en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 348 subscribers, ranking 1 755 in the Transport category and 2 537 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 348 subscribers.

According to the latest data from 18 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 91 over the last 30 days and by 11 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 41.16%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.44% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 491 views. Within the first day, a publication typically gains 2 060 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 19 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 351
Subscribers
+1124 hours
+477 days
+9130 days
Posts Archive
ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል፡፡ ይህን ተግባር መፈጸም የሁላችንም ኃላፊነት እንደሆነ የሚዘነጋ ጉዳይ አይደለም። መንገዶችን ለብልሽት ከሚዳርጉ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛው ከተፈቀደው ክብደት በላይ በመጫን መጓዝ (Axels load) ነው ። በዚህም ረገድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከባድ ጭነትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ሚዛን ጣቢያዎችን በማቋቋም እንደሚሰራ ይታወቃል። የተሽከርካሪዎችን ክብደት የመቆጣጠር ዋና አላማ በመንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸዉ የአክስል ክብደት መጠን በላይ ጭነዉ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የመንገድ አዉታሮች ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ የመከላከል እንዲሁም መንገዶች እና ድልድዮች ሳይበላሹ ለረዥም ጊዜ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረግ ነዉ፡፡ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የሚዛን ጣቢያዎች እና መገኛ ቦታቸው፡- እስካሁንም 14 ሚዛን ጣቢያዎቸን በተለያዩ ቦታዎቸ ተቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን ፣ መገኛ አካባቢያቸውም፡- ሞጆ ፣ ሆሎታ ፣ ሱሉልታ ፣ ሠንዳፋ ፣ ዲማ (ሰበታ) ፣ ጂማ ፣ ሻሸመኔ አዋሽ ፣ ሠመራ ፣ደንገጎ ፣ ኮምቦልቻ ፣ ጢቅ (ደጅን) ፣ወረታ ፣ ኩይሓ (መቀሌ) ናቸው። አዋሽ 7 የሚገኘው የሚዛን ጣቢያ ከነዚህ ሚዛን ጣቢያዎች አንዱ ነው። ይህ መስመር ከበባድ መኪኖች ከጅቡቲ ወደ መሃል ሀገር የሚመላለሱበት እና በቀን ውስጥ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ ዋና አውራ ጎዳና ነው። በመስመሩ ከተፈቀደው መጠን በላይ በመጫን የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች የሚስተዋሉ ሲሆን ፣ እኛም በመስክ ምልከታችን ወቅት ከመጠን በላይ የጫኑ አሽከርካሪዎች ሲቀጡ ተመልክተናል። የተሽከርካሪዎች ክብደት መቆጣጠር ዋና ዋና ዓላማዎች በትንሹ የሚከተሉት ናቸው፦ • መንገዶች እና ድልድዮች ከልክ በላይ በሆነ ክብደት ምክንያት ማገልገል የሚገባቸውን ጊዜ ሳያገለግሉ ለብልሽት እንዳይዳረጉ ለመከላከል፣ • ከልክ ያለፈ ክብደት መንገዶች እና ድልድዮችን ስለሚጎዳ የጥገና እና የመልሶ ግንባታ ወጪዎችን ለመቀነስ፣ • በትርፍ ጭነት ምክንያት በሰውና በንብረት ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመቀነስ፣ • የእቃዎች ዝውውር ወይም መነሻና መድርሻ ለመቆጣጠር ፣ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በኤዶ-ሴሮፍታ-ወርቃ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ የመስክ ስራ ቅኝት ተካሄደ፡፡ ሻሼመኔ ፣ ሐምሌ 21 ቀን ፣ 2015 ዓ.ም (ኢመአ):- በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ሻሸመኔ አካባቢ የመንገድ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ ቤት ስር ቁጥጥርና ክትትል ከሚደረግላቸው የመንገድ ግንባታ ስራዎች መካከል አንዱ በሆነው 75 ኪሎ ሜትር የኤዶ-ሴሮፍታ -ወርቃ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የመስክ ምልከታ ተደርጓል። ከአጠቃላይ የፕሮጀክቱ የስራ እንቅስቃሴ 67 በመቶ የሚሆነው ስራ መገባደዱን እና ቀጣይ ተግባራትን በተያዘው እቅድ መሰረት ለማከናወን እየተሰራ መሆኑን በመስክ ቅኝታችን ወቅት ተመልክተናል። ግንባታውን እያካሄደ ያለው ሀገር በቀሉ አለማየሁ ከተማ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ጎንድዋና ኢንጅነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማሕበር በማከናወን ላይ ነው ። መንገዱ ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ መሰረተ ልማት ያልተዘረጋበትና በጠጠር መንገድ መንገድ ደረጃ ተሰርቶ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ከሚኖረዉ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አኳያ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ 1.7 ቢልየን ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ በእስካሁኑ አፈፃፀም የጠጠር መፍጨትና ፣ የአፈር ቆረጣ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ ቤዝ ኮርስና ፣ የምርጥ ጠጠር (ካፒንግ) ፣ የሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ የቤዝኮርስ ንጣፍ ፣ የከልቨርትና የስትራክቸርስ ግንባታ እንዲሁም 20 ኪሎ ሜትር የሚሆን የአስፋልት ንጣፍ ተከናውኗል፡፡ በሚቀጥለው 2016 በጀት ዓመት የፕሮጀክቱን ዋና ዋና ስራዎች ለማጠናቅ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በአካባቢው የሚስተዋለው ከፍተኛ ዝናብ ፣ የግብዓት እጥረት ፣ የወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ጉዳዮች ፕሮጀክቱ በታሰበው ፍጥነት ልክ እንዳይጓዝ ያደረገው ቢሆንም እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ፣ የአካባቢው ህብረተሰብና ባለድርሻ አካላት በቅርበት እየሰሩ እንደሚገኙ ታውቋል። መንገዱ በገጠር ከተማ 10 ፣ በቀበሌ ከተማ 12 ፣ በዞን ከተማ 21 እና በወረዳ ደግሞ 14 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው፡፡ የመንገዱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱ የቡና ፣ የገብስ ፣ የስንዴ እና የድንች ምርቶችን የትራንስፖርት መስተጓጎል ሳያጋጥም ወደ ገበያ ለማውጣት ያስችላል፡፡ በዚህም ረገድ የአካባቢውን እና የአጎራባች ዞን ነዋሪዎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ለማፋጠን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል። በተያያዘም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሻሸመኔ አካባቢ ኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ፅ/ቤት ግንባታውን እያከናወነ ከሚገኘው የስራ ተቋራጭ ጋር በመሆን ሐምሌ 21 ቀን ፣ 2015 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አካሂዷል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኦሞ-ሳይ እና ሌፍት ካናል ብሪጅ መንገድ በጥሩ የግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል ጂንካ ፣ ሐምሌ 19፣ 2015(ኢመአ):- የደቡብ ኦሞ እና ቤንች ማጂ ዞኖችን የሚያስተሳስረው የኦሞ-ሳይ እና ሌፍት ካናል ብሪጅ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት በጥሩ የግንባታ ሂደት ላይ ይገኛል። የኦሞ-ማጂ ዲዛይን እና ግንባታ ፕሮጀክት አካል የሆነው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 68 ኪሎሜትር ርዝመትን ይሸፍናል። አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ ከ26 በመቶ በላይ የደረሰ ሲሆን፥ የዲዛይን ፣ የለውጥ መንገድ ግንባታ ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ዮቴክ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ/ማ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አስፋልት ፕላንት ለመትከል የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎች እያደረገ መሆኑ ተመልክቷል። በቀጣይ ዓመት አጋማሽም አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ለመጀመር ዕቅድ ተቀምጧል። ለግንባታው የሚውለው ከ1ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በፌዴራል መንግስት ይሸፈናል። ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ይሠራል። በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚነሳው ግጭት የፈጠረው የጸጥታ ስጋት በግንባታው ሒደት ላይ መስተጓጒል መፍጠሩን በፕሮጀክቱ በተደረገ የመስክ ቅኝት መመልከት ተችሏል። ስጋቱን በዘላቂነት ለመቅረፍ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመኒ ሻሻ ወረዳ መስተዳድር አካላት ጋር ውይይቶችን በማድረግ የጸጥታ አካላት እንዲመደቡ ተደርጓል። በሥራ ተቋራጩ እና አማካሪ መሀንዲሱ በኩል የተስተዋሉ የአፈጻጸም ውስንነቶችን በተመለከተ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከበላይ የስራ ሃላፊዎች ጋር ሰፊ ውይይቶችን በማድረጉ ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በግንባታው ሂደት ላይ አዎንታዊ ለውጦች ታይተዋል። በቀጣይም የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። ግንባታው የአካባቢውን ሥነ ምህዳር ባገናዘበ መልኩ የአካባቢ እና ማኅበራዊ ደኅንነት መርሆዎችን ተከትሎ በጥንቃቄ እየተከናወነ ይገኛል። የፕሮጀክቱ መነሻ ኦሞ ወንዝ የሚያቋርጥበት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በሥፍራው የሚገኙትን የግብርና ምርት ውጤቶች በስፋት ወደ ተለያዩ የገበያ ማዕከሎች ለማድረስ ያስችላል። በተለይም በአካባቢው ለተገነቡ ግዙፍ የስኳር ፋብሪካዎች የማምረቻ ግብዓቶችን እንዲሁም የስኳር ምርት በቤንች ማጂ በኩል ወደ ተለያዪ የሀገራችን ከተሞች በተሻለ ፍጥነት ለማድረስ ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ በተጨማሪም የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎብኝዎች በአካባቢው ወደ ሚገኘው የኦሞ ብሔራዊ ፓርክ የሚያደርጉትን ጉዞ በማቀላጠፍ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት ይጨምራል። የዚሁ ፕሮጀክት ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የሳይ-ማጂ አስፋልት መንገድ ግንባታ ከ98 በመቶ በላይ የተጠናቀቀ ሲሆን፣ የማጠቃለያ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የአሳይታ- አፋምቦ-ጅቡቲ ቦርደር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ይገኛል፡፡ አሳይታ ፣ ሀምሌ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ጅቡቲ ለመሄድ አገልግሎት በመስጠት ላይ ከሚገኘው የጋላፊ መስመር በተጨማሪ እንደ አማራጭ ሆኖ የሚያገለግለው የአሳይታ-አፋምቦ-ጅቡቲ ቦርደር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ይገኛል። የፕሮጀክቱ 86 በመቶ ስራ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን በቅርቡ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በእስካሁኑ አፈፃፀም የአፈር ጠረጋ እና ቆረጣን ጨምሮ 96 በመቶ የስብ ቤዝ ስራ ፣ 54 በመቶ ቤዝኮርስ ሥራዎች ፣ 157 የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ ፣ የስትራክቸር ሥራዎች ፣ የሶስት ድልድይ እና 21 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ የመንገዱን ግንባታ ለማከናወን የተመደበው በጀት 1,691,940,084,78 (አንድ ቢሊዮን ብር ስድስት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ሺህ ሰማንያ አራት ብር ከሰባ ስምንት ሳንቲም) ነው። የግንባታ ወጪው የሚሸፈነውም በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ የመንገድ ርዝማኔ 50 ኪ.ሜ ሲሆን የጎን ስፋቱ ትከሻን ጨምሮ በገጠራማ ሥፍራዎች 10 ሜትር ፣ በወረዳ ከተሞች 19 ሜትር እና በዞን 21 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ፡፡ ግንባታውን እያካሄደ የሚገኘው የስራ ተቋራጭ አሰር ኮንስትራክሽን ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ይዲዲያ እንጂነሪንግ ኮንሰልታንት እያከናወነው ይገኛል። መንገዱ በዋናነት ኢትዮጵያን በአሳይታ በኩል ከጅቡቲ ጋራ በቅርበት ያስተሳስራል። ከዚህ በተጨማሪም አሳይታ ዞንን ከአፋምቦ ወረዳ ብሎም በርካታ ወረዳዎችን እርስበስር በማገናኘት የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን ይበልጥ ያጠናክራል። ይህ አካባቢ የአዋሽ ወንዝ ተፋሰስ የሚገኝበት በመሆኑ በርካታ ምርቶች የሚመረትበት መስመር ነው።ከእነዚህ ምርቶች ውሰጥ ጥጥ ፣ ቴምር ፣ሰሊጥ ፣ቲማቲም ፣ ሽንኩርት ብርቱካን ፣ ሃባብ እና በርካታ ፍራፍሬዎች በስፋት ይመረቱበታል። የዚህ መንገድ መገንባት እነዚህን ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ብሎም ወደ ጀቡቲ ለማድረስ ይበልጥ ያግዛል። በአካባቢው ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረ በመሆኑ ህብረተሰቡ በመንገድ እጦት ምክንያት በእግር እና በግመል ከመጓዝ ውጭ ሌላ አማራጭ አልነበረውም። የአካባቢው ህብረተሰብ በመንገድ እጦት ምክንያት ለበርካታ አመታት የተለያዩ ችግሮችን ሲያስተናግድ የቆየ ቢሆንም አሁን ላይ መንገዱ ደረጃውን ጠብቆ እየተገነባ በመሆኑ ፕሮጀክቱ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረውን ችግር በመቅረፍ ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በከፍተኛ የክብደት መጠን ሳቢያ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የጀማ ወንዝ የብረት ድልድይ በአዲስ መልኩ ተሰርቶ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። ዘጠና አራት ሜትር ርዝማኔ ባለው የብረት ድልድይ ላይ አደጋው ደርሶ የነበረው መጋቢት 27 ቀን ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ነበር። የጉዳቱ ምክንያት ተከታትለው ይጓዙ የነበሩት ሁለት ሲኖትራክ መኪኖች በአንድ ጊዜ በድልድዩ ለማለፍ መሞከራቸው እና ከአቅም በላይ የሆነ ክብደት በድልድዩ ላይ ማረፉ እንደሆነ ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ለችግሩ አፋጣኝ መፍትሄ ለመስጠት ይቻል ዘንድ በውስጥ አቅም እና ድልድዩ በሚገኝበት አካባቢ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እያካሄዱ የሚገኙ የስራ ተቋራጮችን በማስተባበር ላለፉት ሶስት ወራት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ከዚህ ቀደም የነበረው የድልድዩ ስፋት 3.2 ሜትር ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት 4.2 ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው ድልድዩ በአዲስ መልኩ ሊሰራ የቻለው፡፡ ተቋሙ በ24 ሰዓታት ውስጥ ተለዋጭ መንገድ በመስራት ለችግሩ ጊዜያዊነት መፍትሄ ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት ከዚህ ቀደም የነበረውን ድልድይ በማንሳት እና አዲስ ተጨማሪ ተሸካሚ ምሰሶ (Pier) በመገንባት ስራው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል፡፡ የክረምት ወቅት መሆኑ እና የወንዙ መጠን መጨመር ከዚህ ቀደም የነበረውን ድልድይ በማንሳት ፣ አዲስ ተጨማሪ ተሸካሚ ምሰሶ (Pier) ገንብቶ ስራውን በአፋጣኝ ለማጠናቀቅ እንዳይቻል ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጥሮ የነበረ ቢሆንም ፤ አስፈላጊው ግብዓትና የሰው ሃይል ተመድቦ ሌት ተቀን ከፍተኛ እንቅስቃሴ በመደረጉ የድልድዩ ስራ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሊሆን ችሏል፡፡ መንገዱን የሚጠቀም አሽከርካሪ በድልድዩ ላይ ከአርባ ቶን በላይ ጭኖም ሆነ ተከታትሎ ወይም ደርቦ ማለፍ የማይቻል መሆኑን በመንዘብ ሃላፊነቱን እንዲወጣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል!!! በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የቢሾፍቱ-ጨፌ ዶንሳ-ሰንዳፋ 55 ነጥብ 14 ኪሎሜትር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ በመከናወን ላይ ነው፡፡ በእስካሁኑ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም የአፈር፣ የሰብ-ቤዝ፣የቤዝ-ኮርስ፣የአስፓልት፣የድልድይ፣ የግንብ፣የጠጠር መፍጨት እና ሌሎች ተያያዥ ስራዎች በመከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን ቀጣይ የግንባታ ምዕራፍ በተያዘለት ጊዜ ለማከናወን የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በአሁኑ ወቅት እየተደረጉ ናቸው፡፡ በመንገዱ ግንባታ የስራ ተቋራጩ አቅም ውስንነት፣የወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ ፣የወሰን ማስከበርና ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች በወቅቱ ባለመጠናቀቃቸው ፕሮጀክቱ በታሰበው ፍጥነት እንዳይከናወን አድርጎታል፡፡ የወሰን ማስከበርና ቀሪ የካሳ ክፍያዎችን በአጭር ጊዜ በመፈፀም በተለይም የስራ ተቋራጩ አስፈላጊ የግንባታ ግብዓቶችን እና ማሽነሪዎችን አስገብቶ በሙሉ አቅሙ እንዲሰራ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ይህ ክትትልና ድጋፍም ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ፡፡ በክረምት ወራት የተጎዳውን የመንገዱ ክፍል ተገቢውን ጥገና በመስጠት ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ ተገቢው ትኩረት ይደረጋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ በገጠር ከተማ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር ፣በቀበሌ ከተማ 12 ሜትር ፣በወረዳ ከተማ 21ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱን ግንባታ ራማ ኮንስትራክሽን ፒ. ኤል .ሲ 914,847,890.47 ( ዘጠኝ መቶ አስራ አራት ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ ሰባት ሺ ስምንት መቶ ዘጠና ብር ከ አርባ ሰባት ሳንቲም) በሆነ ወጪ እየገነባው የሚገኝ ሲሆን ኋይትናይት ኮንስትራክሽን ከስትራይድ ኮንስልቲንግ ጋር በጥምረት የማማከር እና የቁጥጥሩን ስራ እየተከታተሉት ነው፡፡ የቢሾፍቱ-ጨፌ ዶንሳ-ሰንዳፋ የመንገድ ፕሮጀክትን ለመገንባት የሚውለው ወጪ የተሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ መንገዱ በዋናነት የቢሾፍቱ ከተማ መስተዳደር፣ጨፌ ዶንሳ ወረዳን፣በረክ ወረዳን፣አለልቱ ወረዳን እና የሰንዳፋ ከተማ መስተዳደር በቅርበት ያገኛኛል፡፡ መንገዱ ሲጠናቀቅ የአካባቢውን ማህበራዊ እድገት በማፋጠን ጥራት ያለዉ ፣ምቹ እና ፈጣን የሆነ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር እና በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን እንደ ጤፍ ፣ስንዴ ፣ምስር እና የነጭ ሽንኩርት ምርቶችን በማጓጓዝ የንግድ እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍ ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተያዘው ዕቅድ መሠረት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ። በዛሬው ዕለት በተካሄደው መርኃ-ግብር በ
+3
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ በአንድ ጀምበር 500 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል በተያዘው ዕቅድ መሠረት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ። በዛሬው ዕለት በተካሄደው መርኃ-ግብር በሁሉም የጥገና በዲስትሪክቶች እና ሴክሽኖች፣ በመስሪያ ቤቱ ማሰልጠኛ ተቋማት፣ በምርምር ማዕከላት ፣ በተለያዩ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች እና በሞጆ-ሃዋሳ የፍጥነት መንገድ ግራና ቀኝ አቅጣጫ የተቋሙ ሰራተኞች እና የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ ተቋሙ በተመሳሳይ ከሐምሌ 4 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ "ነገን ዛሬ እንትከል" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር መሰረት በማድረግ በተመረጡ አካባቢዎች የተለያየ ዝርያ ያላቸውን ችግኞች ተከሏል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መላው አመራርና ሰራተኞቹን በማስተባበር ባለፉት አራት ዓመታት በተለያዩ አካባቢዎች ችግኞችን በመትከል እየተንከባከበ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጉራጌ፣ ስልጤ እና ሀዲያ ዞኖችን የሚያገናኝው የአጣጥ ማዞሪያ-ጉንችሬ-ቆሴ-ጌጃ-ሌራ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በሦስት ዓመት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። ፕሮጀክቱ ጠቅላላ 97 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው። ከዚህ ቀደም ከአፈጻጸም ውስንነት ጋር በተያያዘ መንገዱ የመዘግየት እክል ገጥሞት የነበረ ቢሆንም፣ ችግሮቹ መፍትሄ በማግኘታቸው ግንባታውን በሦስት ዓመት ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ነው። አሁን ላይ የተለዋጭ መንገድ ጥገና፣ የጠረጋና ምንጣሮ፣ የአፈር ቆረጣ፣ የተመረጠ አፈር ሙሌት እና ድልዳሎ ሥራ እየተሠራ ይገኛል። እንዲሁም በሰብ ቤዝ እና ቤዝ ኮርስ ደረጃ ላይ የደረሱትን የመንገድ ክፍሎች ለቀጣይ የግንባታ ምዕራፍ ዝግጁ የማድረግ ሥራዎችም እየተከናወኑ ነው። የመንገድ ግንባታውን በብር 5,106,525,941.61(አምስት ቢሊዮን አንድ መቶ ስድስት ሚሊዮን) በሆነ የገንዘብ መጠን፣ ሀገር በቀሉ ዓለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ያከናውናል። ወጪው በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል። አይዲኮን ኢንፍራስትራክቸር ዴቨሎፕመንት አማካሪ ኃ.የተ. የግ. ማ.፣ ግንባታውን በማማከር እና በመቆጣጠር ይሳተፋል። ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም በኅብረተሰቡ በኩል የሚነሱ ጥያቄዎችን ባገናዘበ መልኩ የተለያየ የዲዛይን ማሻሻያ ተደርጎለታል። በማሻሻያው መሠረት የሀይማኖት እና የጤና እና ተቋማትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ተጨማሪ የ15 ኪ.ሜ አገናኝ መንገድ የሚገነባ ይሆናል። በተጨማሪም ግንባታው አነስተኛ እና ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፣ ከልቨርቶችና ድልድዮችን ያካትታል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከሦስቱ ዞኖች በተጨማሪ ቸሃ፣እነሞር፣እኖር ኤነር እና መገር፣ እንደጋኝ፣ አመካ እና ምዕራብ አዘርነት ወረዳዎችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ በማስተሳሰር የሕዝብ ለሕዝብ ትስስሩን ያሳልጣል። በአካባቢው የሚገኙትን የተለያዩ የግብርና ምርት ውጤቶች በስፋት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የጎላ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይኖረዋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መንገዱ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቅቆ አገልግሎት መስጠት እንዲችል የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ ያደርጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የወራቤ-ቦዠባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው በደቡብ ክልል ስልጤ ዞን፣ ወራቤ ከተማ አስተዳደር እና አሊቾ ወረዳ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው ፕሮጀክቱ ጠቅላላ 41 ነጥብ 3 ኪ.ሜ ርዝማኔ ያለው ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የሚገነባው፡፡ ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም ከአፈጻጸም እጥረቶች ጋር በተገናኘ ሲጓተት የቆየ ቢሆንም ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። አሁን ላይ መንገዱን ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ የሚያስችሉ የተለዋጭ መንገድ እና የተለያዩ የጥገና ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። ከዚህም በተጨማሪ የሥራ ተቋራጩ፣ የክረምቱ ወራት እንደተገባደደ በሙሉ አቅም ወደ ግንባታ ለመሸጋገር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችንም በማከናወን ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ አነስተኛ እና ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች እና ከልቨርቶች ሥራ ያካትታል፡፡ ግንባታውን የአማራ መንገድ ሥራዎች ድርጅት እያከናወነ ይገኛል። ለፕሮጀክቱ የሚውለው ብር 2,777,252,904.36 (ኹለት ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰባ ሰባት ሚሊዮን) በፊደራል መንግስት በጀት ነው የሚሸፈነው፡፡ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ይሠራል። የወራቤ-በዥባር አስፋልት ኮንክሪት መንገድ፣ መነሻውን ከወራቤ ከተማ አስተዳደር በማድረግ በዋናነት አልቾውሪሮ እና ቀበት ወረዳዎችን በቅርበት በማገናኝት ጠረጋ ድረስ ይዘልቃል፡፡ መንገዱ በከተማ 21.5 ሜ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር10 ሜትር የጎን ስፋት አለው፡፡ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም ወደ ወልቂጤ እና ጅማ ለመሄድ በቡታጅራ በኩል የሚደረገውን አድካሚ እና ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት ቀጥታ በወራቤ-ቦዠባር በኩል ለመጓዝ ያስችላል፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የእንሰት ውጤቶች፣ ጎመን እና ሌሎች የግብርና ምርት ውጤቶች በፍጥነት እና በጥራት ወደ ማዕከላዊ የገበያ ሥፍራ ለማድረስ ያስችላል፡፡በተጨማሪም በሥፍራው የሚገኙትን አነስተኛ መንደሮች ወደ ከተማነት የሚያድጉበት ምቹ ዕድል ይፈጥራል፡፡ ፕሮጀክቱ በቀመጠለት የጊዜ ገደብ እና ጥራት እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተገቢውን ድጋፍ እና ትብብር ያደርጋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et