en
Feedback
Al-inaya Ye Hadra Jemea (Butajira) አል-ዒናያ የሀድራ ጀመዓ ቡታጂራ

Al-inaya Ye Hadra Jemea (Butajira) አል-ዒናያ የሀድራ ጀመዓ ቡታጂራ

Open in Telegram

እንኳን ደህና መጡ አል-ዒናያ የሀድራ ጀመዓ ቡታጂራ ለእናንተ ያዘጋጀናቸው ነገሮች -አስተማሪ የሆኑ ታሪኮች -ቂሷዎች እና ሀዲሶች -የሀድራ ቅጂዎች አስተያየት ካለቹ @Katbaren https://t.me/joinchat/U4q9OHoSPqgy3teR

Show more
567
Subscribers
+224 hours
+117 days
+1230 days
Posts Archive
አሁኑኑ ይዘዙን♥ አድራሻ ቡታጂራ
አሁኑኑ ይዘዙን♥ አድራሻ ቡታጂራ

Repost from INAYA ዒናያ
በአላህ ፈቃድ ረመዷን ሰኞ መጋቢት 2/2016 ወይም March 11/2024 ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል:: ጨረቃ እሁድ ማታ ማለትም 10/03/2024 ወይም 01/07/2016 ከመግሪብ በሗላ ለ13 ደቂቃ የ
በአላህ ፈቃድ ረመዷን ሰኞ መጋቢት 2/2016 ወይም March 11/2024 ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል:: ጨረቃ እሁድ ማታ ማለትም 10/03/2024 ወይም 01/07/2016 ከመግሪብ በሗላ ለ13 ደቂቃ የመቆየት እድል ስላላት በደንብ ልትታይ ትችላለች:: ኢንሻአላህ:: የእስልምና የቀን አቆጣጠር በጨረቃ, የሶላት አቆጣጠር በፀሐይ ሲሆን የገንዘብ አቆጣጠር ደግሞ በንብረት ነው:: ከእነዚህ ከወጣ ለከፍተኛ ውዝግብ እና መጭበርበር ይጋለጣል:: ተፈጥሮ አይዋሽም:: (ዐብዱልቃዲር ኑረዲን)

Repost from INAYA ዒናያ
ረመዳን 4 ቀናቶች ብቻ ቀሩት 💚 ዝግጁ ....

٠♥ የሻዕባን ወር በዐረብኛ ወራት አቆጣጠር ስምንተኛ ወር ሲሆን ከረጀብ በኋላ ከረመዳን በፊት የሚመጣ ወር ነዉ፡፡ እነሆ ዛሬ ይህ ታላቅ ወር አንድ ብሎ ጀምሯል፡፡ =====================
٠♥ የሻዕባን ወር በዐረብኛ ወራት አቆጣጠር ስምንተኛ ወር ሲሆን ከረጀብ በኋላ ከረመዳን በፊት የሚመጣ ወር ነዉ፡፡ እነሆ ዛሬ ይህ ታላቅ ወር አንድ ብሎ ጀምሯል፡፡ ====================== 1. በሻዕባን ወር ዉስጥ ጾምን ማብዛት እጅግ የተወደደ ነዉ፡፡ ሰዪዱና አቢ ሰለማሕ /ረ.ዓ/እሜቴ ዓኢሻን ,/ረ.ዓ / ስለ ሰይዳችን ﷺ ጾም ሲጠይቋቸዉ " በሻዕባን ወር እንደሚጾሙት በሌላ ወር ሲጾሙ በጭራሽ አልተመለከትኳቸዉም ፤ ሻዕባንን ሙሉ ወሩን ይጾሙ ነበር , ከሻዕባን ወር ጥቂትን እንጂ አያፈጥሩም ነበር " ~ሙስሊም 2029~ 2. የሻዕባን ወር ከተጋመሰ በኋላ የመጾም ተለምዶ የሌለዉ እና የፈርድ ጾም ቀዳእ የሌለበት ሰዉ መጾም የተከለከለ ነዉ " ሰዪዱና አባ ሑረይራሕ /ረ.ዓ/ ባስተላለፉት ሀዲሥ ሰዪዳችን ﷺ እንዲህ ብለዋል " ሻዕባን ከተጋመሰ አትጹሙ " ሱነን ~አቢ ዳዉድ 2337~ 3. ሰዎች በሚዘናጉባቸዉ ወቅቶች ላይ ዒባዳ ማብዛት የተወደደ ነዉ፡፡ ሰዪዱና ኡሳመሕ ኢብኑ ዘይድ/ረ.ዓ/ ሰዪዳችንን ﷺ እንዲህ ይሏቸዋል " በሻዕባን ወር የሚጾሙትን ያህል በሌሎች ወራቶች ሲጾሙ አልመለከቶትም ?" "ይህ ወር እኮ ሰዎች በረጀብ እና በረመዳን መሀል ሆነዉ የሚዘናጉበት ነዉ , ስራችን ወደ አለማቱ ጌታ ከፍ የሚልበት ነዉ , እኔ ደግሞ ስራዬ ጾመኛ ሆኜ ከፍ እንዲልልኝ እፈልጋለሁ "~ ነሳኢይ 2329~ * * * አላሑመ ባሪክ ለና ፊ ሻዕባን ወበሊግና ረመዳን

ስለ ቃጥባሬ መውሊድ ማስተካከያ የካቲት 9/10 የነበረው የቃጥባሬ መውሊድ ለሸዋል 15/16 ሚያዚያ 19/20 ተዘዋውሮዋል 🥺
ስለ ቃጥባሬ መውሊድ ማስተካከያ የካቲት 9/10 የነበረው የቃጥባሬ መውሊድ ለሸዋል 15/16 ሚያዚያ 19/20 ተዘዋውሮዋል 🥺

♥ አዲስ አበባ ላይ ለሚሰገዱ ጁምዓዎች ሁሉ መሰረት የጠላች የመጀመሪያ በግልጽ የተሰገደች ጁምዓ ========================= • ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ በይፋ እና በግልጽ ጁምዓ ሰ
♥ አዲስ አበባ ላይ ለሚሰገዱ ጁምዓዎች ሁሉ መሰረት የጠላች የመጀመሪያ በግልጽ የተሰገደች ጁምዓ ========================= • ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ በይፋ እና በግልጽ ጁምዓ ሰላትን ያስጀመሩት ታላቁ ዓሊም ፣ የቃጥባሬ አድባር መስራች ፣ የሀበሻዉ ቁጥብ ፣ የአዉሊዮች አይነታ ፣ ጀግናዉ ፣ አይበገሬዉ ሸይኽ ዒሳ ሐምዛ በጡሬ /የቃጥባሬ ሸይኽ/ ናቸዉ ፡፡ • ነገሩ እንዲህ ነዉ አዲስ አበባ ከተቆረቆረች ጊዜ አንስቶ እስከ ተፈሪ መኮንን ሹመት ጊዜ ድረስ ሙስሊሞች ጁምዓ ሰላትን ተሰብስበዉ በይፋ ሰግደዉ አያዉቁም ፡፡ በወቅቱ ሙስሊሞች ተሰብስበዉ አላሕን ማምለክ ፣ ሰላት መስገድ ፣ መቅራት ወዘተ..... መብታቸዉ አልነበረም ፡፡ • በወቅቱ ጁምዓ ይሰገድ የነበረዉ በጊዜዉ 'አራዳ' ተብሎ ይጠራ በነበረዉ አካባቢ አንድ የመናዊ ነጋዴ ቤት ዉስጥ ነበር ፡፡ እንዲህ ያለዉ ጭቆና እና ግፍ ለሸይኽ ዒሳ ህሊና ከባድ ነበርና አንድ መላ መቱ ፡፡ እቅዳቸዉን በወቅቱ ለነበሩ ዐረቦች አሳዉቀዉ የመስጂድ መስሪያ ቦታን እርሳቸዉ ሊያመቻቹ ወጪዉን ዐረቦቹ ሊሸፍኑ ሀሳብ አቀረቡ ፡፡ • ዐረቦቹ ግን ይችንም ተደብቆ መስገዱን እንዳናጣ የሚል ስጋታቸዉን ቢያቀርቡም ጀግናዉ እና ቆራጡ የዘመናቸዉ ዑመር የነበሩት የቃጥባሬ ሸይኽ ያቀዱትን በልበ ሙሉነት አሳኩት የመስጂድ መስሪያ ቦታዉን ተረክበዉ ዐረቦቹን እና ህዝበ ሙስሊሙን አስተባብረዉ የዛሬዉ ኑር መስጂድ ላይ የመጀመሪያዉን ጁምዓ ሰላት በይፋ እንዲሰገድ አደረጉ ፡፡ * * * ሺሊላ ያቃጥባሪዩ ሺሊላ ያ ቃጥባሪዩ ኑራንዩ ቁጥቡ-ርረባኒዩ ~~~~`~~~`~~~

♥ አዲስ አበባ ላይ ለሚሰገዱ ጁምዓዎች ሁሉ መሰረት የጠላች የመጀመሪያ በግልጽ የተሰገደች ጁምዓ ========================= • ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ በይፋ እና በግልጽ ጁምዓ ሰላትን ያስጀመሩት ታላቁ ዓሊም ፣ የቃጥባሬ አድባር መስራች ፣ የሀበሻዉ ቁጥብ ፣ የአዉሊዮች አይነታ ፣ ጀግናዉ ፣ አይበገሬዉ ሸይኽ ዒሳ ሐምዛ በጡሬ /የቃጥባሬ ሸይኽ/ ናቸዉ ፡፡ • ነገሩ እንዲህ ነዉ አዲስ አበባ ከተቆረቆረች ጊዜ አንስቶ እስከ ተፈሪ መኮንን ሹመት ጊዜ ድረስ ሙስሊሞች ጁምዓ ሰላትን ተሰብስበዉ በይፋ ሰግደዉ አያዉቁም ፡፡ በወቅቱ ሙስሊሞች ተሰብስበዉ አላሕን ማምለክ ፣ ሰላት መስገድ ፣ መቅራት ወዘተ..... መብታቸዉ አልነበረም ፡፡ • በወቅቱ ጁምዓ ይሰገድ የነበረዉ በጊዜዉ 'አራዳ' ተብሎ ይጠራ በነበረዉ አካባቢ አንድ የመናዊ ነጋዴ ቤት ዉስጥ ነበር ፡፡ እንዲህ ያለዉ ጭቆና እና ግፍ ለሸይኽ ዒሳ ህሊና ከባድ ነበርና አንድ መላ መቱ ፡፡ እቅዳቸዉን በወቅቱ ለነበሩ ዐረቦች አሳዉቀዉ የመስጂድ መስሪያ ቦታን እርሳቸዉ ሊያመቻቹ ወጪዉን ዐረቦቹ ሊሸፍኑ ሀሳብ አቀረቡ ፡፡ • ዐረቦቹ ግን ይችንም ተደብቆ መስገዱን እንዳናጣ የሚል ስጋታቸዉን ቢያቀርቡም ጀግናዉ እና ቆራጡ የዘመናቸዉ ዑመር የነበሩት የቃጥባሬ ሸይኽ ያቀዱትን በልበ ሙሉነት አሳኩት የመስጂድ መስሪያ ቦታዉን ተረክበዉ ዐረቦቹን እና ህዝበ ሙስሊሙን አስተባብረዉ የዛሬዉ ኑር መስጂድ ላይ የመጀመሪያዉን ጁምዓ ሰላት በይፋ እንዲሰገድ አደረጉ ፡፡ * * * ሺሊላ ያቃጥባሪዩ ሺሊላ ያ ቃጥባሪዩ ኑራንዩ ቁጥቡ-ርረባኒዩ ~~ የቃጥባሬዉ ጌታ አንዱ ኻስያቸዉ ኑራንይ ይሆናል የገባ ሀድራቸዉ የግንባር ሸቃዋ ያብሳል አይናቸዉ ችጋርም አይነካዉ የገባ ከሳቸዉ ያስታዉቃሉ እርሳቸዉን ያዩ #ቃጥባሬ_መዉሊድ_ቸነም

ከሞት ሲያመልጡ ሞት የቀደማቸው❗️ በዓለማችን አስደናቂ ታሪኮች መካከል ከሞት ሲያመልጡ ሞት የቀደማቸው ሰዎች አንዱ ነው። በተለያዩ ጊዜ ከሞት አደጋ ተርፈው ወዲያው በሞት የተቀደሙ ሰዎች አሉ። ታሪኮቹ እውነተኛ ሲሆኑ 5ቱን መርጬ እነሆ ብያለሁ፦ 1. ከአውሮፕላን አደጋ ተርፋ በእርዳታ አምቡላንስ የተገጨችው #ሱዓን የ16 ዓመቷ ሱዓን ሰንፍራንሲስኮ ኤርፖርት አቅራቢያ ከወደቀችው ኤዥያና 214 አውሮፕላን የተረፈች ብቸኛ ሴት ነበረች። እናም አደጋውን ተከትሎ በርካታ አንቡላንሶች ለእርዳታ ወደቦታው ጎረፉ። ነገርግን ከመሀል አንደኛው ለሱዓን መጨረሻ የተላከ ነበር። ከአደጋው ተርፋ ተደናግጣ በቆመችበት ሄደባት። ታሪኩም ከአደጋው የተረፈ የለም በሚለው ተፃፈ። 2. በቀብር ስነስርዓቷ ላይ የሞተችው #ሙክሃሜትዝያኖቭ የ49 ዓመቷ ፋጂልዩ ሙክሃሜትዝያኖቭ ሞታ የቀብር ስነስርዓት እየተደረገላት ነበር። በመሀል ፀሎት ሲደረግ ከሳጥኑ ውስጥ ሆና ድምፅ አሰማች። ሰዎችም ተደናገጡና ሲከፍቱት በህይወት አለች። ከዚያም ተነስታ ሁኔታውን ስታይ ሞታለች ተብሎ የቀብር ስነስርዓት እየተፈፀመላት ነበር። ይህ ያልታሰበ ክስተትም የልብ ድካሟን ቀሰቀሰው። በዚህም ምክንያት ዳግመኛ ላትነቃ አሸለበች። 3. ከመኪና አደጋ ሲያመልጥ ባስ የገጨው ካሊፎርኒያዊ ካሊፎርኒያዊው አሽከርካሪ የራሱን መኪና ይዞ እየተጓዘ ነበር። በመሀል መኪናዋ ከቁጥጥሩ ውጭ ሆነችበትና ወደ ገደል ገባች። በዚህ ጊዜ ባልተጠበቀ ፍጥነት በሩን ከፍቶ አስፖልቱ ላይ ወደቀ። ይሁን እንጅ ከኋላ እየመጣ የነበረው ባስ ሊምረው አልቻለምና ከወደቀበት ተነስቶ ብዙም ሳይረጋጋ የመጨረሻውን ሞት ሞተ። 4. የዜና እረፍቱን ሲሰማ የሞተው #ጋርቬይ_ማርከስ ጋርቬይ የጥቁር ብሔርተኛ ታጋይ ነበር። እናም አንድ ቀን በውሸት ሞቷል የሚል ዜና ወጥቶ ከመፅሄት ላይ አነበበ። በዚህም እጅግ ከመናደዱ የተነሳ ከዚህ በፊት ሲታከም የነበረው ስትሮክ አገርሽቶበት ህይወቱ አለፈች። 5. ከንብ መንጋ ሲያመልጥ መኪና የገጨው ወታደር የ21 ዓመቱ #ማክ_ጁህ ከካምፑ መጥቶ ትንሽ አልኮል ከቀማመሰ በኋላ ሲመለስ የንብ መንጋ ያጋጥመዋል። መንጋውን በሚችለው ፍጥነት ካመለጠ በኋላ በመሀል ለፖሊስ ደውሎ ሁኔታውን ያሳውቃል። ከዚያም የተሻለ ቦታ ለመደበቅ አስፓልቱል በሩጫ ሲሻገር በፍጥነት ይጓዝ የነበረ መኪና ገጭቶት በሚሸሸው ሞት ተቀደመ። አላህ እንዲህ አለ፦ قُلْ إِنَّ الْمَوْتَ الَّذِي تَفِرُّونَ مِنْهُ فَإِنَّهُ مُلَاقِيكُمْ ۖ ثُمَّ تُرَدُّونَ إِلَىٰ عَالِمِ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ فَيُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ «ያ ከእርሱ የምትሸሹት ሞት እርሱ በእርግጥ አግኛችሁ ነው፡፡ ከዚያም ሩቁንና ቅርቡን ዐዋቂ ወደ ኾነው ጌታ ትመለሳላችሁ፡፡ ትሠሩትም የነበራችሁትን ሁሉ ይነግራችኋል» በላቸው፡፡ ውዶቼ ለአኬራ መልካም ስራን እናስቀድም አደራ !!!!

Repost from INAYA ዒናያ
አንኳን አደረሳቹ አደረሰን 3 ቀን ብቻ 😘
አንኳን አደረሳቹ አደረሰን 3 ቀን ብቻ 😘

ሙሽራው አዲስቱን ሚስት ይዞ ጫጉላ ክፍል ገባ። ፊቷ ላይ የሸፈነችውን መቅረምያ ከፈት ሲያደርገው ፈፅሞ ያልጠበቃት ጥቁር ሴት ሁና ተመለከታት። ተበሳጭቶ ትቷት ተኛ። ብስጭቱ ለቀናት ኩርፍያን ወልዶ ለተከታታይ ቀናት ብቻውን አደረ። ሙሽሪት በጥቁረቷ መ'ጠላቷን በተገነዘበች ግዜ፦‹‹ማሊክ! ምናልባት መልካም ነገር ከመጥፎ ስር ተሸሽጎ ይሆናል›› ብላ በቅኔ ወደ አልጋ ጠራችው። ያችን ሌት አብረው አደሩ። ግና ጥቁረቷ ምቾት የነሳው ባል ዳግም ወደ ኩርፍያው ገባ። በዚህኛው ዙር ግን ኩርፍያው 20 አመታትን የፈጀ ነበር። ባል ከእንዲት ቀን የጫጉላ አዳር በኋላ ከተማይቱን ትቶ ጠፋ። ከ20 አመታት ቆይታ በኋላ ባል ወደ ከተማይቱ ዳግም ተመለሰ። መዲና ሲገባ ወደ ቀዬው ከመሄዱ በፊት መስጅድ ለሰላት ገባ፤ ከመስጅዱ ውስጥ ሰዎች አንድን ሰው ከበውት በተመስጦ እና በፅሞና ሲያዳምጡት ተመልክቶ ጠጋ ብሎ ተቀመጠ። ንግግሩ ማራኪ ነው፣ አገላለፁ እፁብ ነው፦‹‹ይሁ ምጡቅ ማን ይሁን?›› ብሎ ሀገሬውን ጠየቀ። ‹‹አባቱ ማሊክ ይባላል። ይህ ልጅ ሳይወለድ በፊት የዛሬ 20 አመት ነበር ከዚህ ከተማ የጠፋው›› ብለው የገዛ ታሪኩን ባዳ አድርገው አወጉት። ግራ መጋባት ወረረው፣ የጥፋተኝነት ስሜት አሳፈረው። ወደ ልጁ ተጠግቶም፦‹‹እቤታችሁ ውሰደኝ›› ብሎ ተማፀነ። ልጅም እንግዳውን ይዞ ወደ ቤቱ አመራ። ግና እንግዳው ደጅ ላይ ቁሞ፦‹‹ምናልባት መልካም ነገር ከመጥፎ ስር ተሸሽጎ ይሆናል ብለህ ለእናትህ ንገርልኝ›› ብሎ ላከው። ልጅም ገብቶ መልዕክቱን አደረሰ። እናት በትዝታ ወደ ኋላ 20 አመታትን አወሳች፤ ቂም ስሜቷን ውጣ፦‹‹ልጄ ውጣ አባትህን ተቀብለህ አስገባው፤ ለ20 አመታት በመጥፋቱም ፈፅሞ እንዳትወቅሰው›› ብላ ትዳሯ ላይ ዳግም ህይወት ዘራች። ይህች ጥቁር እናት ለበርካታ ዘመናት ትውልዶች የሚሸጋገር የሀዲስ ጥርቅሞችን የሰነደ ልጅም በመልካም አስተዳደግ አሳድጋ ለኡመቱ አበረከተች።

የረጀብ ወር እና ልቅናው ==== ⨳ ===== ⨳ ==== *        *•══༻◉••﷽••◉༺══•* 🌺 إِنَّ عِدَّةَ الشُّهُورِ عِندَ اللَّهِ اثْنَا عَشَرَ شَهْرًا فِي كِتَابِ اللَّهِ يَوْمَ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ مِنْهَا أَرْبَعَةٌ حُرُمٌ ۚ ذَٰلِكَ الدِّينُ الْقَيِّمُ ۚ فَلَا تَظْلِمُوا فِيهِنَّ أَنفُسَكُمْ ۚ 🌺 🌺የወሮች ቁጥር አላህ ዘንድ በአላህ መጽሐፍ ውስጥ ሰማያትንና ምድርን በፈጠረበት ቀን ዐሥራ ሁለት ወር ነው፡፡ ከእነሱ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ ይህ ቀጥተኛው ሃይማኖት ነው፡፡ በእነርሱ ውስጥም ነፍሶቻችሁን አትበድሉ፡፡🌺      🔮 ሱረቱል ተውባ 9፥ 36 * በሒጅራ ካላንደር ሰባተኛ ወር መግባቱን ያበስራል ወርሃ ረጀብ... እንዲሁም በኢስላም ከተመረጡት አራት ወራቶች አንዱ ሲሆን የተቀሩትም ዙል ቃኢዳ ፣ ዙል ሂጃ እና ሙሀረም ናቸው... እነዚህ ወራት ከእስልምናም በፊት በነበሩ የመካከለኛው ምስራቅ አረቦች ይከበሩ እንደነበር መዛግብቶች በሰፊው ይተርካሉ... * 💚💕 ኢማም አልጋዛሊ ሙካሸፍ አል ቁሉብ አል አክበር የተሰኘው ኪታባቸው ላይ ... ረጀብ ... "አት_ተርጂብ" ከሚለው ቃል የመጣ ሲሆን 'ተከበረ' ወይንም 'ተላቀ' ማለት ነው  ... ረጀብ  በሌላ ስሙ "አል-አሰብ" በመባል  ተጠርቷል... ይህንንም ያሰኘው የአላህ እዝነት ፣ ፀጋና ይቅርታ ከወንጀላቸው ለተፀፀቱ  እና በኢባዳ ለሚዘወትሩ ባሮቹ የሚፈስበት እና የሚንቧቧበት ወር በመሆኑ ነው ... ከዚህ በተጨማሪም  "አል-አሲም"  ወይንም ደንቆሮው ተብሎ ተገልጿል የዚህም ምክንያቱ ወሩ በቀደምት አረቦችም የተከበረ እና ውጊያ(ግጭት) የማይፈቀድበት በመሆኑ ነው ብለው ከትበዋል ... * 💚💕 ኢማም አልጋዛሊ በዚሁ ኪታብ ላይ  ረጀብ የሚለው ቃል ከሶስት ፊደላት  የተዋቀረ ሲሆን ... ራ - ራህማ (እዝነት) ፣ ጂም - ጂናያህ /ጁርም (ወንጀል / ሀጢያት) ፣ ባዕ - ቢር (ቸርነት) የሚለውን የሚወክሉ ሲሆኑ ...💚💕 አላህ ሱብሀነሁ ወተአላ 'ወንጀላችሁን በእዝነቴና በቸርነቴ መሀከል  ነው የማስቀምጠው' ማለቱ ነው የሚል  ማብራሪያም አስፍረዋል ... * 💚💕 ኢማም ሙሳ ካዚም እንደተናገሩት ... "ረጀብ ጀነት ውስጥ ያለ ከወተት የነፃ ከማር የጣፈጠ ወንዝ ስም ነው... በዚህ ወር ነብሳቸው ከወንጀል የፆመች በበጎ ስራ የተጠመደች ሰዎች የተመነዳች ናት..." ይላሉ  . * 💚💕 አሽረፈል ኸልቅም ﷺ " ረጀብ የአላህ ወር ነው... ሸእባን የኔ ወር ነው... ረመዳን የዑመቶቼ ወር ናት..." ማለታቸው ይታውቃል... የወራት ሁሉ ባልተቤትነት የአላህ ቢሆንም እቺ ረጀብ የተባለቺው ወር በውስጧ የያዘቺው ፀጋ እና ፍፁምነቷ የአላህ ወር አሰኝቷታል... * 💚💕 ኢማሙ ሻፊዒይ ረህመቱሏሂ ዐለይህ "ኡም"በሚባለው መፅሀፋቸው ስለ ሁለቱ ዒዶች በሚያወራው ርዕስ ውስጥም ይህንን ብለዋል በአምስት ሌሊቶች ዱዐእ ተቀባይነቱ የጎላ ነው ይባል እንደነበረ ደርሶናል፣ እነርሱም:– 1) የጁሙዐ ሌሊት 2) የዒደል አድሀ ሌሊት 3) የዒደል ፊጥር ሌሊት 4) #የረጀብ_ወር_የመጀመሪያው_ሌሊት 5) የሸዕባን 15 ሌሊት ናቸው። * አዕሪፎቹ እንዳመላከቱት ረጅብ የሚዘራበት ወር ሲሆን ፤ ሻዕባን የዘራነውን የምናጠጣበት፤ ረመዳን ደግሞ ምርቱን የምናጭድበት ነው ... በረጀብ ያልዘራ ፣ በሻዕባን ያላጠጣ በረመዳን ሊያጭድ አይችልም  ... ከላይ እንደተጠቀሰው የረጀብ ወር የመጀመሪያው  ሌሊትም ብዙ ትሩፋት  ያሉበት ለይል ነውና ገላችንን ታጥበን በኢባዳ እና በነሻጣ እንቀበለው ... ወሩንም ከወንጀል በመታቀብ እና በኸይር ስራ እናድምቀው *

የእሮብ ዱዓ.. ፡========= ሶሀብዩ ሰይዱና ጃቢር ቢን ዐብዲላህ ረ.ዐ. በዘገቡት ሐዲስ : [.. ሰይዳችን ﷺ ሶስት ቀን - ሰኞ፣ ማክሰኞ እና ዕሮብ - አል-ፈትሕ የተባለው መስጂድ ውስጥ ዱዐ አድርገው እሮብ በሁለቱ ሶላቶች መካከል አላህ ልመናቸውን ተቀብሏቸው ከፊታቸው ላይ ደስታ ታየ.. ] ከዛ እንዲህ አሉ «እኔም አስጨናቂና ከባድ ጉዳይ ሲገጥመኝ ያቺን ሰዓት ተጠባብቄ ዱዐ አደርጋለው ቅቡልነቱንም አውቃለው ..» 📗ሙስነድ ኢማም አሕመድ 14563 📗 አደቡል ሙፍረድ 704 ኢማም አል-በይሃቂ'ይ እንዲህ ይላሉ :- «ለዱዐ የሚጠበቁና የሚለዩ ጊዜያት፣ ሁኔታዎች እና ቅቡልነትን ይገኝባቸዋል ተብሎ የሚከጀሉባቸው ቦታዎች አሉ.. ከጊዜያቶች ውስጥ እሮብ በዙህርና በዐስር ሰላት መሀከል ያለው ጊዜ አንዱ ነው » 📗 ሹዐብ አል-ኢማን (2/46) ጀይላን ሙባረክ ።።።።።።።።።።።።