en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 373 subscribers, ranking 1 753 in the Transport category and 2 530 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 373 subscribers.

According to the latest data from 20 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 129 over the last 30 days and by 8 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 38.47%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.24% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 143 views. Within the first day, a publication typically gains 2 037 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 22 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 373
Subscribers
+824 hours
+697 days
+12930 days
Posts Archive
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የጀመራቸውን የብቃት ሞዴል ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያግዙ የቴክኖሎጂ አቅርቦት የማእቀፍ ስምምነቶችን ዛሬ ከመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (INSA) ጋር
+2
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የጀመራቸውን የብቃት ሞዴል ስራዎችን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር የሚያግዙ የቴክኖሎጂ አቅርቦት የማእቀፍ ስምምነቶችን ዛሬ ከመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (INSA) ጋር ተፈራረመ። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአሁኑ ወቅት ለስራ ምቹ የሆነ አካባቢን በመፍጠር የተለያዩ ተቋማዊ ለውጦችንና የአሰራር ማሻሻያ የብቃት ሞዴሎችን ተግባራዊ ማድረጉን ቀጥሏልን። በዛሬው ዕለት የተካሄደው የውል ስምምነት ፊርማም የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን የሰው ሃይል አቅም በተለይም በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ይበልጥ ለማዘመንየሚያስችል ነው። በዚህም ኢንሳ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን አስመልክቶ ድጋፍ ማድረግ የሚቻልባቸው ዘርፎችን በመለየት ኢመባን ያግዛል፡፡ በውል ስምምነቱ ውስጥ የተካተቱትን ተግባራት በአጭር ጊዜ ፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል ። የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ አጠቃላይ የተደረሰው ስምምነት ተቋሙን የማዘመን አገልግሎትን ተደራሽ የማድረግና ብክነትና መሰል የአገልግሎት አሰጣጥ መሰናክሎችን በዘመናዊ መልኩ ለመተካት የሚረዳ ነው ብለዋል። ኢመባ ዘርፈ ብዙ የማሻሻያ እርምጃዎችን እየወሰደ መሆኑን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ ከኢንሳ ጋር የተደረሰው ስምምነት ይህንኑ ተፈጻሚ በማድረግ ውጤታማ ስራዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ እውን ለማድረግ ሚናው የላቀ ነው ብለዋል። የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሹመቴ ግዛው በበኩላቸው በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለው ግንኙነት ውጤታማና ተመጋጋቢ ለመሆን ይችል ዘንድ ፕሮጀክቱን በተባለው የጊዜ ገደብ ለመፈፀም ተቋማቸው እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። ኢመባ ዘርፈ ብዙ ለውጦችን እያካሄደ መሆኑን ተከትሎ የትብብር ስምምነቱ ዘላቂ ሀገራዊ ስራዎችን ለመከወን ይረዳል ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የ2012 በጀት አመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ዛሬ ገምግሟል ፡፡ በሶስተኛው የሩብ አመት የእቅድ አፈጻጻም የቪዲዮ ኮንፈረንሱ ላይ የተ
+6
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የ2012 በጀት አመት የ9 ወራት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን በቪዲዮ ኮንፈረንስ ዛሬ ገምግሟል ፡፡ በሶስተኛው የሩብ አመት የእቅድ አፈጻጻም የቪዲዮ ኮንፈረንሱ ላይ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ዳይሬክተሮች አማካሪዎችና የቡድን መሪዎች ታድመዋል። ባለፋት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የመደበኛ ስራዎች አፈጻጸም ፣ የማሻሻያ ስራዎች ክንውን ፣ የለውጥ ስራዎች አተገባበር እና ሌሎች ተያያዥ ስራዎችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ቀጣይ አቅጣጫን ያመላከተ ሪፖርት ቀርቦ በኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች ምክክር ተካሂዶበታል። በዚህም ረገድ በኢ.መ.ባ ባሳለፍነው 9 ወራት በዋና መንገዶች ማጠናከርና ደረጃ ማሻሻል 77 ኪ .ሜ መንገድ እና በአገናኝ መንገዶች ደረጃ ማሻሻልና ግንባታ እንዲሁም በመንገዶች ከባድ ጥገና 1 ሺህ 183 ኪ .ሜ ተሰርቷል፡፡https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/4252273724813585

የሻምቡ-ባኮ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ስራ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ፡፡ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ ዞኖችን በአቋራጭ የሚያገናኘው የሻምቡ-ባኮ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል ፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጅክቱ የሚገኘው በኦሮምያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ሲሆን ፣ አጠቃላይ የግንባታ ስራው 993,280,400 (ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሶስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰማንያ ሺህ አራት መቶ) ብር ወጪ ጠይቋል፡፡ ግንባታውን ሲያካሂድ የቆየው የቻይናው ሲጂሲ ኦቨርሲስ አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የግንባታውን የማማከርና የቁጥጥር ስራ ሲያከናውኑ የቆዩት ደግሞ የሊባኖሱ ካህቲብና አላሚን ኢንጂነርስ ፣ ኤኤል(AL) እና ሀገር በቀሉ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ የተባሉ አማካሪ ድርጅቶች በጋራ በመሆን ነው፡፡ 60.2 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በኦሮምያ ክልል ውስጥ የሚገኙ ዞኖችን በተለይም የሆሮ ጉድሩ ወለጋን እና የምዕራብ ሸዋ ዞኖችን ለማገናኘት የሚያስችል ነው፡፡ ይህ መስመር ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልተዘረጋበትና በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ ሲሆን ፣ ከመንገድ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር ታይቶ በአሁኑ ወቅት ደረጃው ወደ አስፋልት ኮንክሪት እንዲያድግ ተደርጓል፡፡ መንገዱ በወረዳ ከተማ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 19 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት አለው፡፡ የፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ ወጪ የተሸፈነውም ከአረብ ባንክ (ባድያ) ፣ ከኦፌድና ከኢትዮጵያ መንግስት በተገኘ በጀት ነው፡፡ የመንገዱ መገንባት በአካባቢው ለሚገኙ ነዋሪዎች ፣ አጎራባች ዞኖች እና ወረዳዎች ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከፊንጫ ስኳር ፋብሪካ የሚመረቱ የምርት ውጤቶችን በአቋራጭ ወደ ገበያ ማዕከላት እንዲቀርቡ ከማስቻል አንፃር የሚኖረው ጠቀሜታ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡

የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ መንገድ ስራ በአፋጣኝ ችግሮቹ ተቀርፈው ፕሮጀክቱ እንዲጠናቀቅ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የመስክ ቅኝት ዛሬ ተካሂዶል ፡፡ በመስክ ቅኝቱ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ ፥ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ፣ የአካባቢው የመስተዳድር አካላትን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትም ታድመዋል ፡፡ የስራ ኃላፊዎቹ በጉብኝታቸው ወቅት የሳንሱሲ- ታጠቅ - ኬላ 13.56 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ ያለበትን አጠቃላይ ደረጃ እና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶች በቦታው በመገኘት ተዟዙረው ተመልክተዋል ፡፡ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የመንገዱ ግንባታ ላይ ያለው እንቅስቃሴ መነቃቃት እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል ። በቀጣይም የክረምት ወቅት እየተቃረበ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጉላላ ተቋራጩ ተጨማሪ የስራ ሰዓት ተጠቅሞ ግንባታውን አንዲያፉጥንም አቅጣጫን አስቀምጠዋል። የመንገዱ ስራ ተጠናቆ ተገቢውን ግልጋሎት መስጠት እንዲችል በመንገዱ ወሰን ክልል ውስጥ ያሉ የመኖርያ ቤቶች እና የዩቲሊቲ ተቋማት (ኤሌክትሪክ ፖል ፣ የቴሌ ኦፕቲክ ፋይበር እና የውሃ መስመር ) በወቅቱ እና ሙሉ ለሙሉ እንዲነሳ የሚመለከታቸው አካላት ትብብር እንዲደረጉ ጥሪ አቅርበዋል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የወሰን ማስከበር ውስብስብና አስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ያለ በመሆኑ አፈጻጻሙ የሚጠበቀውን ያህል እንዳይሆን ምክንያት እንደሆነም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። አሁንም የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን ለማፍጠን መሰናክል የሆኑ የወሰን ማስከበር ስራዎች ያልተጠናቀቁ በመሆናቸው ከሚመለከታቸው የስራ ሃላፊዎች ጋር በቅርበት እንደሚሰራም ተናግረዋል። የቡራዩ ከተማ አስተዳደር ፤የአካባቢው ነዋሪ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እያደረጉ ያሉት ድጋፍ የሚበረታታ ሲሆን ፤ ቀሪ ችግሮችን ፈቶ መንገዱ ፍጻሜውን እንዲያገኝ ትብብራቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ ጠይቀዋል። በህዳር ወር 2010 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው መንገዱ በእስካሁኑ ስራ የአፈር ሙሌትና ድልዳሎ፣የውሃ መፋሰሻ ቱቦ ቀበራ እና 16 ሜትር ርዝመት ያለው የገፈርሳ ወንዝ ድልድይ ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ከዚህም በለፈ በወሰን መስከበር ነጻ በሆኑ የመንገዱ ግራ እና ቀኝ በአንዱ አቅጣጫ የአስፋልት ማንጠፍ ስራው መከናወኑን ቀጥሏል። ፨ስለፕሮጀክቱ ተጨማሪ መረጃ እና ፋይዳዎቹ፨ የሳንሱሲ - ታጠቅ - ኬላ ፕሮጀክት ከ 820 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገባ ያለ መንገድ ነው፡፡ ግንባታው በአገር በቀል ተቋራጩ አሰር ኮንስትራክሽን እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል ፡፡ ሂትኮን እና አለርት ኢንጅነሪንግ የግንባታ ስራውን በአማካሪነት እና በተቆጣጣሪነት እያገለገሉ ይገኛሉ ፡፡ ከሁለት አመት በፊት የተጀመረው ፕሮጀክቱ ተግዳሮቶቹ ተቀርፈው ግንባታው በአንድ አመት ጊዜ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል ፡፡ የሳንሱሲ- ታጠቅ -ኬላ የቀድሞ መንገድ ከ7 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋትና በአገልግሎት ብዛት ሳብያ ለከፍተኛ ጉዳት ተዳርጎ የነበረ ነው። የመንገድ መስመሩ ከሚያሰተናገደው የተሸከርካሪ ብዛትና መጨናነቅ አኳያ እንዲሁም ከከተማው ቀጣይ አድገት መነሻ ስፋቱ እንዲጨመር ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል ፡፡ በዚህም መሰረት ከፕሮጀክቱ መነሻ እሰከ 7 ኪ.ሜ እና በፕሮጀክቱ መጨረሻው ክፍል ማለትም ከኪሜ 11.5 እሰከ ኪሜ 13.54 ድረስ ያለው በ32 ሜትር የጎን ስፋት እየተገነባ ነው ፡፡ የተቀረው በመካካል ያለው የመንገዱ ክፍል ደግሞ በ21 ሜትር ስፋት ይይዛል፡፡ መንገዱ በዚሀ ደረጃ ሲሰፋ በውስጡ በግራና ቀኝ 4 ተሸከርካሪ የሚያስተናግድ አቅም ይኖረዋል ፡፡ በተጨማሪም በውስጡ የመንገድ አካፋይ ፣ እግረኛ መሄጃ እና የመንገድ አቃፊ ትከሻ በግራ እና በቀኝ ያካተተም ይሆናል ፡፡ የመንገዱ ሲጠናቀቅ ከዚህ ቀደም የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ይከሰት የነበረውን መጉላላት በማስቀረት የተሳለጠ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር የጎላ ሚና ይኖረዋል ፡፡ ከአዲስ አበባ ጋር በመተሳሰር እንደ ሳንሱሲ፣ታጠቅና ኬላ አካባቢ ያሉ ብዛት ያላቸው ነዋሪዎችም አመቺ እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ፡፡ ከዚህም ባለፈ የምዕራቡ የኢትዮጵያ ክፍል የወጪ ገቢ ንግድ ኮሪደር የሆነውን ከአዲስ አበባ - ነቀምት - አሶሳ ያለው ዋና መንገድ በአሸዋ ሜዳ በታጠቅ በኩል ይጠቀሙ የነበሩትን ብዛት ያላቸው ተሸከርካሪዎች ላይ ይፈጠር የነበረውን መጨናናቅ ፤ የሳንሱሲ - ታጠቅ - ኬላ መንገድ ሁነኛ አማራጭ ሆኖም ያገለግላል ፡፡ #በኢሳያስ መብራቱ

በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘውን የሞጆ - ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ዛሬ በመሰክ የስራ ስምሪት ተቃኝቷል፡፡ በአራት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተገነባ የሚገኘውን የ202.6
+2
በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኘውን የሞጆ - ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ በከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ዛሬ በመሰክ የስራ ስምሪት ተቃኝቷል፡፡ በአራት ምዕራፍ ተከፍሎ እየተገነባ የሚገኘውን የ202.6 ኪ.ሜ የፍጥነት መንገድ ግንባታ እንቅስቃሴ ያለበትን ደረጃ ለመመልከት ነው የስራ ሃላፊዎቹ በዕለቱ ጉብኝት ያደረጉት ፡፡ በመስክ የስራ ቅኝቱም የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ የተቋሙ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎችን ጨምሮ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ተቆጣጣሪዎችም ታድመዋል ። በጉብኝቱ ወቅት የሞጆ - ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ስራ ያለበት አጠቃላይ ደረጃ እና እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶች ለሚኒስትር ዴኤታው ገለጻ ተደርጎላቿል ፡፡ በዚህም መሰረት ኮንትራት አንድ እና ሁለት የፕጀክቱን 88 እና 81 በመቶ የግንባታ ስራ ያጠናቀቁ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው። የአዲስ አበባ -ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሞጆ-ሀዋሳ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክትከ 13.7 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡ 32 ሜትር የመንገድ ስፋት ያለው ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በግራና በቀኝ በአንድ ግዜ 4 ተሸከርካሪዎችን ማስተናገድ የሚችል ይሆናል ፡፡ https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/4203063396401285

ከ11 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሰባት መንገዶችን ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ፊርማ ተካሄደ ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከ11 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሰባት መንገዶችን በአስፋልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ፊርማ አካሄደ ፡፡ ሰባቱ የተፈረሙት መንገዶች በጥቅሉ 509.11 ኪ.ሜ ርዝማኔ አላቸው ፡፡ ለግንባታቸው የሚውለው ከ11 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው ፡፡ በዛሬው ዕለት የመንገድ ውል ስምምነት ፊርማ የተካሄደላቸው መንገዶች ዝርዝር 1. ደብረብርሃን - ደነባ -ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር -ደነባ 2. ፊቅ - ሰገግ - ገርቦ ደነን (ሎት ሶስት. ዮአሌ-ደነን ) 3. ሁምቦ - ጠበላ - አባያ 4. ዳዬ - ግርጃ - ክብረመንግስት (መልካደስታ) እና መለያ - መጆ መገንጠያ 5. ጅግጅጋ - ገለለሽ - ደገሃምዶ -ሰገግ (ኮንትራ ሁለት እና ሶስት ) 6. ሀወላቱላ-ወተራራሳ-ያዩ-ውራቼ 7. ዛላምበሳ - አሊቴና- መረዋ - እዳጋሃሙስ ( ሎት አንድ. ዛላምበሳ - አሊቴና መገንጠያ ) ናቸው ፡፡ መንገዶቹን ለመገንባት ጨረታውን አሸንፈው ከባለስልጣን መሥሪያቤቱ ጋር የውል ስምምነት ፊርማ ያደረጉት ስድሰቱ አገር በቀል ተቋራጮች ሲሆኑ አንዱ የውጭ ስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ ተቋራጮቹ የተረከቧቸውን መንገዶች ገንብቶ ለማጠናቀቅ ከሶስት ዓመት እሰከ አራት አመት የጊዜ ገደብ ተሰጥቷቸዋል ፡፡ አሁናዊ የመንገዶቹ ይዞታ ደረጃ ጠጠር ሆኖ ለትራንስፖርትም አመቺ ያልሆነ ሲሆን በቀጣይ ደረጃቸው ወደ በአስፋልት ደረጃ የሚያድግ ይሆናል ፡፡https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/4198980586809566