ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 548 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 340 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 158 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 548 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 27، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.05‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.01‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 053 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 491 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 548
المشتركون
-724 ساعات
+147 أيام
+2730 أيام
أرشيف المشاركات
ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ተጨማሪ ደንበኞችን እየጠበቁ ነው …….///…… የመቱ እና የበደሌ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚፈልጉ ደምበኞችን እየጠበቁ መሆናቸውን የየጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ተናገሩ። የመቱ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ አበበ ሰይፉ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያ የማከፋፈያ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እንዲሁም አንድ ባለ 230፣ አምስት ባለ 33 እና ሦስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ ጣቢያው ከበደሌ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ተቀብሎ በ230 ኪሎ ቮልት ለጋምቤላ ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት በዙሪያው ላሉ ወረዳዎች፤ በ15 ኪሎ ቮልት ደግሞ ለመቱ ከተማና አካባቢው እንዲሁም ለመቱ ዩኒቨርሲቲ ኃይል እያቀረበ እንደሆነ ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ 40 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያለው የማከፋፈያ ጣቢያው አሁን ለደንበኞች እያቀረበ ያለው ግን ግማሽ ያህሉን ብቻ በመሆኑ ጣቢያው ያለውን ተጨማሪ አዳዲስ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅም በአግባቡ ለመጠቀም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ደንበኛ የመሳብ ሥራ ማከናወን እንደሚገባ ጠቅሰዋል፡፡ ለጋምቤላ፣ ለመቱ እና ለአጋሮ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል እያቀረበ ያለው የበደሌ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ቀኖ በበኩላቸው በጣቢያው የአቅም ማሳደግ ሥራ ከተከናወነ በኋላ እያንዳንዳቸው 54 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች እንዲኖሩት ተደርጓል፡፡ በጣቢያው ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራ በመስራት 5 ባለ 15 እና 6 ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮችን እንዲኖሩት በማድረግ ተደራሽነቱን ማስፋፋት እንደተቻለም አስረድተዋል፡፡ ጣቢያው በአምስቱ ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ለበደሌ ከተማና ቢራ ፋብሪካ እንዲሁም በበደሌ አካባቢ ለሚገኙ የወረዳ ከተሞች ኃይል እያቀረበ ሲሆን ከ6ቱ ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪዎች ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ ጨዋቃ እና ደጋ ለሚባሉ ቦታዎች ኃይል እያቀረበ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። አቶ ሲሳይ እንደገለፁት ጣቢያው ካሉት 6 ዘመናዊ ብሬከሮች ውስጥ ሁለቱ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን አራቱ ባለ 33 ኪሎ ቮልት ብሬከሮች ግን ደንበኞችን እየተጠባበቁ ይገኛሉ። ቀሪ ብሬከሮችን ወደ አገልግሎት ለማስገባት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎችና ከበደሌ ከተማ አስተዳደር ጋር ምክክር እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 8 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

በህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ያደጉ ህጻናት ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ተሸኙ .......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል ቆይተው ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት የተሸጋገሩ
+6
በህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ያደጉ ህጻናት ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት ተሸኙ .......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህፃናት ማቆያ ማዕከል ቆይተው ወደ ቅድመ መደበኛ ትምህርት የተሸጋገሩ አስራ አንድ ህጻናት የሽኝት ፕሮገራም ተደረገላቸው፡፡ የተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለፁት ማዕከሉ የተቋሙ ሴት ሠራተኞችን ጫና ከማቃለል ባሻገር የነገውን የብልጽግና ጉዞ የሚወስኑ ህፃናትን የተሟላ ስብዕና ከመቅረጽ አኳያ ትልቅ መሰረት እየጣለ ነው። ታዳጊ ህጻናቱ በማዕከሉ የቆይታ ጊዜያቸው ከቀለም ትምህርት ውጪ ፍቅርን፣ አብሮነትን፣ ማህበራዊ መስተጋብርን በመፍጠር ራሳቸውን በተሻለ መልኩ የሚገልጹበት ሁኔታ ተፈጥሮላቸዋል፡፡ ማዕከሉ በአሁኑ ሰዓት ከአራት ወር እስከ አራት ዓመት የሚደርሱ 64 የተቋሙ ሠራተኞች ልጆችን ተቀብሎ በመንከባከብ ላይ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም

በጥቂት ወራት ውስጥ ጣቢያውን ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ርብርበ እየተደረገ ነው ……..///………. ከ6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶላር በላይ እየተገነባ የሚገኘው የማሻ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን እሰከ መጪው ታህሳስ 2017 ዓ. ም. በማጠናቀቅ የሙከራ እና የፍተሻ ሥራ ለመጀመር ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ የፕሮጀክቱ ሳይት ስራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው አሳዬ ገለጹ፡፡ እንደ ስራ አስኪያጁ ገለጻ የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ግንባታ 95 በመቶ እና የአሌክትሮ ሜካኒከል ስራዎች 80 በመቶ እንዲሁም የጣቢያው አጠቃለይ አፈጻጸም 85 በመቶ መድረሱን ተናግረዋል፡፡ የሰርኪዩት ብሬከሮች ተከላ፣ የውስጥ ለውስጥና ጣቢያውን ከዋናው መንገድ የሚያገናኝ የኮንክሪት አስፓልት መንገድ ግንባታ፣ በመቆጣጠሪያ ክፍሉ የሚገኙ እና ሌሎች የፖወር ኬብሎችን የማገናኘት ሥራዎች በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አቶ ጌታቸው ገልፀዋል፡፡ የሁለት የትራንስፎርመሮች ተከላ፣ የማከፋፈያ ጣቢያው የመቆጣጠሪያ ክፍልና የኦፕሬተሮች መኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የስዊች ያርድ እና ሌሎች የብረት ተከላ ሥራዎች ከጥቃቅን የማጠቃሊያ ስራ በስተቀር መጠናቀቃቸውን ጠቁመዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ቀሪ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች እንዲሁም የፍተሻና ሙከራ ሥራዎችን በማጠናቀቅ በተያዘው በጀት ዓመት አጋማሽ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው 50 ሜጋ ዋት የመሸከም አቅም ያላችው ሁለት ባለ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሮች እንዲሁም አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢና ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ይኖሩታል፡፡ ፕሮጀክቱ እስከ አምስት መቶ ለሚሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጠቃሚ ማድረጉ ተጠቁሟል፡፡ የፕሮጀክቱ አካል የሆነው የመቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሶሶዎች ዝርጋታ አማካይ አፈጻጸሙ 70 በመቶ ደርሷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

በጂማ 1 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ባጋጠመ ችግር ኃይል ተቋርጧል ---///--- በጂማ 1 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ላይ ባጋጠመ ችግር በጅማ ከተማ በከፊል ፣ዴዶ እና ሰቃ በተባሉ አካባቢዎች ኃይል መቋረጡን የደቡብ ምዕራብ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፐሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት ኃይል የተቋረጠው በጅማ 1 ማከፋፈያ ጣቢያ የ132/15 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመር ላይ በደረሰ ብልሽት ነው፡፡ ኃይሉ የተቋረጠው ዛሬ መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ ጀምሮ መሆኑንን የተናገሪት አቶ ጌታሁን ትራንስፎርመሩ ከፍተኛ የሆነ ዘይት እያፈሰሰ በመሆኑ እሱን ለመጠገን ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡ ችግሩ ተቀርፎ ማከፋፈያ ጣቢያው ወደነበረበት እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁም አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

በታሪፍ ማሻሻያው ላይ የወጣው ዘገባ የተሳሳተና ህብረተሰቡን የሚያደናግር በመሆኑ ሊታረም ይገባል ……….///………. ከመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ጀምሮ በየሩብ ዓመቱ የኤሌክትሪክ የማመንጫ ታሪፍ በኪሎ ዋት እስከ 95 ብር ድረስ ጭማሪ ሊደረግበት ነው በሚል ሸገር ኤፍ ኤም እና ኢትዮ ኤፍ ኤምን ጨምሮ በአንዳንድ ብዙኃን መገናኛ እና ማህበራዊ ትስስር ገጾች የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞቹ ላይ ተግባራዊ የሚያደርገው የማመንጫ ታሪፍ እና የማስተላለፊያ ታሪፍ ማሻሻያን በተመለከተ የወጣው መረጃ የተሳሳተና የታሪፉን አወቃቀር የተቀመጠውን ሰንጠረዥ ባለመረዳት የቀረበ ነው፡፡ ተቋሙ ባወጣው ሰንጠረዥ መሰረት የማመንጫ ታሪፍ በየሩብ ዓመቱ ቀድሞ በሥራ ላይ ከነበረው በኪሎ ዋት ሰዓት 89 ሳንቲም ከመስከረም ወር ጀምሮ በየሩብ ዓመቱ የ12 ሳንቲም ጭማሪ ይደረግበታል፡፡ በተመሳሳይም የማስተላለፊያ ታሪፍ ቀድሞ ከነበረበት በየሩብ ዓመቱ በኪሎ ዋት የ26 ብር ከ35 ሳንቲም ጭማሪ ይኖረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫዎችን፣ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የሚያስተዳድር እንጂ የሥርጭት መስመሮችን በመጠቀም ለህብረተሰቡ በቀጥታ ኃይል የሚሰጥ ተቋም ባለመሆኑ የተጠቀሰው የታሪፍ ማሻሻያ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎችን እንጂ መላውን ህብረተሰብ እንደሚመለከት ተደርጎ የቀረበው ዘገባ የተሳሳተ ነው፡፡ ቁጥሮች ተተርጉመው ለህብረተሰቡ ሲቀርቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግባቸው የሚገባ ቢሆንም ይህ ባለመደረጉ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ብዥታ በመፈጠሩ መገናኛ ብዙኃንና ብዙ ተከታይ ያላቸው ማህበራዊ ትስስር ገጾች የፈጠሩትን ስህተት እንዲያርሙና የተፈጠረውን ብዥታ እንዲያስተካክሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይጠይቃል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የአርባምንጭ ሁለተኛ የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ 46 በመቶ ደርሷል .......///....... የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አካል የሆነው የአርባምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ 46 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ ምዕራፍ አንድ የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ አንዷለም መላኩ እንደገለጹት የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ከ37 ነጥብ 09 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በጀት ተይዞለት ግንባታው የተጀመረው ሕዳር 2016 ዓ.ም ነው። አሁን ላይ የዲዛይን ሥራው 94 በመቶ፣ የሲቪል ግንባታው 42 በመቶ የደረሰ ሲሆን 43 ሺ ሜትር ኪዩብ የመሬት ቆረጣና 39 ሺ ሜትር ኪዩብ የአፈር ሙሌት ሥራ መከናወኑን ገልጸዋል። ጂ አይ ኤሴ (GIS) ስዊች ጊሮች እና ትራንስፎርመሮችን ጨምሮ የማከፋፈያ ጣቢያ አስፈላጊ ዕቃዎች ጅቡቲ ወደብ እንደሚገኙና በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ተጓጉዘው ሳይት ሲደርሱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው እንደሚጀመር ተናግረዋል፡፡ የኦፕሬተር መኖሪያ ቤቶች ኮለን ኮንክሪት የመሙላት ሥራ መከናወኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የትራንስፎርመሮች፣ የጂአይኤስ እና የእሳት መከላከያ ዕቃዎች ማስቀመጫ ግንባታም ተጠናቋል ብለዋል። የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ቀደም ሲል የነበረውን የአርባ ምንጭ አንድን ኃይል የመስጠት አቅም በአራት እጥፍ እንደሚያሳድገው የተናገሩት አቶ አንዷለም ይህም አርባ ምንጭ ላይ ለመገንባት ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል። ሥራ አስኪያጁ አክለውም የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ሲጠናቀቅ በ120 ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ለሚገኙ የአካባቢው ማህበረሰቦች በቀጥታ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችል ጠቁመዋል። የግንባታ ሥራውን የሚያከናውነው ሃዮሰንግ ሄቪይ ኢንደስትሪስ ኮርፖሬሽን የግንባታ ሥራ አስከኪያጅ ሚስተር ሁይኩን ሊ እንደገለጹት ኩባንያቸው ከአሁን ቀደም የሱሉሉታ - ገብረ ጉራቻ ማስተላለፊያ መስመርን ከመገንባቱ በተጨማሪ ደቡብ ኮሪያን ጨምሮ በዮርዳኖስ እና በኩዌት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን በመገንባት ልምድ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ ሥራዎችን በተያዘው የጊዜ ሰሌዳ ለማከናወን የአካባቢው የአየር ሁኔታ፣ የሲሚንቶ እጥረት፣ የማከፋፈያ ጣቢያ ዕቃዎችን ከወደብ ወደ ሳይት ለማምጣት የትራንስፖርት ችግር እንቅፋት መፍጠሩን የገለጹት ሚስተር ሊ ሆኖም ግንባታውን በታቀደለት ጊዜና ገንዘብ ለማጠናቀቅ የማካካሻ ዕቅድ ማውጣታቸውን ተናግረዋል፡፡ የአርባ ምንጭ ሁለተኛ ማከፋፈያ ጣቢያ ከወላይታ ሶዶ 230 ኪሎ ቮልት፣ ከኦሞ ኩራዝ አንድ በ230 ኪሎ ቮልት መስመርና ከአርባ ምንጭ አንድ በ132 ኪሎ ቮልት መስመር የሚገናኝ ሲሆን በ33 ኪሎ ቮልት አስር እንዲሁም በ15 ኪሎ ቮልት አምስት በድምሩ 15 ወጭ መስመሮች አሉት፡፡ የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አርባ ምንጭ 2ኛን ጨምሮ ሽግዳንና ቲርጋ ላይ የሚገነቡ ሦስት አዳዲስ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ ነባሩ ወላይታ ሶዶ ሁለተኛ እና አርባምንጭ አንድ ላይ የሚከናወን የማስፋፊያ ሥራ እንዲሁም የ424 ኪሎ ሜትር የማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ሥራዎችን ያጠቃልላል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የመቱ - ማሻ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ከ56 በመቶ በላይ ተጠናቋል ………///…… የመቱ - ማሻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ ከ56 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌታቸው አሳዬ እንዳሰታወቁት መስመሩ በሚያልፍበት ቦታ ላይ በዩኔስኮ በቅርስነት የተመዘገበ ጥብቅ ደን በመኖሩ ምክንያት ለአንድ ዓመት ተኩል አዘግይቶት እንደነበረና የግንባታ አቅጣጫውን በመቀየር በአሁን ወቅት የግንባታ ሥራው እየተፋጠነ ይገኛል። 70 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራ 174 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ያሉት ሲሆን ከዚህ ውስጥ የ41 ምሰሶዎች ተከላ መጠናቀቁን ነው የተናገሩት። እንደሥራ አስኪያጁ ገለፃ የምሰሶ መትከያ የመሰረት ቁፋሮ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ፣ የመሰረት ኮንክሪት ሙሊት 97 ነጥብ 7 በመቶ እንዲሁም የምሰሶ ተከላ ሥራ 23 ነጥብ 5 በመቶ የሚሆነው መከናወኑን ገልፀው አጠቃላይ የመስመር ዝርጋታ ሥራውም 55 ነጥብ 3 በመቶ መድረሱን አስረድተዋል። የመስመሩን የግንባታ ሥራ በታህሳስ 2017 ዓ.ም መጨረሻ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል። የመቱ - ማሻ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ለማሻ፣ ለጊዲላሎ፣ ለጌሻ እና ለሰሊኖኖ ወረዳዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ያቀርባል ተብሎ ይጠበቃል። በአካባቢው በኢንዱስትሪ ልማት ለመሠማራት ፍላጎት ያሳዩ ባለሀብቶች የፕሮጀክቱን መጠናቀቅ በጉጉት እየጠበቁ መሆኑን ገልፀው ይህም ፕሮጀክቱን ለፍፃሜ ለማብቃት በርትተን እንድንሠራ አድርጎናል ብለዋል። የማስተላለፊያ መስመሩ ከዓለም ባንክ በተገኘ የ6 ነጥብ 34 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ከ2 መቶ 97 ነጥብ 78 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ በጀት እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት መሆኑን አብራርተዋል። ፕሮጀክቱ ከ500 በላይ ለሚሆኑ የአካባቢው ሰዎች የሥራ ዕድል መፍጠሩም ተገልጿል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

k, it was already replaced

ከ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ጀምሮ በየ3 ወሩ ተግባራዊ የሚደረገው የማመንጫ እና የማስተላለፊያ ታሪፍ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር
ከ2017 የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ጀምሮ በየ3 ወሩ ተግባራዊ የሚደረገው የማመንጫ እና የማስተላለፊያ ታሪፍ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም

የተቋሙ ካፒታል 709 ቢሊዮን ብር ደረሰ ………///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃላይ ሀብት 709 ቢሊዮን ብር መድረሱን በተቋሙ የፋይናንስ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስፈፃሚው አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ተቋሙ ካለው ከ709 ቢሊዮን አጠቃላይ ሀብት መካከል 586 ቢሊዮን ብሩ የተከፈለ ካፒታል ነው፡፡ ተቋሙ በመንግስት እና በራሱ ባከናወናቸው የኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ የተቋሙን ዕዳ ከ55 በመቶ ወደ 20 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሀብቱ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ የወጣባቸው የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 28 በመቶ ድርሻ ያላቸው መሆኑንም ሥራ አስፈፃሚው አስታውቀዋል፡፡ 25 ነጥብ 5 በመቶው አጠቃላይ ሀብት ደግሞ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና የስዊች ያርድ ድርሻ መሆኑን የገለፁት አቶ ደመረ የ150 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው ናቸው ብለዋል፡፡ ቀሪው 46 ነጥብ 5 በመቶ ሀብት ተሽከርካሪዎች፤ ህንፃዎች እንዲሁም ሌሎች ቋሚ እና ተንቀሳቃሽ ንብረቶችን ያጠቃለለ ነው፡፡ ተቋሙ በ2006 ዓ.ም እንደ አዲስ ሲቋቋም 34 ነጥብ 768 ቢሊዮን ብር የተከፈለ ካፒታል በመያዝ እንደነበር ያስታወሱት አቶ ደመረ ይህ አኀዝ በብዙ እጥፍ በማደጉ አዋጁን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ አብራርተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከ19 በላይ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች፤ 20 ሺህ ኪ.ሜ ርዝመት ያላቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፈያ መስመሮች፤ ከ144 በላይ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በርካታ ህንፃዎች እና ከ900 በላይ ተሽከርካሪዎች አሉት፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ሽንፈት አስተናግዷል .........///........ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም በተከናወነ የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫ ኢትዮ ኤሌክትሪክ የእግር ኳስ ቡድን ከፋሲል ከነማ ጋር ለፍፃሜ ተጫውቶ ሁለት ለባዶ ተረቷል። በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10:00 ሰዓት በተካሄደውና ተመጣጣኝ የጨዋታ ፍሰት በነበረው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ጎል ላይ በተደጋጋሚ በመድረስ ረገድ ፋሲል ከነማዎች የተሻሉ ነበሩ። የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ጎሎች ማርቲን ኪዛ በ23ኛው ደቂቃ እንዲሁም አፍቅሮት ሰለሞን በ67ኛው ደቂቃ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል። ውጤቱን ተከትሎ ፋሲል ከነማ የአዲስ አበባ ከተማ ዋንጫን አንስቷል። የዘንድሮ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መስከረም 10 ቀን 2017 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ የሚጀመር ሲሆን ባለፈው የውድድር ዓመት ከከፍተኛ ሊግ ያደገው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በፕሪሚየር ሊጉ ከሚሳተፉ 19 ክለቦች መካከል አንዱ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ ኢድ-ሙባረክ አሸ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1499ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የደስታ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ ኢድ-ሙባረክ አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር)፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ