en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 542 subscribers, ranking 8 329 in the Technologies & Applications category and 2 179 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 542 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 31 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.36%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 097 views. Within the first day, a publication typically gains 2 520 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 542
Subscribers
-124 hours
-167 days
+3130 days
Posts Archive
photo content
+5

የወልዲያ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል ስራ 90 በመቶ፣ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራ ደግሞ 20 በመቶ ተጠናቋል ……….////………. የወልዲያ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል ስራ 90 በመቶ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደገለፁት ለወልዲያና አካባቢው አገልግሎት ይሰጥ የነበረው ተንቀሳቃሽ የማከፋፈያ ጣቢያ በአሸባሪው የህወኃት ቡድን ሙሉ በሙሉ ተነቅሎ በመወሰዱ ምክንያት ከየካቲት 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በምትኩ ቋሚ የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ እየተከናወነ ነው፡፡ ፕሮጀክቱን በተያዘለት የጊዜ መርሐ ግብር መሰረት ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝና የሲቪል ሥራዎች አፈፃፀም 90 በመቶ መድረሱን አቶ ቴዎድሮስ ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በአሁኑ ወቅት የስዊችያርድ እና የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቦታዎች ግንባታ ስራ ሙሉ ለሙሉ ሲጠናቀቅ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል ግንባታ ስራ በመገባደድ ላይ ነው፡፡ ቀሪ የሲቪል ስራዎችን እስከ ሰኔ 30 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ለማጠናቀቅ በርብርብ እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ከፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች በተጓዳኝ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎችም በቅንጅት እየተሰሩ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሱፐርቫይዘር አቶ ጌታሁን ገበየሁ በበኩላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ዘጠኝ ባለ 15 እና አንድ ባለ 66 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት አስታውቀዋል፡፡ የባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር የማስተካከልና የግራውንድ ሽቦዎችን የመትከል እንዲሁም የገቢ መስመር መቆጣጠሪያ የመትከል ሥራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ በቀጣይ ትራንስፎርመር ለመትከል የሚያስችል ሥራ እየተሰራ መሆኑን ሱፐርቫይዘሩ ጠቁመው አጠቃላይ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራው 20 በመቶ መድረሱን ገልፀዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ላይ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው መካከል አቶ ዳዊት ደምሴ፣ ወ/ሮ እርጎ መንገሻ እና አቶ ዝናቤ ግዴ እንደተናገሩት ለወልዲያና አካባቢው ማህበረሰብ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማስገኘት በተጀመረው ሥራ ተሳትፈው ገቢ በማግኘታቸውና ተጠቃሚ በመሆናቸው መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ ግንባታው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ቢሮ አስራ ሁለት ሚሊየን ብር በሚጠጋ በጀት እየተከናወነ ሲሆን በራስ ኃይል መሰራቱ ተቋሙ ሊያወጣ የሚችለውን የውጭ ምንዛሪ በማስቀረትና የራስ የመፈፀም አቅምን በማሳደግ በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ይታመናል፡፡ ግንባታው ተጠናቆ አግልግሎት መስጠት ሲጀምር ቀደም ሲል ከነበረው አገልግሎት በተጨማሪ ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ አካባቢዎች ኃይል መስጠት ያስችላል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 25 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

የሻምቡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ዛሬ ተመረቀ ……….///……… የሻምቡ ባለ 230 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ እና የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ዛሬ ተመርቋል። የማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች ያሉት ሲሆን ከፊንጫ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ሻምቡ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ 83 የኃይል ተሸካሚ ማማዎች ተተክለውለት የማስተላለፊያ መስመር ተዘርግቷል። በሻምቡ ከተማ ዳርቻ በዘጠኝ ሄክታር መሬት ላይ የተገነባው የሻምቡ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ባለ 230 ኮሎ ቮልት ገቢ እና ስድስት 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት። የፕሮጀክቱ ግንባታ ስድስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ስድስት ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 85 በመቶው ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር እንዲሁም 15 በመቶው ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ በዋና ተቋራጭነት፤ ሀገር በቀሉ መላ ኢንጂነሪንግ ደግሞ የሲቪል ሥራውን በንዑስ ተቋራጭነት ሲያከናውኑ የጣሊያኑ ኢ.ኤል.ሲ ኤሌክትሮ ኮንሰልታንት ደግሞ የማማከር ሥራውን ሰርቷል፡፡ ከአዲስ አበባ በ335 ኪ.ሜ ርቀት በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት፤ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፤ በሻንቡ ከተማ የተገነባው የማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢው ማህበረሠብ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 21 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9

የቡታጅራ - ወራቤ የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጀመረ .......///...... የቡታጅራ - ወራቤ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ መጀመሩን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታውቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዐቢይ አታኩሬ እንደገለፁት አዲስ ባለ 132/33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በወራቤ ከተማ እንዲሁም የማስፋፊያ ግንባታ በነባሩ የቡታጂራ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ ይከናወናል፡፡ ከቡታጂራ - ወራቤ 36 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታም የፕሮጀክቱ አንድ አካል እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያውን ለመገንባት በሚያስፈልገው ቦታ ላይ ለነበሩ ነዋሪዎች የካሳ ክፍያ መፈፀሙንና በሳይቱ የተለያዩ የዕቃ ግምጃ ቤቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሆነ ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዝርጋታውን ለማከናወን የቅየሳ ጥናት መጠናቀቁን፣ የአፈር ምርመራ መከናወኑንና ለመሰረት ግንባታ የቁፋሮ ሥራ መጀመሩን እና የአጥር ማጠር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል። የፕሮጀክቱን ግንባታ እና ዕቃ አቅርቦት የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ የሚያከናውን ሲሆን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ የሥራ ክፍል የማማከር ሥራውን የሚሰራ ይሆናል፡፡ ፕሮጀክቱ 8 ነጥብ 91 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና 54 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ የተበጀተለት ሲሆን ፋይናንሱም በዓለም ባንክ እንደሚሸፈን ዋና ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለፕሮጀክቱ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እና የካሳ ክፍያ ጥያቄዎች የሚውል ከ146 ሚሊዮን ብር በላይ ፋይናንስ እንደሚ ያደርግ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5

የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት በሞጆና አካባቢው ኃይል ተቋርጧል ........////....... ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ወደ ሞጆ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ትናንት በተፈጸመ ስርቆት ምክንያት በአካባቢው በከፊል ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አበባው ያለው እንዳስታወቁት ለጊዜው ማንነታቸው ባልታወቀ ሰዎች በኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈፀመ ስርቆት በሞጆ ከተማና አካባቢው ኤሌክትሪክ በከፊል ተቋርጧል። አሁን ስርቆት በተፈፀመበት ስፍራ ከሃያ ቀናት በፊት ተመሳሳይ ስርቆት ተፈፅሞ ኃይል በመቋረጡ ጥገና መከናወኑን ዳይሬክተሩ አስታውሰዋል። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በሪጅኑ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ሁኔታ ከቆቃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ማስተላለፊያ መስመር ፣ ወደ አሰላ በተዘረጋው መስመር እንዲሁም በኢትዮ ጅቡቲ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈጸሙ የስርቆት ወንጀሎች ኃይል መቋረጡ በተቋሙ ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አጋጥሟል። በአሁን ወቅት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጥገና ባለሙያዎች የወደቁትን ምሰሶዎች በሌላ ለመተካት ርብርብ እያደረጉ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል። አካባቢው የብረት ማቅለጫ ፋብሪካዎች የሚገኙበት በመሆኑና የሌባና ተቀባይ ቅብብሎሽ ያለምንም ስጋት እየተከናወነበት በመሆኑ የፀጥታ አካላት ተገቢውን ትኩረት እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 18 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

በ20 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የተከናወኑ የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች ተጎበኙ ......../////....... በአፍሪካ ልማት ባንክ ብድር በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ባሉ ከተሞች በሚገኙ ስምንት ማከፋፈያ ጣቢያዎች የተከናወኑ የማስፋፊያ እና አቅም ማሳደግ ሥራዎች በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በአገልግሎቱ የፕሮጀክት ኃላፊዎች እንዲሁም በባንኩ ተወካዮችና በአማካሪ ድርጅቱ ተጎበኙ። የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዐቢይ አታኩሬ እንደገለፁት በቃሊቲ 1 ፣ በሰበታ 1እና 2፣ በለገጣፎ፣ በገላን፣ በቢሾፍቱ 3፣ በሆለታ እና ኢላላ ገዳ የተሰሩት የማስፋፈፊያና አቅም ማሳደግ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። በስምንቱም ጣቢያዎች ላይ የተለያየ አቅም ያላቸው ትራንስፎርመሮች መተከላቸውንና ቀድሞ የነበራቸውን አቅም የሚያሳድግ ሥራ መሰራቱን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል። ለማስፋፊያ ሥራው የወጣው 20 ሚሊየን ዶላር የተሸፈነው የአፍሪካ ልማት ባንክ በብድር ከሰጠው 40 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ብድር መሆኑን ጠቁመዋል። እንደ አቶ ዐቢይ ገለፃ በጣቢያዎቹ ላይ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የአቅም ማሳደግ ስራ ቢሰራም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሰበታ 1እና 2፣ ቃሊቲ 1 ፣ ገላን ፣ እና ኢላላ ገዳ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ወጪ መስመሮቹን እስካሁን መጠቀም አልጀመረም። በመሆኑም መስመሮችን በአፋጣኝ ዝግጁ በማድረግ ወደተጠቃሚው ለማድረስ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ አቶ ዐቢይ ጠይቀዋል። በማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ላይ የተሰራው ማስፋፊያ ለኢንዱስትሪዎችና ለተጠቃሚው አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 17 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+7

የተሰረቀ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመርና የምሰሶ ብረት ሸሽጎ ሲያጓጉዝ የተያዘ ተከሳሽ በእስራትና በገንዘብ ተቀጣ ........./////....... ከኢትዮ ኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር የተሰረቁ የምሰሶ ብረቶችንና ሽቦዎችን ሸሽገው ያስቀመጠ ግለሰብ በእስር እና በገንዘብ እንዲቀጣ የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰነ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያሳለፈው ከ6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት በተከራዩት ቤት ደብቀው ባስቀመጡ ተከሳሽ ላይ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ነገረ ፈጅ ወ/ት ዮዲት ደረጀ እንደገለጹት የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው ግንቦት 2011 ዓ.ም. በወላይታ ሶዶ ዞን ሁምቦ ቀበሌ በኢትዮ-ኬንያ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ሽቦ እና የብረት ምሶሶዎች ላይ ነው። እንደ ወ/ት ዮዲት ገለጻ በድርጊቱ ተሳትፎ የነበራቸው አምስት ተከሳሾች ከተከራዩት ቤት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-አአ 98099 በሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና በተለያየ ጊዜ ተስርቀው የተከማቸውን ስድስት ኪሎ ሜትር የሚረዝም ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ሽቦ እና ከተለያዩ ምሶሶዎች ተቆረጠው እና ተፈተው የወጡ ብረቶችን ጭነው ሲያጓጓዙ እጅ ከፍንጅ ተይዘው ነበር ክስ የተመሰረተባቸው። በተከሳሾቹ ላይ መረጃ በማጠናቀር አቃቤህግ ያቀረበውን ክስ የተመለከተው የወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከአምስቱ ተከሳሾች መካከል አንደኛውን ተከሻሽ በሰባት ዓመት ጽኑ አስራት እና አስር ሺህ ብር እንዲቀጣ መወሰኑን አስታውቀዋል። አንደኛው ተከሳሽ አሚን አብዱልቃድር የተቀጣው የስርቆት ወንጀሉን በመምራት እና በማስተባበር ሲሆን ከሁለተኛ እስከ አምስተኛ ያሉት ተከሳሾች ግን በነፃ እንዲሰናበቱ ፍርድ ቤቱ መወሰኑን ነገረ ፈጇ ተናግረዋል፡፡ በወላይታ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እና በአርባምንጭ ተዘዋዋሪ ችሎት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ክስ ተመሰረተባቸው መዝገቦች ላይ ምስክር መሰማቱንና ለውሳኔ መቀጠሩን ጠቁመዋል። በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ግለሰቦችና ተባባሪዎቻቸውን ለህግ በማቅረብ አስተማሪና ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግ ተቋሙ፣ ህብረተሰቡ እና የጸጥታ አስከባሪ አካላት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል ፡፡ ህብረተሰቡ ኃላፊነት የጎደላቸው ግለሰቦች በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶችን ሲሰርቁና አደጋ ሲያደረሱ ሲመለከት እንዲሁም የሚያጠራጥር ሁኔታ ሲያጋጥመው በአቅራቢያው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት በመጠቆም ሀገራዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

ለግድቡ ግንባታ የ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደረገ ……..////……. በአሜሪካ የሳክራሚንቶ እና አካባቢው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት የ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፡፡ የማህበረሰቡ ተወካዮች ድጋፉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ሲያስረክቡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ደግሞ ለማህበሩ የምስጋና የምስክር ወረቀት አበርክተዋል፡፡ በርክክብ ሥነስርዓቱ ላይ ሥራ አስኪያጁ ኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ እንደገለፁት የኢትዮጵያ አጋሮችና ኮንትራክተሮች ሳይቀሩ ግድቡን እንዳይሰሩ ጫና እየተረገ ባለበት ጊዜም መላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ለፕሮጀክቱ ግንባታ ያደረጉት ድጋፍ የሚያስደንቅ ነው ብለዋል፡፡ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አንደኛው ዩኒት ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን ሁለተኛውን ዩኒት ወደ ሥራ ለማስገባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ሙሉ ወጭ እየተገነባ የሚገኘው ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለፍሬ ይበቃል ያሉት ኢንጅነር ክፍሌ ለዚህም የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የማህበሩ ተወካይ አቶ አስማማው ኑሬ በበኩላቸው ከኢትዮጵያ ውጭ የሚኖረው አትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የፕሮጀክቱን ግንባታ በቅርበት እየተከታተለ ሲሆን ድጋፉም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነት አለኝ ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+4

የገናሌ ዳዋ - ይርጋለም የኃይል ማስተላለፊያ መሥመር ከወራት በኋላ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ………///…….. በኃይል ማስተላለፊያ መሥመሮችና በምሰሶዎች ሥር በበቀሉ ዛፎች ምክንያት አገልግሎት መስጠት አቁሞ የነበረዉ የገናሌ ዳዋ - ይርጋለም የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መሥመር አገልግሎት መስጠት ጀምሯል፡፡ የማስተላለፊያ መሥመሩ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የአዶላ ዋዩ፣አዶላ ሬዴ፣ አዶላ ጂላ እና አና ሴራ ወረዳዎች እንዲሁም በሲዳማ ክልል የተወሰኑ ወረዳዎችን አቋርጦ የሚያልፍ ነው፡፡ ይሁንና የገናሌ ዳዋ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ 2012 ዓ.ም ላይ ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ያለ አዲስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ቢሆንም ወደ ይርጋለም የተዘረጋው መስመር ሥር ዛፎች በማደጋቸው ጣቢያው የሚያመነጨውን ኃይል ለማስተላለፍ ተቸግሮ ነበር፡፡ ዛፎቹ ከአካባቢው መስተዳደር ጋር አካላትና ከነዋሪዎች ጋር በመነጋገር ከተቆረጡ በኋላ መሥመሩ ዳግም አገልግሎት መሥጠት ጀምሯል፡፡ ለወራት አገልግሎት መሥጠት አቁሞ የነበረዉን የማስተላለፊያ መሥመር ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ ከአካባቢው ህብረተሰብ እና ከፀጥታ አካላት ጋር ለወራት የዘለቀ ምክክር ሲደረግ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ መስመሩን ከዛፎች ለማጽዳት በተደረገው ርብርብ የጉጂ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የፀጥታና አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪ ተወካዮች ላደረጉት ድጋፍ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋናውን ያቀርባል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+7

ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በፍትሐብሔር ክርክር ከ136 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ችሏል ………////……. ክርክር ሲካሄድባቸው ቆይተው ውሳኔ ካገኙ የፍትሐብሔር መዝገቦች ውስጥ ከ136 ሚሊየን ብር በላ
ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በፍትሐብሔር ክርክር ከ136 ሚሊየን ብር በላይ ማዳን ችሏል ………////……. ክርክር ሲካሄድባቸው ቆይተው ውሳኔ ካገኙ የፍትሐብሔር መዝገቦች ውስጥ ከ136 ሚሊየን ብር በላይ ማዳኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የህግ አልግሎት ቢሮ መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ መርክነህ ይገዙ እንዳስታወቁት ክርክር የተካሄደባቸው መዝገቦች የገንዘብ መጠን 151 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር ሲሆን በክርክሩ 136 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር ለተቋሙ 15 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ደግሞ ለተከራካሪዎች ተወስኗል፡፡ ከ730 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር የሚበልጥ የገንዘብ መጠን ያላቸው የተለያዩ መዝገቦች ላይ ክርክሩ መቀጠሉን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ከካሳ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች፣ በአማራጭ የሙግት መፍቻ ዘዴ ክርክርን በመቌጨት፣ በግልግል ዳኝነት እና የህግ አስተያየትና የምክር አገልግሎት በመስጠት ሰፊ ሥራዎችን መከናወናቸውን ዳይሬከተሩ አቶ መርክነህ ይገዙ አስታውቀዋል፡፡ በፍትሐ ብሔር ጉዳይ በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች በ146 መዝገቦች ላይ ክትትል ተደርጎ 57 መዝገቦች ውሳኔ ሲያገኙ 53 መዝገቦች ክትትል እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ሃያ አራጽ በስምምነት ሲጠናቀቁ ሰባት መዝገቦች ደግሞ በፀጥታ ምክንያት ለጊዜው ተዘግተዋል፡፡ አምስት መዝገቦችም በአማራጭ የሙግት ሥርዓት እልባት አግኝተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 06 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5