en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 546 subscribers, ranking 8 351 in the Technologies & Applications category and 2 178 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 546 subscribers.

According to the latest data from 02 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 27 over the last 30 days and by 8 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.76%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.84% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 005 views. Within the first day, a publication typically gains 2 463 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 546
Subscribers
+824 hours
-227 days
+2730 days
Posts Archive
የቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የስቲሊንግ ቤዚን ጥገና ተጠናቀቀ ----------///-------- ከቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ የሚወጣውን ውሃ ፍጥነትና እንቅስቃሴ ለመቀነስ የሚያገለግለው የስቲሊንግ ቤዚን ስራ ተጠናቀቀ፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የራስ ኃይል የሲቪል ሥራዎች ጥገና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ግርማ መንገሻ እንዳስታወቁት በውሃ ማስተንፈሻዎች በኩል ከግድቡ የሚወጣው ውሃ የሚያርፍበት መሬት እየተሸረሸረ በመምጣቱ የሰቲሊንግ ቤዚን ጥገና ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የተከናወነው የጥገና ሥራ የቀድሞውን የአርማታ ወለል በማፍረስና በቦታው የነበረውን ተፈጥሯዊ ዐለት በማስወገድ በግድቡ ግርጌ ባለው የመሬት ወለል ላይ በብረት ንጣፍ የተከናወነው የአርማታ ሙሌት ሥራ የግድቡ መሰረት በውሃ እንዳይሸረሸር የሚያደርገው ነው፡፡ ይህም የግድቡን ደህነነት ለመጠበቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንና ጣቢያውን ለተጨማሪ ዓመታት አገልገሎት እንዲሰጥ የሚያስችለው መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡ ለበርካታ ዓመታት የማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ግንባታዎችን ሲያከናውን የቆየው የራስ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የመፈፀም አቅሙን እያሳደገ በመምጣቱን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የግድብ ጥገናዎች ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ይህም ተቋሙ ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል፡፡ የግንባታ ሥራው ከአንድ መቶ በላይ ለሆኑ ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ያወሱት ሥራ አስኪያጁ በግንባታ ግብዓት ላይ የሚስተዋለው የዋጋ ንረትና አቅርቦት እጥረት የጥገና ስራውን ፈታኝ አድርገውት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ይሁንና በግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መጨመር ምክንያት ተከስተው የነበሩ የሥራ መዘግየት ችግሮች በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች እና የሥራ ክፍሎች ቀና ትብብር ተቀርፈው ሥራው ሊጠናቀቅ ችሏል ብለዋል፡፡ ላለፉት 62 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የቆቃ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 43 ሜጋ ዋት የማንጨት አቅም ያለው ሲሆን ከአዲስ አበባ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በ81 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

ተቋሙ መጤ አረምን ለማስወገድ ያስገባውን ጀልባ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል ...........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጣና ላይ የሚንሳፈፈው መጤ አረም ወደ ኃይል ማመንጫ ተገምሶ እንዳይመጣ ለመከላከል ያስገባው ጀልባ በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የሙላት ኢንደስትሪያል ኢንጂነሪንግ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙላት ባዛዝነው ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙላት እንደገለፁት ጀልባው 50 ኪሎ ዋት ጀነሬተር ሲኖረው 6 መቶ የፈረስ ጉልበት ያላቸው ሁለት ሞተሮች ተገጥመውለታል። 15 ሜ ትር በ6 ሜትር ስፋት ያለው ጀልባ በደለል በተሞላ አካባቢ ያለችግር ለመቅዘፍ የሚያስችል ፕሮፔለር እንደተገጠመለት እና ጀልባው ከውስጥ 12 ብሎኮች እንዲኖሩት ተደርጎ የተገነባ መሆኑን አቶ ሙላት አብራርተዋል። ይህም ከአለት ጋር ተጋጭቶ ቢሰነጠቅ ወይም ቢበሳ ውሃው በተሰነጠቀበት ክፍል ብቻ እንዲቆይና ወደ ሌላ ክፍል ሳይገባ ችግሩን ለመቆጣጠር የሚያስችል ነው ብለዋል። ጀልባው ከዲዛይን ጀምሮ በልዩ ሁኔታ መሰራቱን የተናገሩት ሥራ አስኪያጁ አረም እየቆራረጠ ሊያወጣ የሚችል 50 ቶን ድረስ የማንሳት አቅም ያለውና እስከ 12 ሜትር የሚረዝም ክሬን እንደተገጠመለት አስረድተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከመደበኛ ሥራው ባሻገር አካባቢው ላይ እየተፈጠረ ያለውን ችግር ለማቃለልና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እያደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያሳይ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

ከጎንደር አዘዞ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ጋር ተያይዞ የተፈጠረው ብዥታ እንዲጠራ ተደርጓል ...........///......... ከጎንደር አዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ለአቅም ማሳደግ ሥራ ተነስቶ በሌላ በሚተካው ትራንስፎርመር ዙሪያ ከጎንደር ከተማ አመራሮች ጋር በከንቲባ ጽ/ቤት ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ ላይ የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ዘውዱ የከተማ የፀጥታና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊና የብልፅግና ጽ/ቤት የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ፣ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገናና ኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ውበት አቤና ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአማራ ክልል ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ጣሰው ተገኝተዋል። "ተነስቶ ሊወሰድ ነው" ተብሎ የተሳሳተ መረጃ ስለተሰራጨበት ትራንስፎርመርና በማከፋፈያ ጣቢያው ሊሰራ ስለታሰበው የአቅም ማሳደግ የማሻሻያ ሥራ በሁለቱ የኤሌክትሪክ ተቋማት ተወካዮች ዝርዝር ቴክኒካዊ ማብራሪያ ቀርቧል። ማከፋፈያ ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ለጎንደር በሁለት ወጪ መስመሮች፣ ለጎንደር ውሃ፣ ለአዘዞ፣ ለማክሰኚት፣ ለቆላ ድባ በአንድ አንድ ወጪ መስመር፣ እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ለጭልጋ፣ ደልጊ፣ አርባያና ሳንጃ አገልግሎት እየሰጠ እየሰጠ ቢሆንም ሥራ በመጀመር ላይ ላሉት ኢንዱስትሪዎችና ለነዋሪው ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ በ 33 ኪሎ ቮልት 8 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም የነበረውን ትራንስፎርመር ተጨማሪ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም እንዲፈጠርለት ለማድረግ የተጀመረ እንቅስቃሴ ስለ መሆኑ ለአመራሮቹ ገለፃ ተደርጎላቸዋል። አቅሙ ከፍተኛ የሆነውን ትራንስፎርመር ማጓጓዝ መጀመሩንና በአዘዞ የተጀመረው ሥራ ለሚመጣው ትራንስፎርመር ቦታ የማዘጋጀት እንጂ ሙሉ በሙሉ ነቅሎ የመውሰድ አለመሆኑም በግልፅ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል። የትራንስፈርመሮችን አቅም የማሳደግ ሥራ በቅርቡ በከሚሴ፣ በሀረርና በጅግጅጋ መከናወኑንና በንፋስ መውጫም ተመሳሳይ የአቅም ማሳደግ ሥራ እንደሚሰራ ተገልጿል። ይሁንና በዚህ መካከል ህዝብ ለግጭት ሊያነሳሳ የሚችል የኮሙዩኒኬሽን ክፍተት መፈጠሩ በውይይቱ ወቅት ተነስቷል። ከተማ አስተዳደሩ ሊሰራ የታሰበውን ሥራ በአግባቡ በመረጃቱ ለሚመለከታቸው አካላት ግንዛቤ የመፍጠርና የመረጃ ክፍተቱን የመሙላት ሥራ እንደሚሰራና ለማስፋፊያ ሥራው መጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጧል። ውይይቱ ግልፅና ፍሬያማ እንደነበር አመራሮቹ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

ተቋሙ ረጅም ርቀት በመጓዝ የሚቆራረጡ መስመሮችን ችግር ለመፍታት እሰራለው አለ ...........///......... የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለመቀነስና ኤሌክትሪክ በሌለባቸው አካባቢዎች መልሶ አገልግሎቱን ለማስጀመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጋራ እንደሚሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክና ኃይል እና አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች አረጋገጡ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ እና የአማራ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ በባህርዳር ተወያይተው ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት በጋራ ከመስራት ውጪ ምንም አማራጭ እንደሌለ አረጋግጠዋል። የአማራ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ጣሰው ረጅም ርቀት በመጓዝ እንዲሁም በኃይል ጫና የተነሳ እየተቆራረጡ ያሉ አካባቢዎችን በመለየት የማሻሻያ ሥራ እንዲሰራ ጠይቀዋል። ችግሩ ጎልቶ ታይቶባቸዋል ከተባሉት አካባቢዎች መካከል ከደሴና አቀስታ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚያገኙ የደቡብ ወሎ ዞን ከተሞች፣ከሰሜን ሸዋ መሀልሜዳ፣ ከደቡብ ጎንደር ወረታ፣ እንዲሁም ከምስራቅ ጎጃም ቡሬ፣ ሞጣ እና ብቸና አማራጭ መፍትሔ ሊፈለግላቸው ይገባል ብለዋል። ከጥገና ሥራዎች ጋር ተያይዞ የጥገና መሳሪያዎች፣ ግብዓቶችና የክህሎት ችግር ስላለበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እገዛ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው የሁለቱ ተቋማት ዓላማ ለህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ ማድረስ በመሆኑ በጋራ በመስራት የህብረተሰቡን ችግር ሊፈቱ እንደሚገባ ገልፀዋል። ረጅም ርቀት በመጓዝ የሚቆራረጡ መስመሮችን ችግር ለመፍታት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥርጭት መስመሮች መዘርጋት ላይ ሳይገደብ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ መካከለኛ ቮልቴጅ መጠን ያላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መገንባት ላይ ትኩረት እንዲያደርግ አሳስበዋል። ይሁንና በጊዜያዊነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጨማሪ ትራንስፎርመሮች በመትከል፣ ወጪ መስመሮች በማዘጋጀትና ስዊች ጊሮችን ችግሩ ባለባቸው አካባቢዎች በመትከል መፍትሔ ለመስጠት በዕቅድ ውስጥ ተካቶ እንዲሰራ ጥረት እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል። ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ በሚያጋጥማቸው እና ከፍተኛ ጭነት በሚሸከሙ መስመሮች ላይ ተቋሙ ጥብቅ ፍተሻና የጥገና ሥራ መሰራት ይኖርበታል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+4

የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና መስመሮችን በመፈተሽ ጣቢያዎችን ዝግጁ የማድረግ ሥራ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተባለ ...........///......... በተያዘው በጀት ዓመት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ትራንስፎርመሮች እና መስመሮችን በመፈተሽ ጣቢያዎችን ዝግጁ የማድረግ ሥራ ትኩረት እንዲሰጠው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ የባህርዳር ቁጥር 2 ባለ 400/230 የማከፋፈያ ጣቢያ ከጎበኙ በኋላ ከጣቢያው ሠራተኞችና ኃላፊ ጋር ተወያይተዋል። በውይይቱ ላይ ሠራተኞቹ የመኖሪያ ቤት እንዲሟላላቸው፣ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱና ስዊች ጊር እንዲቀየር እንዲሁም በጣቢያው የሚስተዋለው የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲቀረፍ ጠይቀዋል። ከውይይቱ በኋላ ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የውሃ ችግሩን ለመቅረፍ የአካባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ትኩረት ሊሰጥ ይገባል። የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት እንዲሰጥ፣ የጣቢያውን ግቢ ለሥራ ምቹ የማድረግና በጣቢያው ያሉትን ዕቃዎች መዝግቦ የማስቀመጥ ስራ እንዲሰራ አሳስበዋል። ለሠራተኞች መኖሪያ ተብሎ የተጀመረው ግንባታ በተቻለ ፍጥነት እንዲጠናቀቅና ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ግፊት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። በቀጣይም የራሳቸው የሆነ መስመር ለሚጠይቁ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ወጪ መስመር የማዘጋጀት ስራ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል። ባህር ዳር ቁጥር 2 የማከፋፈያ ጣቢያ አስራ አንድ ባለ 15 እንዲሁም ሁለት ባለ 33 ወጪ መስመር ያለው ሲሆን 169 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው 4 ትራንስፎርመሮች አሉት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 09 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+3

የጎንደር አዘዞ የማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር የሚነሳው አቅም የማሻሻል ሥራ ለመስራት ነው ...........//////......... የጎንደር አዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተነስቶ ሊወሰድ ነዉ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨዉ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት የተሰራጨው መረጃ በማከፋፈያ ጣቢያው ሊሰራ የታሰበውን ሥራና ቴክኒካዊ ጉዳዮችን ከግምት ውስጥ ያላስገባ ነው። ማከፋፈያ ጣቢያዉ ለህብረተሰቡ በቀጥታ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሁለት ባለ 23፣ አንድ ባለ 20 እና አንድ ባለ 8 ነጥብ 4 በድምሩ 74 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው የ15 እና የ33 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመሮች አሉት ፡፡ ይሁን እንጅ ያሉት ትራንስፎርመሮች ከፍተኛ ጭነት ለመሸከም አቅም የሌላቸዉ እና ረጅም ርቀት ተጉዘው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸግሩ በመሆኑ በአገልግሎት አሰጣጡ ችግር ያጋጥም እንደነበር ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል። በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ ባደረጉት ጥናት 8 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለውን ትራንስፎርመር ወደ 39 ነጥብ 9 ሜጋ ቮልት አምፔር ከፍ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል። የተጀመረውን የአቅም ማሳደግ ሥራ ለማከናወን አነስተኛ አቅም ያለውን ትራንስፎርመር በሌላ ለመተካት ትራንስፎርመር ወደ ጎንደር በመጓጓዝ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል። ይህ ዓይነት አሰራር የተለመደና በአካባቢዉ የሚስተዋለዉን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ችግር ለማሻሻል የታስበ እንጂ ትራንስፎርመር ወደ ሌላ አካባቢ ነቅሎ መውሰድ አለመሆኑ እንዲታወቅ አሳስበዋል። በተጀመረው የማሻሻያ ሥራ የሚነሳዉ ትራንስፎርመር በክልሉ የኤሌክትሪክ አቅርቦት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ማስጀመር እንደሚውል ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል። እነወደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በጎንደር አዘዞ የማከፋፈያ ጣቢያ የተጀመረውን ዓይነት የአቅም ማሳደግ ሥራ በንፋስ መውጫ ማከፋፈያ ጣቢያም ይሰራል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 09 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውሃ ለሶስተኛ ጊዜ በግድቡ አናት ላይ ፈሰሰ ………////…….. የአባይ ውሃ ለሦስተኛ ጊዜ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል፡፡ በግድቡ ግንባታ ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችም የደስታ ስሜታቸውን ገልፀዋል። ከለውጡ በኋላ በፕሮጀክቱ ላይ በተወሰደው የማስተካከያ እርምጃ በግድቡ ውስጥ መተከል የነበረባቸው የውሃ ማስተላለፊያ የብረታ ብረት ስራዎችን ተጠናቀው የግድቡን የመካከለኛው ክፍል ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ ስድስት መቶ ሜትር እንዲሁም ግራና ቀኙን ስድስት መቶ አስራ አንድ ሜትር ማድረስ ተችሏል፡፡ ከሶስት ዓመት በፊት ለዘመናት ከባህር ጠለል በላይ በአምስት መቶ ሜትር ከፍታ ላይ ይፈስ የነበረው የአባይ ወንዝ ዛሬ ለሦስተኛ ዙር በግድቡ አናት ላይ የፈሰሰው ከባህር ጠለል በላይ በስድስት መቶ ሜትር ከፍታ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት የግድቡ ግራና ቀኝ ጠርዝ ከባህር ጠለል በላይ ስድስት መቶ አርባ አምስት ሜትር የደረሰ ሲሆን የግድቡ የሲቪል ሥራዎች ግንባታ 95 በመቶ፣ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ፍብረካና ተከላ 61 በመቶ እንዲሁም የብረታ ብረት ሥራ 73 በመቶ፣ አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ 83 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፍታ ከመሬት 145 ሜትር ሲሆን ርዝመቱ ደግሞ 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡ የዋናው ግድብ ውፍረት የግድቡ ግርጌ ላይ 130 ሜትር፥ የግድቡ ጫፍ ወይም የላይኛው ክፍል ደግሞ 11 ሜትር ነው። በበጀት ዓመቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሁለት ዩኒት ኃይል ማመንጨት እንዲጀምር ለማድረግ የያዘው እቅድ ተሳክቷል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 06 ቀን 2014 ዓ.ም

የሕዳሴ ግድብ 2ኛው ተርባይን በይፋ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ጀምሯል .....///....... የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ተርባይን ዛሬ በይፋ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል። የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሣህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ሥነስርዓት ላይ ነው ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው። በማብሰሪያ ሥነስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንደተናገሩት የአባቶቻችንን ትልም እና ፍላጎት በማሳካት ሀገራችንን በጸና መሰረት ላይ ማቆም የዚህ ትውልድ ዋነኛ ኃላፊነት ነው፡፡ “የዛሬ የኢትዮጵያውያን ትውልዶች በሙሉ የዚህ እድልም ድልም ተቋዳሽ ነን፣ ለዚህም እንኳን ደስ አላችሁ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ አባቶቻችን ይህንን አስበዋል፤ ተመኝተዋል ነገር ግን እኛ ያየነውን ማየት አልቻሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያውያን ገንዘባቸውን እውቀታውን አልፎም ህይወታቸውን የገበሩበት ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያን የጸናችና የበለጸገች ሀገር ማቆየት ከቻልን በዚያ ውስጥ የሚኖረውን ሀብትና ንብረት ሁሉ ልጆቻችን በቀላሉ ሊወርሱ ይችላሉም ብለዋል፡፡ ዛሬ በዕድልና በድል እዚህ ስፋራ መቆማችንን አቅልለን ሳናየው ለላቀው ድል እንነሳሳ ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው። አስቀድመው ኃይል እንዲያመነጩ ዲዛይን ከተደረጉት ሁለት ዩኒቶች መካከል ዩኒት 9 ላይ ሲሰራ የነበረው ሥራ ተጠናቆ የተሳካ ፍተሻ እና ሙከራ ከተከናወነ በኋላ ዛሬ በይፋ ኃይል በማመንጨት ወደ ብሔራዊ ኃይል ቋት ኃይል ማስገባት ችሏል። ባለፈው የካቲት ወር ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመረው ዩኒት 10 በተመሳሳይ 375 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አለው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 05 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

ከ480 በላይ የሚሆኑ የተቋሙ ማሽነሪዎችና ተሸከርካሪዎች ጂ.ፒ.ኤስ/ GPS/ ተገጥሞላቸዋል …..///….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት በ600 ተሽከርካሪዎች ላይ ጂ.ፒ.ኤስ.
ከ480 በላይ የሚሆኑ የተቋሙ ማሽነሪዎችና ተሸከርካሪዎች ጂ.ፒ.ኤስ/ GPS/ ተገጥሞላቸዋል …..///….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት በ600 ተሽከርካሪዎች ላይ ጂ.ፒ.ኤስ. ለመግጠም አቅዶ ከ480 በላይ ተሽከርካሪዎች ላይ ገጠማ ማከናወኑን በተቋሙ የትራንስፖርት ስምሪትና ቁጥጥር መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋይ እንደገለፁት የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ከሞደርናይዜሽን መምሪያ ጋር በመሆን ባከናወነው የጂ.ፒ.ኤስ. ገጠማ የዕቅዱን 80 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡ በቀሪዎቹ ተሸከርካሪዎች ላይ ገጠማውን በማጠናቀቅ ስለአተገባበሩ ስልጠና በመስጠት በቅርቡ ውስጥ ወደ ተግባር እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ጂ.ፒ.ኤስ. በተሸከርካሪዎች ላይ መገጠሙ ተሽከርካሪው የት እንዳለ ለማወቅ፤ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ አዛውሮ ለማሰራት፣ የነዳጅና ጎማ አጠቃቀምን ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማስተዳደር፣ የፍጥነት ገደብን በመወሰን አደጋን ለመቀነስ፣ ተሸከርካሪው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የሄደበትን አቅጣጫና ምን ያህል ኪሎ ሜትር እንደተጓዘ በማሳየት የተቋሙን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 04 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+2

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኦፊስ ሰርቪስ ፐርፎርመር 1ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ/ የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

የፈተና ውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በቻይልድ ኬር ጊቨር የሥራ መደብ በኮንትራት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪ
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በቻይልድ ኬር ጊቨር የሥራ መደብ በኮንትራት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍና የቃል ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከነሐሴ 03 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም በዋና መስሪያ ቤት ኬኬር ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናስታውቃለን፡፡

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ መስፈርቶቹን የምታሟሉ ሁሉ በዚህ ሊንክ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል፡፡ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScKjpKqsOy-1lx1Bhkpt_
+1
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ መስፈርቶቹን የምታሟሉ ሁሉ በዚህ ሊንክ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል፡፡ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScKjpKqsOy-1lx1Bhkpt_GxRZcqVilExYecbr2_-omHYM3sfA/viewform?usp=sf_link https://forms.gle/tHUJTwNcFbHbT3437