ባህረ ጥበባት
"ህዝቤ እውቀት ከማጣቱ የተነሳ ጠፍቷል" ት. ሆሴዕ 4:6 አለማወቅ እያጠፋን ነውና እንወቅ። ለማንኛውም አስተያየትና ጥያቄ @Filoppader
Show more1 161
Subscribers
-124 hours
-37 days
-430 days
Posting time distributions
Data loading in progress...
Find out who reads your channel
This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.Publication analysis
Posts | Views | Shares | Views dynamics |
01 Media files | 177 | 1 | Loading... |
02 Media files | 191 | 1 | Loading... |
03 Media files | 187 | 2 | Loading... |
04 https://youtu.be/mUKGmAi6aNI | 233 | 1 | Loading... |
05 https://youtu.be/DclcOEaC3BI?si=RPhsQ4CMM9rOVnJX | 392 | 0 | Loading... |
06 Media files | 371 | 0 | Loading... |
07 Media files | 392 | 0 | Loading... |
08 🍀🕊«ጾም እስከ ስንት ሰዓት ነው?»🍀🕊
የቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ሥርዓቱ በልኬት እና በምክንያት የታጀበ ነው። ጾምን ስንመለከት አብዛኞቻችን በተለምዶ ሰዓት ሳንጠብቅ (እስከ 3፣ 6፣ 7፣ 9፣ 11 ሰዓታት እያልን) እንጾማለን እንጂ የአዋጅ አጽዋማት የተወሰነ የተገደበ ሰዓት አላቸው።
ፍትሐ ነገሥታችን “ሕማማት እስከ 12 ሰዓት ይጹሟቸው፥ ሌሎቹን አጽዋማት በዓለ ልደት እና ጥምቀት ረቡዕ እና ዐርብ የሚውሉባቸው ካልሆኑ በቀር እስከ 9 ሰዓት ይጹሙ” (ፍት.ነገ አን 15፥565-566) ብሏል።
የአጽዋማትን ዝርዝር ካስቀመጠ በኋላም በዚሁ አንቀጽ ቁጥር 572 ላይ ደግሞ “በእነዚህ በታዘዙት ጾሞች ከቀኑ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ይጹሙ፣ ... ከዚህ አብልጦ የጾመ ግን ዋጋው ይበዛለታል፣ ከጥሉላት ምግቦች መታቀብ ካልሆነ በቀር እሑድና ቅዳሜ ግን አይጹሙ” ብሎ ወስኗል።
ዐቢይ ጾም ሁዳዴ፣ ጾመ ዐርብዓ ግን ይለያል። “በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ ፀሐይ እስኪገባ ይጹሙ፣ ሌሎቹን ሳምንታት እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፥ በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ ይጹሙ” ብለዋል። (ፍት.ነገ.አን 15፥595)።
ፍትሐ ነገሥት ቁጥር 578 ላይ ደግሞ “(የሰሙነ ሕማማትን) ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ይጹሟቸው፣ የሚችል እስከ ሌሊት ዶሮ ጩኸት ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው፣ ሁለቱን በአንድነት መጾም የማይቻለው ግን ቅዳሜን ይጹም” ተብሎ ህግ ተሠርቷል።
በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ የተጻፈ
የጾሙ የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ) የሚጾመውእስከ 12 ሰዓት ሲሆን ከቅድስት (ከ2ኛው ሳምንት) እስከ ተጽኢኖ (የኒቆዲሞስ ዓርብ) ድረስ ደግሞ እስከ 11 ሰዓት ይጾማል::
በሰሙነ ሕማማት ግን የምንጾመው "እስከ ይሠርቅኮከብ" (እስከ ምሽት 1 ሰዓት) ድረስ ይሆናል::
+ነገር ግን ሁሉም እንደ መጠኑ ነውና ከመምሕረ ንስሃ
ጋር ሊጨዋወቱት ይገባል:: በዓቢይ ጾም ለቻለ ቂጣ
በጨው እየበላ: ውሃ እየተጐነጨ ሊጾም ይገባል::
በእነዚህ 55 ቀናትም ከዕለተ ሆሳዕና በቀር ከበሮ
አይጐሰምም:: ጸናጽል አይጸነጸልም:: ተድላ ደስታም
አይደረግም:
እንኳን አደረሳችሁ መልካም የፆም ወቅት🙏🙏 | 335 | 2 | Loading... |
09 https://youtu.be/0taqTNWXfC4?si=Wmt0VqOQ_7KjPAqI | 354 | 2 | Loading... |
10 Media files | 601 | 0 | Loading... |
11 https://youtu.be/tP6WGbUbZ60 | 630 | 1 | Loading... |
12 https://youtu.be/vw3aaMp7dVs?si=BVK_pdpXhGH7Eyev | 681 | 0 | Loading... |
13 በ9 ደቂቃ ነፍሳችሁን አድሷት | 578 | 0 | Loading... |
14 https://youtu.be/iFUjWbaM414 | 560 | 1 | Loading... |
15 Media files | 658 | 2 | Loading... |
16 ሚያዚያ 6 ቅድስት ግብፃዊት ማርያም እረፍቷ ነው
+++++ቅድስት ማርያም ግብጻዊት~ የተወለደችው በግብጽ ሲሆን ገና የ12 አመት ልጅ እያለች ነበር ወደ እስክንድርያ በመሄድ ድንግልናዋን ያፈረሰችው:ከዚያም የዝሙት ፍቅር አድረባት:ለ17 አመት ያህል ሰዎችን በሚያቃጥል
የሃጥያት እሳት ታስፈጃቸው ነበር ዝሙት እያሰራች:ብዙዎችንም ታስት ነበር።
ዝሙት ከመውደድ የተነሳ ገንዝብ እንኳን ልስጥሽ ሲሉ አትቀበልም ነበር:በእግዚአብሄርም አታምንም ነበር።
በዛው ፋንታ እንደፈለገች ትሆን ነበር። በልቧ ከዚህ ሲራዬ ማንም አይከለክለኝም ትል ነበር::
አንድ ቀን ሊቢያውያን እና ግብጻውያን ወደ ባህር እየተቻኮሉ ሲሄዱ አይታ ወዴት እንደሚሄዱ ብጠይቃቸው የከበረ የጌታችንን መስቀል በዓል ለማክበር ወደ እየሩሳሌም እንደሚሄዱ ሲነግሯት እና የሚሄደው ሰው ብዙ መሆኑን ሲታይ: ብዙ ዘመዶችን አገኛለው ብላ ከነሱ ጋር ለመሄድ ተነሳች:ለጉዞዋ ወይም ለምግብ የሚሆን አንድም ገንዘብ አልያዘችም ነበር።
በሁኃላም በሰውነቷ ማማር ብዙዎችን በዝሙት ምክንያት አጠመደች ወደ ተቀደሰ ቦታ የሚሄዱቱን ሰዎች በማሳት ዋና የሰይጣን መረብ ሆና ነበር:በዚህም ስራዋ እየተኩራራች ለሰው ሁሉ ትናገር ነበር።
የሃጥያተኛን ሞት የማይወድ እግዚአብሄር መመልሷን እየጠበቀ ይታገሳት ነበር።
በመጨረሻም እየሩሳሌም ደርሰው ከበዓሉ በፊት እንደለመደችው እንደውም በከፋ መልኩ ዝሙትን አብዝታ ትሰራ እና ሰውንም ታስት ነበር።
የበዓሉ ዕለት ጠዋት ብዙ ተሳላሚዎች ጌታችን መቃብር ላይ ወደ ተሰራችው ቤተ-ክርስቲያን ሊሳለሙ ሲሄዱ አየችና እዛ ሄደው ምን እንደሚያደርጉ ለማወቅ ፊላጎት አደረባት እናም ህዝቡ በሚገቡበት በር እየተጋፋች ለመግባት ትሞክር ጀመር በኃላም በሩ ጋር ስትደርስ የሆነ ሃይል ሲገፋት ይታወቃት ጀመር።
ሌሎችን ሰዎች ስታይ በቀላሉ ይገባሉ እና መጀመሪያ ላይ ምንድን ነው እያለች ትስቅ ነበር?!
ደጋግማ ስትሞክር አልቻለችም በኃላም ዝም ብላ በሩ ላይ ቆመች እንደገናም ደጋግማ ሞከረች በኃላም ሲደክማት ግዜ እልፍ ብላ ከበሩ አጠገብ ቆመች።
በህሊናዋም በብዙ መከራ ምን እንደሆነ ታስብ ጀመር: ቅዱስ መስቀሉን ለማየት እሷ ያልቻለችበትን ምክንያት ታስብ ጀመር:የድህነት ቃል የልቦናዋን አይኖች ነካቸው እና እንዳልገባ የከለከለኝ የራሷ የግል ሃጥያት መሆኑን ተረዳች።
በኃላም በማልቀስ እና
ደረቷን እየደቃች ከውስጣዊ ልቧማዘን ጀመረች:"ለምን አልገባም?
እንዳልገባ የከለከለኝ የኃጢአቴ ብዛት ነው?" እያለች ደጋግማ እራሷን ትጠይቅ ጀመር:ያን ግዜ የእመቤታችንን
የቅድስት ድንግል ማርያምን ስዕል (ስዕል አድኖ)ከበሩ ላይ አየችና ሄዳ ስዕሏ ፊት ቆማ የስዕሏን ግርማና ውበት ባየች ግዜ ያለፈ የራሷ ሃጥያት ወለል ብሎ ታያት እና አፈረች።
በኃላም በብዙ ለቅሶ ስዕሏ ስር ወድቃ "ከእንግዲህ በኃላ ጌታየን አገለግል እና ያንቺ ባርያ እሆን ዘንድ እድል
አገኝ ይሆን ?" እያለች ታለቅስ እና ትለምን ጀመር።
ጌታችንንም ካለችበት ስቃይና መከራ እንዲያድናት እና በመንገዱ እንዲመራት ለመነችው:"ቅዱስ መስቀሉን ካየው በኃላም አለም እና ደስታዋን እንደምክድ ቃል ገባለው" ብላ ቃል ገባች። ከጸለየችም በኃላ የመተማመን
ስሜት ተሰማትና ወደ መስቀሉ ቦታ ወደሚያስገባው ቦታ ሄደች ከዚያም ያለችግር ገባች።
በኃላም መስቀሉ ጋር ደርሳ በመንቀጥቅጥ እና በብዙ እምባ ሳመች የእግዚአብሄርን ሚስጥር እና ንስሃን እንዴት እንደሚቀበል አየች:ከዚያም ወታ ቃል ወደ ገባችበት ወደ እመቤታችን ስዕል ጋር ሄዳ "የሃጥአንን ንሰሃ ባንቺ አማላጅነት የሚቀበል እግዚአብሄር የተመሰገነ ይሁን:የከበርሽ እመቤቴ ሆይ ኃጥእት እኔ ምን እላለው?"አለችና "አለቀስች ወደ ሥዕሏም ተመልሳ አለቀሰች፡፡ ከሥዕሏም ድምፅ ወጣና ‹‹ወደ ዮርዳኖስ በረሃ ሂጂ›› አለቻት፡፡ ዮርዳኖስን ተሻግራ ሄዳ 47 ዓመት በበረሃ ብቻዋን ስትጋደል ኖረች፡፡ ሰይጣንም በዝሙት ጦር ይዋጋት ነበር፡፡ 40 ጾምን ሊፈጽም ቅዱስ ዞሲማስ ወደ በረሃው መጣ፡፡
በዚያ በረሃ ውስጥ የሚጽናናበትን ነገር እንዲሰጠው ወደ ጌታችን ጸለየና ማርያምን ገለጠለት፡፡ ሲጠጋት ሮጣ አመለጠችውና ‹‹ዞሲማስ ሆይ ጨርቅ ጣልልኝ›› ብላ በስሙ ስትጠራው እጅግ ደነገጠ፡፡ ልብሱንም ከሰጣት በኋለ ሰገደላት፡፡ ገድሏንም እንድትነግረው በብዙ ለመናትና ነገረችው፡፡ በዓመቱ ሥጋ ወደሙን አምጥቶ እንዲያቆርባት ጠየቀችው፡፡ በዓመቱ መጥቶ አቆረባት፡፡ አሁንም በዓመቱ ይመጣ ዘንድ ለመነችው፡፡ ድጋሚም ሲመጣ ዐርፋ አንበሳ አስክሬኗን ሲጠብቀው አገኛት፡፡ አንበሳውም መቃብሯን ቆፍሮ አሳየውና ገንዞ ቀበራት፡፡ ገድሏንም ለመነኮሳቱ ሁሉ ነገራቸው፡፡
አባ ዞሲማስም ከደጋግ ክርስቲያን ፍልስጤማውያን ወላጆች የተገኘ ጻድቅ ነበር፡፡ ለመምህርም ሰጥተውት በሚገባ ተምሮ ካደገ በኋላ መነኮሰ፡፡ ሲሠራም ሆነ ሲበላ እንኳን ምስጋናን ከአፉ የማያቋርጥ ደገኛ አባት ከሆነ ከ45 ዓመት በኋላ ቅስና ተቀበለ፡፡ ተጋድሎውንም ጨምሮ 13 ዓመት ከቆየ በኋላ ሰይጣን በልቡ ክፉ ሀብን አሳደረበት፡፡ በልቡም ከበጎ ሥራዎች ሁሉ እኔ ያልሠራሁት ምን ነገር አለ?›› ይል ጀመር፡፡ ጌታችንም ሊተወው አልወደደምና መልአኩን ልኮ ወደ ዮርዳኖስ አቅራቢያ ወዳለው በረሃ እንዲሄድ ነገረው፡፡ በዚያም ሌሎች ደጋግ አባቶችን አገኘና ከእነርሱ ተማረ፡፡ በዚያም ሳለ ወደ በረሃው ገብቶ የሚጽናናበት ነገር ይገልጥለት ዘንድ ወደ ጌታችን በጸለየ ጊዜ ነው ማርያምን ያገኛት፡፡ ዞሲማስ ብሔረ ብፁዓንም ድረስ ሄዶ የቅዱሳንን አኗኗራቸውንና ገድላቸውን አይቶ የጻፈልን ታላቅ አባት ነው፡፡
የቅድስት ማርያም ግብፃዊት ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን። አሜን! | 530 | 3 | Loading... |
17 https://youtu.be/1U9Pp7NxtUY | 493 | 2 | Loading... |
18 እስከመጨረሻው ብታዳምጡት ታተርፉበታላችሁ | 586 | 0 | Loading... |
19 https://youtu.be/EFup4m1SRpY | 597 | 1 | Loading... |
Show all...
መንፈስ ታሰረ ስንል እንዴት ነው፤ አጋንንትን ማሰርስ የማን ስልጣን ነው
የህማማት እንዲሁም የንስሐ ስግደት
https://youtu.be/DclcOEaC3BI?si=TuKNvvOOqkkvPLMlከስር ያለፏችሁን ትምህርቶችን አዳምጧቸው ታተርፉበጻላችሁ ሰዎች ይጠሉኛል ምን ላድርግ
https://youtu.be/0taqTNWXfC4?si=fGBLnBkAH-Us8rN8መንፈሳዊ ዝለት
https://youtu.be/c_nlIAjFDC4?si=zcanxukhQqu45w6c🙏 8👍 1
Show all...
🛑የ 22 ቱ አሌፋት የአምልኮ እና የንስሐ ስግደት #በሕማማት የሚሰገድ ደስ የሚል የአምልኮና የንስሐ ስግደት
🙏 6👍 3🥰 1🤔 1
🍀🕊«ጾም እስከ ስንት ሰዓት ነው?»🍀🕊
የቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ሥርዓቱ በልኬት እና በምክንያት የታጀበ ነው። ጾምን ስንመለከት አብዛኞቻችን በተለምዶ ሰዓት ሳንጠብቅ (እስከ 3፣ 6፣ 7፣ 9፣ 11 ሰዓታት እያልን) እንጾማለን እንጂ የአዋጅ አጽዋማት የተወሰነ የተገደበ ሰዓት አላቸው።
ፍትሐ ነገሥታችን “ሕማማት እስከ 12 ሰዓት ይጹሟቸው፥ ሌሎቹን አጽዋማት በዓለ ልደት እና ጥምቀት ረቡዕ እና ዐርብ የሚውሉባቸው ካልሆኑ በቀር እስከ 9 ሰዓት ይጹሙ” (ፍት.ነገ አን 15፥565-566) ብሏል።
የአጽዋማትን ዝርዝር ካስቀመጠ በኋላም በዚሁ አንቀጽ ቁጥር 572 ላይ ደግሞ “በእነዚህ በታዘዙት ጾሞች ከቀኑ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ ይጹሙ፣ ... ከዚህ አብልጦ የጾመ ግን ዋጋው ይበዛለታል፣ ከጥሉላት ምግቦች መታቀብ ካልሆነ በቀር እሑድና ቅዳሜ ግን አይጹሙ” ብሎ ወስኗል።
ዐቢይ ጾም ሁዳዴ፣ ጾመ ዐርብዓ ግን ይለያል። “በዐቢይ ጾም መጀመሪያ ሱባኤ ፀሐይ እስኪገባ ይጹሙ፣ ሌሎቹን ሳምንታት እስከ 11 ሰዓት ይጹሙ፥ በሰሙነ ሕማማት ግን ኮከብ እስኪወጣ ይጹሙ” ብለዋል። (ፍት.ነገ.አን 15፥595)።
ፍትሐ ነገሥት ቁጥር 578 ላይ ደግሞ “(የሰሙነ ሕማማትን) ዓርብንና ቅዳሜን ግን ሁለቱንም በአንድነት ይጹሟቸው፣ የሚችል እስከ ሌሊት ዶሮ ጩኸት ድረስ ምንም ምን አይቅመስባቸው፣ ሁለቱን በአንድነት መጾም የማይቻለው ግን ቅዳሜን ይጹም” ተብሎ ህግ ተሠርቷል።
በዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ የተጻፈ
የጾሙ የመጀመሪያው ሳምንት ዘወረደ) የሚጾመውእስከ 12 ሰዓት ሲሆን ከቅድስት (ከ2ኛው ሳምንት) እስከ ተጽኢኖ (የኒቆዲሞስ ዓርብ) ድረስ ደግሞ እስከ 11 ሰዓት ይጾማል::
በሰሙነ ሕማማት ግን የምንጾመው "እስከ ይሠርቅኮከብ" (እስከ ምሽት 1 ሰዓት) ድረስ ይሆናል::
+ነገር ግን ሁሉም እንደ መጠኑ ነውና ከመምሕረ ንስሃ
ጋር ሊጨዋወቱት ይገባል:: በዓቢይ ጾም ለቻለ ቂጣ
በጨው እየበላ: ውሃ እየተጐነጨ ሊጾም ይገባል::
በእነዚህ 55 ቀናትም ከዕለተ ሆሳዕና በቀር ከበሮ
አይጐሰምም:: ጸናጽል አይጸነጸልም:: ተድላ ደስታም
አይደረግም:
እንኳን አደረሳችሁ መልካም የፆም ወቅት🙏🙏
👍 10🙏 2
Show all...
ሰዎች ይጠሉኛል፤ ብናገር አልደመጥም፤ ብማር አይገባኝም? ጨርሳችሁ አዳምጡት ታተርፉበታላችሁ
ተናግረን የማንደመጠው፣ ሰርተን የማናተርፈው፣ ትዳር ጀምረን የማንጨርሰው፤ተምረን የማይገባን፣ በልተን የማንጠግበው፣ ነግደን የማናተርፈው ለምን ይሆን??
👍 6🥰 2