en
Feedback
ባህረ ጥበባት

ባህረ ጥበባት

Open in Telegram

"ህዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል" ት. ሆሴዕ 4:6 አለማወቅ እያጠፋን ነውና እንወቅ። ለማንኛውም አስተያየትና ጥያቄ @Filoppader

Show more
1 219
Subscribers
+124 hours
+17 days
+630 days
Posts Archive
photo content

photo content

photo content

photo content

༒ ህዳር 21 ጽዮን ማርያም ༒ "ጽዮን" ማለት "ጸወን - አምባ - መጠጊያ" ማለት ነው። አንድም በምሥጢሩ "ማሕደረ አምላክ" ማለት ነው። ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራ : ለኪዳኑ ደግሞ ጽላት ሆኖ ሲያገለግል ትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘላለማዊት ርስት ያገለግላል። እግዚአብሔር ከዘመነ አበው በኋላ በጊዜው ለእስራኤላውያን ክብር፣ ሞገስ፣ አምባ የምትሆናቸውን ታቦተ ጽዮንን በቅዱስ ሙሴ አማካኝነት ሰጥቷቸዋል። (ዘጸ. ፴፩፥፲፰) ታቦተ ጽዮን ብዙ ጊዜ "ጽላተ ኪዳን፣ ታቦተ ሕጉ" እየተባለች ትጠራለች። "ጽሌ" ማለት "ሰሌዳ" እንደ ማለት ሲሆን "ጽላት" ደግሞ በብዙ ቁጥር ነው። "ኪዳን" ደግሞ በፈጣሪና በሰው ልጆች መካከል ያለ "ውል - ስምምነት" ነው። "ታቦት" ማለት "ማሕደር - ማደሪያ" እንደ ማለት ነው። ሕጉ የተጻፈባቸውን ሰሌዳ "ጽላት" ስንላቸው የጽላቱ ማደሪያ ደግሞ "ታቦት" ይባላል። ጽላት (ታቦትን) ያመጣ ፈጣሪ ነው። በሐዲስ ኪዳንም ምሥጢርና ሐተታ ቢኖረውም ሁለት ቦታ ላይ ስለ ታቦት ተጠቅሶ እናገኘዋለን። (፪ቆሮ. ፮፥፲፮ ፣ ራእይ. ፲፩፥፲፱) ++ ኅዳር 21 የምናከብርበት ዋናው ዓለማ ፩ኛ. ታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን)- ለሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ መሰጠቷን እናስባለን። ይህ ሲሆንም ቅዱስ ሙሴ አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ጾሞ እንደ ተቀበለ እያሰብን ማለት ነው። (ዘጸ. ፴፩፥፲፰ ፣ ዘዳ. ፱፥፲ . ፪ በሊቀ ካህኑ ኤሊ ዘመን ታቦተ ጽዮን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካለች። ነገር ግን ዳጐን የሚባለውን የአህዛብ ጣኦት የሰባበረችበትን ቀን እናስታውሳለን (፩ሳሙ. ፭፥፩) ፫ኛ. በዘመነ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በአሚናዳብ ሠረገላ ሁና ከአቢዳራ ቤት ስትመጣ ቅዱሱ ንጉሥ በታላቅ ሐሴት በፊቷ ዘመረ፤ አገለገለ። ምድራዊ ክብሩን እስኪረሳ ድረስ ለታቦተ አምላክ ተቀኘላት። በዚህም ምክንያት ሚስቱ ሜልኮል ንቃው ማኅጸኗ ተዘግቷል እስክትሞትም ደረስ አልወለደችም ነበር እንዲል። (፩ዜና. ፲፭፥፳፭) ሊቃውንትም ይህን ሲያመሰጥሩ "ቅድስትድንግል ማርያምን በትንቢት መነጽር ተመልክተው እንዲህ ብለዋል፦ "ሰላም ለኪ ማርያም እምነ ዘሰመይናኪ ጸወነ ሶበ እምርሑቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየኀይድ ዓይነ ቅድመ ታቦተ ሕግ ኃለየ ወዓዲ ዘፈነ እንዲል ። ፬ኛ. በቅዱስ ሰሎሞን(መፍቀሬ ጥበብ) ዘመንም ግሩም የሆነ ቤተ መቅደስ ተሰርቶላት ስትገባ ታላቅ ሐሴት ሆኖ ነበር። እግዚአብሔርም በደመና ወርዶ ንጉሱን አነጋግሮ ነበር (፪ኛ ዜና ፭፥፩ ፩ኛ ነገ ፰*፩)። ፭ኛ. በዚያ ዘመን ንጉስ ሚኒሊክ (ዕብነ ሐኪም) ታቦተ ፅዮንን ይዞ ገብቷል። ፮ኛ. በዘመነ አፄ ባዜን (፬ኛው ክ.ዘ.መ) አማናዊት ጽዮን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ አክሱም ፅዮን በስደት መጥታ ገብታለች። በዚህም ጊዜ ሁለቱ ጺዮኖች (ታቦተ ፅዮን እና ፅዮን ማርያም) ሲገናኙ አክሱም ከክብራቸው የተነሳ በብርሃን አሸብርቃለች። ፯ኛ. በ፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአፅብሓ ዘመን አስራ ሁለት መቅደስ ያሏትን ቤተ መቅደስ ለእመብርሃን ሰርተዋል: በጌታችንም ተቀድሷል። ፰ኛ. በአረመኔዋና የቤተ ክርስቲያን ቀንደኛ አውዳሚ በሆመችው በዮዲት ጉዲት ቤተ መቅደሷ ስትፈርስ ወደ ዝዋይ ትሰደድ ነበር በኋላም ቤተ መቅደሷ ሲሰራ ተመልሳ እንደመጠችም በኅዳር ፳፩ ቀን ትከበር ነበር። ༒ መልካም በዓል ይሁንላችሁ ༒

photo content

# ፆመ_ነብያት_መቼ_ይገባል ? ለምንስ_እንፆማለን? ፆመ ነብያት ወይም የገና ፆም #ሐሙስ ህዳር 15 ይጀምራል ታህሳስ 29 ይፈታል። ይህ ማለት የዘንድሮ የገና ፆም ቅበላ እስከ ማክሰኞነው ከረቡዕ ጀምሮ የፍስክ ምግቦች አይበሉም። ይህ ፆም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ ፆሞች ውስጥ አንዱ ሲሆን አበው ነብያት የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መውረድ መወለድ በትንቢት መነፅር እየተመለከቱ የፆሙት ታላቅ ፆም ነው። ዛሬም እኛ ክርስቲያኖች የአባቶቻችንን ፈለግ ተከትለን በፆምና በፀሎት ወቅቱን በማሳለፍ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ዝቅ አድርጎ ወደ አለም መምጣቱንና የዓለም ቤዛ መሆኑን የምናስብበት ነው። => ይህ ፆም፣ ፆመ ድህነት፣ ፆመ ማርያም ፣ ፆመ አዳም ፆመ ፊሊጶስ ፆመ ስብከት በመባል ይጠራል። # ፆመ_ድህነት የተባለበት ምክንያት መርገመ ስጋ መርገመ ነብስ የአዳም እዳ በደል ጠፍቶ ድህነት ስለተገኘበት ነው። # ፆመ_ማርያም የተባለበት ምክንያት ንፅይተ ንፁሃን ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስ ድንግል ማርያም ጌታን በማህፀኔ ተሸክሞ ልፆም ልፀልይ ይገባል ብላ ለ40 ቀን እስከ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ድረስ የፆመችው ፆም ስለሆነ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል። # ፆመ_አዳም የተባለበት ምክንያት ለአዳም የተነገረው ትንቢት፣ የሚጠበቀው ሱባኤ እንደደረሰ የሚያበስር በመሆኑ ጾመ አዳም ይባላል፡፡ አዳም ቢበድልም ንስሐ ገብቶ በማልቀሱ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሀለሁ ብሎ የተነገረው ተስፋ መድረሱን፣ ምሥጢረ ሥጋዌ እውን ሊሆን መቃረቡን የሚያስረዳ ጾም ነው፡፡ # ፆመ_ፊሊጶስ የተባለበትም ምክንያት ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ ሲያስተምር በሰማዕትነት ሲሞት አስከሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስከሬን እንዲገልጽላቸው ከኅዳር አስራ ስድስት ጀምረው ሲጾሙ በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስከሬን ቢመልስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል ለዚህም ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ # ፆመ_ስብከት የተባለበትም ምክንያት የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት የሰውልጆች ተስፋ የተመሰከረበት የምሥራቹ የተነገረበት ስለሆነም «ጾመ ስብከት» ይባላል፡፡ ፆሙን የሀጥያታችን መደምሰሻ መንግስተ ሰማያተን መውረሻ ያድርግልን። የቅዱሳን ነብያት አባቶቻችንንም በረከት በሁላችንም ላይ ያሳድርብን። @Filoppader @bahreTibebat 13/03/7515 ዓ.ዓ +251941317410

photo content

photo content