EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 546 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 546 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 546
订阅者
+824 小时
-227 天
+2730 天
帖子存档
15 544
የቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የስቲሊንግ ቤዚን ጥገና ተጠናቀቀ
----------///--------
ከቆቃ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ግድብ የሚወጣውን ውሃ ፍጥነትና እንቅስቃሴ ለመቀነስ የሚያገለግለው የስቲሊንግ ቤዚን ስራ ተጠናቀቀ፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ግንባታ የራስ ኃይል የሲቪል ሥራዎች ጥገና ሥራ አስኪያጅ ኢንጅነር ግርማ መንገሻ እንዳስታወቁት በውሃ ማስተንፈሻዎች በኩል ከግድቡ የሚወጣው ውሃ የሚያርፍበት መሬት እየተሸረሸረ በመምጣቱ የሰቲሊንግ ቤዚን ጥገና ስራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
በ20 ሚሊየን ብር ወጪ የተከናወነው የጥገና ሥራ የቀድሞውን የአርማታ ወለል በማፍረስና በቦታው የነበረውን ተፈጥሯዊ ዐለት በማስወገድ በግድቡ ግርጌ ባለው የመሬት ወለል ላይ በብረት ንጣፍ የተከናወነው የአርማታ ሙሌት ሥራ የግድቡ መሰረት በውሃ እንዳይሸረሸር የሚያደርገው ነው፡፡
ይህም የግድቡን ደህነነት ለመጠበቅ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው መሆኑንና ጣቢያውን ለተጨማሪ ዓመታት አገልገሎት እንዲሰጥ የሚያስችለው መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል፡፡
ለበርካታ ዓመታት የማስተላለፊያ መስመሮችንና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ግንባታዎችን ሲያከናውን የቆየው የራስ የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ የመፈፀም አቅሙን እያሳደገ በመምጣቱን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የግድብ ጥገናዎች ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ ይህም ተቋሙ ሊያወጣ የሚችለውን ወጪ በመቀነስ በኩል ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አብራርተዋል፡፡
የግንባታ ሥራው ከአንድ መቶ በላይ ለሆኑ ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን ያወሱት ሥራ አስኪያጁ በግንባታ ግብዓት ላይ የሚስተዋለው የዋጋ ንረትና አቅርቦት እጥረት የጥገና ስራውን ፈታኝ አድርገውት እንደነበር ተናግረዋል፡፡
ይሁንና በግንባታ ግብዓቶች ዋጋ መጨመር ምክንያት ተከስተው የነበሩ የሥራ መዘግየት ችግሮች በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች እና የሥራ ክፍሎች ቀና ትብብር ተቀርፈው ሥራው ሊጠናቀቅ ችሏል ብለዋል፡፡
ላለፉት 62 ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው የቆቃ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 43 ሜጋ ዋት የማንጨት አቅም ያለው ሲሆን ከአዲስ አበባ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ በ81 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
ተቋሙ መጤ አረምን ለማስወገድ ያስገባውን ጀልባ በሁለት ሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል
...........///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጣና ላይ የሚንሳፈፈው መጤ አረም ወደ ኃይል ማመንጫ ተገምሶ እንዳይመጣ ለመከላከል ያስገባው ጀልባ በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ የሙላት ኢንደስትሪያል ኢንጂነሪንግ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙላት ባዛዝነው ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙላት እንደገለፁት ጀልባው 50 ኪሎ ዋት ጀነሬተር ሲኖረው 6 መቶ የፈረስ ጉልበት ያላቸው ሁለት ሞተሮች ተገጥመውለታል።
15 ሜ ትር በ6 ሜትር ስፋት ያለው ጀልባ በደለል በተሞላ አካባቢ ያለችግር ለመቅዘፍ የሚያስችል ፕሮፔለር እንደተገጠመለት እና ጀልባው ከውስጥ 12 ብሎኮች እንዲኖሩት ተደርጎ የተገነባ መሆኑን አቶ ሙላት አብራርተዋል።
ይህም ከአለት ጋር ተጋጭቶ ቢሰነጠቅ ወይም ቢበሳ ውሃው በተሰነጠቀበት ክፍል ብቻ እንዲቆይና ወደ ሌላ ክፍል ሳይገባ ችግሩን ለመቆጣጠር የሚያስችል ነው ብለዋል።
ጀልባው ከዲዛይን ጀምሮ በልዩ ሁኔታ መሰራቱን የተናገሩት ሥራ አስኪያጁ አረም እየቆራረጠ ሊያወጣ የሚችል 50 ቶን ድረስ የማንሳት አቅም ያለውና እስከ 12 ሜትር የሚረዝም ክሬን እንደተገጠመለት አስረድተዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከመደበኛ ሥራው ባሻገር አካባቢው ላይ እየተፈጠረ ያለውን ችግር ለማቃለልና ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት እያደረገ ያለውን ጥረት እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 11 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
ከጎንደር አዘዞ ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ጋር ተያይዞ የተፈጠረው ብዥታ እንዲጠራ ተደርጓል
...........///.........
ከጎንደር አዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ለአቅም ማሳደግ ሥራ ተነስቶ በሌላ በሚተካው ትራንስፎርመር ዙሪያ ከጎንደር ከተማ አመራሮች ጋር በከንቲባ ጽ/ቤት ውይይት ተካሂዷል።
በውይይቱ ላይ የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ዘውዱ የከተማ የፀጥታና አስተዳደር ዘርፍ ኃላፊና የብልፅግና ጽ/ቤት የኮሙዩኒኬሽን ኃላፊ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ፣ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገናና ኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ውበት አቤና ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የአማራ ክልል ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ጣሰው ተገኝተዋል።
"ተነስቶ ሊወሰድ ነው" ተብሎ የተሳሳተ መረጃ ስለተሰራጨበት ትራንስፎርመርና በማከፋፈያ ጣቢያው ሊሰራ ስለታሰበው የአቅም ማሳደግ የማሻሻያ ሥራ በሁለቱ የኤሌክትሪክ ተቋማት ተወካዮች ዝርዝር ቴክኒካዊ ማብራሪያ ቀርቧል።
ማከፋፈያ ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ለጎንደር በሁለት ወጪ መስመሮች፣ ለጎንደር ውሃ፣ ለአዘዞ፣ ለማክሰኚት፣ ለቆላ ድባ በአንድ አንድ ወጪ መስመር፣ እንዲሁም በ33 ኪሎ ቮልት ለጭልጋ፣ ደልጊ፣ አርባያና ሳንጃ አገልግሎት እየሰጠ እየሰጠ ቢሆንም ሥራ በመጀመር ላይ ላሉት ኢንዱስትሪዎችና ለነዋሪው ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ በ 33 ኪሎ ቮልት 8 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም የነበረውን ትራንስፎርመር ተጨማሪ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም እንዲፈጠርለት ለማድረግ የተጀመረ እንቅስቃሴ ስለ መሆኑ ለአመራሮቹ ገለፃ ተደርጎላቸዋል።
አቅሙ ከፍተኛ የሆነውን ትራንስፎርመር ማጓጓዝ መጀመሩንና በአዘዞ የተጀመረው ሥራ ለሚመጣው ትራንስፎርመር ቦታ የማዘጋጀት እንጂ ሙሉ በሙሉ ነቅሎ የመውሰድ አለመሆኑም በግልፅ ማብራሪያ ተሰጥቶበታል።
የትራንስፈርመሮችን አቅም የማሳደግ ሥራ በቅርቡ በከሚሴ፣ በሀረርና በጅግጅጋ መከናወኑንና በንፋስ መውጫም ተመሳሳይ የአቅም ማሳደግ ሥራ እንደሚሰራ ተገልጿል።
ይሁንና በዚህ መካከል ህዝብ ለግጭት ሊያነሳሳ የሚችል የኮሙዩኒኬሽን ክፍተት መፈጠሩ በውይይቱ ወቅት ተነስቷል።
ከተማ አስተዳደሩ ሊሰራ የታሰበውን ሥራ በአግባቡ በመረጃቱ ለሚመለከታቸው አካላት ግንዛቤ የመፍጠርና የመረጃ ክፍተቱን የመሙላት ሥራ እንደሚሰራና ለማስፋፊያ ሥራው መጠናቀቅ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ አረጋግጧል።
ውይይቱ ግልፅና ፍሬያማ እንደነበር አመራሮቹ ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
ተቋሙ ረጅም ርቀት በመጓዝ የሚቆራረጡ መስመሮችን ችግር ለመፍታት እሰራለው አለ
...........///.........
የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለመቀነስና ኤሌክትሪክ በሌለባቸው አካባቢዎች መልሶ አገልግሎቱን ለማስጀመር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በጋራ እንደሚሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክና ኃይል እና አገልግሎት የሥራ ኃላፊዎች አረጋገጡ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ እና የአማራ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ በባህርዳር ተወያይተው ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት በጋራ ከመስራት ውጪ ምንም አማራጭ እንደሌለ አረጋግጠዋል።
የአማራ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ጣሰው ረጅም ርቀት በመጓዝ እንዲሁም በኃይል ጫና የተነሳ እየተቆራረጡ ያሉ አካባቢዎችን በመለየት የማሻሻያ ሥራ እንዲሰራ ጠይቀዋል።
ችግሩ ጎልቶ ታይቶባቸዋል ከተባሉት አካባቢዎች መካከል ከደሴና አቀስታ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል የሚያገኙ የደቡብ ወሎ ዞን ከተሞች፣ከሰሜን ሸዋ መሀልሜዳ፣ ከደቡብ ጎንደር ወረታ፣ እንዲሁም ከምስራቅ ጎጃም ቡሬ፣ ሞጣ እና ብቸና አማራጭ መፍትሔ ሊፈለግላቸው ይገባል ብለዋል።
ከጥገና ሥራዎች ጋር ተያይዞ የጥገና መሳሪያዎች፣ ግብዓቶችና የክህሎት ችግር ስላለበት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እገዛ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በበኩላቸው የሁለቱ ተቋማት ዓላማ ለህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ ማድረስ በመሆኑ በጋራ በመስራት የህብረተሰቡን ችግር ሊፈቱ እንደሚገባ ገልፀዋል።
ረጅም ርቀት በመጓዝ የሚቆራረጡ መስመሮችን ችግር ለመፍታት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥርጭት መስመሮች መዘርጋት ላይ ሳይገደብ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ መካከለኛ ቮልቴጅ መጠን ያላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች መገንባት ላይ ትኩረት እንዲያደርግ አሳስበዋል።
ይሁንና በጊዜያዊነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ተጨማሪ ትራንስፎርመሮች በመትከል፣ ወጪ መስመሮች በማዘጋጀትና ስዊች ጊሮችን ችግሩ ባለባቸው አካባቢዎች በመትከል መፍትሔ ለመስጠት በዕቅድ ውስጥ ተካቶ እንዲሰራ ጥረት እንደሚያደርጉ ጠቁመዋል።
ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ በሚያጋጥማቸው እና ከፍተኛ ጭነት በሚሸከሙ መስመሮች ላይ ተቋሙ ጥብቅ ፍተሻና የጥገና ሥራ መሰራት ይኖርበታል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና መስመሮችን በመፈተሽ ጣቢያዎችን ዝግጁ የማድረግ ሥራ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል ተባለ
...........///.........
በተያዘው በጀት ዓመት የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ትራንስፎርመሮች እና መስመሮችን በመፈተሽ ጣቢያዎችን ዝግጁ የማድረግ ሥራ ትኩረት እንዲሰጠው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አሳሰቡ።
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ የባህርዳር ቁጥር 2 ባለ 400/230 የማከፋፈያ ጣቢያ ከጎበኙ በኋላ ከጣቢያው ሠራተኞችና ኃላፊ ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ ላይ ሠራተኞቹ የመኖሪያ ቤት እንዲሟላላቸው፣ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱና ስዊች ጊር እንዲቀየር እንዲሁም በጣቢያው የሚስተዋለው የመጠጥ ውሃ ችግር እንዲቀረፍ ጠይቀዋል።
ከውይይቱ በኋላ ሥራ አስፈፃሚው እንደገለፁት የውሃ ችግሩን ለመቅረፍ የአካባቢውን ህብረተሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግ ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ትኩረት ሊሰጥ ይገባል።
የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ ትኩረት እንዲሰጥ፣ የጣቢያውን ግቢ ለሥራ ምቹ የማድረግና በጣቢያው ያሉትን ዕቃዎች መዝግቦ የማስቀመጥ ስራ እንዲሰራ አሳስበዋል።
ለሠራተኞች መኖሪያ ተብሎ የተጀመረው ግንባታ በተቻለ ፍጥነት እንዲጠናቀቅና ለታለመለት ዓላማ እንዲውል ግፊት እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል።
በቀጣይም የራሳቸው የሆነ መስመር ለሚጠይቁ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች ወጪ መስመር የማዘጋጀት ስራ ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል።
ባህር ዳር ቁጥር 2 የማከፋፈያ ጣቢያ አስራ አንድ ባለ 15 እንዲሁም ሁለት ባለ 33 ወጪ መስመር ያለው ሲሆን 169 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው 4 ትራንስፎርመሮች አሉት።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 09 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የጎንደር አዘዞ የማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር የሚነሳው አቅም የማሻሻል ሥራ ለመስራት ነው
...........//////.........
የጎንደር አዘዞ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር ተነስቶ ሊወሰድ ነዉ በሚል በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨዉ መረጃ የተሳሳተ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ።
ሥራ አስፈፃሚው አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት የተሰራጨው መረጃ በማከፋፈያ ጣቢያው ሊሰራ የታሰበውን ሥራና ቴክኒካዊ ጉዳዮችን ከግምት ውስጥ ያላስገባ ነው።
ማከፋፈያ ጣቢያዉ ለህብረተሰቡ በቀጥታ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ የሚያስችሉ ሁለት ባለ 23፣ አንድ ባለ 20 እና አንድ ባለ 8 ነጥብ 4 በድምሩ 74 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው የ15 እና የ33 ኪሎ ቮልት ፓወር ትራንስፎርመሮች አሉት ፡፡
ይሁን እንጅ ያሉት ትራንስፎርመሮች ከፍተኛ ጭነት ለመሸከም አቅም የሌላቸዉ እና ረጅም ርቀት ተጉዘው አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸግሩ በመሆኑ በአገልግሎት አሰጣጡ ችግር ያጋጥም እንደነበር ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል።
በመሆኑም ችግሩን ለመቅረፍ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ ባደረጉት ጥናት 8 ነጥብ 4 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለውን ትራንስፎርመር ወደ 39 ነጥብ 9 ሜጋ ቮልት አምፔር ከፍ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል ብለዋል።
የተጀመረውን የአቅም ማሳደግ ሥራ ለማከናወን አነስተኛ አቅም ያለውን ትራንስፎርመር በሌላ ለመተካት ትራንስፎርመር ወደ ጎንደር በመጓጓዝ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ ዓይነት አሰራር የተለመደና በአካባቢዉ የሚስተዋለዉን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ችግር ለማሻሻል የታስበ እንጂ ትራንስፎርመር ወደ ሌላ አካባቢ ነቅሎ መውሰድ አለመሆኑ እንዲታወቅ አሳስበዋል።
በተጀመረው የማሻሻያ ሥራ የሚነሳዉ ትራንስፎርመር በክልሉ የኤሌክትሪክ አቅርቦት በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኤሌክትሪክ ማስጀመር እንደሚውል ሥራ አስፈፃሚው ጠቁመዋል።
እነወደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በጎንደር አዘዞ የማከፋፈያ ጣቢያ የተጀመረውን ዓይነት የአቅም ማሳደግ ሥራ በንፋስ መውጫ ማከፋፈያ ጣቢያም ይሰራል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 09 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ውሃ ለሶስተኛ ጊዜ በግድቡ አናት ላይ ፈሰሰ
………////……..
የአባይ ውሃ ለሦስተኛ ጊዜ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል፡፡
በግድቡ ግንባታ ላይ የተሳተፉ ባለሙያዎችም የደስታ ስሜታቸውን ገልፀዋል።
ከለውጡ በኋላ በፕሮጀክቱ ላይ በተወሰደው የማስተካከያ እርምጃ በግድቡ ውስጥ መተከል የነበረባቸው የውሃ ማስተላለፊያ የብረታ ብረት ስራዎችን ተጠናቀው የግድቡን የመካከለኛው ክፍል ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ ስድስት መቶ ሜትር እንዲሁም ግራና ቀኙን ስድስት መቶ አስራ አንድ ሜትር ማድረስ ተችሏል፡፡
ከሶስት ዓመት በፊት ለዘመናት ከባህር ጠለል በላይ በአምስት መቶ ሜትር ከፍታ ላይ ይፈስ የነበረው የአባይ ወንዝ ዛሬ ለሦስተኛ ዙር በግድቡ አናት ላይ የፈሰሰው ከባህር ጠለል በላይ በስድስት መቶ ሜትር ከፍታ ነው፡፡
በአሁኑ ወቅት የግድቡ ግራና ቀኝ ጠርዝ ከባህር ጠለል በላይ ስድስት መቶ አርባ አምስት ሜትር የደረሰ ሲሆን የግድቡ የሲቪል ሥራዎች ግንባታ 95 በመቶ፣ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ፍብረካና ተከላ 61 በመቶ እንዲሁም የብረታ ብረት ሥራ 73 በመቶ፣ አጠቃላይ አፈፃፀሙ ደግሞ 83 ነጥብ 3 በመቶ ደርሷል፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከፍታ ከመሬት 145 ሜትር ሲሆን ርዝመቱ ደግሞ 1 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር ይሆናል፡፡
የዋናው ግድብ ውፍረት የግድቡ ግርጌ ላይ 130 ሜትር፥ የግድቡ ጫፍ ወይም የላይኛው ክፍል ደግሞ 11 ሜትር ነው።
በበጀት ዓመቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በሁለት ዩኒት ኃይል ማመንጨት እንዲጀምር ለማድረግ የያዘው እቅድ ተሳክቷል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 06 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የሕዳሴ ግድብ 2ኛው ተርባይን በይፋ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ጀምሯል
.....///.......
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሁለተኛ ተርባይን ዛሬ በይፋ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሣህለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በቤንሻንጉል ጉሙዝ ጉባ ወረዳ በታደሙበት ሥነስርዓት ላይ ነው ሁለተኛው ተርባይን ኃይል ማመንጨት የጀመረው።
በማብሰሪያ ሥነስርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንደተናገሩት የአባቶቻችንን ትልም እና ፍላጎት በማሳካት ሀገራችንን በጸና መሰረት ላይ ማቆም የዚህ ትውልድ ዋነኛ ኃላፊነት ነው፡፡
“የዛሬ የኢትዮጵያውያን ትውልዶች በሙሉ የዚህ እድልም ድልም ተቋዳሽ ነን፣ ለዚህም እንኳን ደስ አላችሁ” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
አባቶቻችን ይህንን አስበዋል፤ ተመኝተዋል ነገር ግን እኛ ያየነውን ማየት አልቻሉም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያውያን ገንዘባቸውን እውቀታውን አልፎም ህይወታቸውን የገበሩበት ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
እኛ ኢትዮጵያውያን የጸናችና የበለጸገች ሀገር ማቆየት ከቻልን በዚያ ውስጥ የሚኖረውን ሀብትና ንብረት ሁሉ ልጆቻችን በቀላሉ ሊወርሱ ይችላሉም ብለዋል፡፡
ዛሬ በዕድልና በድል እዚህ ስፋራ መቆማችንን አቅልለን ሳናየው ለላቀው ድል እንነሳሳ ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመረው ሁለተኛው ዩኒት 375 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው።
አስቀድመው ኃይል እንዲያመነጩ ዲዛይን ከተደረጉት ሁለት ዩኒቶች መካከል ዩኒት 9 ላይ ሲሰራ የነበረው ሥራ ተጠናቆ የተሳካ ፍተሻ እና ሙከራ ከተከናወነ በኋላ ዛሬ በይፋ ኃይል በማመንጨት ወደ ብሔራዊ ኃይል ቋት ኃይል ማስገባት ችሏል።
ባለፈው የካቲት ወር ላይ ኃይል ማመንጨት የጀመረው ዩኒት 10 በተመሳሳይ 375 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አለው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 05 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
ከ480 በላይ የሚሆኑ የተቋሙ ማሽነሪዎችና ተሸከርካሪዎች ጂ.ፒ.ኤስ/ GPS/ ተገጥሞላቸዋል
…..///…..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት በ600 ተሽከርካሪዎች ላይ ጂ.ፒ.ኤስ. ለመግጠም አቅዶ ከ480 በላይ ተሽከርካሪዎች ላይ ገጠማ ማከናወኑን በተቋሙ የትራንስፖርት ስምሪትና ቁጥጥር መምሪያ አስታወቀ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ኃይላይ ተስፋይ እንደገለፁት የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ከሞደርናይዜሽን መምሪያ ጋር በመሆን ባከናወነው የጂ.ፒ.ኤስ. ገጠማ የዕቅዱን 80 በመቶ ማሳካት ችሏል፡፡
በቀሪዎቹ ተሸከርካሪዎች ላይ ገጠማውን በማጠናቀቅ ስለአተገባበሩ ስልጠና በመስጠት በቅርቡ ውስጥ ወደ ተግባር እንደሚገባም አስታውቀዋል፡፡
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ጂ.ፒ.ኤስ. በተሸከርካሪዎች ላይ መገጠሙ ተሽከርካሪው የት እንዳለ ለማወቅ፤ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ አዛውሮ ለማሰራት፣ የነዳጅና ጎማ አጠቃቀምን ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማስተዳደር፣ የፍጥነት ገደብን በመወሰን አደጋን ለመቀነስ፣ ተሸከርካሪው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የሄደበትን አቅጣጫና ምን ያህል ኪሎ ሜትር እንደተጓዘ በማሳየት የተቋሙን ሀብት ለታለመለት ዓላማ ለማዋል ትልቅ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ነሐሴ 04 ቀን 2014 ዓ.ም
15 544
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኦፊስ ሰርቪስ ፐርፎርመር 1ኛ የስራ መደብ ለመቅጠር ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ባወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለፀው አመልካቾች በሙሉ ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሜክሲኮ በሚገኘው ኬ ኬር ህንፃ ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ 20ኛ /ሃያኛ ፎቅ/ የፅሑፍ ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ በፈተናው ቦታ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
15 544
የፈተና ውጤት ማስታወቂያ
በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም በቻይልድ ኬር ጊቨር የሥራ መደብ በኮንትራት ለመቅጠር ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
ስለሆነም ከተመዘገባችሁ ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍና የቃል ፈተና ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከነሐሴ 03 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ነሐሴ 10 ቀን 2014 ዓ.ም በዋና መስሪያ ቤት ኬኬር ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ የሰራተኛ ምደባ ቢሮ የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ፎርም እንድትሞሉ እናስታውቃለን፡፡
15 544
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ
መስፈርቶቹን የምታሟሉ ሁሉ በዚህ ሊንክ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል፡፡
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLScKjpKqsOy-1lx1Bhkpt_GxRZcqVilExYecbr2_-omHYM3sfA/viewform?usp=sf_link
https://forms.gle/tHUJTwNcFbHbT3437
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
