ቅዱሳት መጻሕፍት
Open in Telegram
በዚህ ቻናል 👉ቅዱሳት መጻሕፍት ይጠናሉ:: 👉መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች ይቀርባሉ:: 👉 ለቅዱሳት መጽሐፍት ጥናት የሚያግዙ መጻሕፍት ይለቀቃሉ። ⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ @Holy_scriptures
Show more7 833
Subscribers
+724 hours
+357 days
+15630 days
Posts Archive
7 833
#አዲስ_ዓመት
የእግዚአብሔርን ቃል የማንበብ ጥቅም
ክፍል-1
መጽሐፍ ቅዱሳችሁን በማዘውተር ታነቡ እንደሆነ ልጠይቃችሁ እወዳለሁ፡፡ ቤተሰብ በገበታ ሲሰበሰብ ወይም በተለምዶ እንደሚደረግ ማለቴ ሳይሆን ለራሳችሁ ብላችሁ ብቻችሁን ስትሆኑ ታነቡ እንደሆነ ልጠይቅ ፈልጌ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ ማዘውተሩ ትልቅ ጠቀሜታ አለው፡፡ አማኝ የእግዚአብሔርን ቃል የማያነብ ከሆነ ከእግዚአብሔር ጋር የቅርብ ኅብረት አይኖረውም፤ ደስታውም የተሟላ አይሆንም፡፡
እንደዚህ ማለታችንም የመጽሐፍ ቅዱስን ጥቅም ማጋነን አይሆንም፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነና እግዚአብሔርንና ሐሳቡንም ማወቅ የምንችለው ደግሞ በቃሉ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን እግዚአብሔር በቃሉ ራሱን ገለጠ፤ ቃሉንም እንዲጻፍ አደረገው፡፡ በዚህ ቃሉም ማንነቱን ገለጠ፡፡ ያደረገውን፣ ሊያደርገው ያለውንና ሰው እንዴት ሊያገለግለው እንደሚገባም በቃሉ ተናገረ፡፡ ከዚያም ወልድ ወደ ምድር መጣና እግዚአብሔርን ተረከው (ዮሐ.1፡18) እንደዚሁም ስለወልድ ሕይወት ማለትም ስለ ልደቱ፣ ኑሮውና ሞቱ ስለ ተናገረውና ስለ ሥራውም ማወቅ የምንችለው በቃሉ ብቻ ነው፡፡ አሁን በምድር ላይ በአማንያን የሚያድር እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስም በቃሉ በኩል ሁሉን ነገር ይገልጽልናል፡፡
ስለሆነም መጽሐፍ ቅዱስን የማይወድ አማኝ ካለ አሳዛኝ ነው፡፡ በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት ማደግም ለቃሉ ካለን ፍቅርና ከቃሉ አጠቃቀም ጋር የተያያዘ ነው፡፡
አዲሱ ልደት- በእግዚአብሔር ቃል
ለምሳሌ መዝ.119ን ስንመለከት የዘማሪው እያንዳንዱ መንፈሳዊ ደረጃ ከቃሉ ጋር የተያያዘ ሆኖ እናገኛለን፡፡ በዚሁ መዝሙር ቁ.93ን ስናይ ‹‹በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና ፍርድህን ለዘላለም አልረሳም›› በማለት አዲሱ ሕይወት ከቃሉ እንደሚገኝ ይናገራል፡፡ እንደዚሁም በሌሎች ቁጥሮች ማለትም ቁጥር 25፣ 37፣ 41፣ 50፣ 88፣ 107፣ 116፣ 144፣ 149፣ 154፣ 156፣ 159 እና 175ን መመልከት ይቻላል፡፡ ይህ ሐሳብ በሌሎች በርካታ ምንባቦችም በግልጥ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ‹‹ለፍጥረቱ የበኩራት ዓይነት እንሆን ዘንድ በእውነት ቃል አስቦ ወለደን›› (ያዕ.1፡18) የሚል እናያለን፡፡ በሌላ ስፍራም ‹‹ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፤ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ›› (1ጴጥ.1፡23) ይላል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል የኃጢአተኛን ሰው ኅሊና ወደ እግዚአብሔር ብርሃን እንዲመጣ ያደርገዋል፡፡ በዚህም ሰው ማን መሆኑን አይቶ ራሱን ያወግዛል፤ ወደ እግዚአብሔርም ይናዘዛል፤ ይህም መለወጥ ማለት ነው፡፡ ራስን መመርመርና በራስ መፍረድም የሰውን ልብ ያነፃል፤ መንፈስ ቅዱስም በቃሉ በኩል አዲስ ሕይወትን በሰውዬው ውስጥ ይሠራል፡፡
ስለዚህ ለማያምኑት ሰዎች ወንጌልን ስንነግር የእግዚአብሔርን ቃል ማወቅ አለብን፡፡ የራሳችን ቃል ሰውን ወደ እምነት ሊያመጣ አይችልም፡፡ ሰውን መለወጥ የሚችለው የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነው፡፡ ‹‹እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡›› (ሮሜ.10፡17)፡፡
የአዲሱ ሕይወት ምግብ
በተጨማሪም መዝሙረኛው ስለ እግዚአብሔር ቃል ሲናገር ‹‹ቃልህ ለጉሮሮዬ ጣፋጭ ነው ከማርና ከወለላ ይልቅ ለአፌ ጣፈጠኝ፤››(መዝ.119፡103) ‹‹ከማርና ከማር ወለላም ይጣፍጣል››(መዝ.19፡10) በማለት የቃሉን ጣፋጭነትና ምግብነት በማድነቅ ተናግሯል፡፡ ይህም ጣፋጭ ምግብ ደግሞ ለአዲስ ሕይወት ምግብ ነው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ሰው ‹‹ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም›› በማለት ቃሉ በሕይወት የምንኖርበት ምግብ እንደሆነ ተናግሯል (ማቴ.4፡4፣ ዕብ.5፡12-14፣ 1ጴጥ1፡25-2፡2)፡፡
በቃሉ የተገኘው አዲሱ ሕይወታችን የሚስማማውን ምግብ ማግኘት አለበት፡፡ ይህም ምግብ አዳኛችንና የሞተልን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤(ዮሐ.6፡56) እርሱ በምድር ቅዱስ ሰው ሆኖ የተመላለሰና በሰማይ ደግሞ የከበረ ጌታ ሆኖ የተቀመጠ የአማኞች ምግብ ነው፡፡ እርሱ የምድረ በዳውን መና የተካ፣ የከነዓን የምድር ፍሬ፣ እንደዚሁም ለአማኞች የዘወትር መብል የሆነ ከሰማይ የወረደ አማናዊ መና ነው (ኢያ.5፡11-13) ይህንንም ምግብ የምናገኘው በቃሉ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ ጌታ በብሉይ ኪዳን በጥላዎችና በምሳሌዎች እየሆነ በትንቢቶች እና በነቢያት ይታያል፡፡ በአዲስ ኪዳን ደግሞ በሕይወቱ በሞቱና በክብሩ ከወንጌላት እስከ ራእይ በተጻፈው ይታያል፡፡
ታዲያ ብዙዎች መንፈሳዊ ሕይወታቸው ደክሞ አቅመቢስ ሆነው ጠንካራ ምግብ መውሰድ ተስኖአቸው ወተት ብቻ የሚያስፈልጋቸው (ዕብ.5፡12-14) ወደ ጉባኤ ስለማይመጡ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ስለማይከታተሉ ራሳቸውም ቃሉን ስለማያነቡ አይደለምን? ልናድግና ጤናማ የሆነ መንፈሳዊ ሕይወት ሊኖረን የሚችለው ዕለት ዕለት ያለማቋረጥ ቃሉን ስንመገብ ብቻ ነው፡፡
ይቀጥላል...
ምንጭ፦ gbv-online.org
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ለተጠሩት ግን፥ አይሁድ ቢሆኑ የግሪክ ሰዎችም ቢሆኑ፥ የእግዚአብሔር ኃይልና የእግዚአብሔር ጥበብ የሆነው ክርስቶስ ነው።”
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥24
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።”
ኤርምያስ 29፥11
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የኤፌሶን ከተማ አገልግሎቱን ከፈጸመ በኋላ የቤተክርስቲያን ሽማግሌዎችን ምክርና ሐሰተኞች እንደሚመጡ ያስጠነቀቃቸው የት ከተማ ነበር?
7 833
#እራሳችንን_እንመርምር
ስብከት ምንድነው? ጠቀሜታው ላላመነ ወይስ ላመነም ጭምር?
“በእግዚአብሔር ጥበብ ምክንያት ዓለም እግዚአብሔርን በጥበብዋ ስላላወቀች፥ በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአልና።”
1ኛ ቆሮንቶስ 1፥21
“አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም።”
2ኛ ጢሞቴዎስ 4፥5
“እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?”
ሮሜ 10፥14
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
"እግዚአብሔር የልመናዬን ድምፅ ሰምቶአልና ወደድሁት። ጆሮውን ወደ እኔ አዘንብሎአልና በዘመኔ ሁሉ እጠራዋለሁ።"
መዝሙር 116፥1-2
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
የመጥምቁ ዮሐንስ አገልግሎት
እግዚአብሔር የሰጠን አገልግሎት ምን እንደሆነ ለይቶ ማወቅ በረከት ነው። ጊዜያችንን በሚገባ ለመጠቀምና የእግዚአብሔርን ፈቃድ ጠንቅቆ ለመፈጸም እጅግ አስፈላጊ ነው። የተሰጠንን አገልግሎት ለይቶ አለማወቅ ከመቅበዝበዝ ባሻገር ሌሎችንም ከመጥቀም ይልቅ ስናውክ እንድንሰነብት ያደርገናል። እስቲ ለዮሐንስ ከሰማይ ተሰፍሮ የተሰጠውን አገልግሎት እንመልከት በዚያውም የራሳችንን እንፈትሽ።
1. የልዑል ነቢይ መሆን
“ደግሞም አንተ ሕፃን ሆይ፥ የልዑል ነቢይ ትባላለህ፥” ሉቃስ 1፥76
ይህ የዮሐንስ ዋና አገልግሎት ነበር። እርሱም የእግዚአብሔር ነቢይ መሆን የእግዚአብሔርን መልእክት ለእስራኤል ይናገር ነበር። እርሱ የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን ነቢይ እና በብሉይ እና በአዲስ ኪዳን መካከል ያለው ድልድይ ነበር (ሚል. 3፥1፤ ኢሳ. 40፥3፤ ማቴ. 11፥9-10)።
2. በጌታ ፊት መሄድ
“. . . በጌታ ፊት ትሄዳለህና፤” ሉቃስ 1፥76
የዮሐንስ ተልእኮ ሰዎችን ወደ ራሱ መጠቆም ሳይሆን ለመሲሑ ለኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ማዘጋጀት ነበር። በጌታ ፊት በመሄዱም ዋና አገልግሎቱ ይህ ነበር።
3. የጌታን መንገድ መጥረግ ወይም ማዘጋጀት
“. . . መንገዱን ልትጠርግ . . . ” (ሉቃስ 1፥76)
ዮሐንስ ሰዎች ክርስቶስን እንዲቀበሉ መንፈሳዊ እንቅፋቶችን ያስወግድ ነበር (ሉቃስ 3፥3–6)።
ዮሐንስ ሰዎችን በመንፈሳዊ መንገድ ያዘጋጀው፦
👉ንስሐን በመስበክ።
👉እስራኤልን ወደ እግዚአብሔር በመጥራት።
👉ንስሐ የገቡትን በማጥመቅ።
4. የመዳንን እውቀት መስጠት
“. . . የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤” (ሉቃስ 1፥77)
ዮሐንስ ለሰዎች መዳን እንዴት እንደሚመጣ አስተምሯል። በዘር ሐረግ ወይም ሕጉን ብቻ በመጠበቅ ሳይሆን በእግዚአብሔር ተስፋ በተሰጠው መሲሕ በኩል ሰዎችን ወደ ኢየሱስ መርቷል።
5. የኃጢአትን ይቅርታን ማወጅ
“እንደዚህም የኃጢአታቸው ስርየት የሆነውን የመዳን እውቀት ለሕዝቡ ትሰጣለህ፤” ሉቃስ 1፥77
ዮሐንስ ሰብኳል። ምን በማለት? "ንስሐ ግቡ!"
6. ስለሚመጣው ብርሃን መመስከር
ሉቃስ1፥78–79 መሲሑን ከሰማይ የሚወጣ ፀሐይ እንደሆነ ይገልፃል። የዮሐንስ ተግባር ይህ ብርሃን እንደሚመጣ ማወጅ ነበር።
ይህም ከዚህ ጋር ይስማማል፦ "ከእግዚአብሔር የተላከ ስሙ ዮሐንስ የሚባል አንድ ሰው ነበረ፤ ሁሉ በእርሱ በኩል እንዲያምኑ ይህ ስለ ብርሃን ይመሰክር ዘንድ ለምስክር መጣ። ስለ ብርሃን ሊመሰክር መጣ እንጂ፥ እርሱ ብርሃን አልነበረም።" ዮሐንስ 1፥6-8
7. ሰዎች በሰላም መንገድ እንዲሄዱ መርዳት
“. . . እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።” ሉቃስ 1፥79
ዮሐንስ በስብከቱ አማካኝነት ሰዎችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ያለውን ሰላም እንዲቀበሉ አዘጋጅቷል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ስለ እግዚአብሔርም ቤት አገልግሎት በጀመረው ሥራ ሁሉ፥ በሕጉና በትእዛዙም፥ አምላኩን ለመፈለግ በፍጹም ልቡ አደረገው፥ ተከናወነለትም።”
2 ዜና 31፥21
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
Title: Smith's Bible Dictionary
Author: Smith, William
Publisher: Grand Rapids, MI: Christian Classics Ethereal Library
Year: 1884
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“ብርሃኑም በጨለማና በሞት ጥላ ተቀምጠው ላሉት ያበራል እግሮቻችንንም በሰላም መንገድ ያቀናል።”
ሉቃስ 1፥79
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
በቅዱሳት መጻሕፍት አንድ ሰው ቅዱስ ጳውሎስን በራእይ ወደ መቄዶንያ ተሻገርና እርዳን ብሎ ከለመነው በኋላ ጳውሎስ ወደየትኛው ከተማ ሄደ?
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥”
ኤፌሶን 4፥23
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
ነገረ ፍጻሜ (Eschatology)
ክፍል-3
2. Dispensational Premillennialism (ዲስፐንሴሽናል ቅድመ ሚሊኒየም)
ይህ አስተምህሮ በአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን የዳበረ ሲሆን በመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ውስጥ ካሉት እጅግ ተደማጭነት ካላቸው ትርጓሜዎች አንዱ ሆኗል። እግዚአብሔር የመቤዠት እቅዱን በተለያዩ ሥርዓቶች (አስተዳደር ወይም መጋቢነት) እንደሚያስተዳድር ያስተምራል።
የዚህ አመለካከት አንድ ግልጽ ገጽታ በእስራኤል እና በቤተክርስቲያን መካከል ያለው ልዩነት ነው። እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ተስፋዎች በሥራ ላይ እንደሚቆዩ እና በክርስቶስ የሺህ ዓመት መንግሥት ዘመን ቃል በቃል እንደሚፈጸሙ ያስተምራል። ስለዚህ ቤተክርስቲያን እና እስራኤል በእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ የተለያየ ሚናዎች አሏቸው።
አብዛኛዎቹ የዲስፔንሽናል የቅድመ ሚሊኒየም አስተምህሮ ተከታዮች ክርስቶስ ከሰባት ዓመት መከራ በፊት አማኞችን ወደ ሰማይ ለመውሰድ በድብቅ የሚመጣበትን የቅድመ መከራ መነጠቅ ያስተምራሉ። ከመከራው በኋላ ክርስቶስ ምድራዊ መንግሥቱን ለመመስረት ከቅዱሳኑ ጋር በግልጽ ይመለሳል።
የዚህ አስተምህሮ ዋና ዋና ባህሪያት
👉ክርስቶስ ከሺህ ዓመቱ በፊት ይመለሳል።
👉እስራኤል እና ቤተክርስቲያን በእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ የተለዩ ሆነው ይቆያሉ።
👉አብዛኛዎቹ ከመከራ በፊት የሚመጣ መነጠቅን ይይዛሉ።
👉የወደፊት የሰባት ዓመት መከራ የክርስቶስን የሚታይ መመለስ ይቀድማል።
👉ክርስቶስ በሺህ ዓመቱ በሚታይ መልኩና በተጨባጭ ከኢየሩሳሌም ይነግሳል።
👉ለእስራኤል የተሰጡት የብሉይ ኪዳን ተስፋዎች ቃል በቃል ተፈጽመዋል።
የመጽሐፍ ቅዱስ ድጋፍ
👉ዳንኤል 9፥24–27
👉ማቴዎስ 24
👉ዮሐንስ 14፥1–3
👉1 ተሰሎንቄ 4፥13–18
👉ራዕይ 3፥10
👉ራዕይ 19–20
ጥንካሬዎች እና የተለመዱ ትችቶች
ጥንካሬዎች
👉ራዕይ 20ን በቁም ነገር እንደ የወደፊት ክስተት አድርጎ መውሰድ።
👉የክርስቶስን ተጨባጭ እና የሚታይ አገዛዝ አፅንዖት መስጠት።
👉የክርስቶስን መመለስ በጠንካራ ተስፋነት መጠበቅ።
👉የብዙ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን ወጥ የሆነ ትርጓሜ መስጠት።
የተለመዱ ትችቶች
👉አንዳንድ ትርጓሜዎች ስለ አፖካሊፕቲክ ሥነ ጽሑፍ ከልክ በላይ ቃል በቃል ናቸው።
👉በእስራኤል እና በቤተክርስቲያን መካከል ያለው ልዩነት ይከራከራል። (በተለይም የዲስፐንሴሽናሊስቶች አመለካከት)
👉ከዳግም ምጽአት በፊት የተለየ ሚስጥራዊ መነጠቅ የሚለው ሀሳብ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ በግልጽ የተገለጸ አይደለም እና በአንጻራዊነት የቅርብ ጊዜ ሥነ-መለኮታዊ ግኝት ውጤት ነው። (ይህ በተለይም ዲስፐንሴሽናሊስቶች የሚተቹበት ነገር ነው። ሚስጥራዊ ንጥቀት በቅዱሳት መጻሕፍት በግልጽ አልሰፈረም።)
👉አዲስ ኪዳን ብዙውን ጊዜ የክርስቶስን ዳግመኛ መመለስ፣ ትንሣኤ እና የመጨረሻ ፍርድን በአንድ ጊዜ እንደሚከሰት እንጂ በተለያየ ወቅት እንደሚከሰት አያስተምረንም።
ይቀጥላል . . .
Blaising, C. A., & Bock, D. L. (Eds.). (1993). Progressive dispensationalism. Baker Academic.
Grudem, W. (2020). Systematic theology: An introduction to biblical doctrine (2nd ed.). Zondervan Academic.
Ladd, G. E. (1974). The presence of the future: The eschatology of biblical realism. Eerdmans.
Ryrie, C. C. (2007). Dispensationalism (Rev. and expanded ed.). Moody Publishers.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
7 833
. ──•◈•─────•◈•─
የዕለቱ ጥቅስ
──•◈•─────•◈•─
“በርናባስና ጳውሎስም ስለ ጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሕይወታቸውን አሳልፈው የሰጡ ናቸው።”
ሐዋርያት 15፥26 (አዲሱ መ.ት)
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
