en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 679 subscribers, ranking 8 043 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 679 subscribers.

According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 111 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.35%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.94% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 974 views. Within the first day, a publication typically gains 2 500 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 679
Subscribers
-124 hours
-157 days
+11130 days
Posts Archive
photo content
+9

ክሊኒኩ ለጣቢያው ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው .....//...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግልገል ጊቤ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ክሊኒክ የጣቢያው ሠራተኞች ጤንነታቸው ተጠብቆ ሥራቸውን ውጤታማ በሆነ መልኩ እንዲያከናውኑ በቅርበት የህክምና አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ። የክሊኒኩ ነርስ ሲስተር የትናየት አደረግሽ እንደገለጹት ክሊኒኩ የላቦራቶሪ አገልግሎትን ጨምሮ ተኝተው ለሚታከሙና ተመላላሽ ታካሚ ሠራተኞች የተሟላ የሕክምና አገልግሎት እየሰጠ ነው። የጣቢያው ሠራተኛ በሥራ ላይ ለሚገጥማቸው አደጋም ሆነ ህመም ክሊኒኩ ሙሉ የሕክምና አገልግሎት እና የመድሃኒት አቅርቦት በነጻ እየሰጠ መሆኑን ገልፀዋል። ማመንጫ ጣቢያው የሚገኝበት ቦታ በርሃማ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሚያጋጥውን የወባ በሽታን ጨምሮ ልዩ ልዩ ወረርሽኞችን ለመከላከል በአካባቢው ከሚገኙ የጤና ተቋማት ጋር በመተባበር የአጎበር እደላ እና የመድኃኒት ርጭት እንደሚከናወንም ተናግረዋል። ከህክምና አገልግሎቱ ባለፈ ተላላፊ የሆኑ በሽታዎችንና ወረርሽኞችን ቀድሞ መከላከል የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫዎች ለጣቢያው ሠራተኞች እንደሚሰጡም ጠቁመዋል። ከክሊኒኩ አቅም በላይ በሚሆንበት ጊዜ ሠራተኞች ለተጨማሪ ህክምና ተቋሙ አብሮ ለመስራት ስምምነት ወደፈጸመባቸው ሆስፒታሎች ሪፈር እንደሚላኩም ጠቁመዋል። በ2017 የመጀመሪያው ሩብ ዓመት ክሊኒኩ ለ256 የጣቢያው ሠራተኞች የተመላላሽና ተኝተው የማከም ህክምና አገልግሎት መስጠቱን የጠቆሙት ሲስተር የትናየት ይህ የታካሚዎች አሃዝ በድግግሞሽ የህክምና አገልግሎት ያገኙ ሠራተኞችን ቁጥር ታሳቢ ያደረገ ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በዋናው መስሪያ ቤት ካለው መካከለኛ ክሊኒክ በተጨማሪ በማመንጫ ጣቢያዎች 12 ክሊኒኮች አሉት። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን አሸነፈ ........///....... በ7ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ፋሲል ከነማን ገጥሞ 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሁለተኛ ተከታታይ ድሉን አስመዝግቧል። ሁለቱ ቡድኖች በድሬዳዋ ስቴዲየም ዛሬ ባከናወኑት ጨዋታ አቤል ሀብታሙ፣ ናትናኤል ገ/ጊዮርጊስ እና ያሬድ የማነ ለኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሶስቱን የማሸነፊያ ጎሎች አስቆጥረዋል። ፋሲል ከነማን ከሽንፈት ያልታደጉትን ሁለት ጎሎች አንጋፋው አጥቂ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል። ብርቱ ፉክክር በታየበት የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በመስመር ላይ የተመሰረተ የማጥቃት እንቅስቃሴ ሲከተል ፋሲል ከነማ በአንፃሩ ኳስን በመቆጣጠር የጨዋታ ብልጫ ለመውሰድ ቢሞክርም ሳይሳካለት ቀርቷል። ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ12 ነጥብ በሊጉ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

photo content

የሁለቱ ተቋማት አመራሮች የደዴሳ ማከፋፈያ ጣቢያን ጎበኙ ........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የፌደራል ፖሊስ አመራሮች የደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያን ዛሬ ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት የፌዴራል  ፖሊስ የምዕራብ ኦሮሚያ አዛዥ ኮማንደር ማሙዬ አባተ እንዳሉት የተቋሙ አመራሮች በግዳጅ ላይ ያሉትን የሠራዊት አባላት መጎብኘታቸው ለሠራዊቱ አባላት የሞራል ጥንካሬ ይሰጣል። ማከፋፈያ ጣቢያው በረሃማ ቦታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ የውሃ አቅርቦት እንዲስተካከል እና የወባ መከላከያ አጎበር እንዲሰጣቸው እንዲሁም የጥበቃ ማማ እንዲገነባላቸው ጠይቀዋል። በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የመሠረተ ልማት ደህንነትና ቁጥጥር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደተናገሩት ተቋሙ ከፌደራል ፖሊስና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን የመሠረተ ልማት ስርቆትን ለመከላከል በትኩረት እየሰራ ይገኛል። በሠራዊቱ አመራሮች ለቀረቡት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር እንደሚነጋገሩም ገልፀዋል። በተቋሙ የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ በበኩላቸው  ለጥበቃ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የንብረት ማስቀመጫ መጋዘን ለመገንባት መታቀዱንና ያልተሟሉ ፋሲሊቲዎችን ከሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች ጋር በመነጋገር ለመመለስ ጥረት እንደሚደረግ አረጋግጠዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያው የማስፋፊያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ……...///…….... የቦሌ ለሚ ባለ 230/33/15 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የማከፋፈያ  ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የማከፋፈያ ጣቢያዎች ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ተስፋዬ እንዳስታወቁት በማከፋፈያ ጣቢያው የማስፋፊያ ግንባታ የተከናወነው ጣቢያው ኃይል የመጫን አቅሙ በመቀነሱ ሳይሆን በ15 ኪሎ ቮልት ተጨማሪ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ በመታሰቡ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአካባቢው የ15 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥር መጨመር ለማስፋፊያ ግንባታው ዋና ምክንያት እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። እንደ አቶ ዮሐንስ ገለፃ የማስፋፊያ ሥራው የተለያዩ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግንባታዎችን ጨምሮ አንድ ባለ 50 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው ትራንፎርመር የማስቀመጥ፣ የኃይል መቆጣጠሪያ ቤት ግንባታ፣ የጂ.አይ.ኤስ ስዊችጊር ገጠማና በ230 ኪሎ ቮልት በኩል የቤይ ዕቃዎችን የመትከል እንዲሁም የፍተሻና የሙከራ ሥራዎችን ያጠቃልላል። የቦሌ ለሚ የማከፋፈያ ጣቢያ በተደረገለት የማስፋፊያ ግንባታ በአሁኑ ወቅት ስድስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንደተገነቡለት የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ይህም ለቦሌ አራብሳ፣ በሻሌና አካባቢው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ተናግረዋል። ዝግጁ የተደረጉት አዳዲሶቹ ወጪ መስመሮች ኃይል መስጠት የሚጀምሩት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል የማሰራጫ መስመሮች ከተዘረጉ በኋላ በመሆኑ ለአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ለዲስትሪክቱ የማሳወቅ ሥራ መሰራቱን አስታውቀዋል፡፡ የማስፋፊያ ግንባታው በሪጅኑ አቅም መከናወኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም አዳዲስ መሐንዲሶች እና የቴክኒክ ባለሙያዎች የልምድና የዕውቀት ሽግግር እንዲያገኙ መልካም አጋጣሚ መፍጠሩን አብራርተዋል። የማስፋፊያ ግንባታው በሪጅኑ አቅም በመከናወኑ ተቋሙን ከተጨማሪ ወጪ ማዳን እንዳስቻለም ነው አቶ ዮሐንስ የገለፁት። የማስፋፊያ ሥራው በሪጅኑ አቅም እንዲከናወን የተቋሙ የሥራ አመራር እና የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለሰጡት ዕድልና ኃላፊነት እንዲሁም በሥራው ላይ ለተሳተፉ ባለሙያዎች ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል። የቦሌ ለሚ የማከፋፈያ ጣቢያ ካሉት 14 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች መካከል ለኢንዱስትሪዎችና ለከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ኤሌክትሪክ እያቀረቡ የሚገኙት ዘጠኙ ብቻ ናቸው። ማከፋፈያ ጣቢያው ከ240 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል የመጫን አቅም ያላቸው አንድ ባለ 50 እና  ሁለት ባለ 125 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች አሉት። በ15 ሚሊየን ብር በጀት የተከናወነውን የቦሌ ለሚ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ለማጠናቀቅ ሁለት ዓመት ጊዜ ወስዷል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በኃላፊነት ስሜት እንዲጠበቅ ማድረግ ይገባል ……….///……… ሁሉም የቀበሌ እና የወረዳ አመራሮች በየአካባቢያቸው የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን በኃላፊነት ስሜት እንዲጠብቁ የምስራቅ ወለጋ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አሳሰቡ፡፡ የነቀምቴ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ምስጋኑ ቱሉ በበኩላቸው ያለ ኤሌክትሪክ የትኛውንም ዕቅድ ማሳካት ስለማይቻል በአጥፊዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮች ትናንት የምስራቅ ወለጋ ዞን እና ከዞኑ 18 ወረዳዎች የተውጣጡ አመራሮች እንዲሁም የነቀምቴ ከተማ አመራሮች በተሳተፉባቸው ሁለት መድረኮች ላይ በመገኘት ተቋሙን እየፈተኑት ስላሉት የመሰረተ ልማት ስርቆት ወንጀሎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በመድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመሠረተ ልማት ደህንነት ቁጥጥር እና ክትትል ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት በዞኑ ሥርቆት በሚበዛባችው ጉቶ ወረዳ - ሶረቃ ቀበሌ፣ ሁኪ ከተማ ዙሪያ፣ ሌቃ ዱለቻ ወረዳ፣ ደዴሳ አካባቢ፣ ጅማ አርጆ ወረዳ፣ ጊዳ አያና ወረዳ -ጉትን ከተማ አመራሩ ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በአዋጅ ቁጥር 464/97 አንቀጽ 3 እንደተደነገገው ሁሉም የመንግስት መዋቅር የኤሌክትሪክና የቴሌኮም መሠረት ልማቶችን የመጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡ በአዋጁ የተጣለባቸውን ግዴታ በማይወጡ አመራሮች ላይ ተጠያቂነትን ለማስፈን የሚያችል አሰራር መዘርጋት እንደሚገባም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በየደረጃው ከሚገኙ አመራሮች ጋር የመሰረተ ልማቶቹ በሚጠበቁበት ሁኔታ የተጀመረው ወይይት በመላው ሀገሪቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ በተቋሙ የንብረት እና ጠቅላላ አግልግሎት ዘርፍ የንብረት አስተዳደር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ በበኩላቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ረጅም ኪሎ ሜትሮችን ስለሚያቆራርጡ የመሰረተ ልማቱን መጠበቅ የሁሉንም ተሳትፎ ይፈልጋል ብለዋል፡፡ በመሆኑም ከማህበረሰቡና በየደረጃው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት አስፈላጊ መሆኑን አንስተው አመራሩ በኃላፊነት ስሜት እንዲሰራ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል፡፡ ምክትል አስተዳዳሪው አቶ ገመዳ ተረፈ በዞኑ በተዘጋጁ መድረኮች ላይ ለተሳተፉ ከ18 ወረዳ ለተውጣጡ አመራሮች እንደገለፁት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መጠበቅ ለሁሉም የተሰጠ በመሆኑ የቀበሌና የወረዳ አመራሮች በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቅ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም በዞኑ ሁኬ ከተማ በተካሄደ የተቀናጀ ፍተሻ ብዛት ያላችው የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት አካላት በጋሪ ላይ የበየዱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ በማካሄድ ለህግ እንዲቀርቡ መደረጉን ተናግረዋል፡፡ መሰረተ ልማቱን በማስጠበቅ ረገድ የተገኙ ምርጥ ተሞክሮዎችን በማስፋት አመራሮቹ የተሻለ ወጤት ለማምጣት እንዲሰሩም አሳስበዋል፡፡ የነቀምቴ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ምስጋኑ ቱሉ በበኩላቸው ያለ ኤሌክትሪክ የትኛውንም ዕቅድ ማሳካት ስለማይቻል በአጥፊዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ይወሰዳል ብለዋል፡፡ የህዝብ እና የመንግሥትን ንብረት የማይጠበቅ አመራር ካለ ተጠያቂነት እንደሚኖርበት ሊያውቅ ይገባል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

10 ሰዓታት የፈጀው የጥገና ሥራ በስኬት ተጠናቋል ……..///……… ከትናንት በስቲያ በእሳት አደጋ ምክንያት በጊዜያዊነት አገልግሎት መስጠት ያቋረጠውን የድሬዳዋ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ መስመር የማዛወር ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት ትናንት ምሽት ከ1:00 ሰዓት እስከ ሌሊት 11፡00 ከሁርሶ ወደ ድሬዳዋ አንድ፣ ወደ ሀረር እና ጅግጅጋ የሚሄዱ መስመሮችን የማዛወር ሥራ ተሰርቷል፡፡ ዛሬ ረፋድ መስመሩን የመፈተሽ ሥራ ተከናውኖ ወደሁሉም አካባቢዎች ኃይል እንደደረሰ መረጋገጡን ገልፀዋል። የሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ጉዳት እንዳጋጠመው ተደርጎ የተሰራጨው ዘገባ የሀሰት መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ከሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ወጪ መስመር በማዘጋጀት ችግሩ መፈታቱን አስታውቀዋል፡፡ ፈታኝ የሆነው የመስመር ማዛወር ሥራ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ የኃይል መቋረጥ አጋጥሟቸው በነበሩ አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች በትዕግስት ስለጠበቁ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የሴቶች ቡድን ሊጉን በድል ጀምሯል ........///........ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያው ጨዋታ ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ድል ቀንቶታል። ቡድኑ ዛሬ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከቂርቆስ ክ/ከተማ ጋር ባከናወነው ጨዋታ አምስት ለባዶ አሸንፏል። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ እንስቶች ሙሉ የጨዋታ የበላይነት ባሳዩበት መርሃግብር  ማህሌት ምትኩ ለቡድኗ ሁለት ጎል ስታስቆጥር ቀሪዎቹን ሶስት ጎሎች ህዳት ካሱ፣ ዙፋን ደፈርሻ እና ሳባ ኃ/ሚካኤል ከመረብ አሳርፈዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ኳስን ተቆጣጥሮ በመጫወት እና ቶሎ ቶሎ ወደ ግብ በመድረስ ከተጋጣሚያቸው የላቀ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል። ቂርቆስ ክፍለ ከተማ በአንፃሩ በመከላከል ላይ የተመሰረተ አጨዋወት ቢከተልም ከሽንፈት አልዳነም። የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የአማካይ ተጫዋች ሀና ሲሳይ ኮከብ ተጫዋች በመሆን ተመርጣለች። በሁለተኛ ሳምንት የጨዋታ መርሃ ግብር ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ከሐዋሳ ከተማ በመጪው ቅዳሜ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ጣቢያው የማህበረሰቡን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እየሰራ ነው .......//...... የመልካ ዋከና የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን አስታወቀ። የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ በቀለ እንደገለጹት ጣቢያው ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች ተከናውነዋል። በጣቢያው ዙሪያ በሚገኙ አምስት ቀበሌዎች ላይ የውሃ ጉድጓዶችን በማስቆፈር ማህበረሰቡን የንጹህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር የኃይል ማመንጫ ጣቢያው ኢብሳ ጤና ጣቢያን ሰርቶ ማስረከቡን ገልጸዋል። በኃይል ማመንጫ ጣቢያው ዙሪያ የሚገኙ 12 ቀበሌዎችን ከ65 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት የመብራት ተጠቃሚ መደረጋቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ቀሪ አካባቢዎችን ተጨማሪ 330 ሚሊዮን ብር በመመደብ የመብራት ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። እንደ አቶ ቴዎድሮስ ገለፃ ሮቤ ጌርጀዳን ከጌዴዶ ከተማ የሚያገናኝ 10 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ ጣቢያው መስራቱንም ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም ከጣቢያው እስከ በቆጂ መገንጠያ ያለውን 26 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና ከጣቢያው እስከ አዳባ ያለውን 30 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ የጥገና ሥራ ለመስራት በሂደት ላይ መሆኑን ጠቅሰዋል። በጣቢያው ግቢ የሠራተኞችና የአካባቢው ማህበረሰብ ልጆች የሚማሩባቸው ከኬጂ እስከ 8ኛ ክፍል የሚያስተምሩ ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የተናገሩት አቶ ቴዎድሮስ 250 ለሚሆኑ የቅድመ መደበኛ የአካባቢው ተማሪዎችም የትራንስፖርት አገልግሎት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል። የዋቤ ኢብሳ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር የሆኑት አማና ፈቶ እንደገለጹት ጣቢያው ውሃ፣ መብራት እና የትምህርት ቁሳቁስ ለትምህርት ቤቱ እያቀረበ ነው። ይህም ልጆቹ ርቀው ሳይሄዱ ጥራት ያለው ትምህርት እንዲያገኙ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል። የአካባቢው አባገዳ የሆኑት ሐጂ እንድሪስ ሐጂ ጉራሪ በበኩላቸው ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣቢያና መንገድ ከመስራት ባለፈ የውሃና የመብራት ተጠቃሚ እያደረገ ነው ብለዋል። በዚህም የአካባቢው ማህበረሰብ ርቆ ሳይሄድ ንጹህ የመጠጥ ውኃ እንዲያገኝ፣ ልጆቹን እንዲያስተምርና የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረጉን ጠቁመዋል። የኃይል ማመንጫ ጣቢያው እያከናወነ ላለው የልማት ስራ ምስጋናቸውን ያቀረቡት አስተያየት ሰጪዎቹ በዚህም ማህበረሰቡ በጣቢያው ላይ ያለው የእኔነት ስሜት እያደገ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በቀጣይም ከጣቢያው የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የጣቢያውን ደህንነት ለመጠበቅ እንደሚሰሩ ተናግረዋል። የመልካ ዋከና ውኃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ የጀመረው በ1980 ዓ.ም ሚያዚያ 15 ቀን ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9