የሚከናወነው " የሚል ነበር። ከዛን ጊዜ በኋላ የዮርዳኖስን ምክር ለመቀበል ብትሞክርም ሙሉ በሙሉ ግን ከጥርጣሬዋ ልትወጣ አልቻለችም። ቢሆንም ግን አሁን ላይ የተሻለ አቀባበል ነው ያላት። በዚህ ውጥንቅጥ መሀል ሆና ወደ ፈተናው አመራች። ** ናሆም ሜላትን " ሜሊ እኔ አሌቻልኩም መቅደላዊትን ሳያት እያፈርኩ ነው የሆነ ከባድ ነገር ነው የደበኳት በዚህ መሀል የሆነ ነገር ብትሆንስ እ? ፀፀቱን የምችለው ይመስልሻል ሁሌም ቢሆን ራሴን ስጠላው ነው የምኖረው ግዴለሽም የፈለገው ነገር ይምጣ ምርጫውን ለእሷ እንተወውና ልንገራት ነግረናት የራሷን ውሳኔ ትወስን? አይመስልሸም? እኔ አልቻልኩም እንዴ እሷን ሳገኛት የምታወራኝ ስለ ባሩክና ስለባሩክ እንዴት እሱን እንደምታገኘው እና ደግሞ ሰሞኑን የሆነ ነገር እንደተፈጠረ ስሜቷ ነግሯታል። ባሩክ እንደቀረባትና አብሯት እንዳለ ። እናም ውዴ በጣም ተጨነኩ ምን ላድርግ እሽ ግራ ገባኝ እኮ? አለ ባሩክ ፊቱ ክርትት እያለ " እረዳሀለሁ እኮ የኔ ማር ሳልረዳህ ቀርቼ አይደለም ህመምህም ያመኛል ግን ሳትነግራት ቀርተህ ከምትጎዳው በላይ ነግራሃት የምትጎዳው ስለሚበልጥ ነው። ስለዚህ አለመንገርህ ከመንገርህ አንፃር ጎልቶ ከታየ ይሄ ይሻላል ብየ ነው! በእርግጠኝነት ብትነግራት ወይ አዲስ አበባ ልሂድ ትላለች ወይም ደግም እዚሁ ይመጣል ጠብቂ ብንላት እንኳ ደህና ሆና የምትጠብቀው ይመስልሃል በቃ እሱን እያሰበች አታነብም።አሁን ግን ስላልነገርናት እሱን ለማግኘት አጥብቃ ትምህርቷን እያጠናች ፈተናዋን እየተፈተነች ነው ስለዚህ ካለችበት ጥሩ ማዕድ እንደማንሳት ስለሚሆንብን እንተዋት ጊዜው ሲደርስ ፈተናው ሲያልቅ ባሩክም ስለሚመጣ ያኔ ታውቃለች። ስታስበው ባሩክስ ፈተና መች ነው የምትጨርሱት ያለው ለምን ይመስልሀል? እ? ስለዚህ አይዞህ መጨረሻ ላይ ደስ ይልሃል እሽ የኔ ፍቅር " አለችና ከንፈሩን ቀስ አድርጋ ጎረሰችው። ሳብ አድርጎ እሱም አፀፋውን ሰጣት ደረቱ ላይ አቀፈና አጣደፋት ።ሜላት ለአመታት የተራበችው ፍቅረኛዋ እስኪመስላት ድረስ እያዟዟረች ሳመችው። ናሆም አቅፏት ተቀመጠ ጭኑ ላይ አስቀምጦ ሜላትን አግኝቷት እንደማያውቅ እያዟዟረ ሳማት እሷም የዋዛ አሌነበረችም። ብዙ ጊዜ ሜላት ለናሆም ፍቅሯን የምትገልጥለት በአሳሳሟ ነው! አይኖቿን ጨፍና አንድ ጊዜ ታችኛውን ከንፈሩን ሌላ ጊዜ ላይኛውን ከንፈሩን እያቀያየረች ትስመዋለች ትመጠዋለች በአኔዳች የሀሴት መንፈስ በአየር ሊይ የሚያቀዝፋት ይመስላታል። ከናሆም ከኔፈር የሚነጥላትን ምንም ነገር ትጠላለች አንድ ጊዜ እሱን መሳም ስትጀምር ሁሉም ነገር እንዲጠፋ ይሉኝታ ትዝብት የሚባሉ ነገሮች እንዳይኖሩም ትሻለች። ሜላት ናሆምን በደንብ ታፈቅረዋለች! **** ባሩክ ፕሌን ውስጥ ሆኖ አንዴ የያዘውን የ ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት "the Ethiopian history " የሚለውን መፅሐፍ እያነበበ በሌላኛው ደግሞ አድዋ ሲደርስ ከመቅደላዊት ጋ ሊኖረው የሚችለውን የደስታ እና የመናፍቅ ስሜት እያሰበ ከምድር በውል ባልታወቀ ከፍታ ላይ እየበረረ ነው። አጠገቡ አንዲት ወጣት ቀይ ቆንጆ ተቀምጣ በዝምታ ትመለከተዋለች ከብዙ ተመስጦ በኋላ የአስተናጋጇን የምን ላምጣልህ ጥያቄ ለመመለስ ዘወር ሲል አጠገቡ ያለችው ቆንጆ እንደምትመለከተው አጤነ። በዚህን ጊዜ ፊቷን በደንብ ሲመለከታት የትግራይ ቆንጆ እንደሆነች አሰበ። በትንሹም ቢሆን በሚችላት ትግርኛ ሊተዋወቃት ስለፈለገ " ከመይ ደኃን ደኁ "አለ ልጅቷም ሳቅ አለችና ከአነጋገሩ ትግረኛ እንደማይችል እንዲሁም የሚችለውን ትግረኛ እንኳ የንግግር ለዛውን እንደማያውቀው አውቃ " ደህና ነኝ አንተስ እንዴት ነህ ትግረኛ ትችላለህ ?" ብላ እየሳቀች ጠየቀችው ባሩክም አለማወቁን ስላወቀችበት እንደማፈር ብሎ በእርግጥ ትግረኛ አልችልም ግን መልመድ እፈልጋለሁ እ ለዚህም እጥራለሁ የተወሰነም ቢሆን ለማወቅ ችያለሁ! " አላት " ጎበዝ ነህ አንዳንዶች እንደ አንተ አይጥሩም ማወቁ አይከፋም በቀላሉ ሰው ጋ ያላምድሃል ራስሄኔ ቀለልም ያደርገልሃል። እኔም እንደ አንተ የትግረኛ አለማመድ ነው አማረኛን የለመድሁት እናም ይሄው በደንብ አቀላጥፌ መናገር ችያለሁ አንተም ያለምንም መሰላቸት በደንብ ከተለማመድክ በትግረኛም ቅኔ ልትዘርፍ ትችላለህ " ብላ ሳቅ አለች " ኧረ ቅኔው ቀርቶብኝ ቀኔን በዘረፍኩበት " አለ ባሩክ " ወደየት እየሄድክ ነው?" አለችው ኮረዳዋ ቆኔጆ በደንብ ለማውራት ራሷን ለተለያዩ ጥያቄዎች እያዘጋጀች " አድዋ ነው የምሄደው " እ ? አድዋ ? አድዋ ዩኒቨርስቲ ?" አዎ ምነው ? " አለ ባሩክ ጥያቄዋ አስገርሞት " አይ ምንም እዛ ነው የተማርኩት አምና ነው የጨረስኩት " አለችው " ዋው ደስ ይላላ የኔ ሲኒየር ነሽ እኔ ሶስተኛ አመት እያለሁ ነው የተመረቅሽው " አላትና ባሩክ እባላለሁ " ብሎ እጁን ዘረጋላት " ማን?" ደግማ ጠየቀችው " ባሩክ " ደገመላት ። በአንድ ጊዜ ፊቷ ክስም አለ ገፅታዋ ተቀያየረ አይኗ በርበሬ መሰለ ።ባሩክ በሁኔታዋ ደነገጠ። " ምነው ችግር አለ እናት?" አለ ። ዝም አለችው ደግሞ ጠየቃት ዝም አለችው ።ወዲያው ሁሉም ነገር መጣላት...... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 38♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_36 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ " ይህ የኔ እጣ ፈንታ ነው! አፍቅሮ የማጣት ወይም አምኖ የመካድ ዕጣ! አውቃለሁ ከእኔ የሚጠበቀው ማመን ነው። መቅደላዊትን አምናታለሁ! በእርግጥ የተዋደድን ጊዜ እንደዚህ እንደምንሆን እኔም ሆንኩ መቅደላዊት አናውቅም! እኔም በአንዳች መግነጢሳዊ ሀይል ነው አይኖቿ ላይ አይኔን በአጋጣሚ ያተምሁት! እሷን ሳይ ራሴን የተመለከትሁ ያህል ይሰማኛል አሁንም እንደዛ ነው የሚሰማኝ ካለፉት ነገሮች የማስታውሰው ከእሷ ጋር ደስተኛ የሆንኩትን ጊዜ ብቻ ነው!" አለ ባሩክ ሁሌም ሲጨንቀውና ሲከፋው የሚያዳምጣትን ተወዳጇን ሙዚቀኛ የጂጂን መዚቃ አቋርጦ ጂጂ ለእሱ የመንፈስ መነጠቅ መራቀቅ ምስጢር ናት በጂጂ ውብ ስንኝ የተሰደሩትን የተፈጥሮ ሀቆች ያፈቅራቸዋል። ባሩክ ለተፈጥሮ እጅና ጭንቅላቱን ይሰጣል ለሁሉም ነገር መልስ ለመስጠት የተፈጥሮ ዳስ ላይ መግባትን እንደ መጀመሪያም እንደመጨረሻም አማራጭ ይወስደዋል። በአሁን እድሜው ልጅነቱን የሚኖረው በጂጂ የልጅነት ትዝታ ነው ጂጂ ሰይጣንን ራሱ አሞካሽታ ብትዘፍን ጂጂ ልክ ናት! ከዚህ አንፃር ተመልክታው ነው " ብሎ ይመልሳል ከሚያምሰለስልበት የሀሳብ አለም እንደምንም ወጥቶ ወደ እውኑ ይመለስ ዘንድ ማሳረጊያ የጂጂን ሙዚቃ ከፈተ። " ምን ትጠብቃለህ ? " አቦ ሸማኔ አቦ ሸማኔ እንዲያ ወዲያ ወዲህ አቦ ሸማኔ አቦ ሸማኔ ትንቆራጠጣለህ አቦ ሸማኔ አቦ በሰፋው ደረትህ አቦ ሸማኔ አቦ ባማረው ባትህ አቦ ሸማኔ አቦ እስኪ ተለመነኝ አቦ ሸማኔ አቦ በአይን በጥርስህ። : እያለች በጥዑም ቅላፄዋ ጂጂ ታንጎራጉራለች። ባሩክ ደግሞ ስንኟን ቃል በቃል ወረቀቱ ላይ እያሳፈረ ያመሰጥራል።የብዙዎችን ቀልብ የሚገዛው የባሩክ ጂጂን ለየት ባለ መነፅር ምልከታ ሁሌም እንደ አዲስ አነጋጋሪ ይሆናል ። በዚህ ሁሉ የሌሊት ጥሞናው አንዳች የጥርጣሬ መንፈስ እንዲህ ሹክ አለው። " አንዳንድ ጊዜ ሴት ልጅ ግራ የሚያጋባ ባህርይ አላት። ሄደች ስትባል ትመጣለች። መጣች ስትባል ትሄዳለች። ደረሳ ከመላዕክትነት ወደ ሉሲፈርነት ልትቀየርብህ ትችላለች ። በጠበከው ቀርቶ ባላሰብከው ልትሆን ትችላለች " የሚል አጠራጣሪ ስሜት ነበር በሌላኛው ህዋሱ ሲያደምጥ የነበረው። ባሩክ እምር ብሎ ተነሳና ለጥርጣሬየ ቦታ ልሰጠው አይገባም በፍፁም እኔ እሷን እንዲህ እንደጥርጣሬየ ላስባት አልሻም በቃ አሁን የኔ ትልቁ ህይወቴ እሷን ማመን ነው። ማመን አማራጭ የሌለው መፍተሔ ነው። ደግሞ እሷ የዋህ ናት ይህንን አምናለሁ ያለፉት ጊዚያቶችን እንደ እኔ በስቃይ ነው ያሳለፈችው መልከ ገጿ ይናገራል። አዎ በናፍቆት ተኮራምታ ስታነባ የነበረው እንባዋ የአይኖቿ ሰርክ በእንባ መታጠብና የአይኖቿ መጠን መቀነስ ለዚህ ማሳያ ናቸው!!! ፍቅር ዋጋ ያስከፍላል ፣ ከራስ ጋራ ያጣላል ፣ ከቤተሰብ ጋራ ያቆራርጣል ግን ላመነለት እስከ መጨረሻው ያታግላል። እኔ እንደዛ ነው የማስበው መቅደላዊት ደግሞ ብዙም ዋጋ ሳታስከፍለኝ ሳታደክመኝ ያገኘኋት የኋላ እሸት ሲሳዬ ናት። ስለዚህ ለመቅደላዊት እስከ መቅደላ አፋፍ ድረስ እሄዳለሁ።" አለና ባሩክ እጆቹን አጣምሮ አይኖቹን ወደ ሰማይ አቃንቶ በዝምታ አየሩን ይምግ ጀመር። * መቅደላዊት የሰሞኑ ስሜቷ አንዳች እውነት እንዳለው በልቧ ማይክ እያዳመጠች እያወጣች እያወረደች ከራሷ ጋር ብቻ እያወራች ቀናቶችን አሳልፋለች። ናፍቆት በየመንገዱ ህዳግ እየገተራት መፅሐፍ የያዘ ሰው ባየች ቁጥር ልቧ መከፈል ከጀመረ ጊዜ በኋላ በእያንዳንዱ ቅፅበት ባሩክን ከአልፎ ሂያጁ ማስታወሻው ጋር በክታብ መልክ ፊቷ ላይ እንደብራና ይገለጣል። " እሽ ለማን ልንገረው በእርግጠኝነት የሆነ ነገር ተፈጥሯል ልቤ የሚለኝ እውነት አለ ሳዳምጠው እንደዛ ነው የሚለኝ! በቃ ለናሆም ልንገረው!" በማለት ከራሷ ጋር ተስማምታ ለናሆም ደውላ ሁሉንም ነገረችው ። የሚሰማትን ስሜት በሙሉ ። ናሆም መቅደላዊት በተሰማት ስሜት እጁን አፉ ላይ አስቀምጦ ራሱን አነቃነቀ። የመቅደላዊት ልብ አስደነቀው። ሁሉም ነገር ታይቷት ኖሯል ። ናሆም አለመናገሩ ምንም እንዳልፈየደ ተረዳና ዝም ብሎ ' ምንም ሳይለኝ ቀረ 'ብላ እንዳትታዘበው መንተፍረቱን " አንዳንድ ጊዜ በጣም የምናፈቅራቸው ሰዎች ርቀውን እንኳ አጠገባችን ያሉ ይመስለናል። ሁሌም በምናባችን እያስታወስናቸውና እየዘከርናቸው ስለምንውል ስለ እነሱ ብዙ እናስባለን እነሱ አጠገባችን ያሉ እስኪመስለን ድረስ በህልማችን እናመላልሳቸዋለን! እና የአንቺ ህልምም ግንዱ ከዚህ ዘር ነው! ግን ህልምሽም አንዳንድ ጊዜ ቀን የምታስቢው እንደሆነ ብታውቂም ግን ህልምሽ እውን እነዲሆን አልሚ ልክ ልትሆኝ ትችያለሽ ። ግን አሁን በእንደዚህ አይነት ህልምና ትዝታ ከምትዘፈቂ ፋይናልሽን በደንብ አንብበሽ ስሪና ዶክተር የዋሸልሽን ስጦታ ተቀበይ።" አለ ናሆም " እሱስ ልክ ነህ ግን four የማመጣ ይመስልሃል? " አለች በሚያሳዝን ሁናቴ " እንዴ ይሄ ምን ጥርጥር አለው መቅዲ በደንብ ነው የምታመጪው በአንቺ ሙሉ እምነት አለኝ ከ four በላይ ራሱ ታመጫለሽ ይሄ ማለት ሁሉንም የትምህርት አይነቶች ከ90 በላይ በማምጣት ሁሉንም A+ ታመጫለሽ ይሄም ውጤትሽ አዲስ የሴት ሪከርድ ሆኖ ይቀመጣል። አንቺም ወደ አሜሪካ ትሄጃለሽ ያለምሽውን ህይወት መኖር ትጀምሪያለሽ እኛም እዚች በዘመናት መሄድ ታሪኳ ከማይነጥፍ ሀገር ዝክሯንና በአሏን በአንድ ቀን እያከበርን እንኖራለን " አለ ናሆም በተመስጦም በፈገግታም ሆኖ እየተመለከታት " አይ ናሆ ምነው በተሳካልኝ እስኪ ፀልይልኝ ሌላ ምንም ነገር አልፈልግም ባሩክን ብቻ ነው የምፈልገው ባሩክ ባሩክ ባሩክ ነፍሴ እሱን ብቻ ነው የምትፈልገው የምታርፈውም እሱን ስታገኝ ነው።" አለች መቅደላዊት በበረሃ ጋመን እንደከሰመች አበባ ጥንዝል ብላ። ናሆም ያለውን እውነት በመደበቁ ይበልጥ ተሸማቀቀ አፈረ አይኗን በሙሉ አይኑ ማየት አልቻለም። ምን አለ ብነግራት ? ከዛ የፈለገችውን ብታደርግ ይሻል ነበር ? ፅፅፅፅ አሁን በኋላ እንዴት ነው የምትታዘበኝ ወይ መከራዬ " አለ ናሆም " ምነው ዝም አልክ? አለች ለብቻው እያብሰለሰለ ለአፍታ መልስ ያልመለሰላትን ናሆምን ! " እ? ኧረ ዝም አላልኩም መቅዲ ያው መቼስ የሚታሰብ አይጠፋ ዝም ብዬ የባጥ የቆጡን አወርድ ብዬ" በማለት ከጥያቄዋ መአት ለመሸሽ ጣረ። ከእሷ ቢያመልጥም ከእሱ "ለምን ዋሸኋት?" ጥያቄ ግን ማምለጥ አልቻለም! ** " በቃ እህቴ ልሂድ ወደ አድዋ በቶሎ አስተካክዬ መመለስ አለብኝ! ስለዚህ ጊዜ ሳላቃጥል ያለኝ የፈቃድ ጊዜም ውስን ስለሆነ " አለ አነስ ያለች ሻንጣውን እያስተካከለ " እንዴ ባሩክ አልፈጠንክም ትንሽ አትቆይም ?" አለች ኤሊያና " አይ አልፈጠንኩም ውዷ እህቴ ትንሽ ጊዜ ነው ያለኝ ቶሎ ነው መመለስ ያለብኝ የግድ ስለሆነብኝ ነው። ይህንም ጊዜ ለመቆጠብ በፕሌን እስከ መቀሌ እሄድና ከዛ ባስ እጠቀማለሁ !! " እና በቃ አሁን ልትነሳ ነው?" አለች ኤሊያና " አወ " አለ ባሩክ ይቀጥላል ........... ሼር ቢደረግ ኮ ግን ታሪኩ ላልደረሳቸው የመድረስ አቅሙ ሰፊ አይመስላችሁም በቃ ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 37♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_35 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ የአይኖቿ ቆብ ያለቅጥ ይርገበገባሉ። ትንፋሿ ቁርጥ ቁርጥ ይላል ። የልቧ ምት በፍጥነት ይመታል። የዛፎቹ ሽውሽውታና ውዝዋዜ ከወፎቹ ድምፅ ጋር ተዳምሮ አንዳች የመንፈስ ከፍታ ላይ የሚያደርስ ዝማሬ ይመስላል። በውል ድምጣቸው የማይታወቅ አራዊቶች ያላዝናሉ። ምንም አይነት የሰው ድምፅ የለም። ምንም የሚያነብ ተማሪ የለ ሆኖ ይሁን ተማሪዎች ጥናታቸውን አጠናቀው ምንም የሚያስታውቅ ነገር የለም! በብዙ ደመና ታጅባ ጨረቃ ያልጠነከረውን ብርሃኗን ለማጉላት ትጥራለች። መቅደላዊት ይህን ሁሉ እየታዘበች ልቧን ተደግፋ ገብርዬ ዋርካው ስር ተቀምጣለች። ፍቅር የልብ ቋንቋ ነው ሳትነጋገር የሚያግባባህ አሁንም አሁንም ቀልብያህ የሚነግርህ ። መቅደላዊት የሰሞኑን ሁኔታዋን ተጠራጠረችው ረፍትም ነስቷታል ይሄን ጉዳይ ደግሞ ለናሆምም ሆነ ለሜላት አለዚያም ለዮርዳኖስ እንዳትነግራቸው ሌላ ጭንቀት ያለሁ መስሏቸው ሊጨናነቁ ይችላሉ ብላ ስለሰጋች ለአንዳቸውም ስሜቷን ለመናገር አልፈቀደችም። አሁን ግን ሁኔታው በጣም ግራ እያጋባትና የልቧ እንዲህ መሆን እረፍት ስለነሳት የሆዷን የምታጫውተው ሰው ፈለገች በዚህም ለሜላት ወይም ለዮርዳኖስ ማማከር እንዳለባት ወስና ከተቀመጠችበት ተነሳች። ስአቱ የሚያስፈራ ቢሆንም ገገር ግን መቅደላዊት በልበሙሉነት ብቻዋን ከራሷ ጋር ስታወጣ ስታወርድ ቆይታ ነገ በጠዋት ነግራቸው ምክራቸውን ለመቀበል ወሰነች። *** " የአለም ነገስታትና የጦር መሪዎች የወደቁት በፍቅር ነው በሃይማኖታዊ አስተምህሮት መሠረት ራሱ ሶምሶም የፀጉሩን ሀይል ያጣው ለፍቅሩ ሲል ባደረገው ተጋድሎ ነው ። ፍቅር የውድቀት ምሳሌ የምትሆነው በፍቀር ዝግጁ ለሆነ ብቻ ነው። ስአሊና ገጣሚያን በጥበብ የሚራቀቁት በማፍቀራቸው ነው። ፍቅር የሁሉም ነገር መነሻና መድረሻ ነው። አልፋና ኦሜጋ እኔ ከመቅደላዊት ፍቅር ራሴን ላሸሽ አልችልም ራሴንም ማታለል አልችልም። በዚች ቅፅበት በራሷ አንዳች መግነጢሳዊ ሀይል ከእሷ አጠገብ ባስቀመጥኝ ብየ እምጠይቀው መንስኤው ሌላ ሳይሆን እሷን ጥልቅ በሆነ ሀሳብ ስለማፈቅራት ብቻ ነው። መቅደላዊት የኔ የፍቅር ኦሜጋ ወዴት ነው ያለሽው በዚህ ስአት ምን እያደረግሽ ነው? አዲስአበባ መምጣቴንስ ታውቂ ይሆን ወይስ መረጃውን የሰማይ በራሪ ለራሱ ክንፍ ማማቻ ተጠቅሞበት ለአንቺ ሳያደርስሽ ቀረ? አልቻልኩም መቅደላ መጥቻለሁ በፍቅር የተጎዳውን ክንፌን ትጠግኝልኝ ዘንድ ከላይ ከታች በማለት የምትባዝነውን ነፍሴን እንድታሳርፊያት መጣሁ!" እያለ ባሩክ እየጣለ ያለውን ዝናብ እምዲበረታ መፀለይ ጀመረ በወጀቡና በዝናቡ መአት መቅደላዊት አጠገቡ የምትመጣ መስሎት። *** ናሆም የባሩክን መምጣት መቅደላዊትን በመዋሸቱና ባለመናገሩ እራሱን እያሸማቀቀ ሳይወድ በግዱ ሀንድ አውቱን ለማንበብ ይሞክራል ። ሲያነሳውም የሚመጣበት የባሩክ አነጋገር ሁኔታውን የሜላትን ድንጋጤ የራሱን ድንጋጤ አንድ በአንድ በምልሰት እየደጋገመ ይመጣበት ያዘ። በፍጥነት ነገሮች እየተቀያየሩ እንደሆነ ታየው። ትላንት ጨለማ ነው ሻማ ቢገኝ ራሱ እንዴት ማለፍ ይቻላል የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በማሰብ ላይ እያለ ሻማው በራሱ እየበራ ይሄዳል። አሁንም አሁንም እየተመላለሰ የሚመጣበት የመቅደላዊት ፊት ባሩክን ሲያየው ፊቷ ላይ ውስጧ ላይ ሊፈጠር የሚችለው ነገር በአይነህሊናው እየመጣበት በሀሴት ዝቅ ከፍ ይላል። "አንድ አመት ባልሞላኝ ጊዜ ውስጥ የሰው ህይወት እንደቀልድ ሲመሰቃቀል ተመልክቻለሁ። ሕይወት ምን ማለት እንደሆነች ጠንቅቄ ተምሪያለሁ። አሁን በራሱ ብዙ ነገር እየተማርኩባት ነው። በእኔ ምክንያት ብዙ ሰው ከብዙ ነገር ተገለለ። አኔድ ጊዜ መቼም ከእድለኛ ያልተጣጣፈ ሰው መጨረሻው አያምርም። እናቴን እህቴን አግኝቻለሁ። አባቴን ከመቼውም ጊዜ በላይ ሳነግሰውና ሳከብረው እኖራለሁ። እሱ ያደረገልኝን የሰጠኝን ፈጣሪ ራሱ የሚሰጠኝ አይመስለኝም!" አለና አይ አምላኬ ሆይ እንኳንም አባቴን እንደዚህ ሆደ ባሻ ምስኪን አድርገህ ፈጥረህህ እንዲህ እንዲያበቃኝ አደረክ።ክበርና ምስጋና ለአንተ ይገባሀል። የእሱን አለመኖር አይተህ ደግሞ ለሰጠኸኝ ወንድምና እህት እንዲሁም ኤንደ ልቤ ንፃት ሳይሆን እንደ አንተ መልካም ፈቃድ ለሰጠኸኝ የምታፈቅረኝን ሴት ለዘላለም ክብር ይግባህ የኔ ጌታ " አለና አንሶላውን ወደ ግራ በኩል ለብቻው ሰብስቦ ከአልጋው ተነስቶ ወደ በሩ በረንዳ መውጫ በኩል ወዳለው አቅጣጫ አይኖቹን አሻግሮ ተመለከተ። ውሃ የመሠለ ሰማይ እና ከብዙ ርቀት ኋላ የሚታይ ትንንሽ ደመናወች በባህር እና በሀይቅ ላይ እንዳሉ ደሴቶች ቅርፅ ጉሞች በትንሽየ የካርታ ምስል ሆነው ያያል። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 36♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_34 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ በሶስት ቦታ አስገብቼ ነው የማስባት አንደኛው፦ መቅደላዊትን በአንቺ ቦታ አድርጌ የማስበው ሀሳብ ሲሆን በዚህም መሠረት እህቴ ስትጎዳ ማየት እንደማልፈልግ ሁሉ እሷም መጎዳት የለባትም ብዬ አስባለሁ። ሁለተኛው ደግሞ መቅደላዊትን በራሷ በመቅደላዊት ቦታ አስገብቻት ምን ልታስብ እንደምትችል የማስበው ነው። ሶስተኛው ራሴን በራሴ ቦታ አድርጌ ድርጊቶችን የምወስንበትን ሀሳብ የምመለከትበት ነው። እና በዚህ የአስተሳሰብ ልክ ሆኜ ነው እያሰብኩ ያለሁት ስለዚህ ትንሽ ነፃነት ስጭኝ አይዞሽ የኔ ውድ እህት ያለፈውን እንደማትደግመው ልቤ እርግጠኛ ነው። ግን ደግሞ ደግማ ብትከዳኝም እኔ ደስተኛና ንፁህ እንጅ የምሆነው አልጎዳም። ምክንያቱም እኔ ማድርግ ካለብኝ በላይ ስላደረኩ ስለዚህ አታስቢ ሁሉም ነገር ይስተካከላል እሽ " አለና ባሩክ ወደ ደረቱ አቅፎ ፀጉሯን በጣቶቹ አመሳቸው። ኤሊያና በእሽታ ራሷን ነቅንቃ ዝም አለች።" አዎ በሁለት ልብ ሆኜ ወደ እሷ እሄዳለሁ። በአንደኛው አምኛት በሁለተኛው ደግሞ አምኛት!!! ከዛ እኔ የሚደርስብኝን ሁሉ እቀበላለሁ። ምክንያቱም በዚህ ስአት ለመቅደላዊት ብዬ ሳይሆን መቅደላዊትን ለናፈቀው ልቤ ነው የምሄደው ስለዚህ ልቤን ደግሞ አምነዋለሁ " አለና ለራሱ ኤሊያናን አባብሎ አስቀመጠ። ** " ሜሊ ፀሎቴ ተሳካ ባሩክ መጣ ሁሉም ነገር ወደነበረበት ተመለሰ ኡፍፍፍፍ " አለ ናሆም በደስታ በረጅሙ እየተነፈሰ" በትክክል!!!! ታውቃለህ እስካሁን ማመን አልቻልኩም ። " አለች ሜላት " ሁሉም ነገር ለበጎ ነው የሚባለው እውነት ነው ለካ " " በጣም እኔ አምናለሁ አሁን ለመቅደላዊት ብንነግራትስ ?" " አይ ሜሊየ አይሆንም ፈተናውን ትታው ወደ አዲስአበባ ትሄዳለች በፍፁም!!"" " እና ዝም ብለን ይሄን ብስራት ሰምተን ዝም እንበላት???" " አዎ እሱ እስኪመጣ መታገስ አለብን ባይሆን ለዮርዳኖስ እንገራት" " አዎ እሽ ልክ ነህ ለእሷ መናገር አለብን " ብላ ደወለች " ዮርዳኖስ ስልኩን አነሳችውና " አቤት ሜሊ " አለች " እንዴት ነሽልኝ ዮርዲ " " አለሁልሽ አንቺ እንዴት ነሽ ሁሉ ሰላም ነው ተጠፋፋን አይደል? ፈተና ሲደርስ እኮ ሁሉም ነገር ለየብቻው ሆነ " አለች " አዎ ልክ ነሽ ቢሆንም በልብ እንገናኝ የለ? አታስቢ የኔ ቆንጆ።" አለች ሜላት ስለባሩክ ለመናገር ፈራ ተባ እያለች " እና ዛሬ እንዴት ተገኘሽ?" " ዛሬ የሆነ ሰርፕራይዝ ልነግርሽ ነው እንግዲህ ወገብሽን ጠበቅ አድርጊ " አለች ሜላት ለማጓጓት እየሞከረች " እህህህህ ደግሞ ምን አይነት ዜና ይሆን ? " አለችና ዮርዳኖስ መልሳ ጠየቀቻት " በቃ አሁን የምነግርሽ ፍፁም የማትጠብቂው ነገር ነው። " " ኧረ በቃ ንገሪኝ አታጓጊኝ ይሄን ያህል" " እሽ በቃ ባሩክ መጥቷል?" "ምን? እውነትሽን ነው?" አዎ እውነቴን ነው እኔ ራሱ አሁን ትንሽ እየተረጋጋሁ ነው። አዲስ አበባ ገብቷል እኔና ናሆምን አውርቶን ነበር። በቅርብ ወደዚህ ይመጣል። " "የሚገርም ነው እውነት ባሩክ መጣ? በእውነት እግዚአብሔርማ የምስኪን እምባ ያያል። መቅዲ ከልቡ አልቅሳ ነበር። ወድቃ ተንበርክካም ለምናዋለች። እሰይ እንኳን ተሳካላት እንዴት ተሰቃይታ እንደነበርኮ ውይ አምላኬ ተመስገን!" አለች በረጅሙ እየተነፈሰች።" እና ግን ለመቅዲ ነገራችኋት?" አለች ተመልሳ ትዝ ሲላት " ውይ ዮርዲየ ለእሷ እንኳ አልነገርናትም አሁን ላይ በጥሩ መንፈስ ሆና እያነበበች ነው። እሱን መረበሽ የለብንም ብለን ነው ። ደግሞም መሆን ያለበት እንደዛ ነው" ልክ ናችሁ ጥሩ ነው ያሰባችሁ! እንደዛ ይሻላል።" አለች ዮርዳኖስ በነ ሜላት ውሳኔ እየተስማማች። *** ናታኔም ብዙ ሀሳቦችን ሲያወጣ ሲያወርድ ከቆየ በኋላ ለመርዕድ ደወለ። መርዕድ የናታኔምን ስልክ በንቀት እየተመለከተው ዝም አለ። ናታኔምም በንዴት በተደጋጋሚ ይደውልለታል በስተመጨረሻ መርዕድ ስልኩን አንስቶ በተሰላቸ ድምፅ " እ ምንድነው " አለው " ምን እኔን ነው እንደዚህ ምታወራኝ ነውስ ማን እንደሆንኩ አላወከኝም" " ምን አገባኝ ማንስ ብትሆን አሁን ወደ ደወልክበት ጉዳይ ግባ አለዚያ ስልኩን ልዘጋው ነው።" አለ መርዕድ ። ናታኔም ራሱን በሀዘኔታ እየነቀነቀ " ለነገሩ ከአንተ ጋ ወትሮስ ቢሆን ምን መልካም ነገር ይኖራል። ለማንኛውም ጨው ለራስህ ስትል ጣፋጥ ነውና ነገሩ ከዚህ በኋላ ለራስህ ስትል በስርዓት ታወራኛለህ አይ ካልክ አይመለከተኝም። ከዚህ በኋላ አንተም እንዳትደውልልኝ " በማለት ናታኔም በንዴት ስልኩን ጀሮው ላይ ዘጋበት። መርዕድ ናታኔም ጀሮው ላይ ስለዘጋበት በጣም ተናደዳና መልሶ ደወለለት ነገር ግን ናታኔም የመርዕድን ስልክ ወዲያው ብላክ ሊስት ውስጥ አስገብቶት ኖሯል ለካ መስመሩ ተይዟል። የምትለዋ ንግግር በየ ሰከንዱ ትለፈልፍ ይዟታል። መርዕድ እንደ እብድ ሆነ በናታኔም ድርጊት ! * " አሁን በዚህ ታሪክ ውስጥ አብረውኝ የነበሩትን ሰዎች የተጨነቁትን ሰዎች የማመሰግንበት ጊዜ ላይ ነኝ። ተመስገን ይህን ሁሉ በሰላም ስላደረስከው አሁንም ፍፁም በጥበብ ድርጊቴን እንድትከውንልኝ። " አለ ባሩክ ሽቅብ ወደ ሰማይ እየተመለከተ። ተፈጥሮ እና እውነት ውበታቸው እየቆየ እየጎላ ነው የሚሄደው። አሁን በቶሎ መሄድ አለብኝ ሄጄ መቅዲን ላቅፋት ይገባል። ሙቅ ገላየን በትንፋሿ ልታቀዘቅዝልኝ ብትችል" አለ ባሩክ መቅደላዊትን የተናፈቀውን ሰውነቱን እየደባበሰ። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 35♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_33 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ እና አንተ ማንነህ?" " ባሩክ!" " ምን? "ሜላት ስልኩን ቁልቁል ለቀቀችውና አፏን አፈነች ናሆም በድንጋጤ " ምን ሆንሽ ?" ብሎ ደገፋት ሜላት ፀጥ አለች " ምን ሆንሽ ንገሪኝ እንጅ የኔ ፍቅር " ብሎ አቀፈና አስቀምጦ ደረቱ ላይ አስደግፎ የወደቀውን ስልኩን በቀኝ እጁ አነሳው ስክሪኑ ሰንጠቅ ብሏል። " ማን ነኝ ነው ያለሽ የኔ ፍቅር ?" ብሎ በድጋሚ ጠየቃት " ብ.....ብ.....ብ....ባ......ባ...ባባባባ.....ባ......" ኧረ አትንቀጥቀጭ የኔ ቆንጆ ንገሪኝ አታስጨንቂኝ " አለ ናሆም " ባ ... ባ .. ባሩሩሩሩ ባሩክ!" አለች " ምን?" አለ ናሆም ቀኝ እጁን አፉ ላይ አሳረፈ። " እንዴት? ከየት ? " መቼ?" ብሎ ስልኩን አንስቶ ሊደውል ሲል ስልኩ ባትሪው አልቆ ይሁን ስለወደቀ ተበላሽቶ አይሰራም የማስነሻ በተኑን ተጭኖ ለሰከንድ ከቆየ በኋላ ስልኩ በራ ። በፍጥነት ፓስወርዱን አስገብቶ ደወለ ።ከሁለት ጥሪ በኋላ ባሩክ ስልኩን አነሳው። " ሃሎ ሜላት " አለ ባሩክ " ሜላት ያለችውን ለማመን የባሩክን ድምፅ ለማዳመጥ ወስኖ የነበረው ናሆም ሜላትኔ ላለማመን ሳይሆን የነገረችው ነገር ትንሽ አስደንግጦት ነበር። በዚህም ደግሞ ምን አልባት እነ ናታኔምና እነ መርዕድ እነሱን ለመረበሽ የዘየዱት ዘዴ መስሎ ታይቶትም ነበር። ናሆም የባሩክን " ሃሎ ሜላት " የሚለውን ድምፅ ከሰማ በኋላ ግን ጥርጣሬዎቹ በሙሉ በአንድ ጊዜ እንደ ጥር ጉም ተነኑ።" አወ ራሱ ባሩክ ነው " አለ ናሆም በለሆሳስ ያለውን አዳምጣ ሜላት እንደ አዲስ ወደ ናሆም ዞረች። ናሆም ፊቱ ከመቅፅበት በብርሃን ተሞላ ሳያስበው እንባወቹ ወረዱ። " እንዴት ነህ ወንድሜ " አለ ባሩክ ናሆም የሚሆነውን ነገር በምናቡና ለሜላት በሚነግራት ቃላቶች ለመረዳት አፍታ ሳይፈጅበት " ደ....ደህና ደህና ነኝ! "አለ ናሆም እየተንተባተበ " አውቃለሁ ወንድሜ ናሆም በድንገት እንደመጣሁ መናገር ነበረብኝ ግን ያው ብዙ ነገሮች ስለነበሩ ነው ያላሳወኳችሁ።" አለ ባሩክ ቀድሞ ላለማሳወቁ ምክንያት ለማሰቀመጥ እየሞከረ ።ናሆም ግን ምክንቱን በትክክል አላዳመጠውም " እንዴት ነህ ግን ባሩክ በጣም ናፍቀኸኝ ነበር ወንድሜ" አለ ሆደ ባሻነቱ ፈንቅሎት እየወጣ " ባሩክ በናሆም ንግግር ውስጡ ተነካ: ባሩክ ለትንሽ ሰከንድ ዝም ካለ በኋላ " እኔም ናፍቀኸኝ ነበር ወንድሜ ግን ይሄው በስተመጨረሻ መጣሁ!" አለ ባሩክ " የት ነው ያለኸው አሁን " አለ ናሆም ግራ በገባው መንፈስ ያለበትን እንኳ ለማሰብ ግራ ገብቶት ባሩክ በኤሊያና ስልክ እያወራው እንደሆነ ዘንግቶት " አሁን አዲስ አበባ ነኝ " " እሽ መች ነው የምትመጣው " አለ ሰፍ ብሎ የሚመጣበትን ቀን እንዲያቀርበው እየለመነ " አላወኩም ረፍት ማድረግ እፈልጋለሁ ከትንሽ ቀናት በኋላ እመጣለሁ , መች ነው ፈተና የምትጀምሩት?" አለ ባሩክ " በቃ አሁን ልንጀምር ነው ትንሽ ቀን ነው የቀረን " ምን ያህል ቀን ይፈጅባችኋል ፈተናችሁ " አለ ባሩክ " 3 ሳምንት ይመስለኛል እነ መቅደላዊት ግን ቀድመው ነው የሚጨርሱት " አለ " አሁን መቅደላዊት እንዴት ናት " አለ ባሩክ አይኖቹ እንባ እያቀረሩ በጣም ናፍቃዋለች አዲስአበባ ከመጣ ጀምሮ ራሱ በአይነ ህሊናው እየመጣችበት ነው።" ደህና ለመምሰል እየሞከረች ነው ባሩክ ሰሞኑን ደግሞ ዶክተር ወንድማገኝ በአሁኑ ሲሚስቴር ጥሩ ውጤት ካስመዘገብሽና ያለፈውን ውጤትሽን ካስጠበቅሽ አሜሪካ ላይ ከምትፈልጊው ዩኒቨርስቲ የትምህርት ዕድል እናመቻችልሻለን " ብሏት ይሄው ጠዋት ማታ ላይብረሪ ናት ከራሷ ጋር እያወራች እንደ ህፃን ልጅም እንደ አዋቂም እያደረጋት ።እኛም ቀርበን ስንጠይቃት " ወደ ባሩክ የሚያደርሰኝን መንገድ ጀመርሁ ባቡሩ ላይ ተሳፍሪያለሁ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ እርሱ ዘንድ እደርሳለሁ " ነው የምትለን " አለ ናሆም ። የባሩክ አይኖች በቅፅበት በእንባ ተሞሉ በወፍራሙም ቀስ እያሉ ከአይኖቹ ዱብ ዱብ እያሉ ይወረዱ ጀመር" በቃ ወንድሜ ሁሉንም ስመጣ በሰፊው እንጫወታለን ሜላትን ሰላም በልልኝ እስክንገናኝ መልካም ጊዜ " አለ ባሩክ በእንባ የራሰውን ጉንጩን በመዳፉ እያበሰ " እሽ " አለ ናሆም ። ባሩክ ስልኩን ከዘጋው በኋላ " አዎ የምትፈልገውን ለማግኘት የማትፈልገውን ታደርጋለህ የምትፈልገውን ደግሞ እንደየሁኔታው የሰው ልጅ ፍላጎት ውስብስብ ነው በተለይ በፍቅር ላይ ደግሞ ይበልጥ ግራ ይጋባል ። በደመነፍስ ያስጉዝሃል። የምታደርገውን የምታውቀው አንደዛ ነው ሁሉም ነገር ። የራስህን ሰው ለመፈለግ መሄድ መሄድ መሄድ መንገዱ ምንም ይሁን!!" አለና ባሩክ በረጅሙ ተነፈሰና ተነስቶ ፊቱን ታጥቦ አልጋው ላይ በጀርባው ተኛ። ኤሊያና ባሩክን ተከትላው ወደ መኝታ ክፍሉ ገባችና " አንተ ልጅ ግን ያምሃል እንዴ ? በድጋሚ መሰበር ፈልገህ ነው? እንዲህ ቅብዝብዝ የሚያደርግህ ከአሜሪካ ድረስ ሲያበርህ መጥተህ ደግሞ ካልሄድኩ የምትለው ምን አስበህ ነው?። በጣም ያበዛኸው አልመሰለህም ቆይ ራስህን እንዴት ነው የምታየው?" አለች ኤሊያና ንዴት በሚያንቀለቅለው ስሜቷ ቃላቶቿን እያወረደች "መስመርሽን እያለፍሽ ነው! " ባሩክ ከተኛበት ብድግ አለ፡ " ኤሊ ከዚህ በላይ ምንም እንድትናገሪ አልፈልግም " አለና ፊቷን በዝምታ ተመለከተው አይኖቹን ከአይኖቿ ላይ በብስጭት አንከራተታቸው። ባሩክ ፊቱ በአንዴ ተለዋወጠ ። ኤሊያና ከእኝደገና ያለችውን ነገር ስታስብ የባሩክን ፊት ስትመለከት የምትገባበት ጠፋት ጨነቃት ወዲያው " ምን አለ ምንም ባላልኩት አምላኬ ሆይ ምንድን ነው ያረኩት ራሷን እያፈራረቀች መጠየቅ ጀመረች።" ምን ያህል እንደተጓዘችና ምን ያህል እሱን ለመጫን እንደሞከረች አሰበች በራሷ ተናዳ ራሷን በሁለት እጇ ጨመቀች። ትንሽ ከራሷ ጋር ከቆየች በኋላ ባሩክን በፍርሃት ተከተለችውና ውጪ ላይ " ይቅርታ እሽ " አለች ።ኤሊያና ባሩክ ዝም ብሎ በሆነ ባልሆነው የሚነጫነጭ የሚያመናጭቅ የሚያመናቅር እንዲሁም የሚጮህ ልጅ እንዳልሆነ በደንብ ታውቃለች። ለዚህም ነው በቶሎ ስህተቷ ገብቷት ብዙም ሳትቆይ ይቅርታ ለማለት የፈለገችው " በጣም ይቅርታ እሽ ወንድሜ " ብላ ከኋላው አቀፈችው። ኤሊያና ሲበዛ ባሩክን ትወደዋለች። ታከብረዋለችም ግን ደግሞ አሁን እያደረገ ያለው ነገር በድጋሚ እንዳይጎዳ እንደ እህት ስለሚያሳስባት ነው እንዲህ የምትለው። " ችግር የለውም ኤሊ ልጮህብሽ አስቤ አልነበረም እኔም ስለጮኩብሽ ይቅርታ። እኔ ስለ እኔ ብቻ አይደለም የማስበው አሁን እኔ ልብ ላይ ምን እየተመላለሰ እንዳለ አታውቂም። መቅደላዊትን እንደመቅደላዊት ብቻ አድርጌ አይደለም ልስላት የምችለው። መቅደላዊትን በሶስት ሰዎች ቦታ አስገብቼ ነው የማስበው። አንደኛው...... ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 34♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_31 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ አወ የኔ ፍቅር ተወው ጊዚያችንን ያበላሽብናል።............ " ብላ ሜላት ግንባሩን ሳም አደረገችው " በቃ አላነሳውማ የኔ ፍቅር ለምን ስልካችንን አጥፍተን ልባችን እስኪጠፋ በፍቅር አንከንፍም?" " እንደዛማ አይሆንም ምን አልባት እኛን በጣም የሚፈልግ ሰው ሊኖር ይችላል። ማለቴ እኛ የምናስፈልገው ሰው። ለምሳሌ መቅደላዊት " " ምፅፅፅ አዎ እሷ አለች በቃ ተውኩት በአንች የሚገርም ሀሳብ ምክንያት " " ኡፍ ለዚህ እኮ ነው የምወድህ የማፈቅርህ ታቃለህ ኣ ያለ አንተ መኖር እንደማልችል ከአንተ ውጭ በጭራሽ " " አውቃለሁ የኔ ቆንጆ በአንች ከእኔ ውጭ አለመኖር ምክንያት የተነሳ እኔ ያለ አንች መኖር እንደማልችል አድርገሽኛል። ለዚህ ደግሞ አመሰግናለሁ በጣም ብዙ ነገር ነው ያስተማርሽኝ ለሰው መኖርን፣ ማፍቀርን፣ ንፁህነትን ፣ እና ለዚህ ሁሉ ውለታሽና ስጦታሽ ደግሞ ምንም አድርጌልሽ ለመልሰው አልችልም ምክንያቱም ይሄን ሁሉ ነገር መመለሻ ትልቅ ልብ እንደ አንቺ ስለሌለኝ ' እንደዛማ አትበል የኔ ፍቅር ምንም ያደረኩት ነገር የለም ያደረኩትም ለራሴ ለእኔ ፍቅር ስል ነው" የናሆም ስልክ በድጋሚ ጠራ አየው ' ውይ ይሄ ስልክ ምንድነው ደግሞ ደወለ" " ውይ ለምንድነው ነው ጥሩ ጊዜ እያሳለፍን ሲሆን የሚበጠብጠን የማይጠፋው ? እድለቢሶች ነን ደግም የአሁኑ ዜና ምን ይሆን ወይ መከራ!" አለች ሜላት " ፍቅር በቃ የሆነው ይሁን ላንሳው?" አለ ናሆም ሜላት ዝም አለች " ምን ላድርግ እየደወለም እየበጠበጠን ስለሆነ አንስተን በአንድ ጊዜ የሚለውን ሰምተን እንገላገል አይሻልም?" አለ ናሆም " በቃ እሽ አንሳው " አለች እሽ ብሎ ሊያነሳ ሲል የስልክ ጥሪው አለቀ። ሁለቱም ተያዩ " ልደውልለት እንዴ?" አለ " ኧረ መደወልማ አትደውልም ባይሆን አሁንም ከደወለ ታነሳዋለህ" " እሽ " ብሎ ወሬውን ሲጀምር ስልኩ ጠራ ሲያየው የተደወለበትን ቁጥር የተለየ ነው ከቅድሙ ናሆም ደንገጥ አለና " ይሄን ቁጥር የማውቀው መሰለኝ " አለ ሜላት ስልኩን ተቀበለችውና ስትመለከተው የኤሊያና ስልክ ነው! "እንዴ ይሄ ኮ የኤሊያና ስልክ ነው " አለች ና " አቤት ኤሊያና " " ሄይ ሜላት እንዴት ነሽ?" አለ የወንድ ድምፅ " እንዴ የኤሊያና ስልክ አይደለም እንዴ?" አለች ሜላት በድንጋጤ " ነው እንጅ " አለ ናሆም " እና አንተ ማንነህ?" " ባሩክ!" " ምን? "ሜላት ስልኩን ቁልቁል ለቀቀችውና አፏን አፈነች ናሆም በድንጋጤ " ምን ሆንሽ ?" ብሎ ደገፋት ** "ይገርማል የአንዳንድ እናት ማህፀን! የተባረከ ልጅ ይወልዳሉ ንፁህ ልብ ያላት እናት ንፁህ ልብ ያለው ልጅ እንደ ባሩክ አይነቱን ወልዳ ከራሷ አልፋ ለሌሎች የደስታ ምንጭ ትሆናለች። እንዴት የታደለች ናት ይህን የመሰለ ልጅ ያገኘች እናት እንደ ወጣት ያልሆነ ብርቱና ትሁት ልጅ እንዴት አድርጋ አሳድጋው ይሆን እንዲህ መላዕክ የሆነው?" ስትል ራሷን ጠየቀች " እኔ ግን የቤተሰቦቹ የአስተዳደግ ሁኔታ ብቻ አይመስለኝም የእሱ የዚህ ስብዕና ምክንያት ራሱ ልጁም በቃ እንዲህ ሁን ተብሎ ስለተፈጠረ ነው እንጅማ እያየን አይደል እንዴ በየ ቦታው ስንት ስርአት ያላቸው ቤተሰቦች በስርአት እያሳደጓቸው ዘወር ሲሉላቸው የሚያደርጉትን " አለች የናሆም እህት " እሱስ ልክ ነሽ ልጄ ለዛም ነው የተባረከ ልጅና ጤነኛ ልጅ ስጠኝ ተብሎ የሚለመነው። ግን አግኝቼ ባመሰግነው ምንኛ ደስ ባለኝ አይኑን ባየሁት። ያጣሁትን ልጄን ነው የመለሰልኝን ሰው። ውለታው አለብኝ ሲበዛ የህይወቴን ደስታ ነው የመለሰልኝ ቢያንስ ሌላው ቀርቶ አግኝቼ አመሰግናለሁ ልጄ ልለው ይገባል።" አለች የናሆም እናት " በትክክል እማየ አሪፍ ሀሳብ ነው። ምሳ ልንጋብዘው ይገባል። አሁን እድሜ ለዛ ባሩክ ለሚባል ልጅ ናሆም እኔንም እንደ እህቱ አንቺንም እንደናቱ ማየት ከጀመረ ሰንበትበት ብሏል።ባሩክ ያደረክልንን ነገር አንረሳውም " አለች የናሆም እህት ** " ልጄ አሁን ወደ ራሷ ተመልሳለች አዎ ፈጣሪየ ፀሎቴን ሰምቶኛል መሰል ክፉዋን አራቀልኝ እንደወትሮዋ ፍልቅልቅና ሳቂታ ሆናልኛለች። አሁን አንድ እና አንድ ትምህርቷ ላይ አዙራልኛለች። ተመስገን እንኳን ይሄን አሳየኸኝ።" ይላል የመቅደላዊት አባት የዘመን ቆይታውን ለማሳጠር ከሚታትር የእድሜ ባላንጣው ጋር እየታገለ። ላለፉት ወራቶች የልጁ ጉዳይ እንቅልፍ የነሳው አባት አሁን የሰላም እስትንፋስ እየተነፈሰ ያለ ይመስላል ። እድሜው ያለፉት የመቅደላዊት ሁኔታ እንቅልፍ ነስቶት እና ሌት ተቀን አሁን ምን ሆና ይሆን በማለት በሀሳብና በሰቀቀን ያሳለፈው አባት አሁንም በመጠኑም ሰቀቀኑ ቀንሶለታል። በሰሞኑ የመቅደላዊት ሁኔታ ቤተሰቡ ከጭንቀት ተገላግለው ወደ አለፈው ትዝታዋ እንዳትመለስ ለማድረግ አንድ ሁለት የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥም እናትና አባት እየተወያዩ ነው። ** " ባሩክን አሜሪካ አገኘዋለሁ ሲያገኘኝ እንደሚደመምብኝ እርግጠኛ ነኝ ምክንያቱም ጥረቴ እና የውጭ ዕድል ማግኘቴን እንደ ትልቅ ጥንካሬ ና ጀግንነት ይቆጥረዋል። ከዛ ይቅርታ ያደርግልኛል። እሱ ጋር ደስተኛ ሕይወት መኖር እጀምራለሁ ። ያኔ ቤተሰቦቼም ሆኑ ጓደኞቼ ደስ ይላቸዋል።የፍቅር አምላክ ደግሞ ያሳካልኛል።" እያለች ደጋግማ ለራሷ ታልማለች በየ እርምጃዋና ሀሳቧ ውስጥ የማይጠፋውን ባሩክ ታስበዋለች። ፍቅርና እምነት አንድ ናቸው። አሁንም ነገም ተስፋ አልቆርጥም እስከመጨረሻዋ ጊዜ ድረስ እስኪሳካልኝ እጥራለሁ።" እያለች ከራሷ ጋር ታወራለች። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 32♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_30 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ከብዙ የአየር ላይ ጉዞ በኋላ አመሻሽ ባሩክ አዲስ አበባ አየር ማረፊያ ደረሰ። ኮንትራት ታክሲ ይዞ ቤት ሲደርስ ኤሊያና የሞተ ሰው ተነስቶ ያየች እስኪመስላት ድረስ ደርቃ ቀረች። አይኖቿን እየከደነች ገለጠቻቸው የተለወጠ ነገር የለም ፊቷ ላይ የምታየው ከወራት በፊት የሄደው ወንድሟን ነው። ባሩክ እሷን ለመታዘብ ጊዜ አልወሰደም " እንዴት ነሽ እህቴ ?" ብሎ ወደ ቤት እየገባ " አውቃለሁ ድንገት እንደመጣሁብሽ ነገር ግን ብዙ አትገረሚ " አለና ሶፋው ላይ ዘፍ ብሎ ተቀመጠ። "ማለቴ እንዴት? " ራሷን ወዲያና ወዲህ አወዛወዘች " ምንም እኮ ያልከኝ ነገር የለም ማለቴ.... እንዴት?" በድጋሚ ጠየቀች " በቃ ውዷ ማስተካከል ያለብኝ ጉዳይ ነበርና ዶክተር ወንድማገኝ ሲደውልልኝ ነው እዛ ለተወሰነ ጊዜ ፈቃድ ወስጄ የመጣሁት " አለ ኤሊያና ፊቷን ኮስተር አደረገችና " በኤሊያና ምክንያት ነዋ የመጣኸው?" አለች " አዎ የመጀመሪያው እሱ ነው " አለ ኤሊያና ወገቧን ያዘችና ጠርጥሪያለሁ የዛች ጦሰኛ ጉዳይ እንደሆነ ቆይ ምን ልሁን ነው የምትለው? ምን ብትሆንላት ነው የምትደሰተው ምንድን ነው የሚያዝናናት ከአገር ወጣህላት አይደል?" አለች " ኤሊያና!" ባሩክ ጮኸባት " ገና ከጉዞ ከመግባቴ በነገር ትቀበይኛለሽ? ምን አይነት እህት ነሽ?" ተናዶ ተነሳ እና ሻንጣው ላይ ልብስ አውጥቶ ወደ ሻወር ቤት ገባ። " እሽ ይቅርታ ወንድሜ ግን ምን ላድርግ በጣም አናዳኝ እኮ ነው " አለች " ከአንድ ወገን የአድሎ መመልከቻ መነፀር ውጭና በሚዛናዊነት ለመመልከት ሞክሪ እንደዛ ካልሆነ ጥሩ አይንና ልብ አይኖርሽም! በእሷም ቦታ በእኔም ቦታ ሆነሽ ለማሰብ ሞክሪ የሁለታችንንም ችግር ውሳኔዎች በገለልተኛ አቋም ተመልከች ያኔ ከጥላቻ የፀዳ ውሳኔ ይኖርሻል።" አለ ባሩክ " ኤጭ አጉል ፍልስፍና ..." ባሩክ በአባባሏ በረጅሙ ሳቀ " እውነቴን እኮ ነው ይሄ ፍልስፍናህ ምን ሲያመጣ አየን? ሲጎዳህ እንጅ ሲጠቅምህ አላየሁ እንዴት ብየ ነው ጥሩ ምክር ነው ብየ የምወስደው እ?" መልሳ ጠየቀችው ። አሁንም ባሩክ ሻወር ቤት እንዳለ " እኔን የጎዳ ከመሰለሽ እንኳ አንቺን ሊጠቅምሽ ይችል ይሆናል" ብሎ ዝም አለ ። ኤሊያና ከሻወር እስኪወጣ ለመተው ያሰበች ትመስል ዝም አለችው ። *** መቅደላዊት ልታነበው ያነሳችውን ደብተር ከድና አስቀመጠችውና ከዶርሟ ወጥታ ወደ ስቴዲየም ሄዳ የእለት ውሎዋን አገባዳ ወደ ማደሪያ አዘቅዝቃ በምዕራብ አቅጣጫ ታዘግማለች። መቅደላዊት በፍቅርና በስስት ቀይ ግርደሽ ላይ እግሯን የዘረጋችውን ፀሀይ ትመለከታለች። ከፅሀይ ምልከታ ስትዞር በአጠገቦቿ ያሉት ዛፎች ሳይቀሩ ያንሾካሹካሉ። በዚህ የተመስጦ ስአቷ ላይ አባቷ ደወለ ። " አቤት አባዬ " አለች ወዲያው እንደጠራ አንስታ " ደህና ነሽ ልጄ?" " ደህና ነኝ አባዬ ብዙ አትጨነቅ ሁሉም ሰላም እየሄደ ነው እኔም ለስኮላሩ የሚሆን ዝግጅት እየተዘጋጀሁ ከእስከዛሬው የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እፈልጋለሁ ። እና ለዚህም በርትቼ እያጠናሁ ነው የምፈልገውን ነገር በዚህ ውጤት እንደማገኝ እርግጠኛ ነኝ ስለዚህ አታስብ " አለች " እሽ ልጄ እንዳልሽ አለማሰብማ እንዴት እችላለሁ ደህንነትሽ እኮ ያሳስበኛል ። እናትሽም ተጨንቃለች " " አትጨነቂ በላት አባ ያለውን ነገር አስረዳት ምንም የተፈጠረ ነገር የለም እግዚአብሔር ይመስገን አሀለን አሪፍ እየሄደ ነው። " " እሽ በቃ ልጄ አንብቢ አንረብሽሽ " አለ። መቅደላዊት የተወሰነ ያህል የአባቷንና የእናቷን ደግነት በአእምሮዋ ካብሰለሰለች በኋላ " ለእማየና ለአባዬ ይሄ አይገባቸውም በቃ አባ እስካሁን ስላስጨነኳችሁ በጣም ይቅርታ ከዚህ በኋላ ግን በጭራሽ አላሳዝናችሁም በእኔም አታፍሩም አኔገትም አትደፉም አትፈሩምም " ብላ ፊቷን አበስ አበስ አደርጋ ተነስታ ከእንደገና ወደ ዶርሟ ተመለሰች። *** ሜላትና ናሆም የፍቅር ቄጠማቸውን ሲነሰንሱ ከቆዩ በኋላ ተቃቅፈው ወክ ማድረግ ጀመሩ። በእግር አነሳሳቸው አብሯቸው በሚዞረው ጥላቸው ሳይቀር ኤየተሳሳቁ መንገድ ለመንገድ ይጓተታሉ። በየመናፈሻ ስፍራወቹም እየተቀመጡ ይተሻሻሉ ይላፋሉ ይሳሳማሉ። " አሁን ባሩክ መጥቶ ከመቅደላዊት ጋር ታርቆ እኔና አንቺ ጋር በዚህ መንገድ ፊትና ኋላ እየተጠባበቅን አኔድ ላይ አራታችንም ተደርድረን ስናወራ ኡፍ " በሀሳብ ናወዘች ሜላት " እንደዛ ኤንኳ አይሆንም " " እንዴት? " አለች ሜላት " ምክንያቱም ባሩክ እንደዚህ አይነት ነገር ደስ አይለውም ለእሱ እያንዳንዷ ደቂቃ ሰከንድ ሀብብ ናት ጭራሽ ወክ በማድረግ ጊዜውን ሊያቃጥል ? አያደርውም ምነው ይሄ አብሮነቱ ቀርት አጠገባችን ባየነው ኖሮ የኔ ፍቅር ልጅቱ ደርስተኛ በሆነች እንጅ የእኛ ይሄ ፍላጎትስ ትርፍ ነበር። ይልቅ ወይ እሱ ኤኔዲመጣ ወዬ እሷ ወደ እሱ የምትሄድበት መንገድ በተፈጠረ።" አለ " ልክ ነህ የኔ ፍቅር እሷ መጀመሪያ ደስተኛ በሆነች አሁን ካለችበት መከራ በወጣችልን ይሄ ከሆነ ለእኛ ትልቅ ነገር ነው። **** ባሩክ ሻወር ወስዶ ከተረጋጋ በኋላ እና ኤሊያናን ካሳመነ በኋላ ስልኩን አውጥቶ ለናሆም ደወለ። ናሆም ስለኩን አየው " የማነው ስልክ " አለች ሜላት " አላውቀውም የኔ ቆንጆ " አታንሳው የኔ ፍቅር እንደባለፈው ሊሆን ይችላል " አለች " ላይሆንም ይችላል የኔ ውድ መቼም ከዛ በኋላ ይለመዳቸዋል ብየ አላስብም "አለ " አይ ናታኔም ክፉ ሆኗል በዛ ላይ አሁን ወደ አዲስአበባ እንደሄደ ሰምቻለሁ ስለዚህ እዛ ቁጭ ብሎ ነገርና ክፋት ብቻ ሊሸርብ ይችላል። " አለች " እና አታንሳው እያልሽኝ ነው? " አወ የኔ ፍቅር ተወው ጊዚያችንን ያበላሽብናል።............ ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 31♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_29 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ዩኒቨርስቲው ለአንዲት ሴት ባዘጋጀው አሜሪካ የሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ scolarship ሆታ ሊሰጥሽ ማሰቡን ለመንገር ነው ያስጠራሁሽ ያው ይሄ ሀሳብ ከማጠቃለያ ፈተናው በፊት መስማትሽ እንዲያጠነክርሽና እንዲያጎበዝሽ ስላሰብኩ ነው።" አለ መቅደላዊት ተነስታ ተቀመጠች አፏን ያዘች በደስታ ዘላ ዶክተርን አቀፈችው ስቆ እሱም አቀፋት " በእውነት ዶክተር በጣም ነው የማመሰግነው ከአሁን ጀምሮ አነባለሁ።" አለች " አውቃለሁ ጎበዝ ነሽ መስራት የምትችይ ልጄ እንደሆንሽም ያለፉትን ሲምስቴሮች መመልከት ለእኔ በቂየ ነው። እንደው ይቺን ያልኩሽ እንድትበርቺ ነው እንጅ " " ኧረ በደንብ ነው የሚያበረታኝ ዶክ ምን ያህል ደስ እንዳለኝ አታውቅም " " እሽ ስለዚህ ጉዞሽን ጀምሪ የምትወጅውን ነገር ለማግኘት አሁኑኑ መጀመር አለብሽ ለነገ እንዳትይ " " እሽ ዶክተር በእውነት ተስፋ ወደ መቁረጥ ደርሼ እስከማቋረጥ አስቤ ነበር " " ለምንድነው ለማቋረጥ ያሰብሽው?" መቅደላዊት ትንሽ አሰብ አደረገችና " ያው ማለቴ የመጀመሪያ ሲሚስቴር ፈተና ላይ የደረሰብኝ ነገር መልሶ በዚህ ሲሚስቴርም የሚደርስብኝ መስሎኝና ጥሩ ሁኔታ ላይ ስላልሆንኩ ነበር አሁን ግን እንደዛ አላስብም ዶክተር ይሄው ከአሁን ነው የምጀምረው ዶክተርየ በጣም ነው የማመሰግነው ተስፋየን ሁሉ ነገሬን ነው ያበሰርከኝ ብላ " በደስታ እየተፍነከነከች ተነሳችና ከወገቧ ጎንበስ በማለት አክብሮቷን ገልጣ ወጣች። መቅደላዊት ዶክተር ያላትን እየደጋገመች እየሳቀች የአስተዳደር ህንፃውን ወጣችና " ባሩክ እየመጣውልህ ነው! የኔ ፍቅር የኔ ሁሉ ነገር ሁሉም መንገዶች እየተስተካከሉልኝ ነው ደግሞ ስለምትፀልይልኝ ነው መሰል ሁሉም ነገር በሀሪፍ እየሄደልኝ ነው። አሁን ከአንተ ጋር በአሜሪካ ጎዳናዎች እጅ ለእጅ ተያይዘን ዎክ እያደረግን ተመልካችን ስናስቀና ድክም ሲለን ደግሞ ከአንዱ ካፌ አረፍ ብለን ኬካችንን አዘኔ ሳንበላው እየተቀባባን ብቻ ደስተኛ ሕይወት ሲኖረን እየታየኝ ነው። " እያለች ሳታስበው ዶርም አካባቢ ደረሰች። " ይሄን ዜናማ ለሜላት ና ለዮርዳኖስ መናገር አለብኝ።ብላ ስልኳን ከኪሷ አወጣች። ፍልቅልቋ ዮርዳኖስ ከመቅደላዊት የሰማችውን የብስራት ዜና ለማዳረስ ጊዜ አልፈጀባትም። ወዲያው ከመቅደላዊት ጋር አውርተው እንደጨረሱ ነበር ለነ ሜላት ደውላ ሁሉንም እንደወረደ የነገረቻቸው። መቅደላዊት ደውላ ስትነግራቸው " ሰማንኮ " ሲሏት በጣም ነበር የተገረመችው በዮርዳኖስ ፍጥነት ።መቅደላዊት የሷ ደስታ ለምን ያህሎቹ ደስታ እንደሆነ ስታውቅ ይበልጥ ደስተኛ ለመሆን ፈለገች። በቃ በደስታ መሞላት ብቻ፣ ፈገግ ማለት አለመናደድ መቻልን ስታስብ ነፍሷ ሀሴት አደረገች። እጆቿን ወደ ላይ ዘርግታ የፈጠራትን ጌታ እያለቀሰች አመሰገነችው። የምስጋናዋ አይነት ሲታይ ባሩክን ያመጣላት እንጅ እንዲህ ገና ባልተረጋገጠ የውጭ እድል ማግኘት አይመስልም። ፍቅርና ትዝታ እንደወጀብ የሚያናውጧት ጀልባ መቅደላዊት ። በትዝታ ስለወደፊቷ ከወዲሁ ጉባኤ ተቀምጣ ማውጠንጠኗን ቀጥላለች። እንዲህ አለች " ፍቅር ማለት ግን አስደሳች ነው ሌላ ምንም አይነት ትርጉም የለውም በቃ ባሩክ የእኔ የማብቂያየ የህይወት ዘመን መቋጫየ ወንድ ነው። ከሱ ውጭ ማንንም ማየት አልችልም። ከሱ ጠረን ውጭ የማንንም ጠረን መልመድ አልችልም ባሩክ የኔ ፍቅር በጣም ናፍቀኸኛል። እኝደምትኮራብኝ አውቃለሁ ይበልጥ ደግሞ አሜሪካ ምድር ስመጣ ትኮራለህ ።ትደሰታለህም ምክንያቱም አንተ የእኔ የብርታቴ የጥንካሬየ ምሳሌ እና ደጋፊየ ስለሆንኽ።" ** ባሩክ የልቡ አንድ አካል ወደ ሆነችው ወደሚወዳት ሀገሩና ፍቅረኛው ለመሄድ በዕለቱ ተረኛ ከሆነው Et 367 የኢትዮጵያ የመንገደኞች አውሮፕላን በመገኘት በትኬት ወንበር ቁጥሩ ላይ ተቀምጦ ታብሌቱን አውጥቶ የቴዎድሮስ ካሳሁንን ( ቴዲ አፍሮ ) ሙዚቃ ኢትዮጵያ የሚለውን ከፍቶ ማዳመጥ ጀመረ። በእያንዳንዱ የዘፈን ስንኞች የኢትዮጵያ የአሁን ገፅታ የበፊትና የሚመጣው ሀናቴዋን በሚጣፍጥ አገላለጽ በተዋቡ ቃላቶች ድምፃዊ ቴዎድሮስ ገልጦታል። ባሩክ ከጂጂ ቀጥሎ የሚወደው ቴዎድሮስ ካሳሁንን ቴዲ አፍሮን ነው። የኢትዮጵያን የሙዚቃ እድገት ከፍ እንዲል እና በመላው አለም ታዋቂነት እንዲኖረው አስተዋፅኦ ካደረጉ ጀግና ዘፋኞች አንዱና ግንባር ቀደሙ ነው። የዚህ ትውልድ ጀግና እሱ ነው። ኢትዮጵያውያንን ከሌሎቹ ወገኖቻቸው ኤርትራውያን ጋር አንድ በማድረግ በዘፈን ስንኞቹ ገልጧል የተለየ ነገር እንደሌላቸውና አኗኗራቸው ቋንቋቸውና አመጋገባቸው አለባበሳቸው አንድ እንደሆነ በስንኞቹ አስቀምጧል " ፍቅር ያሸንፋል " በሚለው ንግግሩና መሪ ቃሉም ይከበራል።ቴዲ የኢትዮጵያን ታሪክ ጥንቅቅ አድርጎ የሚያውቅ አርቲስት ነው። **** ናሆም እናት ናሆም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንዳለና ከሷም ሆነ ከልጇ ጋር ያለው ግንኙነት ጥሩ እንደሆነ ነገር ግን አሁንም እረፍት ያልሰጣት ነገሮች አሉ። ደርሶ ጥፍት ይልባታል አልፎ አልፎ ስትደውልለት ደግሞ አያነሳም። አልፎ አልፎ ሲያወራት ደግሞ ቅርዝዝ ድብር ይልባታል የዚህ ሁሉ ምንጭ እንደዚህ የሚያደርገው ምን እንደሆነ ለማወቅ ስትጠይቀው " ምንም ችግር የለም አታስቢ እናቴ ደህና ነኝ " ከሚል መልስ ውጭ ሌላ ነገር ሊነግራት አልቻለም ይሄ ደግም እረፍት ነስቷታል። ከስንት መከራ በኋላ ያገኘችውን ልጇን የምታጣው እየመሰላት ትፈራለች። ደፈር ብላም እንዳትጠይቀው ቢናደድብኝስ የበፊቱን አስታውሶ ቢርቀኝስ ብላ ታስባለች። ይህንንም ጉዳይ ለልጇ ስታወራት " ተይው እማዬ ምን አልባት እንዲህ በቶሎ ሊላመደን አይችል ይሆናል ይከብደዋል፣ ጊዜ ልንሰጠው ይገባል በዛ ላይ ባሩክም ከአገር ስለወጣ ደብሮት ይሆናል ለማንኛውም አሁን ክረምት እየደረሰ ስለሆነ ያኔ ሲመጣ ይበልጥ እንግባባለን እኛ ጥሩ ሆነን እንጠብቀዋለን ፍቅር እንሰጠዋለን ተዋደን ጥሩ ቤተሰብ እንመሰርታለን " ነው የምትላት። በዚህ በልጇ ንግግርም እረፍት የለሽ ሰቀቀኗን ታስታግሳለች። ግን ደግሞ አጥታ ስላገኘችው ነገር በብዙ ታስባለች ልጇን እንዴት አድርጋ መያዝ እንዳለባት ደጋግማ ታስባለች። ከጉያዋ እንዳይወጣ ምንም ነገር እንዳይሰማው አባቱን ማጣቱን እንዳያስታውስ ለማድረግ፣ የሚፈልገውን ነገር ስለማሟላት ወደ ፊት ስለሚሆነው ነገር ጭምር ታልማለች። ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 30♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_28 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ናሆም ልመናና ማስጠንቀቂያ የተሞላበትን ፀሎቱን ጨርሶ ቀስ እያለ ከዶርም ወጣ። ሜላት ከናሆም ጋር ወደ ገብርየ ዋርካ ሄዱ።" ናሆም በእናትህ እንዲህ አትሁን እባክህን እጨነቃለሁ እያንዳንዱን ነገር ከአንተ ሕይወት ጋር አታገናኘው። ጠንካራ ሁኝ ትለኝ የል? ታዲያ አንተ ሳትጠነክር እንዴት ነው እኔ የምጠነክረው?" አለች ሜላት " ምን ላድርግ ብለሽ ነው የኔ ፍቅር አዲስ ሕይወት ጀመርኩ ብየ ገና መደሰት ስጀምር እንዲህ ትላንቴን የሚያስታውስ ነገር አላጣም። ይቺ ልጅ ለእኔ ብላ ምን አይነት ሕይወት እንደገጠማት ተመልከች ሜሊ " አለ እንባው እየተናነቀው " እያየሁኝ ነው ግን ደግሞ የአኔተ እንዲህ መሆን ምንም የሚፈጥረው ነገር የለም ራስህን ከመጉዳት በቀር።" አለች ሜላት **** የአዲስ አበባ ሰማይ ያለ ወትሮዋ በፅሀይ ሞቃለች። ለፅሀይ ቅርብ ከሆነችው ፕላኔት ሜርኩሪ በላይ የአዲስአበባ መሬት እጅጉን ለፅሀይ ቅርብ መስላለች ። ሰው በሰው ላይ ይርመሰመሳል። መኪና በመኪና እየታከከ ይሄዳል። በዚህን ጊዜ አንድ ከወደ ሰሜን የመጣ ባላገር ፀሀይዋን ቀና ብሎ ተመልክቶ "ኧሯ የዝናብ ጠሀይ"አለ! ከትንሽ ደቂቃዎች በኋለ ዝናቡ ጣለ። ዝናቡ እስከ ምሽት አራት ስአት መዝነቡን ቀጠለ። ናታኔም ፒያሳ መሀሙድ ጋ ዝናቡን ካባራ በኋላ ሽቅብ ወደ ዳግማዊ ምንሊክ አደባባይ ቀስ እያለ እየተራመደ ግራ ቀኙን ይመለከታል። አእላፍ እንስቶች በጥቅሻ ያጣድፉታል። ገና በውል ያልጠነከሩ ለጋ ህፃናት ገላቸውን አጋልጠው ካገኙት ለመዳራት ተዘጋጅተዋል። ናታኔም ይህን ሁሉ በትዕግስት እየተመለከተ ያልፋል። ደሐብ ሆቴልን አልፎ ሽቅብ ወጣ። አንድ ሰው ከግሮሰሪው ወጥቶ አንዷን ህፃን ቢጤ ሴተኛ አዳሪ " አንቺ ህፃን ልጅ ለአዳር ስንት ነው ምትይው?" አለ ልጅቷ በቄንጠኛ አስተያየት ያው አንተ ስለሰከርህና ብዙ ጊዜ ስለማትቆይ ቶሎ ስለምተኛ 550 ብር" አለች " ሀምሳዋ የቫት ናት?" አለና በረጅሙ ሳቀ ሰካራሙ ፡ ልጅቱ " መሆኑ ነው" አለች " ግን ትችይኛለሽ ? በኋላ በአስገድዶ መድፈር እንዳልከሰስ ?" አለ " ውይ እንግዲህ አትሟዘዝብኝ ስራ ነውኮ የያዝኩት ከተመቸኽ እንሂድ ካልተመቸህ ደግሞ ቦታውን ልቀቅ"አለችና ኮስተር ብላ አጠገባቸው ንግግራቸውን ወደ ሚመለከተው ናታኔም ዞራ በግራ አይኗ ጠቀሰችው። ፈገግ አለች። ጭኖቿን ከፈት ዘጋ አደረገች። ስትስቅ መላ አካላትን ታነዝራለች። እድሜዋ በ20 ዎቹ መጀመሪያ ናት። በናታኔም አቋምና ወጣትነት የሻፈደች ትመስላለች። ሽፍደቷን ተጠቅማ እንቅስቃሴዋ ናታኔምን ለማማለል ነው። ሰካራሙ ወጣት ተናደደና " እኔ እዚህ ቆሜ እያወራሁሽ ከሌላ ጋ ለመ...ነው? እኔን እንዲህ የምታናግሪኝ ቅንዝራም " አለና ከእንደገና ንዴቱን ትቶ እየተቅለሰለሰ " ቆይ ደንበኛ እንዲህ ነው የሚያዘው? እኔኮ ሁሌም እጠጣለሁ ስጠጣ ደግሞ ብቸኝነቴን ምታስረሳኝ ሴት እፈልጋለሁ።" አለ " ውይ ሰውየ ለእሱማ ማግባት ነዋ! አሁን ከዚህ ሂድልኝ ምን የማይረባ ሰከራም ነው። " ብላው ናታኔምን በጥቅሻ እንዲከተላት ምልክት በመስጠት ቦታ ቀየረች። አሁንም ሰካራሙ ተከተላትና " እ ..ሽ.. ሾ ..ር..ት ስንት ነው?" አለ " 250 " አለች ውይ ውይ አንቺ ልጅ ዋጋሽ ውድ ነው የአንቺ ማዕድን አለው እንዴ?" ብሎ ትቷት ወደ ሀውልቱ ተሻገረ።ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በክብር ከነ ፈረሳቸው ሆኖ አየው ለደቂቃዎች አትኩሮ ከተመለከተው በኋላ ወደ ሀውልቱ አጥር ጠጋ ብሎ " ቆይ ግን እምዬ ምንድነው ነው ያደረከው? የኔ ጀግና እኮ ነህ ዝንተዓለም በልቤ ነው የምትኖረው። እንደ አንተ እዚች ምድር ላይ ሞቶ የኖረ ጀግና የለም። ወዲያው በአእምሮው አጤ ቴድሮስ ከነ አንበሶቹ ውል አለበት። ሰካራሙም እንደመበርገግ አለና እእእእእእ " ኧረ መይሳው አትቆጣኛ አንተም ጀግና ነህኮ የኔ አብዮተኛ ባለሹርባው ንጉስ። ባ..ትልስ አንተ አንድ ባታደርገን ኖሮ እስካሁን ተከፋፍለን ከክልልነት አልፈን በየ ዞኑ ሀገር መስርተን አልነበር። አንተ እኮ ነህ ለዚህ ሁሉ መሰረታችን አንተ ትለያለህ አባ ታጠቅ! ግን የያኔዋ ኢትዮጵያ ምን ትመስል ነበር ቴዲየ?" ብሎ ፊቱን የአጤ ቴዎድሮስ ሀውልት ወደ ተሰራበት ቸርቸል አደባባይ ላከ። ነገር ግን ሀውልቱን አልተመለከተውም ነበር። " አየ አጤ ቴድሮስ ግን እውነት በጣም ነው የምትገርመው በቃ አንተ ትገርማለህ ስራህ አስተሳሰብህ" አለና የአጤምኒሊክ ሀውልት አጥርን እንደተደገፈ እንቅልፍ አሸለበው!! ናታኔም ሴተኛ አዳሪዋን ልጅ ከእግር እስከ ራሷ ለደቂቃዎች ተመለከታት! " ሰውየ ምንድነው እየሳልከኝ ነው? አፍቅርኸኝ ነው? አፈጠጥክብኝኮ " አለች ናታኔም አልመለሰላትም። " አቦ ተንቀሳቀሰ የየቱ አጁዛ ነው" ብላ እጇን አወራጨች። ናታኔም በሁለቱም ጉንጮቹ የእንባ ዘለላዎቹን እየጣለ ልጅቱን ትቶ ሽቅብ ተራመደ። ወደ አዲሱ ገበያና ሰሜን ሆቴል የሚያስወስደውን መንገድ ትቶ ወደ ገዳም ሰፈር ገባ። **** ዶክተር ወንድማገኝ መቅደላዊትን ቢሮው ድረስ አስጠራት። መቅደላዊትም ትንሽ ተሽሏት ስለነበር ሄደች። ዶክተር የመቅደላዊትን ገፅ በሀዘኔታ ተመለከተ። በሀዘን እንደተጎዳች ለማወቅ አፍታ አልፈጀበትም። " በቅድሚያ እንኳን ደህና መጣሽ መቅደላዊት " አለ ዶክተር መቅደላዊት ለአክብሮቷ አንገቷን ቁልቁል አጎነበሰች። " ለአንዲት ቁምነገር ነው የጠራሁሽ እና አሁን እንዴት ነሽ?" "ደህና ነኝ ዶክተር " " ጥሩ የአንደኛው ሲሚስቴር ውጤትሽ ከሴቶች የተሻለ ነው እና የአሁን የሁለተኛው ሲሚስቴር ውጤትሽ ከመጀመሪያው ጋር እኩልና ወይም ከዚያ በላይ ከሆነ ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 29♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ::

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_27 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ሜላትና ዮርዳኖስ ባሉበት መቅደላዊትን ከመሀል አድርገው ገደም እንዳሉ በዚያው እንቅልፍ ወሰዳቸው። የሞት መላዕክ በሌሊት ወፍ ተመስሎ ያንቋርራል። ሌሊቱ ከፅልመት እያፈነገጠ ለብርሃን እጅ የሰጠ ይመስላል። መቅደላዊት በሰመመን ሆና ከእንቅልፏ ነቃች። ፀሀይ ያልጠነከረ ብርሃኗን በመስኮቱ አሾልካ ሐጠዋት ስጦታዋን ለገሰቻት ። መቅደላዊት አይኗን ጋረድ አድርጋ ለመነሳት ስትሞክር ወደ ነበረችበት መለሳት ደግማ ሞከረች አሁንም አልቻለችም። ለሶስተኛ ጊዜ ሞከረች ቦታዋን ትታ ወደ ሜላት በኩል ወደቀች። ሜላት ብርግግ ብላ ነቃች። " ምን ሆንሽ መቅዲ " አለች ሜላት አይኗን እያሻሸች " አላውቅም ልነሳ ስሞክር እወድቃለሁ። አለች " በቃ አረፍ በይ ትንሽ ቆይ አሁን ይሻልሻል " አለችና ቀኝ እጇን አስደግፋ አስተኛቻት ። " ግን ፈጣሪ ምን አድርጌው ነው? እንዲህ መከራየን የሚያበዛው? በጣም አሰቃየኝኮ ወይ ፍዳየ ምንም አልቻልኩም ባሩክን አለማሰብ አሌቻልኩም እሱን ለሰከንድ እንድረሳው አልፈቀደልኝም ባሩክ የሰውነት አካሌንና አእምሮየን ተቆጣጥሮታል ምን ማድዴግ እንዳለብኝ አላውቅም ሜሊ ብቻ። እንጃ እኔ አልቻልኩም " አለችና እንባዋን ዘረገፈችው እንባዋ ከየት እንደተጠራቀመ ይገርማል። " አይዞሽ በቃ ተረጋጊና መወሰን ያለብሽን ነገር ወስኝ። ባሩክን ደግሞ እርሽው በቃ የተወሰነ ስሜት ለአንቺ ቢኖረውማ እንደዛ እያለቀስሽ አይዘጋብሽም ነበር። አይዞሽ ይልሽ ነበር። ነገር ግን እሱ አሁንም ቂም እንደያዘብሽ ነው ስለዚህ ውዴ እሱን እሱን ማለትሽ ስህተት የሆንሽ እየመሰለኝ ነው ስለዚህ ተረጋጊና አስቢ ባሩክ በጣም ጨካኝ እየሆነ ነው። " አለች ሜላት የመቅደላዊትን ውሳኔና አቋም ለማስቀየር እየሞከረች። " ምን ያድርግ እሱ የማለቅሰው እውነቴን ስለመሆኑ ተጠራጥሮ ይሆናል ምን አልባት የማለቅሰው የውሸቴን እንደሆነ ና እያስመሰልኩ እንደሆነ ሊያምን ይችላል። ህህህህ መቼም አንድ ጊዜ እምነቱን አጤቻለሁ። እኔ እያለቀስኩ ያለሁት እምነቱን ስለማጣቴ ነው። መጠራጠር የጎሪጥ መተያየት ባሩክ እንደዛ የሚመለከተኝ ነው የሚመስለኝ እናም ለዛ ነው ብዙም ድርጊቱ ያላስገረመኝ ነገር ግን እኔ ስለሆንኩ አንድ ጊዜ ከመጀመሪያው ያጠፋሁት እስኪረዳኝና እስኪያምነኝ የእውነቴን እያለቀስኩ እየተጎዳሁ እጠብቀዋለሁ። እሱ ያኔ የኔ ይሆናል ምክንያቱም አውቀዋለሁ ልቡ ንፁህ ነው ክፋት የለበትም በጭራሽ ለሰው መጥፎ ነገርን አይመኝም። እሱ ቢጎዳ ይሻለዋል እንጅ ሰው እንዲጎዳ አይፈልግም። " ብላ መቅደላዊት በባሩክ ጉዳይ ላለመነቃነቅ ከአለት ብሳ ፀናች። *** ባሩክ መሙላት ያለበትን ሁሉ ሞልቶ መጨረስ ያለበትን ጨርሶ ለመሄድ ከራሱ ጋር ተስማማ። " ሄጄ ምንም እንኳ በሽታዋን ልጋራው ባልችል ላስታመም ግን እችላለሁ ። እኔ ካለሁበት የምንም አለም የምታስወጣኝ መቅዲ ነች። ስለማስፈልጋት ሳይሆን ስለምታስፈልገኝ ብቻ እሄዳለሁ። አዎ በፍቅሯ ልትፈውሰኝ ይገባል። በሷ መዳሰስ ይኖርብኛል። መቅደላዊት የጉድለቴ ሙላት ናት። አዎ እሷ በአይኖቿ አምፖሎች ነው ራሴን የምመለከተው። እሷ የእኔነቴ መገለጫ ናት። ልቤ ያለ ቅጥ የሚመታው፣ ስታወራ በዝምታ የምዋጣው ስለምወዳት ሳይሆን ስለማፈቅራት ነው አሁን ሁሉን ነገር አረጋግጣልኛለች። እንደምወዳት አረጋግጣልኛለች ያ እኔ ማን እንደሆንኩ አቅሜ የት ድረስ እንደሆነም አሳይታኛለች። ስለዚህ ወደ ሀገሬ ወደምወዳት ልጅ የኑሮየን መቅረዝ ወደ ሆነችው ልጅ እሄዳለሁ እንደመጣሁ እመለሳለሁ። ሁሉም ነገር ከሷ በታች እንጅ ከሷ በላይ አይደለም። ምን አልባት እሷ ግራ ተጋባታ አለዚያም በሁኔታየ ተደናግጣ ተስፋ ቆርጣ ይሆናል። ወይም የእኔ እንደዛ መሆን አልገባት ይሆናል ምን አልባት አሁንም የትላንት ታሪክ ውስጥ ያለሁ ይመስላት ይሆናል ነገር ግን እውነቱ እኔ ራሴን መሆን ስላልቻልኩ ነው። እኔ ራሴን አልሆንኩም በማስመሰል አለም ነው ያለሁት እኔ ለእሷ የምገባ ሰው ስላልሆንሁ መስሎ ስለተሰማኝ ነው። አመክንዮ ባሩክ ራሱን ስለሚያስቀድም? ራሱን ስለደበቀ? ከሰዎች መግባባት ስለማይችል? አመክንዮየ ጥራዝ ነጠቅ እውቀት እንዳለው ሰው ሊሆን ይችላል ግን ደግሞ ያሰብሁት ማሰብ የምችለውን ነው። * ናሆም የሰማው ነገር ውስጡን ነክቶታል ። ምን ማድረግ እንዳለበት ግራ ገብቶት ተቀምጧል አሁን ሁሉም ነገር ከአቅሙ በላይ ሆኖበት ዝም አለ። በባሩክ ግን አዝኛለሁ መቅዲ እጅግ በጣም አስከፍቶኛል። ምን አልባት ግምቴ የተሳሳተ ሊሆን ይችላል አንደሰውም የጠበኩት ነገር እንደማይሳካ አምናለሁ ። ግን ባሩክን በዚህ መልኩ አልጠበኩም እንዴት እያለቀሰች እየታመመች እየናፈቀችው ዝም ብሎት ይዘጋል ብሽቅ ነው።" ናሆም ባሩክ ጉዳይ እየቆየ ተብሰለሰለ ራሱን ጠላው። መቅደላዊት አሳዘነችው። በትውስታ ወደ ራሱ ህይወት ተመለሰ ሁሉም ነገር በሱ ምክንያት ነው። የናታኔም እንደዚህ መሆን የባሩክ ከአገር መውጣት የመቅደላዊት የስቃይ ህይወት ሁሉም ህይወታቸው መታመሱ በሱ ምክንያት ነው።" አዎ በእኔ ምክንያት ነው። እኔ እደለኛ ሆኜ አልተፈጠርኩም ሁሌም ትላንቴን እንዳስታውስ ነው የተፈጠርኩት። ባሩክ እባክህን ልብህን ያራራውና መቅደላዊትን ታደግልኝ ፈጣሪ ሆይ እባክህ ሌላ አለምንህም ይችን ብቻ አድርግልኝ ባሩክ ወደ ሀገር ቤት እንዲገባ አድርገው ለአንተ ምንም የሚሳንሀ ነገር የለም ካልሆነ ፈጣሪየ ራሴን በጣም ነው የምጠላው!!!! Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 28♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_26 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ አሁንም በዝምታ በአርምሞ አንገቱን ከደፋበት ቀና ብሎ የምትለውን ማድመጥ እንጅ ምንም አላለም። የመቅደላዊት አይኖች ከላፕቶፑ እስክሪን ተሻግረው የባሩክ ጎን ደርሰዋል። በስጋ እንጅ በነፍስ ከራሷ ጋ አልነበረችም። ሁሉም ነገር ህልም መስሎ ታያት የምታየው ባሩክ ሳይሆን ባሩክን የሚመስል ሌላ ሰው መስሎ ታያት። ሰማይና ምድሩ ተደበላለቀባት። ለካ ሰው የፍቅሩን መጀመሪያ ሲያገኝ ሁሉም ነገር ይጠፋበታል። ቁጭ ብላ ራሱ ጉልበቷ ይብረከረካል። ሁለቱን እጆቿን አገጯ ላይ አስደገፈችና በሙሉ አይኗ ተመለከተችው። እሱም አያት ዮርዳኖስ እስካሁን ይዛ የነበረውን እንባ ለቀቀችው ሳታውቀው በጉንጯ እየወረደ ቀሚሷን ያረሰርሰው ይዟል። ሜላት በሌላኛው አፅናፍ በእጆቿ ተጋርዳ ተንሰቅስቃ ታለቅሳለች። ሰሶስቱም የሚያለቅሱበት ታዕምር ያልተገለጠላቸው የዋይፋይ ተጠቃሚዎች በነ ሜላት ሁኔታ እየተጎሳሰሙ ያንሾካሹካሉ። በመጨረሻ ሜላት እንባዋን አበሰችና መቅደላዊትን ሄዳ አቀፈቻት። ትከሻዋን ትጨምቃት ያዘች ።ፊቷንም ትደባብሳት ጀመር። በመጨረሻ ባሩክ ለራሱ በሚመስል ነገር ግን አፈትልኮ የመቅደላዊት ጆሮ ላይ የደረሰ ንግግር ተናገረ " ሁሉም ነገር የሚሆነው አንዴ እንዲሆን ስለተፃፈ ነው " አለና አጠገቡ ጠረምጴዛ ላይ እጆቹን አቆላልፎ ፊቱን ሸፍኖ ሄድ ሴቱን አወጣና ላፕቶፑን ዘጋው። መቅደላዊት ባሩክ ሲዘጋጋው " አትዝጋው ልይህ መች ጠገብኩህ ?መች አየውህ ባሩክየ ናፍቀኸኛል? ስለ አንተ ብቻ ነው የማስበው ።እባክህን አትጨክንብኝ የኔ ጌታ በጣም ነው የማፈቅርህ ነፍሴኮ የአንተ ናት ።" እያለች በሀዘኔታና በልመና የላፕቶፑን ስክሪን እየቧጨረች ጠነዘለች። ሜላትና ዮርዳኖስ አቅፈው አነሷት ።ላፕቶፑን ዘጉትና እሷን ደግፈው ወደዶርም ይዘው ለመሄድ ተነሱ ነገር ግን መቅደላዊት ተደግፋም ለመሄድ አቅም አጠራት! ሁሉም ነገር እያየችው እንደ ጥር ጉም ደመና እየተነነ ሄደ። አልቻለችም ሌሎች አላፊ ልጆች አቅፈው እስከ ዶርም ይዘዋት ሄዱ። አልጋዋ ላይ ሆና በለቅሶ ማጣጠር ጀመረች ሁሉም ስለሷ እንዲያ መሆን አዘኑላት። ባሩክ አይኑ ቀላ ፊቱ ተቀያየረ " ባሩክ አትዝጋው መች ጠገብኩህ ልይህ " ላፕቶፑን እየዘጋው እያለ ስትናገረው የነበረው አቃጨለበት " በጣም ከስታለች ጠቁራለች በጣም ተዳክማለች አዎ ከባድ ሕይወት እያሳለፈች ነበር ፀፀት ክፉ በሽታ ነው። አሁን ምን ላድርግ? " አለ ባሩክ ሁሉም ነገር ግራ እያጋባው። ወደ አስር ደቂቃ ገደማ ከራሱ ጋር ሲያወራ ከቆየ በኋላ " ሁሉንም ነገር ማስተካከል ራሴንም ማከም ሳይኖርብኝ አይቀርም ስለዚህ ወደ ሀገሬ መሄድ አለብኝ አዎ መሄድ አለብኝ የመቅደላዊትን ስቃይ ልጋራት ይጋባል ናፍቆቴን ፍቅሬን ላሳያትና ላካፍላት ይገባል። ስለዚህ መሄድ አለብኝ።" አለና በመሄዱ ተስማማ *** መቅደላዊት እያለቀሰች በዛው አሸልቧታል። እንቅልፍ ወስዷታል። ሜላትና ዮርዳኖስ መቅደላዊት የተኛችበት አልጋ ጫፍ ላይ ተቀምጠው አይን አይኗን ያይዋታል። " ባሩክ በጣም አበዛው ቢያንስ ስቃይዋ ባይሰማው መረዳት ያቅተዋል? ሲበዛ ራስ ወዳድና ቂመኛ ነው እንዴት እንደዛ እየለመነችው ይዘጋባታል። " አለች ሜላት በባሩክ ድርጊት እየበሸቀች " አላውቅም ሜሊ እኔም እንግዳ ነገር ነው የሆነብኝ እንደዚህ ለመሆን ከሆነ ለመን ላግኛት አለ። እኔም ላግኛት ሲል እሽ ብየ ደስ ብሎኝ የነበረውኮ ስቃይዋንና ህመሟን ያስታግስላታል ብየ ነው። ለዚህ ለዚህ ባይደውል ባያገኛት ይሻል ነበር። ሲያስጠላ ይበልጥ ልጁቱን እሳት ውስጥ አስገብቷት ስቃይዋን አብዝቶት ሄደ። አሁን እንዴት ነው ከዚህ ነገር ራሷን የምታወጣው። እንዴት ነው የዛሬውን ምሽት ሁኔታስ በቀላሉ ከአእምሮዋ ለመርሳት የምትሞክረው?" ዮርዳኖስ በብሸቀትና በንዴት ሆና ጥያቄ ሀሳቧን ለሜላት አቀረበች። " አሁን ግን የግድ ትምህርቷን ማቋረጥ ሳይኖርባት አይቀርም። ሲሻላት ትቀጥለዋለች ሙሉ በሙሉ ባሩክን መርሳት ስትችል ሌላ ሕይወት ስትጀምር " አለች ሜላት " ኧረ ሜሊ ከአቋረጠችማ ይበልጥ ከባድ ነገር ውስጥ ትገባለች ማቋረጥማ የለባትም እዚሁ እንደምንም መቀጠልና ፈተናዋን ሲሚስተሯን መጨረስ አለባት። ከዛ ክረምት ራሷን አጠንክራ ትመጣለች እንደዛ ነው መሆን ያለበት በዛ ላይ ከዚህ በኋላ ምንም ልትሆንም አይገባም ባሩክን እስከወዲያኛው ለመርሳት መነሳት አለባት ለእሷ እንደማይሆን ማሰብ አለባት" አለች ዮርዳኖስ በእልህና በንዴት " ብቻ እንጃ ዮርዲ መቅዲ ብቻ ደድና ትሁን ሌላው ነገር እንኳ ሌላ ነው። አሁን እያሳሰበኝ ያለው ነገር የእሷ ጤንነት ነው እንደው በዚሁ ለሌላ በሽታ እንዳያጋልጣት እንጅ " ብላ ሜላት ስጋቷን አስቀመጠች። ዮርዳኖስ ዝም አለች። ሜላት ዝም ብላ ስታስብ ከቆየች በኋላ " ወይኔ ለናሆም ሳልደውልለት?" ብላ ስልኳን አውጥታ ደወለች። ናሆም በሶስተኛው ጥሪ አነሳው " ናሁ ተኝተክ ነበር እንዴ " አለች ሜላት ስልኩን ለማንሳት ሲዘገይባት ጊዜ " በትንሹም ቢሆን ወሰድ አድርጎኝ ነበር። እንዴት ነበር ቆይታችሁ ተሳካላችሁ? " አለ ናሆም የሆነውን ነገር ለመስማት እየጓጓ " ኧረ ተወው ናሁ እሱስ አይነሳ በጣም ይገርም ነበር " አለች " እ ምን ተፈጠረ? "አለ " ባሩክ ሌላ ህመም ጨምሮባት ሄደ " " ማለት?" " ማለትማ ምንም ሳያወራት ዘጋባት አትዝጋው እያለችው ዘጋው አንዲት ቃል ትንፍሽ አላለም!" አለች " ምን ሁኖ ነው?" አለ ናሆም ያልጠበቀው ነገር ስለነበር የሰማው " ኧረ ተወው ጭራሽ ቀና ብሎም አላያት ይባስ ብሎ እንደዛ እያለቀሰች ልይህ አትዝጋው አሌጠገብኩህም እያለች እየለመነችው። ምንም ሳይመስለው ዘጋው ብሽቅ ነው። ራሱን ምን ላይ እንዳስቀመጠ ብታየው። " አለች " እሽ አሁን ታዲያ መቅደላዊት እንዴት ናት?" " ከዛ በኋላ መሄድ ራሱ አልቻለችም የሆኑ ልጆች ናቸው ከዋይፋይ ጀምሮ አዝለው ያመጧት። በጣም ተጎድታለች። ስታለቅስ ቆይታ አሁን አካባቢ ነው እንቅልፍ የወሰዳት " አለች። ናሆም በተፈጠረው ነገር አዘነ " መቅደላዊት ይሄ አይገባትም ያ የውሻ ልጅ ነው ይሄ የሚገባው " ብሎ ለብቻው አጉረመረመ " ምን አልከኝ " " አይ ምንም ሜሊ በቃ አንችም አረፍ በይ "" አለ " እሽ ነገ መጥቼ አይሀለሁ እሽ"አለች "ችግር የለውም ደድና እደሪልኝ የኔ ፍቅር እወድሻለሁ " " እኔም ውድድድ አደርግሀለሁ" Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 27♥️ እሀድ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_25 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ በሁለተኛው ጥሪ ማንሳት እንዳለባት አሰበችና እጇን ወደ ኪቦርዱ አስጠግታ ቀረች መወሰን አልቻለችም። ከዛ እጇን መለሰችውና ለዮርዳኖስ መደወል ፈለገችና ስልኳን መንካት ስትጀምር እነ ዮርዳኖስ ራቅ ብለው እዬተሳሳቁ እየመጡ አየቻቸው መቅደላዊት ጮክ ብላ " ኧረ ዮርዲ ፈጠን በይ እየተደወለልሽ ነው ከውጪ" አለችና ስቅቅ አላት ልቧ ለሁለት ክፍል አለ። ትንሽ ራሷን ያዝ አደረገች ወዲያው ከውጪ የሚለውን ቃል ስታወጣው የመጣላት ባሩክ ነበር። ዮርዳኖስም እየሮጠች መጥታ " እንዴ መቅዲየ አታነሽውም ነበር ?" አለች " እንዴ ፈራሁ የግል ጉዳይሽ ነው ብየ " አለች " ኧረ ችግር አልነበረውም ለነገሩ እንደሚደወል ባውቅ አንሽው እልሽ ነበር እና ስንት ጊዜ ተደወለ?" አለች " ሁለት ጊዜ ነው የተደወለው " አለች መቅደላዊት " ውይ እስኪ እኔ ደግሞ ልደውል " አለችና ዮርዳኖስ በተደወለበት ቁጥር ደግማ ደወለች ።መቅደላዊት እጇን ልቧ ላይ አስደገፈች ልቧ ያለ ልክ ሲፈጥን ይሰማታል ። ሜላት የመቅደላዊት ሁኔታን ተመልክታ " ምን ሆንሽ መቅዲየ " አለቻት አላውቅም " በድንገት ከውጪ ብየ ለዮርዳኖስ ስነግራት ደነገጥሁ ልቤ ያለ ልክ መታ ሐፍራት ጀመርሁ ለምን እንደሆነ አላውቅም ውጪ ባልኩ ውጪ በተባለ ቁጥር ባሩክን የማየው እየመሰለኝ እፈራለሁ እናፍቀዋለሁ " አለች ሜላት መቅደላዊትን በግራ ኤጇ ሳብ አደረገቻትና አቀፈቻት " አይዞሽ የኔ ቆንጆ ሁሉም ነገር ይስተካከላል " አለች እያባበለቻት ዮርዳኖስ ልትደውል ስትል በመሀል በድጋሚ ሲደወልላት የነበረው ስልክ ደወለላት ለሶስተኛ ጊዜ ዮርዳኖስ መቅደላዊትን ዘወር ብላ አየቻትና አነሳችው ። " ሄይ ባ እንዴት ነህ " አለች ትንሽ ሰከንድ ከቆየ በኋላ " ዮርዳኖስ እንዴት ነሽ " አለ ባሩክ ሄዴ ሴቱን እያስተካከለ " ደህና ነኝ ወንድሜ ሁሉ ሰላም ነው? ጠፋህ እኮ እንደው ሀገርም ሰው አትናፍቅም ማለት ነው?" አለች በአንድ ጊዜ ሰብሰብ አድርጎ እንዲመልስላት እና ለአንድ ጥያቄ መልስ ሰከንዶችን ላለመጠበቅ። አሁንም ትንሽ ዘግየት ብሎ ለጠየቀችው ጥያቄ " ሁሉ ሰላም ነው ዮርዲ በደንብ ነው እንጅ የምናፍቀው ዳሩ ናፍቄ ምን አመጣለሁ " አለና መለሰላት። እሷም ከቆይታ በኋላ ምላሹን አደመጠችና " እሽ አሁን ደግሞ የሆነች ጓደኛየን ላቅርብልህ " አለችና ሄድ ሴቷን አውርዳ " መቅዲ ነይ" አለች መቅደላዊትም ፊቷን ጨፍገግ አድርጋ " ለምን ምን አደርጋለሁ " አለች " ነይ የኔ ቆንጆ የሆነ ሰው ላስተዋውቅሽ " አለች ዮሬዳኖስ " እኮ ማንን " መቅደላዊት ደግማ ደረቀች " እንዴ ውዴ ነይና ታቂዋለሽ ?" ብላ እንደመኮሳተር ስትልባትና ሜላትም " ሂጅ ነይ ካለችሽ ተዋወቂላት ደስ ይበላት ምን አልባት በአንቺ ስለምትኮራና የምትወዳትን ጓደኛዋን ለማስተዋወቅ ካላት ፅኑ ፍላጎት የተነሳ ሊሆን ይችላል የራሷን ሰው ልታስተዋውቅሽ የምትሻው " ብላ ከኋላ ገፋ አደረገቻት። መቅደላዊት ዮርዳኖስንም ሆነ ሜላትን እምቢ ላለማለት እሽም እምቢም ሳትሌ በደመነፍስ ወደ ዮርዳኖስ ተጠጋች ። ዮርዳኖስም ሄድ ሴቱን ቀስ አድርጋ ጆሮዋ ላይ ገጠመችላት። መቅደላዊት ዮርዳኖስን ቀና ብላ አየቻት። ዮርዳኖስም ፈጠን ብላ ላፕቶፑን ቀና አድርጋ አስተካከለችው ። መቅደላዊት ላፕቶፑ ላይ አፈጠጠች። ፊት ለፊቷ ላይ ፊቱን ያዞረ ሰው ተመልክታ ስለነበር " ዮርዲ ፊቱንኮ አዙሯል ብላ ወደ ኋላዋ ዞር ብላ ስታናግራት መቅደላዊት የተናገረችውን ባሩክ ሰምቶ ኖሮ ወንበሩን አዞረና " ሄሎ " አለ መቅደላዊት የጀሮዋ ታንቡር የተቀደደ መሰላት ድምፁ መላ ሰውንቷን አነዘረው እይታዋን ከዮርዳኖስ ወደ ድምፁን ወደ ሰማችበት የላፕቶፕ ስክሪን አደረገች። መቅደላዊት በመጀመሪያ እይታ ያየችውን ሰው በድጋሚ ለማየት ብትፈልግም አይኖቿ ጉልበት አጠራቸው። ዝም ብለው ጭራቸውን ብቻ ያርገበግባሉ። መቅደላዊት አፏ ተያያዘ ሰውነቷ ተዝለፈለፈ ወኔዋ ከዳት በድንጋጤ በደስታ በፍርሀት ራደች የኋላት ልትወድቅ ስትል እነ ሜላት ሁኔታዋን ከጀርባዋ ሆነው ይከታተሉ ስለነበር ደገፍ አደረጓት ወደ ሜላት በከኩል ጋደል አለችና አይኖቿን ቀስ አድርጋ ገለጠቻቸው ። ባሩክ ደግሞ በጥሞና ሲከታተላትና ሲያያት ነበር። ፊቱ ላይ ምንም አይነበብም ምንም ነገር አይታይም። መቅደላዊት ደግሞ ራሷን መቆጣጠር አልቻለችም እንደምንም ለመረጋጋት ሞከረችና " አንተ ባሩክ ነህ አይደል?" ባሩክ ያለምንም ቃል ራሱን በአወንታ ነቀነቀ። በሙሉ ማየት ያልደፈሩት አይኖቿ ባሩክን ለመመልከት አልፏ አልፎ ይመላለሳሉ። በጭራሽ በሙሉ አይኗ ልታየው አልቻለችም። ባሩክም በሙሉ አይኑ ሊያያት አልደፈረም ግን አልፎ አልፎ በድፍረት ያያት ነበር። መቅደላዊት ስሜቷን መቋቋም ሲያቅታት አለቀሰች ሄድ ሴቱን አወጣችውና አይኖቿን ሸፈነች።ሁሉም ነገር ከአቅሟ በላይ ሆነ። ከልቧ ተንሰቅስቃ አለቀሰች ሜላት በለቅሶ አጀበቻት ። ባሩክ አንገቱን ደፍቶ ፊቱ ላይ ምን ይኑር ምን አይነት ስሜት ይኑር የሚያስታውቅ ነገር የለም። ዮርዳኖስ ባሩክንም መቅደላዊትንም ሜላትንም እያፈራረቀች በሀዘኔታ ትመለከታቸው ጀመር። መቅደላዊት እንደ ዥረት የሚፈሰውን እንባዋን እያበሰች ከእንደገና ሄድ ሴቱን ጆሮዋ ላይ አደረገችውና በሚንቀጠቀጥ ድምጿ " ባሩክ ዝም አትበለኝ እባክህን በፀፀት ተሰቃየሁ! ፍቅርህ አደከመኝ ባሩክ!" አለች ከንግግሯ በላይ የአይኖቿ ሸፋሽፍት እንዲሁም ጣቶቿ እየተንቀጠቀጡ ስሜቷን ለመግለጽ ይጥራሉ ነገር ግን ስሜቷ ከዛም በላይ ነው። ነገር ግን ባሩክ....... Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 26♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_24 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ፀሀይ የተለመደ ተግባሯን ስትከውን ውላ ወደ ምዕራብ ልታሸልብ እየተንደረደረች እያለ ገና በውል እንኳ እግሯ ቀይ አንሶላዋ ላይ ሳያርፍ ከየት መጣ የማይባል ዝናብ የአድዋን ምድር አጥለቀለቀው። ፀሀይዋ ሳትጠልቅ የዘነበውን ዝናብ መሠረት በማድረግ አንድ ተማሪ " ጅብ ወለደች!" አለ " አጠገቡ ያለው ጓደኛው " ይህን በምን ያህል እርግጠኛ ነህ? " አለው " ያን ያህል እርግጠኛ አይደለሁም ግን እኔ ቤተሰቦቼ ሲሉ የሰማሁትን ነው።" በማለት ይህ አባባል ሲወርድ ሲወራረድ የመጣ እንጅ ራሱ የፈጠረው አለመሆኑን ለጠየቀው አስረዳ። " ሆ በጣም እኮ ነው የሚገርመው እንዴት ፅሀይ እያለች በሚዘንብ ዝናብ ጊዜ የሆነ የማይሆን ነገር ይሰጣል " በማለት ጅብ ወለደች የተባለውን ነገር አላምንም በማለት እጁን አወራጨ። እንዲህ እያሉ እየሄዱ መቅደላዊትን አጠገባቸው ያለው ልጅ ተመለከታት " አንተ እንዴት አባቱ ነው ያማረባት ፐ ወደ ቀድሞ አቋሟ እየተመለሰች ነው!" አለ። " አይመስለኝም ልጅቱ ግራ ገብቷታል አንዳንድ ጊዜ እንደዚህ ልዕልት መስላ ትወጣለች ሌላ ጊዜ ደግሞ ጉፍንጉፍ ትሆናለች። አሁን እንደዚህ ለመሆኗ ራሱ የሆነ ነገር ምክንያት አግኝታ ነው የሚሆነው ብቻ የልጅቱ ባህሪ አይጨበጥም ግራ ይገባኛል " አለ። መቅደላዊት ሽቅር ቅር ብላ ወደ ከተማ እየሄደች ባለበት ጊዜ ነበር ዮርዳኖስ የደወለችላት። " ሄሎ ዮርዲ " አለች መቅደላዊት ፍፁም በሆነ በተረጋጋ ስሜት " እንዴት ነሽ?" " አለሁልሽ " " አኔምልሽ መቅዲ ዛሬ ማታ ለአንድ ትልቅ ጉዳይ ፈልጌሽ ነበር። ላገኝሽ እችላለሁ?" አለች ዮርዳኖስ " እንችላለን አሁን ከተማ እየሄድኩ ነው ስመለስ እደውልሻለሁ!" " መልካም እሽ ስትገቢ ደውይልኝ " ዮርዳኖስ ፀሀይ ፀሀይዋን እየተመለከተች ቶሎ እንድትመሽ እንድትጨልምላት የምትፀልይ ትመስላለች። " መቅደላዊት ምሽት 2:30 ሲል በቃሏ መሰረት ለዮርዳኖስ ደወለችላትና ተገናኝተው ወወደ ዋይ ፋይ ቦታ ሄዱ። **** " እና ዛሬ ልታገኛት ነው?" አለች ኤሊያና አይኗ እንባ እየቋጠረ። " አዎ ማግኘት እንዳለብኝ ተሰምቶኛል ከዚህ ውጪ ምንም አማራጭ የለኝም" አለ ባሩክ " እኔ ግን ድጋሚ የምትጎዳህ እየመሰለኝ እፈራለሁ " " አትፍሪ የኔ ውድ እህት እሷ እኔን የመጉዳት አቅም የላትም ማንም ማንንም የመጉዳት ስልጣን የለውም። ስለዚህ ብዙ አታስቢ እኔ የማገኛት የመጀመሪያው በእኔ ምክንያት እንደዚህ እንድትሆን ስላልፈለኩ ነው ሁለተኛው ደግሞ ዶክተር ስላወራኝና የሷ ጉዳይ ምን ያህል ወደ ሁሉም ጆሮ እንደደረሰ ነው። እንጅ በዚህ ስአት ለመቅደላዊት ምንም አይነት ስሜት የለኝም ግራ የተጋባ ስሜት ነው ያለኝ። ነገር ግን ደግሞ የሷ ሕይወት እንዲህ መሆን ቀጣም ያሳስበኛል ምክንያቱም መነሻው እኔ ስለሆንኩ። እና ደግሞ መቅደላዊት ጥሩ ልብ ያላት ልጅ ናት። በጣም የዋህ ቅን ናት። " " ህ ቅን? ጥሩ ልብ ያላት? በጣም የምትገርም ነህ ጭራሽ እንጀዚህ ትላለህ ቅንና ጥሩ ልብ ቢኖራት ነው አንተን የጎዳችህ? እ ወንድሜ? መልስልኝ እስኪ" አለች ኤሊያና እየበገነች " ውዷ እንደዚህማ አትበይ ምንም ቢሆን እኮ የወደድኳት የተሸነፍኩላት ልጅ ናት በዛ ላይ በምን አይነት መልኩ እንደተገናኘን ማወቅ የልጅቷን ስብዕና ለመረዳት አያዳግትም! ብቻ እህቴ መቅደላዊት ይህ አይገባትም ለዛነው ላገኛት ነፈለኩት እኔን ማግኘት ትልቅ ደስታን ከፈጠረላት ለእኔ ቀላል ነገር ነው ማድረጉ አይመስለሽም ምንሿ?" አለ ባሩክ ኤሊያናን እየጠቀሰ " አላውቅልህም ምን አገባኝ በኋላ ግን ከዳችኝኮ ምናምን ብለህ ብትነግረኝ ወዮልህ " " እህ አወራኋት ማለት ወደ ቀድሞው ጓደኘነታችን ተመለስን ማለት ነው እንዴ?" " አዎ በትንሹም ቢሆን ማውራታችሁ መንገድ ይጠርጋል ካዘንክላት ለሷ ደስታ መጨነቅህ በራሱ " " እሱማ ሊሆን አይችልም የተጨነቅሽለት ሰውን ሁሉ ወደሽው ነው ማለት ነው? ተሳስተሻል" " ባክህ አታጃጅለኝ አንተም ናፍቃህ ነው እንጅ ለሷ ብቻ አስበህ አይመስለኝም " " ለማንኛውም እንዳትተኝ እሷን ካወራኋት በኋላ አወራሻለሁ " አለና ስለኩን ዘጋው **** " ዛሬ ለምን ፈልገሽኝ ነው " አለችና መቅደላዊት ዮርዳኖስን ጉንጯን ስማ አጠገቧ ተቀመጠች። " አብረን እንድናመሽ ፈልጌ ነው በዛ ላይ ከተገናኘን ቆየንኮ " አለች ዮርዳኖስ እንዲህ እየተጨዋወቱ ሜላት ተቀላቀለቻቸው " ዛሬ እንዴት ነው ነገሩ ?" አለች መቅደላዊት " ምንም ነገር የለውም አብረን እየተጨዋወትን ማምሸት ይኖርብናል ብየ ስላሰብሁ ነው " አለች ዮርዳኖስ ነገሮች በጥሩ ሁኔታ እንዲሄዱላት ትንሽ አብረው ዋይፋይ ቦታ ተቀምጠው የተወሰኑ የአማርኛ ፊልሞችን ካወረዱ በኋላ ለመቅደላዊት ላፕቶፑን ሰጥተዋት አጠገባቸው ወደሚገኘው ሱፐር ማርኬት ጎራ አሉ። መቅዲም የተለያዩ አዝናኝ ሾወችን እያወረደች ሳለ በመሀል ተደወለ። መቅደላዊት ግራ ተጋባች ላንሳው አላንሳው በሚል አመነታች እነ ዮርዳኖስንም መጥራት ፈለገች ልታነሳውም ዳዳት ግን ደግሞ እንዳታነሳው የሷ እንዳልሆነ በማሰብ ተወችው። በእንደዚህ አይነት ሀሳብ ላይ ሆና የመጀመሪያው ደወል ጥሪ አለቀ። ሁለተኛ ተደወለ እጇን ወደ ማንሻ ኪቦርዱ ልትጠለው አነሳች................ Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 25♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_23 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ስሪንቃ ላይ ሲደርሱ እነናታኔምን ይዞ የሚያሽከረክረው ሾፌር ድንገት ወደ አስፓልቱ የገባችውን ፍየል አድናለሁ ብሎ በገደሉ ሊገባ ሲል አፋፉ ላይ ሲደረስ የእጅ ፍሬን በመሳብ ተጓዡንና ራሱን አተረፈ ። ውስጥ ያሉት ተጓዦች ሁሉም በየ እምነታቸው በመትረፋቸው ለፈጣሪ ምስጋና አቀረቡ። አንዷ ባልቴት " እናቴ ግሽን ወትሮስ ከአንች ስፍራ ታዕምር ሊጠፋ ነው?" በማለት ተንበርክካ አለቀሰች። አንደኛው ደግሞ ከውስጥ እየወጣ " ወላሂ በጣም ይገርማል የአላህ ስራ አላህ እኮ ትረፉ ሲል አይሳነውም። " በማለት በፈጣሪው ታዕምር ተገርሞ ተናገረ። አንደኛው ወጣት የአዲስ አበባ ፒያሳ ሰፈር ልጅ ይመስላል። " ሹፌው ግን የሌለ አንበሳ ነው! ፌሬን አያያይዙን ሾፈኸዋል። ፐ ፐ ፐ የአራዳው ጊዮርጊስን ይችላል ። " በማለት ሁሉም ተሳፋሪ የራሱን እይታ በገባውና በሀይማኖቱ አስታኮ ትንታኔ በመስጠት ላይ ተጠምደዋል። ከዚህ ሁሉ ተሳፋሪ ግን የተለየ አንድ ልጅ ነበር ምንም አላለም። የተፈጠረው ነገርም ብዙም ያሳሰበው ያስጨነቀው ያስፈራው አይመስልም። ናታኔም በደንዘዘ ስሜት ባለበት ቁጭ ብሎ አድማስ ማዶ ተሻግሮ ይመለከታል። አጠገቡ የነበረው ልጅ ተመልሶ መጣና " ወንድሜ ተነስ እንጅ ውጡ ተባሏል እኮ " በማለት የተባለውን በድጋሚ ደገመለት የገር ግን ልጁንም የሰማው አይመስልም። ደጋግሞ ቢነግረውም በጭራሽ ሊሰማ አልቻለም ። ልጁ ግራ ቢገባው አብሮት ተቀመጠ። ናታኔም ግን እስከ ወዲያው በትዝታ አሸልቧል። ከናሆም ጋ ከመቅደላዊት ጋር በኋላ ደግሞ ከባሩክ ጋር የነበረውን ወዳጅነት አንድ በአንድ እያስታወሰ እያወራ በሚያስቀው እየሳቀ በሚያናድደው እንደመናደድ እያለ ። ልጁ ናታኔምን እንደምንም ከመኪናው አስወጥቶት ውጪ ላይ ቁጭ አድርጎ " ወንድሜ ምን ሆነህ ነው?" አለው ናታኔምም ወደ ራሱ ተመልሶ ኖሮ " ኧረ ምንም አልሆንኩም ምን ሆንኩ ወዳጄ "ብሎ የራሱን ጥያቄ አስከተለ * ዮርዳኖስ የሰማችውን ዜና ለማን መናገር እንዳለባት ካሰላሰለችና በደንብ ከአሰበች በኋላ ለሜላት ደወለችላት ሜላት ናሆምን እያጎረሰች ስለ ነበር በመጀመሪያው ደወል ስልኳን ሳታነሳ ቀረች።ዮርዳኖስ ፈራ ተባ እያለች ደግማ ደወለች። ሜላት በቀኝ እጇ እያጎረሰች " ማነው የሚደውለው? አለችና በግራ እጇ ስልኩን ለማንሳት እጇን ስልኩ ወዳለበት የአልጋ ስፍራ ላከች። ስልኳን ስታየው ዮርዳኖስ ይላል ። " ማነው?" አለ ናሆም " ዮርዳኖስ ናት " አለች ሜላት ቅር እያላት " እህ እና አንሽላታ በጣም ፈልጋሽ ቢሆን ነው ደግማ የደወለችልሽ " አለ ናሆም ። ሜላት ማንሳት ባትፈልግም ናሆም ስላዘዛትና በሱ በኩል ተቃርኖ እንዳይገጥማት ስትል ብቻ ስልኩን አነሳችው። ዮርዳኖስም ስልኩ እንደተነሳ ስታውቅ " እ ሜሊ ሰላም ነሽ?" አለች " " ደህና " አለች ሜላት መልሷን እያሳጠረች በዛውም ወደ ደወለችበት ጉዳይ እንድትገባላት በመሻት። " እየውልሽ ሜሊ ከቻልሽ ወጣ ብለሽ አውሪኝ የስልኩን ላውድ ስፒከርም አጥፊው " አለች ናሆም ዮርዳኖስ ያለችውን እንድትፈፅም በአይኑ ምልክት ሰጣት ። ሜላትም በስ ብላ ከአልጋው ላይ ተነስታ ወደ በረንዳው አመራች። " እሽ ዮርዳኖስ ምንድን ተፈጥሮ ነው ደግሞ?" አለች ሜላት በቸልተኝነት ስሜት " አይ ምንም አልተፈጠረም የሆነ ነገር ላማክርሽ ነው!" አለች ዮርዳኖስ ከየት መጀመር እንዳለባት ጠፍቷት ። ሜላት የምፀት ሳቅ እንደመሳቅ ብላ " በምን ጉዳይ ነው የማማክርሽ ስለምንስ ነው የምንመካከረው?" አለች " እየውልሽ ሜሊ የባሩክ እህት ደውላልኝ ነበር እና እርሷ ምንድን ነው ያለችኝ ባሩክ መቅደላዊትን ማግኘት የምችልበትን መንገድ አመቻቹልኝ ብሏል አለችኝ ከዛ ደግሞ ዶክተር ወንድማገኝንም አወራሁት አዎ ከባሩክ ጋር አውርተናል እናም መቅደላዊትን እንዲያገኛት ተስማምተናል። ብሎኛል እና ለዛሬ ተቀጣጥረናል። በምን አይነት መልኩ እናገናኛቸው እኔ ዋይፋይ ጋ እናምሽና በዛው በድንገት እናገናኛቸው!ብየ አሰብኩ እና አንቺ ምን ታስቢያለሽ?" አለች ዮርዳኖስ " የእውነት " አለች ና ሜላት ደነገጠች ። " ወይኔ መቅዲ ይህን መቋቋም አትችልም ይከብዳታል ብላ ብቻዋን ማውራት ጀመረች በደስታ ትሞታለች።" አለችና ትዝ ሲላት ለካ ከዮርዳኖስ ጋር እያወራች ነው። " እኔ አላውቅም ዮርዲ ደስ ያለሽን አድርጊ ብቻ መቅዲ በጣም እንዳትደነግጥና እንዳትታመም!!! በይ የፈለግሽውን አድርጊ እኔ ይሄን ለፍቅሬ ልንገረው አለችና እየሮጠች ከበረንዳ ወደ አልጋው ገብታ ተስፈንጥራ አጠገቡ ተቀመጠችና ጉንጩን እያገላበጠች አይኑን ግንባሩን አንገቱን ትሰመዋለች። " ኧረ የዛሬው ወረራ ደግሞ ምን በማስመልከት ነው? አለ ናሆም " ዝም ብለህ አትሳምም እንዴ የምን መቃወም ነው " አለች እየሳቀች " አይ ግን የኔ ማር ምን ተፈጥሮ ነው እንዲህ ደስታ በደስታ የሆንሽው?" አለ ናሆም ሁኔታዋ በጣም እያስገረመው! " አንተም ደስታ በደስታ ነው የምትሆነው ....." " እና ንገሪኛ እኔም ልደሰት " አለ ናሆም እየጓጓ " ትንሽ ቆይ እስኪ " አለች ሜላት " እ እ ጎኔን አመመኝ " አለ ናሆም ። ሜላት በረጅሙ ሳቀችና " እኔን ይመመኝ አይዞህ ያመመህ ወሬው ስለዘገየብህ ነው አይደል አታስብ ስነግርህ ቆመህ ትሄዳለህ " አለች " እህ ጨነቀኝኮ ንገሪኝ ልቤ እኮ እየመታ ነው።" አለ ናሆም " ባሩክ ኮ መቅደላዊትን ሊያገኛት ነው?" " ምን መጣ?" " አይ ኧረ አልመጣም የኔ ፍቅር በስካይፒ ነው። " ናሆም ሳቅ በሳቅ ሆነ ከልቡ ተደሰተ " እንዴት ሊሆን ይችላል ?" አለ ናሆም ከሳቁ ገታ እያለ "ዮርዲ የመቅደላዊትን ጉዳይ ለዶክተር ወንድማገኝ አስረድታው ኖራ ቆይቷል። እሱ ነው አውርቶት ለዚህ የበቃው" አለች የሰማችውን በከፊልም ቢሆን እየተናገረች። " መቅዲ እንደ አዲስ ነው የምትወለደው በእርግጠኝነት! በለው እና መች ልትነግሯት ነው?" አለ ናሆም " አይ አንነግራትም ዮርዳኖስ ያመጣችው ሀሳብ ደስ ብሎኛል ነገ ሶስታችን ዋይ ቦታ እናመሻለን ከዛ ልክ ባሩክ በተቀጣጠሩበት ስአት ስካይፒ ከፍቶ በድንገት ማውራት ' የሚል ሀሳብ ነው ያመጣችው ተመችቶኛል በዚህ መልኩ ነው መሆን ያለበት" አለች ሜላት " ጥሩ ሀሳብ ነው ግን ፌንት እንዳታደርግ እሷን ከመሀል አድርጋችሁ የአንዳችሁን ግራ እጅና የአንዳችሁን ቀኝ እጅ በጀርባዋ መያያዝ አለባችሁ ምከረ ሀሳቤ ነው " አለ ናሆም " ችግር የለውም ሀሳብማ እንቀበላለን! " በማለት ራሷን በአወንታ ነቀነቀች። Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 24♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።

#መቅደላዊት #ምህራፍ_ሁለት #ክፍል_22 #በአምባዬ_ጌታነህ ልብ አንጠልጣይ የፍቅር ታሪክ ድንገት ከመሬት ተነሰቶ መቅደላዊትን ማግኘት የምችልበትን ሁኔታ በአንቺ በኩል እፈልጋለሁ አለኝ" አለች። " ምን?????" ዮርዲ አፏን ከፍታ ቀረች።ትንሽ ቆይታ በቀኝ እጇ አፏን ከደነችው። "ቆ.. ቆ.. ቆ ..ይ ..ቆይ እንዴት ላገኛት አለ? " ዮርዳኖስ እየተንተባተበች ጠየቀቻት። ኤሊያናም " አላውቅም በደንብ አልነገረኝም ነገር ግን ከእናንተ ዩኒቨርስቲ የሆነ መምህር ዶክተር የደወለለት ይመስለኛል። በየ ወሬው መሀል ስሙን እየጠራ ነበር። ብቻ ሌላ ነገር አይደለም ያለው ላገኛት ነው ያለው ብዙ ተስፋ አታድርጊ የኔ ወንድም አንዴ ከወሰነ ወሰነ ነው። " አለች ኤሊያና " ችግር የለውም ተስፋ አላደርግም ብቻ እንኳን ሊያወራት ፈቃደኛ ሆነ እንጅ ሌላው ከዛ በኋላ ይታያል። እውነት ኤሊ ስለደወልሽ ደስ ብሎኛል ይበልጥ እንደዚህ አይነት ዜና ስላበሰርሽኝ አመሰግናለሁ አሁን ለሱ ይሄን ስልክ ስጭው 0921........ በዚህ ስልክ ይደውልልን ነገ ማታ ዋይፋይ ቦታ እናመሻለን "ብላ ዮርዳኖስ እየፈነደቀች የመቅደላዊትን ስልክ ሰጥታት ቸው ተባብለው ወሬያቸውን ጨረሱ። ዮርዳኖስ ስልኩን ከዘጋች በኋላ ከእንደገና ሁለት እጇን አፏ ላይ ጭና በሰማችው ዜና ተገረመች። " ወይኔ መቅዲ ጓደኛየ ምስኪን በስተመጨረሻ ያዘንሽውን ያህል ልትደሰች ነው? ይገባሻል የኔ ቆንጆ። ብዙወች ጥፋታቸውን በሌላ ሰው ላይ አላከው ራሳቸውን እንደ ፃደድቅ ቆጥረው በሚኖሩ ሰወች መሀል ሆነሽ ስለ ጥፋትሽ ራስሽን መቅጣትሽ ራስሽን ማስጨነቅሽ ተጠያቂ ማድረግሽ ለዚህ ውጤት ዳረገሽ አንቺ የፅናት ምሳሌ የፍቅር ምልክት። " እያለች ስለመቅደላዊት አኳኋን እና እስከ አሁን የነበራትን ስሜት እርሷ በተረዳችበት ሀሳብ ስታወጣ ስታወርድ ቆይታ ይህን ጮማ ወሬ ለማን በቅድሚያ መንገር እንዳለባት ግራ ገብቷት ስልኳን አፏ ላይ አስደግፋ ቁጭ አለች። "ለናሆም ላሳውቀውና የሚዘጋጅበትን ነገር ይዘጋጅ " አለች በዚህ መሀል ዶክተር ወንድማገኝ ደወለላት ቶሎ አነሳችውና " አቤት ዶክተር " አለች ዮርዳኖስ እየተሽቆጠቆጠች እየፈራች እያፈረች " እንዴት ነሽ?" " ደህና " " ትምህርት እንዴት ነው? እያነበብሽ ነው?" " አዎ ዶክተር እያጠናሁኝ ነው" " መልካም በደንብ አጥኚ እንዳትዘናጊ አሁን የደወልኩልሽ ባሩክን እንዳወራሁት ና መስማማት ላይ ኤንደደረስን ልነግርሽ ነው እና በቅርቡ መቅደላዊትን አገናኙትአገናኙት፣ አስማሟቸው አግባቧቸው! ባሩክ ትንሽ ወጣ ያለ አመለካከትና እሳቤ ያለው ልጅ ነው! እና እንደዛ አድርጉ " አለ ዮርዳኖስ ዶክተር ወንድማገኝ ያላትን ሙሉ ሀሳብ ተቀብላ በሁኔታዎች መስመር እንደ ፈንዲሻ ቆሎ እየፈነደቀች ልብሷን እስተካከለች። * ናሆም ተሽሎት ወደ ዶርሙ ተመልሷል። ሁሉም ነገር እየተስተካከለ ያለ ይመስላል። ወደ ወንዶች ማደሪያ ህንፃ ለበሽተኛ ሴቶች መግባት ስለሚችሉ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ሜላት ፍቅረኛዋን ናሆምን እየተንከባከበችው ነው! እግረ መንገዷንም እንደነገሩ ያለውንና ብዙም በፅዳት በኩል ደካማ የሆነውን የነ ናሆምን ዶርም እያፀዳችላቸው ነው። ዶርሙ ዶርም መስሏል። የናሆም የዶርም ጓደኞችም ሜላት በዘገየች ቁጥር ከብሎክ ወጥተው ወደ ሴቶች ዶርም ማንቃረራቸውን ይዘዋል ። ለነገሩ " በልጅ አመካኝቶ ይበሏል አንጉቶ " እንዲሉ ለናሆም የሚበላ ስታመጣ እነሱንም ስለማትረሳቸው እሱንም ጭምር ይሻሉ። የምታመጣላቸውን ምግብም እየተሻሙ ይመገባሉ። የፍቅርን ጥግ የስጦታ ዳር ከውቅያኖስ ጥልቀት ሲርቅ በሜላት አይን እና እጆች አንደበት ይታያል። ** ናታኔምና መርዕድ በመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ከእስር ቤት ተለቀቁ። ናታኔም ወዲያው ወደ ቤተሰቦቹ ሄደ። መርዕድም የሚሰራውን ማስተርስ ሪሰርች ለመስራት ሪሰርች ወደ ሚሰራበት ቦታ ላልተወሰነ ጊዜ ለመጥፋት ወስኖ ለመሄድ እያኮበከበ ይገኛል። አሁን ሁሉም ነገር ሰላም ለመሆን የተስተካከለ ይመስላል ነገር ግን አሁንም መርዕድ ላይ የጥላቻና የእልህ የፍቅር ስሜት ይነበባል" ሁሉም ነገር ይስተካከላል አንድ ቀን ሁሉንም ህልሞቼን ይፈታቸዋል ያነጋቸዋል እንደ ጨለሙ አይቀሩም ።ምን አልባት አሁን እድለቢስ ልሆን እችላለሁ ነገር ግን ሁሉም ይስተካከላል " በማለት ለራሱ እተየናገረ ከዶርሙ ቁምሳጥን ላይ ከለጠፈው መስታወት ራሱን ይመለከታል። ፂሙን ይነካካል፣ ፀጉሩን ያበጥራል፣ ጥርሱን ብልጭ ድርግም እያደረገ የጥርሱን ቆሻሻወች ለማፅዳት ጠረንጴዛ ላይ ያስቀመጥውን ውሃ እያነሳ ይጉመጨመጫል። ** ናታኔም መቼ እንደሚመለስ አያውቅም ግን ደግሞ ብዙም ቤት እንደማይቆይ ያውቀዋል። ክፋት በቀል ያረገዘው ልብ በብዙ ጥያቄወች እየተብከነከነ ለተወሰነ ወራት ርቋቸው የነበሩትን ቤተሰቦቹን ለማግኘት ረዝሙን የትግራይ መንገድ ተያያዘው ከአድዋ-መቀሌ ከመቀሌ እስከ ማይጨው ጠመዝማዛውን የግራካሶ አቀበት አልፎ ራያ ምድር ውቧ አለማጣ ከአለማጣ ራያ ቆቦ ከቆቦ ወልደያ የራያን ድንቅ ምድርና የተባረከ ሰብል በአውቶብሱ መስኮት በኩል አይኑን እንደ አንቴና አስግጎ ይገረምማል። የከብቶቹ ቀንድና የህዝቡ የአለባበስ ባህል ቀልብን ገዝቶ አይንን ይስባል። የሚያገለድሙት ግልድም የሚታጠቁት ዝናር ከያዙት ሽመልና ጉተናቸው ላይ የተሰካው ሚዶ ( ማበጠሪያ )ራያነታቸውን ያሳብቃል። ፊታቸው ላይፈገግታና ሩህሩህነትም ይታያል።ሁሉም ነገር ያስደስታል ጉዞው ሲቀጥል ዳገታማ መልክዓ ምድር ተንተርሶ የተዋበችው ወሎ መጀን " ከርቀት ለሚመለከታት በአደስና በወገርት ጭሷ ጉልላት ሰርታ በከፍታ ያለች ትመስላለች። የመኪናው ዘዋሪ የየአካባቢውን ባህልና አኗኗር ይገልጻል ብሎ ያሰበውን ዘፈን ከመልቀቅ አልተቆጠበም። " የወሎ ልጅና ቀጭን መቀነት፣ ሰርስሮ ሰርስሮ ይገባል ከአንጀት። " የምትለው የዘፈን ስንኝ የመጣችለት መርሳን በማለፍ ላይ እያሉ ወገብ ይኑራት አይኑራት የማታስታውቅ ሳዱላ በተመለከተ ጊዜ ነበር። አንድ ጊዜ ብቻ በሄደባት ወሎ በተመስጦ እየታዘበ በምናቡ ማስታወሻ የሚያሰቀምጠው ናታኔም ስሪንቃ ላይ ሲደርሱ........... Join and Share ይቀጥላል.... አቅራቢ @Tesh5050 ✎🌺ክፍል 23♥️ ይቀጥላል. ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ ሼር ማድረግ አይርሱ።