en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 544 subscribers, ranking 8 357 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 544 subscribers.

According to the latest data from 01 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 22 over the last 30 days and by 4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.24%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.50% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 921 views. Within the first day, a publication typically gains 2 563 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 544
Subscribers
+424 hours
-357 days
+2230 days
Posts Archive
photo content
+2

ከአቢአዲ - አድዋ በተዘረጋው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የፍተሻ ሥራ ተጀመረ ……....//.......... ከአቢአዲ- አድዋ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የፍተሻ ሥራ መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና እና ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቴ እንደገለፁት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን የፍተሻ ሥራ በፍጥነት በማጠናቀቅ ጥገናውን ለማስጀመር እየተሰራ ነው። የፍተሻ ሥራው እየተከናወነ የሚገኘው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን የጉዳት መጠን ለማወቅ እንደሆነ የገለፁት አቶ ተስፋዬ ጥገናውን እስከ ቀጣይ ሳምንት ለማጠናቀቅ ዕቅድ እንደተያዘም ነው የጠቆሙት። የአቢአዲ - አድዋ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የጥገና ሥራ ሲጠናቀቅ ለአክሱም እና አድዋ እንዲሁም በአቅራቢያቸው ለሚገኙ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ለመስጠት እንደሚያስችል ገልፀዋል። ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የነዳጅና የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት፣ የፀጥታ ስጋቶች፣ የተሽከርካሪዎች ጥገና በአካባቢዎቹ ያለመኖር፣ የመልክዐ - ምድሩ ተራራማነትና የአየር ሁኔታው ሞቃታማ መሆን በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ለመጠገን ፈታኝ ሆኖ ነበር። ይሁን እንጂ ይላሉ አቶ ተስፋዬ የወልቃይት - ሰቲት ሁመራ አስተዳደርና ማህበረሰብ እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት የጥገና ሠራተኞች የፀጥታ ስጋት እንዳይገጥማቸው ከማድረግ ጀምሮ ነዳጅ በሚፈለገው መጠን በማቅረብ የጥገና ሥራው በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ በማድረጋቸው ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል። የተቋሙ የጥገና ሠራተኞች የጥገና ሥራውን በዕቅድ ከተያዘው ጊዜ ባነሰ ለማጠናቀቅ ያደረጉት ርብርብ የሚደነቅ መሆኑን የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ ለከፈሉት ዋጋ ምስጋና እንደሚቸራቸው ተናግረዋል። እየተካሄደ ባለው የጥገና ሥራ ላይ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ የተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን እንዲሁም የራስ ኃይል ሠራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 06 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ክፍት የሥራ ማስታወቂያ
ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

photo content

photo content
+3

የወልዲያ ዶሮ ግብር ማከፋፋያ ጣቢያ ግንባታ ሥራ 65 በመቶ ተጠናቀቀ ……///…… የወልዲያ ዶሮ ግብር ባለ 230/33/15 የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ አጠቃላይ ሥራ 65 በመቶ መጠናቀቁን በማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የግንባታው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ አስኪያጅ አብርሃም አባተ እንዳስታወቁት የዶሮ ግብር 230/33/15 ኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፋያ ጣቢያ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር ሲኖረው፤ አምስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር አለው፡፡ ጣቢያው አንድ 63 ሜጋ ቮልት አምፒር የሆነ 230/33/15 ትራንስፎርመር ያለው መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ የኤሌክትሮ መካኒካል አጠቃላይ ሥራው 34 በመቶ መድረሱን፣ የመቆጣጠሪያ ክፍሉ እና የስዊችያርድ ሥራዎች በአብዛኛው መጠናቀቃቸውንም ገልፀዋል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው የሲቪል ሥራዎች ሥራ አስኪያጅ ቴዎድሮስ ከፈለኝ በበኩላቸው የሲቪል ሥራው 94 በመቶ መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ የዲዛይን ለውጥ ተደርጎበት ለላሊበላ 66 ኪሊ ቮልት እንዲሰጥ ታስቦ የነበረው የዶር ግብር ማከፋፈያ ጣቢያ አሁን የአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ በመጀመሩ ምክንያት ወደነበረበት እንዲመለስ ተደርጓል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጆቹ ገለፃ ከነባሩ የወልዲያ 66 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል እያገኙ የነበሩት ሃራ፣ ጭፍራ፣ ሮቢት፣ ጎብዬ እና አካባቢው ከዶሮ ግብር የማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ማግኘት እንዲችሉ እየተሰራ ነው፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያው ከተንቀሳቃሽነት ጣቢያነት ወደ ቋሚነት በመቀየሩ በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚነሳውን የኃይል ጥያቄ መልስ መስጠት እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡ የዶሮ ግብር ማከፋፈያ ጣቢያ ከተጀመረ ስምንት ወራት የሆነው ሲሆን በቀጣዮቹ ሁለት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ኢንጅነር አብርሃም ገልፀዋል፡፡ የግንባታው አፈፃፀም 65 በመቶ የደረሰ ሲሆን 80 ለሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ፈጥሯል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 04 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

በተጀመረውን የፀረ - ሙስና ንቅናቄ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞች ሊሳተፉ ይገባል ..........///……..... በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጀመረውን የፀረ - ሙስና ንቅናቄ ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞች ሊሳተፉ እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፀረ-ሙስና እና ሥነ-ምግባር ጽ/ቤት ሥራ አስፈፃሚ አቶ መርጋ ተረፈ አሳሰቡ፡፡ ዓለም አቀፍ የፀረ- ሙስና ቀንን የጊቤ 1ኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ እና የምስራቅ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ሠራተኞችሲያከብሩ ሥራ አስፈፃሚው ባቀረቡት ጽሑፍ እንደገለፁት ሙስና በሀገሪቱ እያሳደረ ያለውን ሁሉንአቀፍ ኪሳራ አጥብቆ መታገል ይገባል። ሥራ አስፈፃሚው በጽሑፋቸው ስለሙስና ትርጉምና መገለጫዎቹ፣ የሙስና እና ብልሹ አሰራር መንስኤዎች፣ የሙስና ዓለም አቀፍዊ ሁኔታና በኢትዮጵያ ላይ ስላሳደረው ተፅዕኖ፣ ስለስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ትግሉ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መረጃ አቅርበዋል፡፡ የሙስና ወንጀል ድንጋጌዎች፣ በሥልጣን ያለ አግባብ ስለመገልገል፣ የማይገባ ጥቅም ሰለመቀበል፣ የመንግሥት ሥራን በማያመች አኳኋን ስለመምራት፣ በሥልጣን ስለመነገድ፣ ያለአግባብ ጉዳይን ስለማጓተት፣ ዋጋ ያለውን ነገር ያለክፍያ ወይም ያለበቂ ክፍያ ስለማግኘት፣ በሌለው ሥልጣን ስለመጠቀም በሚሉ ጉዳዮች ላይ የሥራ ክፍሉ ባለሙያዎች ለመርሀግብሩ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የፀረ-ሙስና ቀን ሲከበር አሁን የተጀመረውን ንቅናቄ ወደ ህብረተሰቡ በትክክል ማውረድ በሚያስችል አግባብ መሆን እንዳለበትም አመልክተዋል። ሠራተኛው ለተጀመረው የፀረ-ሙስና ትግል የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክትም ነው መልዕክት ያስተላለፉት። የዘንድሮው የፀረ-ሙስና ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ እንዲሁም በኢትዮጵያ ለ18ኛ ጊዜ "ሙስናን መታገል በተግባር" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 03 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ላይ በተፈጸመ ስርቆት ተቋሙ የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ አጋጥሞታል ………///……… በ2014 ዓ.ም ብቻ ከኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ላይ በተሰረቀ 756 ቶን ብረት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ እንዳጋጠመው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የምስራቅ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚያስተዳድራቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ተደጋጋሚ ስርቆት እየተፈፀመ ነው፡፡ በ2014 ዓ.ም ብቻ 24 የሚደርሱ ከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊ የብረት ማማዎች ሙሉ ለሙሉ ተቆርጠው የወደቁ ሲሆን የብረትና የኮንዳክተር ዘረፋ እንደተፈጸመባቸው እና በቁጥር 30 ሺ 257 የሚሆኑ የተለያዩ የታወር ብረቶች ደግሞ በቁማቸው ካሉ ማማዎች ተፈታተው መወሰዳቸውን ገልጸዋል፡፡ ከወደቁትና በቁማቸው ከተዘረፉት ማማዎች 756 ቶን ብረት መሰረቁን የተናገሩት ዳይሬክተሩ ይህም በገንዘብ ሲሰላ 72 ነጥብ ሶስት ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪሳራ መድረሱንና የተሰረቀውን ብረት መልሶ ለመተካት ተቋሙ 23 ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ብር ማወጣቱን አስታውቀዋል፡፡ በ2014 ዓ.ም በስርቆት፣ በመልሶ ግንባታና ከአገልግሎት መቋረጥ ጋር ተያይዞ የባከነውን 2 ሺ 396 ሜጋ ዋት ሰዓት ኃይል ጨምሮ ተቋሙ ከመቶ ሚሊዮን ብር ያላነሰ ኪሳራ እንዳጋጠመው ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በበኩላቸው ስርቆትን ለመከላከል ከህብረተሰብ ተወካዮች፣ ከጸጥታ እና ከፍትህ አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይቶች መካሄዳቸውንና ውጤት እያስገኘ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች በህብረተሰቡና በባለድርሻ አካላት ትብብር ወንጀሉን ለመከላከል ቢሞከርም በሌሎች አካባቢዎች አሁንም ችግሩ መቀጠሉን ገልጸዋል፡፡ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ተከሰው በሚቀርቡ ወንጀለኞች ላይ የፍትህ አካላት የሚጥሉት ቅጣት አስተማሪ አለመሆኑና ግብዓት ለማግኘት ሲሉ ስርቆቱን የሚደግፉና የሚረከቡ የብረታብረት ፋብሪካዎችና ባለሀብቶች እንቅስቃሴ ሊፈተሸ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 03 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+6

ሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ከሁለት ዓመት በኋላ ኤሌክትሪክ አግኝቷል ……….////……… ከሁለት ዓመት በላይ ኤሌክትሪክ ተቋርጦበት የቆየው ሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል አግኝቷል፡፡ አካባቢው ከሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያገኝ የነበረ በመሆኑ አስቸጋሪ መልክዐምድርና የአየር ሁኔታ ያለው የሁመራ - ሽሬ 230 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ሲጠገን ቆይቷል። ይሁንና ጥገናው ተጠናቆ ከሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ለማገናኘት ሲሞከር ከተከዜ ወደ ሽሬ የሚመጣው መስመር ላይ ችግሮች በማጋጠሙ ኃይል ሽሬ ከተማ ለማድረስ አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጥሮ እንደነበር መግለፃችን ይታወሳል። አስቸጋሪ የነበረው የተከዜ መስመር ጥገና ከተጠናቀቀ በኋላ ሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ማድረስ ተችሏል። በመሆኑም ከሁመራ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ያገኙ የነበሩ ከተሞች በሙሉ ኃይል የሚያገኙበት ሁኔታ ተፈጥሯል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን በተከናወነው ሥራ የተገኘው ውጤት እንዳስደሰታቸው ገልፀዋል። በቀጣይም ኃይል ያላገኙ አካባቢዎችን መልሶ ለማገናኘት በትኩረት እንደሚሰራ አስታውቀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 02 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content
+8

ተቋሙ የዓለም የኤችአይቪ/ኤድስ እና የፀረ-ፆታዊ ጥቃት ቀንን አከበረ …….//…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞችና ሥራ አመራሮች ዓለም አቀፍ የኤችአይቪ/ኤዲስ እና   የፀረ- ፆታዊ ጥቃት  ቀንን በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አክብረዋል፡፡ በመርሃ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት በተቋሙ የሴቶች፣ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንደገለፁት በሴቶችና ህፃናት ላይ እየተፈፀሙ ያሉ ጥቃቶችንና ትንኮሳዎችን ያለወንዶች ተሳትፎ መቀነስም ሆነ መቆጣጠር አይቻልም፡፡ ፆታዊ ጥቃትን ለመከላከል እንዲቻል ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የድርሻውን እንዲወጣም ነው ዳይሬክተሯ  የጠየቁት፡፡ የተቋሙን  ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ በበኩላቸው ተቋሙ የሴቶችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የተለያዩ አሰራሮችን ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ሴቶች ለሀገር ብልፅግና እና ዕድገት የማይተካ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ በማህበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ኋላቀር አመለካከቶች መቅረፍ እንደሚገባም አሳስበዋል። በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ዓለም አቀፋዊ ቀውሶች መሆናቸውን ያነሱት አቶ ሙላት ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች ለሴቶች ተገቢውን ክብር በመስጠትና ከጥቃት በመከላከል የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል። የኤችአይቪ ቫይረስ በደማቸው ውስጥ የሚገኝ የተቋሙ ሠራተኞች ተገቢውን ድጋፍና አገልግሎት እንዲያገኙ የተቋሙ ሥራ አመራር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራም ነው ያረጋገጡት፡፡ የተቋሙ የህግ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ ስለ ሴቶች መብትና ፆታዊ ጥቃት፣ ስለ ሰብዓዊ መብት ምንነት፣ ስለሚያስከትለው ውጤት፣ ስለ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጉዳትና መንስኤዎቹ እንዲሁም ስለ ህግ ማዕቀፎቹ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሁፍ አቅርበዋል። በተያያዘ ዜና የተቋሙ የኤችአይቪ/ኤድስ መከላከያና መቆጣጠሪያ ቢሮ አስተባባሪ አቶ ዓለምሰገድ ባሲሊዮስ የኤች.አይ. ቪ/ ኤድስ ሥርጭትና የመቆጣጠር ሒደቱን አስመልክቶ ለመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል። በተቋሙ የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዲሁም ፕሮጀክቶች ላይ ለሚገኙ ሠራተኞች በኤችአይቪ/ ኤድስ እና አባላዘር በሽታዎች ላይ ያተኮሩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል። ዓለም አቀፍ የኤችአይቪ/ኤድስ ቀን በሀገራችን "ፍትሐዊና ተደራሽ የኤችአይቪ/ኤድስ አገልግሎት" በሚል መሪ ቃል በመከበር ላይ እንደሚገኝ የጠቆሙት አስተባባሪው መሪ ቃሉ አገልግሎቱን ተደራሽ የማያደርጉ አለመመጣጠኖች መወገድ እንዳለባቸው የሚያሳይ ነው ብለዋል። የፀረ-ፆታዊ ቀን በዓለም ለ31ኛ ጊዜ እንዲሁም በሀገራችን ለ17ኛ ጊዜ"ሴትን አከብራለሁ፤ ጥቃቷንም እከላከላለሁ" በሚል መሪ ቃል ከህዳር 16 እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እየተከበረ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

የከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይልን በመጠቀም ሀገርን መለወጥ ይቻላል ………///………. የከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይልን በመጠቀም ሀገርን መለወጥ እንደሚቻል የከርሰምድር እንፋሎት የቁፋሮ ኢንጂነር ሰለሞን ከበደ ገለፁ፡፡ ኢንጂነር ሰለሞን እንደገለፁት የከርሰምድር እንፋሎትን ከኤሌክትሪክ ኃይል ባለፈ ለጨርቃጨርቅ፣ ለኮንስትራክሽን፣ ለለስላሳና ለአልኮል መጠጥ ኢንዲስትሪዎች፣ ለመዝናኛ፣ ለፈውስና ለሌሎችም ዘርፎች መጠቀም ይቻላል፡፡ አብዛኛው ኢንዱስትሪ የእንፋሎት ኃይልን የሚፈልግ ቢሆንም እንደሀገር ያለውን እምቅ ሀብት ለማልማት ብዙ ሥራ መስራት እንደሚፈልግ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በከርሰምድር እንፋሎት ሀብት በተፈጥሮ የታደለች ብትሆንም ከሀብቷ የተጠቀመችው ግን እጅግ ጥቂቱን ብቻ ነው ብለዋል፡፡ ዘርፉ ከፍተኛ ፋይናንስ፣ የሰለጠነ የሰው ኃይልና ቴክኖሎጂ የሚጠይቅ በመሆኑ ኢትዮጵያ እንደሀገር ያላትን ሀብት በማልማት የዜጎቿን ህይወት ለማሻሻል የጀመረቻቸው ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እንደ ኢንጂነር ሰሎሞን ገለፃ በአሉቶ ላንጋኖ ፕሮጀክት የሀገር ውስጥ ባለሙያዎች ከውጭ ሀገራት ባለሙያዎች ጋር በመሆን ልምድ እንዲቀስሙ የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል፡፡ የትምህርትና ምርምር ተቋማትም የዘርፉን ዕድሎች በአግባቡ በማሳየት የመሪነት ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ባለሙያው ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም

ሽረ ከተማ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አገኘች ……….////……… በትግራይ ክልል የምትገኘው ሽረ ከተማ ከረጅም ጊዜ በኋላ ዳግም የኤሌክትሪክ ኃይል አግኝታለች፡፡ ከሁመራ እስከ ሽሬ ያለው 230 ኪሎ ሜትር ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ በሶስቱም ጥምር መስመሮች ያጋጠሙት 92 ቦታዎች ሙሉ በሙሉ ቢጠገኑም ከተከዜ የሚመጣው መስመር ላይ ችግሮች በማጋጠማቸው ኃይል ሽሬ ከተማ ማድረስ አልተቻለም ነበር፡፡ ይሁንና አስቸጋሪ የነበረውን ከተከዜ እስከ ሽሬ ያለው የ160 ኪሎ ሜትር የጥገና ሥራ በስኬት በመጠናቀቁ ሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ማምሻውን የተሳካ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙከራ ተደርጓል፡፡ ይህም ከሁለት ዓመት በላይ ኃይል ተቋርጦባቸው ለቆዩት ወልቃይት፣ ሁመራና አካባቢያቸው ኃይል ለማድረስ የተጀመረውን ጥረት እንደሚያፋጥነው ይታመናል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ባጠናቀቀቻቸውና ኃይል ዝግጁ ባደረገባቸው አካባቢዎች የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሥርጭት መስመሮች እንደተጠናቀቁ ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ እንደሚያገኝ ይጠበቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ ባስተላለፉት መልዕክት በጥገና ሥራው ላይ የተቋሙ ሰራተኞች ያሳዩትን ጽናትና ቁርጠኝነት አድንቀው የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶችን ለመጠገን የተከናወነው ሥራ መንግስት ለሰላም ስምምነቱ መተግበር ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 29 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5