en
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Open in Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Channel ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 13 307 subscribers, ranking 1 759 in the Transport category and 2 546 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 13 307 subscribers.

According to the latest data from 15 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 88 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 40.23%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.41% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 352 views. Within the first day, a publication typically gains 2 050 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 17.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 16 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Transport category.

13 307
Subscribers
+224 hours
+297 days
+8830 days
Posts Archive
የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በመካሄድ ላይ ነው ምሥራቅ ጉራጌ ዞን፣ ጥር 17/2018 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የቱሉ ቦሎ - ኬላ የመንገድ ፕሮጀክት የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በመካሄድ ላይ ነው። በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ-መሥተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፣ የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስትር ደኤታ የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር)፣የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደርየኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ም/ዋና ዳይሬክተር ብርሃኑ ተስፋዩ (ኢንጅነር) ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የመንግሥት የሥራ ኅላፊዎች ተገኝተዋል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ሲኾን፥ 81 ኪሎሜትር ይሸፍናል። የመንገድ ግንባታውን የቻይናው ሁናን ሁንዳ አከናውኖታል። ሀገር በቀሉ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ተሳትፏል። ለፕሮጀክቱ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግሥት ወጪ ተደርጎበታል። የመንገድ ፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የኅብረተሰቡን የረጅም ጊዜ ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ከመኾኑም ባሻገር፣ በርካታ ማኅበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ ጠቀሜታዎችን ያበረክታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ ያሉ ጫናዎችን ደረጃ በደረጃ ለማቃለል ጥረት እየተደረገ ነው:- ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራሕማን (ኢንጅነር) አዲስ አበባ፣ የመንገድ ፕሮጀክቶች ላይ ያሉ ጫናዎችን ደረጃ በደረጃ ለማቃለል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመኾን ጥረት እየተደረገ ነው ሲሉ የኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራሕማን (ኢንጅነር) ተናግረዋል። ዋና ዳይሬክተሩ ይኽንን ያሉት የኮንስትራክሽን ዘርፍ ተግዳሮቶቹ እና ቀጣይ እጣ-ፈንታዎቹ በሚል ርዕስ ከዘርፉ የባላድርሻ አካላት ጋር በተቋማችን የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደ የውይይት መድረክ ላይ ነው። በዚሁ ወቅት በቀረበ ጥናት፥ መዋቅራዊ/የዘርፍ፣ ተቋማዊ/የውስጥ እንዲሁም በሥራ ተቋራጮች እና አማካሪ ድርጅቶች በኩል ያሉ ችግሮች የኮንስትራክሽን ዘርፉ መሠረታዊ ማነቆዎች መኾናቸው ተገልጿል። ከመዋቅር ጋር በተያያዘ የግብዓት ዕጥረት እና ዋጋ መናር የጸጥታ ስጋቶች፣ ብቁ እና ተወዳዳሪ የሀገር ውስጥ የሥራ ተቋራጮች እጥረት እንዲሁም ሙስና እና ተጠያቂነት አለመስፈን ቀዳሚ ችግሮች መኾናቸው ተነስቷል። ተቋምን በሚመለከት የፕሮጀክት አመራር እና አሥተዳደር ክፍተቶች፣ የኮሙኒኬሽን ክፍተቶች እና የሰለጠነ ባለሞያ እጥረት በዋናነት ተጠቅሰዋል። በሥራ ተቋራጮች በኩል ደካማ የሰው ሃብት አመራር፣ የአፈጻጸም እና የአቅም እጥረቶች መኖራቸው ጥናቱ አመላክቷል። እነዚህ ጫናዎች ፕሮጀክቶች ለተጨማሪ የጊዜ እና የገንዘብ ጭማሪዎች እንዲጋለጡ እንዲሁም የጥራት መጓደል ችግሮች እያስከተሉ መኾናቸውን ጥናቱ አትቷል። ችግሮቹን ለመቅረፍ ጥረቶች መደረጋቸው የተጠቆመ ሲኾን፥ የዋጋ ልዩነት ማስተካክያ ጣሪያው (price cap) መነሳቱ፣ በጸጥታ ምክንያት ቆመው ከነበሩት ፕሮጀክቶች ውስጥ 10 ያህሉ ወደ ግንባታ እንዲመለሱ መደረጉ፣ ሀገር-በቀል የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች አጠቃላይ በግንባታው ዘርፍ ላይ አዎንታዊ ለውጥ ማምጣታቸውን ጥናቱ ይፋ አድርጓል። ውይይቱ ላይ የተገኙ ሀገር-በቀል የሥራ ተቋራጮች እና አማካሪ ድርጅቶች በበኩላቸው፤ የነዳጅ እጥረት፣ የክፍያ መዘግየት፣ ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ ያሉ የግንዛቤ ክፍተቶች መኖራቸውን አንስተዋል። በጉዳዩ ላይ ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራሕማን (ኢንጅነር) ምላሽ የሰጡ ሲኾን፥ ችግሮችን እንዳሉ እንገዘባለን፥ ጫናዎቹን ደረጃ በደረጃ ለመቅረፍ እና ፕሮጀክቶችን በሚፈለገው ፍጥነት ለማከናወን በዕውቀት እና በጥናት ላይ የተመሠረተ ጥረት እናደርጋለን ብለዋል። ችግሮቹ ውስብስብ በመሆናቸው በመንግሥት ወይም በጥቂት ግለሰቦች ብቻ የሚፈቱ ባለመሆናቸው፣ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመቀናጀት እና በመቀራረበ መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል። የዘርፉ ተዋንያን፥ ችግር አለ ተብሎ ራስን ከኅላፊነት ከማሸሽ ይልቅ በሙያዊ ብቃት እና ሥነ-ምግባር እንዲሁም በተጠያቂነት ስሜት ፕሮጀክቶችን በተቀመጠው ጊዜ እና የጥራት ደረጃ መፈጸም እና ለአገልግሎት እንዲውሉ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው የተቋማችን ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራሕማን በጥብቅ አሳስበዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢንስታግራም https://www.instagram.com/ethioroads › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመሥክ ጉብኝት አካሄደ አዲስ አበባ፣ ጥር 13፣ 2018 (ኢመአ) የከተማ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮ - ጅቡቲ ትራንስፖርት ኮሪደር አካል በሆነው በአዳማ- ኪሜ 60 (መልካጂሎ) የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት ላይ የመሥክ ጉብኝት አካሂዷል። በጉብኝቱ ላይ የትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሀመድ አብዱራህማን እና የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የጉብኝቱ ትኩረት የአዳማ - ኪሜ 60 (መልካጂሎ) ፈጣን መንገድ አጠቃላይ የግንባታ ሂደት አፈፃፀም ለመገምገም ያለመ ነው። ቋሚ ኮሚቴው የመንገዱን አሁናዊ የግንባታ እንቅስቃሴዋችን ፣የመንገዱ የጥራት ሁኔታ የሚረጋገጥበት የላቦራቶሪ ክፍል እንዲሁም የመንገዱ አካል የሆኑትን የድልድዮችን ግንባታን ተመልክተዋል። ከጉብኝቱ በኋላም ቋሚ ኮሚቴው ከኢመአ የሥራ ኃላፊዎች ጋር መንገዱን የሚመለከት ምክክር በአዳማ ከተማ አከናውነዋል ። በምክክሩም ላይ የቋሚ ኮሚቴ አባላት በሀገሪቱ ከፍተኛውን የገቢና የወጪ እንቅስቃሴ ለማከናወን ከፍተኛ ድርሻ ያለው የዚህን መንገድ የግንባታ ሥራ ማፍጠን የሚቻልበትን ሁኔታ፣ ከወሰን ማስከበር ፣ከግብዓት እጥረቶች ፣ ከፀጥታ ጉዳዮች እና ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች አንስተዋል። የተነሱትን ሀሳቦች አስመልክቶም በፕሮጀክቱ ያጋጠሙ ችግሮች  አሁን ላይ መፍትሄ  አየተሰጣቸው  የሚገኝ  በመሆኑ የመንገዱ ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ  በትኩረት  እየተሰራ  እንደሚገኝ  የኢትዮጵያ  መንገዶች አስተዳደር ዋና  ዳይሬክተር  ኢንጅነር  መሀመድ አብዱራህማን  ገልፀዋል። አያይዘውም  ፕሮጀክቱን  በሚፈለገው ልክ ለማከናወን በቋሚ ኮሚቴው በኩል የተነሱትን ጥያቄዋችና አስተያየቶች ጠቃሚ ግብዓቶች መሆናቸውን ጠቅሰው የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ ይሰራል ብለዋል፡፡ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ፕሮፈሰር መሀመድ አብዶ በበኩላቸው መንገዱ ከፍተኛ ትኩረትና ድጋፍ የሚያስፈልገው በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ትብብር እንደሚያስፈልግ በአፅንኦት ገልፀዋል።ቋሚ ኮሚቴው ለመንገድ መሰረተ ልማት የሚያደርገው አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

የበሻሻ - ጌራ  የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት  ለማፋጠን  እየተሰራ ይገኛል ጅማ፣ ጥር 12፣ 2018 (ኢመአ):- 31 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የበሻሻ -ጌራ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ለማፋጠን  እየተሰራ  ይገኛል። በግንባታው  የሥራ  ሂደት  ላይም  የአፈር ቆረጣና  ሙሌት፣የቁፋሮ ፣ የውኃ  ማፋሰሻ ቱቦ  ግንባታና  ቀበራ  ሥራዎች  በመከናወን  ላይ የሚገኙ  ሲሆኑ ፤ይህንንም  በአጭር ጊዜ ውስጥ  በማጠናቀቅ  ፕሮጀክቱን  ወደ ቀጣዩ የግንባታ ምዕራፍ ለማሸጋገር ጥረት  እየተደረገ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች  አስተዳደር  የራስ  ሀይል  ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት የመንገዱን  ግንባታ  እያከናወነው የሚገኝ ሲሆን ኦሜጋ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ህ/የተ/የግል ማህበር ደግሞ የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ  እየሰራ ይገኛል። በኢትዮጵያ  መንግስት 3 ነጥብ 58 ቢሊዮን ብር  በጀት የተመደበለት ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት፤ በገጠር 10 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር፣ በወረዳ 19 ሜትር እንዲሁም በዞን 21.5 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ የሚገነባ ነው። ፕሮጀክቱ   በጅማ  ዞን  ውስጥ  የሚገኙትን  የጎማ እና የጌራ ወረዳዎችን እንዲሁም 9 ቀበሌዎችን የሚያስተሳስር ከመሆኑም ባሻገር  በኦሮሚያና  በደቡብ ምዕራብ  ክልል መካከል የሚኖረውን ግንኙነት  ይበልጥ ያጠናክራል። በተጨማሪም  በአካባቢው በስፋት የሚመረቱ እንደ ቡና፣ ማር፣ ቅቤ፣ የቀንድ ከብት እና የቅመማ ቅመም ውጤቶች በፍጥነት ለገበያ እንዲቀርቡ በማስቻልም አምራቹንና ሸማቹን ተጠቃሚነት ይጨምራል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

መልካም በዓል !!
መልካም በዓል !!

የአዘዞ - ጎንደር መንገድ ግንባታ እና የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት አሁናዊ ገጽታ:- የአዘዞ - ጎንደር መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ✍️ የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የሚገነባ ሲኾን፥ 12 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ይሸፍናል። ✍️ የመንገድ ግንባታውን ቀሪ ውስን ሥራዎች ለማጠናቀቅ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስቀመጡት አቅጣጫ መሠረት በኢትዮጵያ መንገዶች አሥተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ፕሮጀክቱን ተረክቦ በራስ-ኅይል በመሥራት ላይ ይገኟል። ✍️ የመንገድ ፕሮጀክቱ በፌደራል መንግሥት በተመደበ 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወጪ ነው በመከናወን ላይ የሚገኘው። ✍️ መንገዱ ከ28 እስከ 38 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲኾን፥ በነባሩ መንገድ ይስተዋሉ የነበሩ የትራፊክ መጨናነቆችን የሚያስቀር ነው። ✍️ ከዚህም በተጨማሪ ምቹ እና ቀልጣፋ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር በማስቻል ረገድ አስተዋጾዖው የጎላ ነው። ✍️ የነዋሪው ብሎም የሀገር ውስጥ እና የውጪ ጎብኚዎችን እንቅስቃሴ ይበልጥ ምቹ ከማድረጉም ባለፈ የጎንደር ከተማን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያፋጥን ነው። ✍️ ከጎንደር ከተማ ዙሪያ ወደ ሰሜን ጎንደርም ሆነ ወደ የተለያዩ አቅጣጫዎች የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ውስጥ ለውስጥ መሄድ ሳይጠበቅባቸው በቀጥታ ለማለፍ ያስችላቸዋል። የጎንደር ከተማ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ✍️ ከመንገድ ግንባታው ጎን ለጎንም በመንግሥት በተሰጠው ልዩ ትኩረትና መመሪያ መሠረት ተቋማችን በአዲስ አበባ እና ጎንደርን ጨምሮ በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ ከተሞች ላይ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች በማከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን፣ በሁለት ዙር የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፤ በዚህም መሠረት:- ✍️ በመጀመሪያ ዙር የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፣ ከጃንተከል እስከ ቴዎድሮስ አደባባይ 804 ነጥብ 58 ሜትር የአስፋልት ኮንክሪት፣ 104 ነጥብ 58 ለመስቀል አደባባይ የአስፋልት መደራረብ፣ ለተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ቱቦዎች እና ማንሆሎችን፣ የመንገድ አካፋይ፣ የእግረኛ መንገድ ግንባታ እና ስማርት የመንገድ መብራት ምሰሶዎች መሰረት ግንባታን አካትቶ ጥር 2017 መጀመሪያ ለአገልግሎት ክፈት ሆኗል፡፡ ✍️ ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ከማራኪ መገንጠያ እስከ ቴዎድሮስ አደባባይ ድረስ 5 ነጥብ 6 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ 15 ሜትር የጎን ስፋት አለው። ነባሩ መንገድ ረጅም ጊዜ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ እና በትራፊክ መጠን መጨመር ምክንያት በከፍተኛ ደረጃ የተጎዳ በመሆኑ በአስፋልት ንጣፍ (Asphalt Overlay) ተገንብቶ ጥር 8 ቀን 2018 መጀመሪያ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ የመሰረተ ልማት ሚኒስቴር ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር የልምድ ልውውጥ አደረጉ ። አዲስ አበባ፣ ጥር 5 ቀን 2018 ዓ/ም(ኢመአ) : የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሀመድ አብዱራህማን በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመሰረተ ልማት ሚኒስትር ክቡር ጆን ባንዛ ሉንዳ የተመራ ልዑካን የቡድን በዛሬው ዕለት ተቀብለው አነጋገሩ ። ዋና ዳይሬክተሩ በመንገድ ልማት ዘርፍላይ ያተኮረ ገለፃ አድርገዋል፡፡ የመንገድ ግንባታ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንዳለና በዋነኝነት በመንግስት ፋይናንስ እንዲሁም ከአለም አቀፍ ተቋማት በሚገኝ ድጋፍ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ለልኡካን ቡድኑ ገልጸዋል ። አክለውም የአፍሪካ ሀገራት የእርስ በእርስ የልምድ ልውውጥ ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል ። በአጠቃላይ በሀገሪቱ በመንገድ ዘርፍ የተከናወኑ ያሉ ተግባራት የተገኙ ውጤቶች እና ፋይዳ በተመለከተ ለልዑካን ቡድኑ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በመጨረሻም የዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ ኮንጎ የመሰረተ ልማት ሚኒስቴር ክቡር ጆን ባንዛ ሉንዳ የተመራ ልዑካን ቡድን የተደረገላቸውን አቀባበል አመስግነዉ ኢትዮጵያ በመንገድ ዘርፍ ያስመዘገበችዉ ዉጤት ከፍተኛ ልምድ ሊወሰድበት የሚገባ መሆኑን ተናግረዋል። ለዚህም የሚመለከታቸዉን ባለሙያዎች እና ሀላፊዎችን ያካተተ የልኡካን ቡድን ይዘዉ መምጣታቸዉ በመግለፅ በሚኖራቸዉ ቆይታ በዘርፉ ያለዉን ልምድና ተሞክሮ በመቅሰም በጋራ ለመስራት ያላቸዉን ፍላጎት ገልፀዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በወልደሃኔ - ዱርጊ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ንጣፍ ለመጀመር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ በመከናወን ላይ ነው ወላይታ ሶዶ፣ ጥር 02፣ 2018 (ኢ መ አ):- የማዕከላዊ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎችን በሚያገናኘው የወልደሃኔ - ዱርጊ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ንጣፍ ለመጀመር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ በመከናወን ላይ ነው። የመንገድ ግንባታው በዳውሮ ዞን እና በጠምባሮ ልዩ ወረዳ በኩል በሁለት አቅጣጫ በመከናወን ላይ ሲኾን፥ አጠቃላይ 41 ኪሎሜትር ይሸፍናል። አሁን ላይ የሰብቤዝ፣ ቤዝኮርስ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪ በጠምባሮ በኩል ያለውን የፕሮጀክት ክፍል በአጭር ጊዜ ውስጥ አስፋልት ለማንጠፍ የሚያስችሉ የጠጠር መፍጨት፣ የአስፓልት ፕላንት ተከላ እና ሌሎች ተያያዥ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቅቀዋል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር-በቀሎቹ ኤም ሲ ጂ ኮንስትራክሽን ከሜልኮን ኮንስትራክሽን ጋር በጋራ በመኾን በማከናወን ላይ ይገኛሉ። የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ኒች ኢንፍራስትራክቸር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ከሁብ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጋር በጥምረት በመሥራት ላይ ይገኛሉ። የመንገድ ግንባታው ከፌደራል መንግሥት በተመደበ 2 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ወጪ ነው በመከናወን ላይ የሚገኘው። የመንገዱ መገንባት የማኅበረሰቡን የዓመታት ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ከመስጠቱም ባለፈ በመንገድ መሠረተ-ልማት አለመኖር ለዘመናት ተራርቀው የነበሩትን የዳውሮ እና የጠምባሮ ሕዝቦች በቅርበት የሚያገናኝ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቀ ከዚህ ቀደም ከዳውሮ ተነስቶ በወላይታ ሶዶ በኩል ጠምባሮ ለመድረስ ይወስድ ይነበረውን የ250 ኪ.ሜ አድካሚ እና ጥልፍልፍ ጉዞ በቀጥታ ወደ 62 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል። በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የዓሣ እንዲሁም የተለያዩ የግብርና እና የመዓድን ውጤቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ ያስችላል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከ400 እስከ 500 ለሚደርሱ ዜጎች የሥራ ዕድል እና የዕውቀት ሽግግር የሚያገኙበትን ምቹ አጋጣሚ ፈጥሯል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የእስቴ - ስማዳ መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ጥር 01፣ 2018 (ኢ መ አ):- በደቡብ ጎንደር ዞን የእስቴ - ስማዳ መንገድ ግንባታ ዋና ዋና ሥራ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። የመንገዱ መገንባት ከዚህ በፊት ወደ የተለያዩ አካባቢዎች ለመጓዝ የነበሩ እንግልቶችን የሚያስቀር ነው። ከዚህ በተጨማሪም አርሶ-አደሩ የተለያዩ የአዝርዕት ምርቶቹን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ የሚያስችል ነው። በርካታ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ የመንገድ መሠረተ-ልማት በማስተሳሰርም ማኅበራዊ እና ምጣኔ-ሃብታዊ መስተጋብሩን የሚያጠናክር ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ የተገነባ ሲኾን፥ 50 ነጥብ 4 ኪሎሜትር ይሸፍናል። የ5 ድልድዮች እንዲሁም ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ ከልቨርቶች ግንባታ ተከናውኗል። የመንገድ ግንባታውን ዓለም-አቀፉ የሥራ ተቋራጭ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ አከናውኖታል። ሀገር-በቀሉ ፕሮሚናንት ኢንጅነሪንግ ሶሉሽንስ' ግንባታውን በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ተሳትፏል። ፕሮጀክቱ ከፊደራል መንግሥት በጀት በተመደበ 1 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ወጪ ነው የተከናወነው። የአካባቢው አስቸጋሪ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ፣ የጸጥታ ስጋቶች እንዲሁ ከወሰን ማስከበር ጋር የተያያዙ ችግሮች፣ በግንባታው ሂደት ላይ እክል ፈጥረው የነበረ ቢኾንም፥ ተቋማችን ከአማካሪ ማሀንዲሱ እና የሥራ ተቋራጩ እንዲሁም ከአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመሆን ባደረገው የተቀናጀ ጥረት ፕሮጀክቱን ከግብ ማድረስ ተችሏል። ወገዳ ከተማ ላይ የሚቀሩ ጥቃቅን ሥራዎች በቀጣይ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ የሚጠናቀቁ ይሆናል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሐሙሲት - እስቴ መንገድ ግንባታ በመከናወን ላይ የሚገኝ ሲሆን፥ በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads