en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 692 subscribers, ranking 8 014 in the Technologies & Applications category and 2 155 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 692 subscribers.

According to the latest data from 30 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 145 over the last 30 days and by 2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 31.28%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.96% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 909 views. Within the first day, a publication typically gains 2 661 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 31 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 692
Subscribers
+224 hours
+187 days
+14530 days
Posts Archive
በተቋሙ ላይ የተከናነው የለውጥ ሥራ ውጤት ተገኝቶበታል .......///........ መንግሥት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያከናወነው የለውጥ ሥራ ውጤት እንደተገኘበት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢ
+9
በተቋሙ ላይ የተከናነው የለውጥ ሥራ ውጤት ተገኝቶበታል .......///........ መንግሥት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል  ያከናወነው የለውጥ ሥራ ውጤት እንደተገኘበት የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ምረቃ ላይ እንደተናገሩት አርሲ በስንዴና ገብስ ምርት ብቻ ሳይሆን በኢነርጅ ዘርፍም ከፍተኛ አቅም አለው። በአካባቢው ከአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ በተጨማሪ ሁለት የከርሰ ምድር እንፋሎት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ ብለዋል። ከለውጡ በፊት በኢትዮጵያ 4 ሺህ ሜጋ ዋት አካባቢ የነበረው ኃይል የማመንጨት አቅም አሁን ላይ ወደ 10 ሺህ ሜጋ ዋት መጠጋቱን እንዲሁም 7 ቢሊዮን ብር የነበረው የተቋሙ ዓመታዊ ገቢ ከ75 ቢሊዮን ብር በላይ መድረሱን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-ላይ-የተከናነው-የለውጥ-ሥራ-ውጤት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

የፈተና ማስታወቂያ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት /Child varegivers/ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማ
+1
የፈተና ማስታወቂያ .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት /Child varegivers/ የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ሚያዚያ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ  ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ያደረጉ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ ገለፁ፡፡ ከጋና የመጡ ባለሙያዎች ተቋሙ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች የኃይል አቅርቦት ዙሪያ እያከናወናቸው ባሉ ሥራዎች ዙሪያ በተዘጋጀው የልምድ ልውውጥ መድረክ ላይ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር ያለውአይቀር ማንደፍሮ እንደገለጹት እንደ ሀገር እ.ኤ.አ እስከ 2029 የሚቆይ የብሔራዊ የኤሌክትሪክ መኪኖች ትግበራ ስትራቴጅ ተቀርጾ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገራዊ የቴክኒክ ኮሚቴ አባል ሆኖ እየሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ የአፍሪክ የታዳሽ ኃይል ማዕከል የመሆን ርዕይ ሰንቆ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል ያሉት አቶ ያለውአይቀር ኢትዮጵያ አሁን ላይ 100 ሺህ የሚደርሱ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን ወደ ሥራ በማስገባት ከአፍሪክ ቀዳሚ መሆኗንም ጠቁመዋል፡፡ ተቋሙ በስትራቴጅክ ዕቅዱ ላይ በተቀመጠው መሠረት በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ሊኖሩ የሚችሉ የኤሌክትሪክ መኪኖችን ታሳቢ በማድረግ በግሪድና በኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ ሊፈጥር የሚችለውን ተጽዕኖ በተመለከተ የባለሙያዎች ቡድን አዋቅሮ ጥናት ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የኢነርጅ ሴኪዩሪቲ ከኃይል አቅርቦት በተሻገረ የሀገር ደህንነት መሆኑን ያነሱት ተወካይ ሥራ አስፈጻሚው የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ፈጣን ቻርጀሮች በግሪዱ እና በኃይል መሰረተ ልማቶች ላይ ተፅዕኖ እንዳያሳድሩ በጥናት ላይ የተመሰረቱ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር የአየር ንብረት ለውጥ ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ይዘንጋው ይታይህ የትራንስፖርት ዘርፉ ከአየር ብክለት የጸዳ እና የዘመነ እንዲሆን እንደ ሀገር የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን በስፋት ወደ ሥራ እንዲገቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በ2030 ላይ 500 ሺህ የኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎችን እና 2 ሺህ 230 የቻርጅ ማዕከላት እንዲኖሩ በስትራቴጅው በዕቅድ ተይዞ እየተሰራበት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ይህም በዓመት ለነዳጅ የሚወጣውን ከ5 እስከ 6 ቢሊዮን ዶላር ወጪ እና ወደ ከባቢ አየር የሚለቀቀውን የበካይ ጋዝ ልቀት በ13 ነጥብ 9 ሚሊዮን ቶን ካርቦን ዳይኦክሳይድ ለመቀነስ የሚረዳ ነው ብለዋል፡፡ የጋና ልዑካን ቡድን አባልና በጋና ፐብሊክ ዩቲሊቲ ሪጉላቶሪ ኮሚሽን ሪጅናል ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ሚስተር አልሃጂ አቡካሪ በበኩላቸው ኢትዮጵያ በአፍሪክ በኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ አተገባበር ላይ የተሻለች በመሆኗ እስከ አሁን ከመጣችበትና እየተገበረቻቸው ካሉ አሰራሮች ልምድ ለመውሰድ እና በዘርፉ ውጤታማ ሥራ ለማከናወን ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውን አብራርተዋል፡፡ በኤሌክትሪክ መኪኖች ላይ ባለድርሻ የሆኑ የትራንስፖርትና የኃይል ዘርፎችን እንዲሁም ተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ላይ የልምድ ልውውጥ ማድረጋቸውንና በቆይታቸው ተጨባጭ እውቀቶችንና ልምዶችን መቅሰማቸውን ገልጸዋል፡፡ በኢትዮጵያ ለኤሌክትሪክ ተሸከርካሪዎች ትግበራ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ከፍተኛ የመንግስት አካላት ትኩረት ሰጥተው በመስራታቸው ከፍተኛ ውጤት ሊመዘገብ መቻሉን እንደታዘቡም ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+7

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቶቹን የም
ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል (EEP) በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት መቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች በ https://vacancy.eep.com.et/VacancyList በመግባት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። የምዝገባ ጊዜ፡ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል፡፡ ዝርዝሩን በተያያዘው ምስል ይመልከቱ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 5 ቀን 2018 ዓ.ም

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች፣ የተቋማችን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፤ ......///...... በመጀመሪያ እንኳን ለጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የትንሳዔ በዓል በሠላም አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ። ትንሳዔ ሞትን ድል የማድረግ፣ ከውድቀት የመነሳትና ጨለማን በብርሃን የመርታት ተምሳሌት እንደሆነው ሁሉ፣ ተቋማችንም በመንግስት ልዩ ትኩረትና እገዛ የታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ከነበረበት መጓተትና ተግዳሮት አውጥቶ ለስኬት ማብቃቱ የድል ጉዞ ማሳያ ነው።  ይህ ታላቅ ፕሮጀክት ለፍሬ መብቃቱ ልክ እንደ ትንሳዔው ሁሉ ተስፋ የመቁረጥን ጨለማ ገፎ በታላቅ ብርሃንና በድል መነሳታችንን ያበሰረበት ታላቅ አገራዊ ስኬት ነው። በተጨማሪም ትንሳዔ የአዲስና የተስፋ ምልክት እንደሆነው ሁሉ፣ ተቋማችንም በሌሎች የልማት ዘርፎች ወደ ላቀ አፈፃፀም በመሸጋገር አዲስ የታሪክ ምዕራፍ የከፈተበት ዓመት ላይ ነው። በተለይ በበጀት ዓመቱ መባቻ ላይ የታላቁ ሕዳሴ ግድብን፣ በግማሽ ዓመቱ ደግሞ የአይሻ ንፋስ ኃይል ማመንጫን ማስመረቅ መቻላችን እንዲሁም በቅርቡ የምናስመርቀው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ጨምሮ ተቋማችን ለመጀመሪያ ጊዜ ከኪሳራ ወጥቶ ወደ ትርፋማነት መሸጋገሩ ትልቁ ድላችንና የሪፎርማችን ውጤት መሆኑን በኩራት እገልፃለሁ። እነዚህ ስኬቶች ተቋማችን ለያዘው የልማት ግብና የታዳሽ ኃይል ስብጥርን ለማሳደግ ያለውን ጽኑ ቁርጠኝነት የሚያረጋግጡ ናቸው። ውጤቶቹ የሀገራችንን የኢኮኖሚ ዕድገት ለማፋጠን በሚደረገው ርብርብ ላይ ትልቅ አቅም የሚፈጥሩና የተቋማችንን ብሩህ ተስፋ የሚያመለክቱ በመሆናቸው ትርጉማቸው የላቀ ነው። በመሆኑም እያንዳንዱ የሥራ ኃላፊና ሠራተኛ እነዚህን አገራዊና ተቋማዊ ድሎችን መነሻ በማድረግ፣ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነትና በታማኝነት የአገልጋይነት መንፈስ ለሀገራችን ሁለንተናዊ ለውጥና ለተቋማችን ዘላቂ ውጤታማነት የድርሻችንን እንድንወጣጥሪዬን አቀርባለሁ። በድጋሚ በዓሉ የሠላም፣ የደስታ እና የአብሮነት ይሁንላችሁ። መልካም የትንሳኤ በዓል! ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 4 ቀን 2018 ዓ.ም

.
.

photo content

የህብረት ሥራ ማህበሩ በሥራ ምክንያት ለተጎዱ ሠራተኞች የበዓል ስጦታ አበረከተ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ ህብረት ሥራ ማህበር የሥራ አመራር ቦርድ አባላት በሥራ ላይ ጉዳት ደርሶባቸው በደጃዝማች ባልቻ ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ሠራተኞችን በመጠየቅ የበዓል ስጦታ አበርክተዋል። ይህ የማህበሩ የሰብአዊነት ተግባር ከገላን፣ ከጭሮና ከአዲስ አበባ አካባቢዎች በተለያየ የሥራ አጋጣሚ ጉዳት ደርሶባቸው በሆስፒታሉ ተኝተው ለሚታከሙ ስምንት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የተደረገ ሲሆን ለእያንዳንዳቸውም የ10 ሺህ ብር የገንዘብ ስጦታ ተበርክቶላቸዋል። በሥራ አመራር ቦርዱ የማህበራዊ ዘርፍ ሰብሳቢ አቶ ደመላሽ ንጉስ በወቅቱ እንደተናገሩት በህክምና ላይ የሚገኙት ሠራተኞች ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጡ በመሆናቸው ይህ የጥየቃ መርሃ ግብር ቤተሰባዊ ቅርርብን ለመፍጠርና ለታካሚዎቹ በጎ የሞራል ተነሳሽነትን ለመስጠት ያለመ ነው። የሥራ አመራር ቦርዱ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ ጉዳት የደረሰባቸውን የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች የማህበሩ አባል ቢሆኑም ባይሆኑም ያለምንም ልዩነት በመጠየቅና ስጦታ በማበርከት አጋርነቱን እያሳየ እንደሚገኝም አቶ ደመላሽ አብራርተዋል። የህብረት ሥራ ማህበሩ ሂሳብ ሹም ወ/ሮ ዝናሽ ደረሰ በበኩላቸው ማህበሩ የተለያዩ ማህበራዊ ኃላፊነቶችን ለመወጣት በጀት መድቦ ድጋፎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸው የሠራተኞች ጥየቃና የበዓል ስጦታውም የዚሁ ሰፊ ተግባር አካል ነው። በመሆኑም የማህበሩ አባል ያልሆኑ የሁለቱ ተቋማት ሠራተኞች ወደ ማህበሩ በመቀላቀል የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ሊያጠናክሩ እንደሚገባ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። በማህበሩ የሥራ አመራር ቦርድ የማህበራዊ ዘርፍ ጸሐፊ አቶ እስከንድር ጌታቸውም ይህ ተግባር ማህበሩ ለቁጠባና ለብድር ብቻ የተቋቋመ አለመሆኑንና በማቋቋሚያ ደንቡ የተሰጠውን ማህበራዊ ኃላፊነት ጭምር በብቃት እየተወጣ መሆኑን ትልቅ ማሳያ ነው ሲሉ ገልጸዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

🇪🇹 ⚡️ ኢትዮጵያ የኃይል ማማ (Power Hub) የመሆን ጉዞዋን አፋጥናለች! ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች። አጠቃላይ ሀገራዊ የማመንጨት አቅማችን አሁን ላይ 9,760 ሜጋ ዋት (MW) ደርሷል፤ ይህም ለኢንዱስትሪዎቻችን ዕድገትና ለቀጣናዊ ትስስር ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ይታመናል፡፡ 🇪🇹የውሃ ኃይል ማመንጫዎቻችን ድርሻ በኃይል ማመንጨት ሂደት ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዙት የውሃ ኃይል ማመንጫዎቻችን ሲሆን ከሚመነጨው 96% አስተዋጽዖ አላቸው፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD)፦ በ 5,150 MW ግዙፍ አቅሙ የኃይል ማመንጫችን በመሆን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ከመነጨው የ51% ድርሻ ነበረው፡፡ ጊቤ III (1,870 MW)፣ በለስ (460 MW) እና ሌሎችም የኃይል ማመንጫዎች እንደ ማመንጨት አቅማቸው ለኃይል አቅርቦቱ የራሳቸውን አስተዋጽዖ በማበርከት ላይ ይገኛሉ። እያደገ የመጣው የንፋስ እና የሌሎች ታዳሽ ኃይሎች ድርሻ የንፋስ ኃይል (~504 MW)፦ በአዳማ፣ በአሸጎዳ፣ በአይሻ እና በአሰላ የሚገኙ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የንፋስ ኃይል ቀዳሚ እያደረጓት ይገኛሉ። ♻️ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ፡- በረጲ የተገነባው ከደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአፍሪካ የመጀመሪያው ጣቢያ ሲሆን ከኃይል ማመንጨት በተጓዳኝ የከተማዋን ቆሻሻ በማስወገድ ረገድ አርአያ የሆነ ተግባር እያከናወነ ነው፡፡ ♨️🌋 ጂኦተርማል፦ በአሉቶ ላንጋኖ፣ በቱሉ ሞዬና በኮርቤቲ የሚከናወኑ የከርሰ-ምድር እንፋሎት ፍለጋዎች አዲስ የኃይል አማራጭ ይዘውልን እየመጡ ነው። ቀጣይ ግባችን - የማመንጨት አቅምን 17,000 ሜጋ ዋት ማድረስ! የሀገራችንን የኃይል አቅርቦት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በግንባታና በሂደት ላይ ይገኛሉ፦ ኮይሻ (1,800 MW) የውሃ ኃይል ማመንጫ፤ አይሻ I እና III የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች ቱሉ ሞዬ እና ኮርቤቲ የግል ባለሀብቶች (IPPs) የሚሳተፉባቸው ግዙፍ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ 🇪🇹 ኢትዮጵያ የራሷን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ የቀጣናው የኢኮኖሚ ትስስር ማዕከል እየሆነች ነው። ይህ የሁላችንም ኩራትና የብልጽግናችን መሠረት ነው!

photo content
+2

የማከፋፈያ ጣቢያው መጠናቀቅ የኢንዱስትሪ ፓርኩን የኃይል ፍላጎት ያሟላል ….….///…….. የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክን የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለ
+4
የማከፋፈያ ጣቢያው መጠናቀቅ የኢንዱስትሪ ፓርኩን የኃይል ፍላጎት ያሟላል ….….///…….. የይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክን የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመረው የወይናንታ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ የጀመሩ ፋብሪካዎችን የኃይል ጥያቄ እንደሚመልስ የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ባዴጎ በቀለ እንደገለፁት የወይናናታ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ከ50 ሜጋ ዋት በላይ ኤሌክትሪክ ያቀርባል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪ ፓርኩ ምርታቸውን ለሀገር ውስጥና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ እየሰሩ ለሚገኙ ዘጠኝ ፋብሪካዎች እያቀረበ ያለው የኃይል መጠን 12 ሜጋ ዋት ብቻ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያው-መጠናቀቅ-የኢንዱስት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

⚡️🇪🇹 የኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍና የግል ባለሀብቶች ተሳትፎ፦ ከውጥን ወደ ተግባር! ኢትዮጵያ የኃይል ማመንጨት ዘርፉን ለግል ባለሀብቶች (Independent Power Producers - IPPs)
⚡️🇪🇹 የኢትዮጵያ የኃይል ዘርፍና የግል ባለሀብቶች ተሳትፎ፦ ከውጥን ወደ ተግባር! ኢትዮጵያ የኃይል ማመንጨት ዘርፉን ለግል ባለሀብቶች (Independent Power Producers - IPPs) ክፍት በማድረግ አዲስ ምዕራፍ ጀምራለች። ይህ ታሪካዊ ውሳኔ የሀገሪቱን ታዳሽ የኃይል ፀጋ በግል ባለሀብቶች የፋይናንስና የቴክኖሎጂ አቅም በማልማት የኢኮኖሚ ዕድገታችንን ለማፋጠን ትልቅ ዕድል ይፈጥራል። 🏗⚡️ በዘርፉ ለመሰማራት ተግዳሮቶች አይኖሩም ወይ? በእርግጥ እንደማንኛውም ግዙፍ ኢንቨስትመንት፣ በኃይል ግዥ ስምምነት (PPA)፣ በመሬት አቅርቦትና በጸጥታ ሁኔታዎች ዙሪያ ፈታኝ ሁኔታዎች ሊያጋጥሙ ይችላሉ። ሆኖም መንግሥት እነዚህን መሠረታዊ እንቅፋቶች ለመቅረፍ ቁርጠኝነቱን በተግባር እያሳየ ይገኛል፡፡ ⚡️🇪🇹 የማክሮ-ኢኮኖሚ ማሻሻያ፡ 💡 የምንዛሪ ተመን በገበያ እንዲወሰን መደረጉ ባለሀብቶች ትርፋቸውን በቀላሉ ወደ ውጭ መላክ (Repatriation) እንዲችሉ መንገድ ይከፍታል። ⚡️🇪🇹 የታሪፍ ማሻሻያ፡ 💡 የኤሌክትሪክ ሽያጭ ዋጋ ከማምረቻ ወጪው ጋር እንዲመጣጠን መደረጉ ፕሮጀክቶች አትራፊና በራሳቸው የሚቆሙ (Bankable) እንዲሆኑ ያስችላል። ⚡️🇪 የPPP ሕግና መዋቅር፡ 💡 በመንግሥትና በግል አጋርነት አዋጅ አማካኝነት የባለሀብቱ መብትና ግዴታ በግልጽ ተቀምጧል። ⚡️🇪🇹 የአንድ ማዕከል አገልግሎት፡ 💡 ቢሮክራሲን በማሳጠር ባለሀብቶች ፈቃድና መሬት በቀላሉ እንዲያገኙ እየተደረገ ነው። 🏗⚡️ የግል ዘርፉ ተሳትፎ ሲጎለብት የኃይል አቅርቦታችን አስተማማኝነት ያድጋል፡፡ የኢንዱስትሪ ፓርኮቻችን በሙሉ አቅማቸው የሚያመርቱበት ሁኔታ ይፈጠራል፡፡ ሀገራችን የቀጣናው የኃይል ማዕከል የመሆን ራዕይዋ እውን ይሆናል!

የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ከ65 መቶ በላይ ተጠናቋል ……...///…..…. የሺግዳን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ አፈፃፀም ከ65 በመቶ በላይ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ
+6
የማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ከ65 መቶ በላይ ተጠናቋል ……...///…..…. የሺግዳን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ አፈፃፀም ከ65 በመቶ በላይ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት የሳይት 2 ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አርጋው ታዲ እንዳስታወቁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራ 70 በመቶ እንዲሁም የኤሌክትሮሜካኒካል ሥራ 35 በመቶ ተጠናቋል። በአሁኑ ወቅት የአምስት ትራንስፎርመሮች እና የሁለት ሻንት ሪአክተሮችን ተከላ በማጠናቀቅ ዘይት የመሙላት ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያው-ግንባታ-ከ65-መቶ-በላይ-ተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም

ለፓርኩ የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው ……..///……... የወይናንታ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል ሥራ ከ71 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ
+5
ለፓርኩ የኃይል አቅርቦት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እየተሰራ ነው ……..///……... የወይናንታ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል ሥራ ከ71 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች አስተባባሪ አስታወቁ፡፡ አስተባባሪው አቶ ኤሊያስ መሀመድ እንደገለፁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ ለይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ያስችላል። ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ኃይል ለማቅረብ ከአራት ዓመት በፊት ሥምምነት ቢፈረምም በወቅቱ ከውጭ ምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ ግንባታው መዘግየቱን ገልፀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ለፓርኩ-የኃይል-አቅርቦት-ጥያቄ-ምላሽ-ለመ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም

🇪🇹⚡️ 🇪🇹 የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ጸጋ፦ ያልተነካው ግዙፍ የኢንቨስትመንት ዕድል! ኢትዮጵያ በታዳሽ የኃይል ምንጮች የታደለች ሀገር ብትሆንም፣ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው እምቅ አቅም ከመቶ ሰባት (7%) እንኳን አይበልጥም። ይህ ክፍተት ዘርፉ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ኢንቨስትመንት ምን ያህል ክፍት እንደሆነ ማሳያ ነው። ዋነኞቹን የኃይል አማራጮች፣ ያላቸውን እምቅ አቅም እና በሀገሪቱ ያላቸውን ስርጭት እንደሚከተለው በዝርዝር ማየት ይቻላል፦ 🇪🇹⚡️ የንፋስ ኃይል (Wind Energy) ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የንፋስ ኃይል እምቅ አቅም ካላቸው ቀዳሚ ሀገራት አንዷ ናት። 💡 አጠቃላይ እምቅ አቅም፦ 1,350 ጊጋ ዋት (GW) በላይ፤ 🌱 ተስማሚ አካባቢዎች፦ የንፋስ ፍጥነታቸው በሰከንድ ከ6.5 ሜትር በላይ የሆኑ አካባቢዎች ለኃይል ማመንጫነት ይመረጣሉ። 💨 ⚡️ ክልላዊ ስርጭት፦ 📍 o ትግራይ ክልል፦ መቐለና አካባቢው፤ o ሶማሌ ክልል፦ አይሻ (Aysha) — ይህ አካባቢ በሀገሪቱ ከፍተኛው የንፋስ ፍጥነት ያለበት ነው፤ 🌪 o ኦሮሚያ ክልል፦ አዳማ፣ ኢተያ (Iteya) እና የምሥራቅ ሸዋ አካባቢዎች፤ o አማራ ክልል፦ ደብረ ብርሃንና የሰሜን ወሎ አካባቢዎች። የፀሐይ ኃይል (Solar Energy) ☀️🔅 ኢትዮጵያ በምድር ወገብ አቅራቢያ የምትገኝ በመሆኗ ዓመቱን ሙሉ ከፍተኛ የፀሐይ ብርሃን ታገኛለች። 💡 አጠቃላይ እምቅ አቅም፦ በዓመት 2.1 ሚሊዮን ቴራዋት ሰዓት (TWh)፤ በአማካይ በቀን በአንድ ካሬ ሜትር ላይ 5.5 ኪሎዋት ሰዓት (kWh) ኃይል ማግኘት ይቻላል። ክልላዊ ስርጭት፦ o ከፍተኛ አቅም ያላቸው፦ አፋር፣ ሶማሌ፣ ትግራይ፣ አማራ እና ምሥራቅ ኢትዮጵያ፤ o መካከለኛ አቅም ያላቸው፦ ኦሮሚያ እና ደቡብ ኢትዮጵያ። ☀️ ልዩ ባህሪ፦ የፀሐይ ኃይል በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ከግሪድ ጋር ላልተገናኙ (Off-grid) የገጠር ማህበረሰቦች ተደራሽ ለማድረግ እጅግ አመቺ ነው። 🇪🇹⚡️ የጂኦተርማል ኃይል (Geothermal Energy) 🌋♨️ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ (Rift Valley) መካከል ላይ በመገኘቷ ከፍተኛ የከርሰ-ምድር እንፋሎት አቅም አላት። 💡 አጠቃላይ እምቅ አቅም፦ ከ 10,000 ሜጋ ዋት (MW) በላይ። ⚡️ ክልላዊ ስርጭት፦ 📍 በዋነኝነት በስምጥ ሸለቆው መስመር ላይ በሚገኙት አፋርና ኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ ይገኛል። 🌱 ተስማሚ አካባቢዎች፦ አሉቶ ላንጋኖ (Aluto Langano)፣ ኮርቤቲ (Corbetti)፣ ቱሉ ሞዬ (Tulu Moye) እና ፈንታሌ፤ ጥቅሙ፦ እንደ ንፋስና ፀሐይ ሳይሆን፣ ጂኦተርማል በቀን 24 ሰዓትና ዓመቱን ሙሉ ያለማቋረጥ ኃይል የመስጠት (Base-load) ብቃት አለው።

photo content

🇪🇹⚡️ 🇪🇹 የኢትዮጵያ የታዳሽ ኃይል ጸጋ፦ ያልተነካው ግዙፍ የኢንቨስትመንት ዕድል! ኢትዮጵያ በታዳሽ የኃይል ምንጮች የታደለች ሀገር ብትሆንም፣ እስካሁን ጥቅም ላይ የዋለው እምቅ አቅም ከመቶ ሰባት (7%) እንኳን አይበልጥም። ይህ ክፍተት ዘርፉ ለሀገር ውስጥና ለውጭ ኢንቨስትመንት ምን ያህል ክፍት እንደሆነ ማሳያ ነው። ዋነኞቹን የኃይል አማራጮች፣ ያላቸውን እምቅ አቅም እና በሀገሪቱ ያላቸውን ስርጭት እንደሚከተለው በዝርዝር ማየት ይቻላል፦ 🇪🇹⚡️ የንፋስ ኃይል (Wind Energy) ኢትዮጵያ በአፍሪካ ከፍተኛ የንፋስ ኃይል እምቅ አቅም ካላቸው ቀዳሚ ሀገራት አንዷ ናት። 💡 አጠቃላይ እምቅ አቅም፦ 1,350 ጊጋ ዋት (GW) በላይ፤ 🌱 ተስማሚ አካባቢዎች፦ የንፋስ ፍጥነታቸው በሰከንድ ከ6.5 ሜትር በላይ የሆኑ አካባቢዎች ለኃይል ማመንጫነት ይመረጣሉ። 💨 ⚡️ ክልላዊ ስርጭት፦ 📍 o ትግራይ ክልል፦ መቐለና አካባቢው፤ o ሶማሌ ክልል፦ አይሻ (Aysha) — ይህ አካባቢ በሀገሪቱ ከፍተኛው የንፋስ ፍጥነት ያለበት ነው፤ 🌪 o ኦሮሚያ ክልል፦ አዳማ፣ ኢተያ (Iteya) እና የምሥራቅ ሸዋ አካባቢዎች፤ o አማራ ክልል፦ ደብረ ብርሃንና የሰሜን ወሎ አካባቢዎች። የፀሐይ ኃይል (Solar Energy) ☀️🔅 ኢትዮጵያ በምድር ወገብ አቅራቢያ የምትገኝ በመሆኗ ዓመቱን ሙሉ ከፍተኛ የፀሐይ ብርሃን ታገኛለች። 💡 አጠቃላይ እምቅ አቅም፦ በዓመት 2.1 ሚሊዮን ቴራዋት ሰዓት (TWh)፤ በአማካይ በቀን በአንድ ካሬ ሜትር ላይ 5.5 ኪሎዋት ሰዓት (kWh) ኃይል ማግኘት ይቻላል። ክልላዊ ስርጭት፦ o ከፍተኛ አቅም ያላቸው፦ አፋር፣ ሶማሌ፣ ትግራይ፣ አማራ እና ምሥራቅ ኢትዮጵያ፤ o መካከለኛ አቅም ያላቸው፦ ኦሮሚያ እና ደቡብ ኢትዮጵያ። ☀️ ልዩ ባህሪ፦ የፀሐይ ኃይል በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ከግሪድ ጋር ላልተገናኙ (Off-grid) የገጠር ማህበረሰቦች ተደራሽ ለማድረግ እጅግ አመቺ ነው። 🇪🇹⚡️ የጂኦተርማል ኃይል (Geothermal Energy) 🌋♨️ ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ (Rift Valley) መካከል ላይ በመገኘቷ ከፍተኛ የከርሰ-ምድር እንፋሎት አቅም አላት። 💡 አጠቃላይ እምቅ አቅም፦ ከ 10,000 ሜጋ ዋት (MW) በላይ። ⚡️ ክልላዊ ስርጭት፦ 📍 በዋነኝነት በስምጥ ሸለቆው መስመር ላይ በሚገኙት አፋርና ኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ ይገኛል። 🌱 ተስማሚ አካባቢዎች፦ አሉቶ ላንጋኖ (Aluto Langano)፣ ኮርቤቲ (Corbetti)፣ ቱሉ ሞዬ (Tulu Moye) እና ፈንታሌ፤ ጥቅሙ፦ እንደ ንፋስና ፀሐይ ሳይሆን፣ ጂኦተርማል በቀን 24 ሰዓትና ዓመቱን ሙሉ ያለማቋረጥ ኃይል የመስጠት (Base-load) ብቃት አለው።