en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 542 subscribers, ranking 8 329 in the Technologies & Applications category and 2 179 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 542 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 31 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.36%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.21% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 097 views. Within the first day, a publication typically gains 2 520 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 542
Subscribers
-124 hours
-167 days
+3130 days
Posts Archive
የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ከ30 በመቶ በላይ ደርሷል -የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ …………………………….////………………………………….. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ አጠቃላይ የግንባታ አፈፃፀም ከ30 በመቶ በላይ መድረሱን የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተሰማ ኡርጌቻ እንደገለፁት ለተርባይን መትከያ ቦታ የማስተካከል፣ የዲዛይን ግምገማ እና የካሳ ክፍያ ሥራዎች 94 በመቶ እንዲሁም የኮንክሪት ማዘጋጃ ወይም ባቺንግ ፕላንት ተከላ ሥራ 75 በመቶ ተጠናቋል፡፡ የ230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ዕቃዎች እና የተርባይን ዕቃዎች ፍብረካ ሥራ 93 በመቶ መከናወኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ለተርባይን መሠረት የሚያስፈልጉ ዕቃዎች ሙሉ በሙሉ ተጓጉዘው ሳይት መድረሳቸውን ጠቁመዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ፕሮጀክቱ ከሚኖሩት 29 የንፋስ ተርባይኖች መካከል የ27 ተርባይኖች ፍብረካ መጠናቀቁንና አስራ አምስቱ ተጓጉዘው ጅቡቲ ወደብ ደርሰዋል፡፡ ቀሪዎቹን የተርባይን አካላት ፍብረካ በማጠናቀቅ ወደ ሳይት የማጓጓዝ ሥራ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን ተናግረዋል፡፡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያና የውስጥ ለውስጥ መጋቢ መንገዶች ግንባታም መጀመሩን ገልፀዋል፡፡ ፕሮጀክቱ እያንዳንዳቸውም 3 ነጥብ 46 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅም ያላቸው 29 የንፋስ ተርባይኖች የሚኖሩት ሲሆን ግንባታው ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ ተጨማሪ 100 ሜጋ ዋት ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ግንባታውን የጀርመን እና ስፔን ጥምር ኩባንያ የሆነው ሲመንስ ጋሜሳ ሪኒዌብል ኢነርጂ እያከናወነ ነው የተባለ ሲሆን የማማከሩን ሥራ ደግሞ የዴንማርኩ ኮዊ ኤ/ኤስ (COWI A/S) እየተሳተፈበት እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ በአርሲ ዞን በሂጦሳ ወረዳ ኢተያ ከተማ አቅራቢያ እየተገነባ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታውን አጠናቆ ለአገልግሎት ለማብቃት ከ126 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዩሮ በላይ በጀት የተያዘለት ሲሆን የፋይናንስ ወጪውንም ከዴንማርክ መንግሥት በተገኘ ብድር እና ስጦታ የሚሸፈን ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ከ300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፍጠሩን አቶ ተሰማ ኡርጌቻ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 03 ቀን 2014 ዓ/ም

ማከፋፈያ ጣቢያው የማህበረሰቡን እና የኢንቨስተሮችን የረጅም ግዜ ጥያቄ የመለሰ ነው ……..////…….. የአፍዴራ ባለ 230 ኪቮ. የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር በአካባቢው በተለያዩ የስራ ዘርፍ የተሰማሩ የግል አልሚዎችን እና የአካባቢውን ማህበረብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ እንደመለሰ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምስራቅ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የሰመራ ንዑስ ሪጅን ስራ አስኪያጅ አቶ ሰለሀዲን ዋሴ እንደገለጹት አካባቢው በተለያዩ የተፈጥሮ ማዕድናት የሚገኝበት እንደመሆኑ በአካባቢው የሚቀሳቀሱና ለመቀሳቀስ የሚፈልጉ የተለያዩ የግል አልሚዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ጥያቄ ዋንኛ አጀንዳቸው ነበር፡፡ በመሆኑም ከ20 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ በሆነ ወጪ የተገባው የማከፋፈያ ጣቢያው እስከ 25 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል መስጠት ስለሚችል የአልሚዎችንም ሆነ የአካባቢውን ማህበረሰብ ሙሉ በሙሉ የመመለስ አቅም አለው ስላለው አልሚዎች የተፈጠረላቸውን አድል በአግባቡ እንዲጠቀሙም አቶ ሰለሀዲን ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በሰሜን ምስራቅ ሪጅን ትራስሚሽን ሰብስቴሸን ኦፕሬሽን የሰመራ ንዑስ ሪጅን ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ሀሰን መሀመድ በበኩላቸው ማከፋፈያ ጣቢያው የኪልበትረሱ ዞንን 50 በመቶ የኃይል ጥያቄ የሚመልስ ይሆናል ብለዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው በዞኑ የሚገኙትን አፍዴራ እና ቢዱ ወረዳች ሙሉ ለሙሉ የመሸፍን አቅም እንዳለው ጠቁመዋል፡፡ በቀጣይም በማከፋፈያ ጣቢያው አስተማማኝና የማያቋርጥ ኃይል ለማቅረብ እና በክልሉ ከተለያዩ አማራጮች ኃይል የሚገኝበት የቀለበት (ring) ሲስተም ትስስር ለመፍጠር መታሰቡን ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 03 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2

photo content
+9

photo content
+9

የጽሁፍ ፈተና ጥሪ ተቋማችን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የካቲት 25 ቀን 2014 ዓ.ም በሪሰፕሽን 1ኛ ባለው ክፍት የስራ መደብ አመልካቾችን መጋበዙ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም መስፈርቱን በመሟላት የተመረጣችሁ አመልካቾች ሰኔ 07 ቀን 2014 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ሰዓት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ንግድ ስራ ኮሌጅ (ኮሜርስ) ለጽሁፍ ፈተና እንድትገኙ እናስታውቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 01 ቀን 2014 ዓ/ም

የአፍዴራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢውን አየር ንብረት መሰረት አድርጎ በልዩ ሁኔታ መገንባቱ ተገለጸ ……..///…….. በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የተገነባው የአፍዴራ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ ዘመናዊ ማከፋፈያ ጣቢያ የአካባቢውን አየር ንብረት ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምሩ ባቱ ገለፁ፡፡ አቶ ታምሩ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው ያለውን ከፍተኛ ሙቀት ተቋቁሞ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ ከዲዛይን አንስቶ በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ጥራት ተገንብቷል፡፡ የማከፋፈያ ጣቢያውን ትራንስፎርመር እና ጂ.አይ. ኤስ (GIS) ሲስተሙን ሙሉ ለሙሉ በቤት ውስጥ በማስቀመጥ ደረጀውን የጠበቀ የማቀዥቀዣ ሥርዓት እንዲኖረው መደረጉን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ለማከፋፈያ ጣቢያው ብቻ የሚያገለግል 392 ኪሎ ዋት ከፀሐይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት የሚችል 60 የፀሐይ ኃይል መሰብሰቢያ ፓኔሎች እንደተገጠሙለትም ገልፀዋል፡፡ ይህም በማከፋፈያው ጣቢያው የናፍጣ ጄኔሬተር ስለማይኖረው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የነዳጅ ወጪ ከማስቀረቱ ባሻገር የማያቋጥ ኃይል እንዲያገኝ ያስችለዋል ብለዋል፡፡ የሠራተኞች መኖሪያ ቤትም የሠራተኞቹን ምቾት እንዲጠብቁ ሙቀትን ሊቋቋሙ ከሚችሉ የግንባታ ግብዓቶች መገንባታቸውንና በቂ የማቀዥቀዣ ሲስተም አንዲኖረው መደረጉን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ ከሠራተኞች መኖሪያ ቤት በተጨማሪ ለእንግዶች ማረፊያ የሚሆኑ ደረጀውን የጠበቁ ስድስት ክፍሎች ያሉት G+1 ህንጻ መግንባቱን አቶ ታምሩ አስረድተዋል፡፡ ከአዲስ አበባ በ 780 ኪሎ ሜትር ርቀት ማከፋፈያ ጣቢያው ሰመራ ከሚገኘው ማከፋፈያ ጣቢያ በ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር ያለው ሲሆን አምስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች አሉት፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 29 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+6

ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ......./////....... የሠመራ አፍዴራ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክት ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የፕሮጀክቱ የሳይት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ታምሩ ባቱ እንደገለፁት በአፍዴራ ከተማ የተገነባው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው አንድ ፓወር ትራንስፎርመር አለው። 195 ኪሎ ሜትር ርዝመት ላለው የሠመራ አፍዴራ የማስተላለፊያ መስመር 466 ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች እንደተተከሉለት አቶ ታምሩ ገልፀዋል። የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ ለአካባቢው ማህበረሠብና በአቅራቢያው ለሚገኙ የጨውና የአዮዲን ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ኢኮኖሚውን እንደሚያነቃቃ ይታመናል። የፕሮጀክቱን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የገነባው የህንድ ኩባንያ የሆነው ካልፓቱሮ ሲሆን ናንጂንግ ዳጂ የተሰኘው የቻይና ኩባንያ ደግሞ የኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክቱን ግንባታ አከናውኗል። የጀርመኑ ትራክት ቤል ኩባንያ በማማከር ሥራው ላይ ተሳትፏል። ለኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክቱ ሰባት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና 44 ሚሊዮን ብር ገደማ የተበጀተለት ሲሆን ለኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ግንባታ ደግሞ 13 ሚሊዮን ዶላር እና ከ125 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ወጪ ተደርጎበታል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+5

በኃይል ማስተላለፊያ ምሰሶዎች አቅራቢያ የህገ-ወጥ ቤቶች ግንባታ እየተበራከተ ነው ……………..//……………. በኢትዮ-ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎች አቅራቢያ የህገ-ወጥ ቤቶች ግንባታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን የኢትዮ-ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ኮንቨርተር ጣቢያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አያሌው እንደገለፁት ካለፉት ሁለት ዓመታት ወዲህ በአርባ ምንጭ ከተማና አካባቢው የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን ተከትሎ በርካታ ህገ-ወጥ ቤቶች እየተገነቡ ነው፡፡ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎቹ አቅራቢያ እየተከናወኑ የሚገኙትን ህገ-ወጥ የቤቶች ግንባታ እና የመሬት ወረራ ለማስቆም ከከተማው አስተዳደር እና ከዞን ጽ/ቤት አመራሮች ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች ቢደረጉም ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ ነው አቶ ቴዎድሮስ የገለፁት፡፡ ተቋሙ የጉዳዩን አሳሳቢነት ለሚመለከታቸው የክልል እና የፌዴራል የመንግሥት ተቋማት ማሳወቁንም ነው ያብራሩት፡፡ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታው ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ምንም ዓይነት ግንባታም ሆነ የመሬት ወረራ አልነበረም ያሉት ሥራ አስኪያጁ ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ የፍተሻ ሥራ እየተከናወነ ባለበት ወቅት ከ300 በላይ የህገ-ወጥ ቤቶች ግንባታ መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩን ደህንነት ለመፈተሸ ህገ-ወጥ ቤቶቹ ወደ ተሰሩበት አካባቢ መግባት ከፀጥታ አኳያ አስቸጋሪ ሁኔታ ፈጥሯል ብለዋል፡፡ ተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ በሚያልፍባቸው ቦታዎች ሁሉ ተገቢውን የካሳ ክፍያ ከወረዳ አስተባባሪዎች ጋር በመሆን ፈፅሟል ያሉት አቶ ቴዎድሮስ ይሁን እንጂ በአርባ ምንጭ ከተማ እና በምዕራብ አባያ አንዳንድ አካባቢዎች የወሰን ማስከበር ሥራው አደጋ ላይ መውደቁን ጠቁመዋል፡፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ዲዛይን ሲደረግ ከምሶሶው 32 ነጥብ 5 ሜትር ርቀት ምንም ዓይነት የቤቶች ግንባታ ማካሄድ እንዲሁም ከ30 ሜትር ወዲህ ማናቸውንም አዳጊ ዕፅዋቶች መትከል የማይፈቀድ መሆኑ በህግ ቢደነገግም በተጠቀሱት አካባቢዎች ግን ህጉን ተግባራዊ ማድረግ አልተቻለም፡፡ በተያያዘ ዜናም በያቤሎ ከተማ የኃይል ማስተላለፊያ ምሶሶዎቹ አቅራቢያ የአራት ቤቶች ግንባታ ቢከናወንም ከከተማው አስተዳደር ጋር በተደረገ ውይይት ህገ-ወጥ ቤቶቹን የማፍረስና ተጨማሪ ግንባታዎችና የመሬት ወረራዎች እንዳይፈፀሙ ለመከላከል ሥምምነት ላይ መደረሱን ጨምረው ገልፀዋል፡፡ የግንባታ ሥራው በ2008 ዓ.ም የተጀመረው የኢትዮ-ኬንያ ባለ 500 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት ከ183 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብቶ መጠናቀቁን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+4

ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸውን ብረታብረቶች የመረከብና የማጓጓዝ ሥራ እየተሰራ ነው ......///// ………… ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸውን ብረታ ብረቶች የመረከብ እና የማጓጓዝ ሥራ እያከናወነ መሆኑን የተቋሙ ንብረት አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ አበበ ጉዲሳ እንደገለፁት ብረታብረቶቹ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በቀድሞ የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን በአሁኑ ኢትዮ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ በኩል ከውጭ ሀገር ተገዝተው የገቡ ናቸው፡፡ ኢትዮ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ ብረታ ብረቶቹን ለግድቡ ግንባታ በሚል ገዝቶ ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባቸው ቢሆንም የጥራት ደረጃቸው አነስተኛ በመሆኑ ምክንያት በሞጆ፣ በቢሾፍቱ፣ በአቃቂና በመካኒሳ ቅርንጫፍ ጣቢያዎቹ አከማችቷቸው መቆየቱን አቶ አበበ ገልፀዋል፡፡ የተለያየ መጠን እና ዓይነት ያላቸውን ብረታ ብረቶች በመረከብ በ529 ተሽከርካሪዎች ወደ ቆቃ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የማጓጓዝ እና የመደርደር ሥራዎች መከናወኑን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል፡፡ ቢሮው ብረታ ብረቶቹን ከኢትዮ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ ቅርንጫፍ ጣያቢያዎች ወደ ቆቃ የኃይል ማመንጫ ላጓጓዘበት እስካሁን ከ12 ሚሊየን ብር ያላነሰ ወጪ እንዳወጣ የገለፀ ሲሆን ቀሪ ብረታ ብረቶችን እያጓጓዘ በመሆኑ ወጪው ከዚህም ከፍ ሊል ይችላል ብለዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ለመልካ ሰዲ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ጥቅም ላይ ይውላሉ ተብለው ተገዝተው የነበሩ የአርማታ ብረታ ብረቶችን እና የመሬት ውስጥ ተቀባሪ የኤሌክትሪክ ገመዶችን የመረከብ ሥራ እየተሰራ እንደሆነ አቶ አበበ አስታውቀዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ንብረቶቹን ኮተቤ ወደሚገኘው የተቋሙ ዕቃ ግምጃ ቤት የማጓጓዝ ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ በቁጥር 14 ሺህ ሶስት መቶ አስራ ዘጠኝ የሚሆኑ የተለያየ ክብደት እና ዓይነት ያላቸው የአርማታ ብረቶች እና 35 ድራም የሚመዝኑ የተለያየ ስፋት እና ርዝመት ያላቸው የመሬት ውስጥ ተቀባሪ የኤሌክትሪክ ገመዶች ርክክብ ተደርጎባቸዋል፡፡ ለተቋሙ አገልግሎት ሊውሉ የሚችሉትን ብረታ ብረቶች በመለየት ቀሪውን ለሽያጭ በማቅረብ ተጨማሪ ገቢ የሚገኝበት ምክረ ሃሳብ ለተቋሙ ሥራ አመራር እንደሚቀርብ አቶ አበበ ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 24 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

የዲቼቶ እና ጋድ የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሥምምነት ተቋረጠ ……////……. የዲቼቶ እና ጋድ ከፀሐይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ሥምምነት እንዲቋረጥ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግ ቢሮ የመንግሥትና የግል አጋርነት (ፒ.ፒ.ፒ) እና የግል የኤሌክትሪክ ኃይል አልሚዎች (አይ.ፒ.ፒ) ፕሮጀክት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ጥላዬ እንደገለፁት ሥምምነቱ የተቋረጠው አክዋ ፓወር የተሰኘው የሳውዲ አረቢያ ኩባንያ ፕሮጀክቱ የሚያስፈልገውን ፋይናንስ ማቅረብ ባለመቻሉ ነው፡፡ ኩባንያው ለአራት የተለያዩ ጊዜያት የማራዘሚያ ጥያቄ አቅርቦ የተፈቀደለት ቢሆንም የፋይናንስ አቅርቦቱን ማሳካት እንዳልቻለ ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል፡፡ ኩባንያው በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በሀገሪቱ የፀጥታ ሁኔታዎች ሳቢያ ውሉን እንዳቋረጠ ቢገልፅም ዋናው ምክንያት ግን የውጭ ምንዛሬ ቅያሪ ዋስትና መንግሥት እንዲሰጠው መፈለጉ እንደሆነ አቶ ተስፋዬ ተናግረዋል፡፡ የኃይል ግዥ ሥምምነቱ በታህሳስ ወር 2012 ዓ.ም ላይ መፈረሙን የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ ኩባንያው ፕሮጀክቶቹ ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጠው እንዲቆዩለት መጠየቁና በሌሎች የመደራደሪያ ነጥቦች መግባባት ላይ መድረስ ባለመቻሉ በመንግሥትና የግል አጋርነት ቦርድ ውሳኔ መሠረት ኮንትራቱ በሁለቱ ወገኖች ሥምምነት እንዲቋረጥ መደረጉን ገልፀዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ኩባንያው አንድ ኪሎ ዋት በ2 ነጥብ 526 የአሜሪካን ሳንቲም የኤሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ ተስማምቶ የነበረ ቢሆንም በጊዜ ገደብ ብርን ወደ ዶላር የመቀየር ዋስትና በኮንትራቱ ውስጥ እንዲካተትለት መጠየቁ ለውሉ መቋረጥ መንስኤ ሆኗል፡፡ ችግሩን ለመቅረፍም የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የመንግሥትና የግል አጋርነት ቦርድ እና ብሔራዊ ባንክ በጋራ ውይይት በማድረግ በቀጣይ በግል አልሚዎች ለሚገነቡ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ዋስትና እንዲሰጣቸው መፈቀዱን ተናግረዋል፡፡ ኩባንያው እስከ 75 በመቶ የፕሮጀክቱን ፋይናንስ ከአበዳሪ ተቋማት እንዲሁም እስከ 25 በመቶ የሚሆነውን ከግል አልሚው፣ ከባለአክሲዮኖች እና ከስፖንሰሮች በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ሊያቀርብ ተስማምቶ ነበር፡፡ የዲቼቶ እና ጋድ ከፀሐይ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች እያንዳንዳቸው 125 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሲሆን ኩባንያው የዲቼቶን በ18 እንዲሁም የጋድን በ15 ወራት ግንባታቸውን አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ለማድረግ አቅዶ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 22 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+1

የህብረት ስምምነቱ የቅሬታ እና የግጭት ምንጮችን የሚያስቀር ይሆናል ……..////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሶስተኛው የህብረት ስምምነት ከዚህ ቀደም በተቋሙ እና በሠራተኛው መካከል የቅሬታ እና የግጭት ምንጭ የሆኑትን ችግሮች በመቅረፍ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው የህብረት ስምምነት ድርድር ኮሚቴ ሰብሳቢ አስታወቁ፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደረጄ አጥናፌ እንደገለጹት አሁን የጸደቀው ሶስተኛው የህብረት ስምምነት የሠራተኛውን ጥቅምም ሆነ መብት በማስከበር ረገድ የተሻሻሉ አንቀፆች የተካተቱበት ነው፡፡ በቀድሞው የህብረት ስምምነት ተቋሙ ይሸፍን የነበረውን 90 በመቶ የህክምና ወጪ በተሻሻለው የህብረት ስምምነት ተቋሙ ሙሉ በሙሉ እንዲሸፍን መደረጉን ሰብሳቢው ተናግረዋል፡፡ እድገት እና ዝውውር ደረጃ( ግሬድ) ጠብቆ እንዲከናወንና የዕድገትና ዝውውር ማስታወቂያ በየሩብ ዓመቱ እንዲወጣ፤ የሥራ ልብስ እና የደንብ ልብስ ዓይነትና መጠን በግልጽ ተለይቶ እንዲቀመጥ እና ከዚህ ቀደም አላሰራ ያሉ አንቀጾች እና አሻሚ ቃላት እንዲስተካከሉ መደረጉ እንዲሁም የቅሬታ እና የግጭት ምንጮችን የሚያስወግዱ አንቀፆች መካተታቸውን አቶ ደረጀ አስረድተዋል፡፡ ከእረፍት ቀን እና ከትርፍ ሰዓት ክፍያ ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የሚያስተካክሉ አንቀፆች እንዲገቡ መደረጉንም ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የመሰረታዊ ሠራተኛ ማህበር ሊቀ መንበር እና የህብረት ስምምነት ድርድር ኮሚቴ አባል አቶ መኮንን ከፍሌ በበኩላቸው የህብረት ስምምነቱ ሲዘጋጅ የነበረው የህብረት ስምምነት ሰነድ፤ የሌሎች አቻ ተቋማት የህብረት ስምምነት ሰነድ እና ከተቋሙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ግብአት ተሰብስቦ መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም በሁለተኛው የህብረት ስምምነትላይ የቅሬታ እና የግጭት ምንጮች ሆነው የተነሱት ጉዳዮች በጥንቃቄ ታይተው ተስተካክለዋል ብለዋል፡፡ ሠራተኛው መብቱ እና ጥቅሙ ሲጎድል እንደሚጠይቅ ሁሉ ግዴታውን በድንብ አውቆ እና ተጠያቂ እንደሚሆን ተረድቶ ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ አሳስበዋል ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 22 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+1

የሻምቡ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል ……///……. በሻምቡ ከተማ የተገነባው ባለ 230 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ፕሮጀክት ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ አሸናፊ ሙሉብርሃን እንዳስታወቁት ማከፋፈያ ጣቢያው ለሻምቡ ከተማ እና ለአሊቦ ቀበሌ በአማካኝ ሁለት ሜጋ ዋት ኃይል እየሰጠ ይገኛል፡፡ ጣቢያው አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ገቢ መስመር እና ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች እንዳሉት ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ከወጪ መስመሮቹ ሁለቱ አገልግሎት እየሰጡ ሲሆን አራቱ ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን በመጠባበቅ ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ ማከፋፈያ ጣቢያው እያንዳንዳቸው 31 ነጥብ 5 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፈርመሮች፣ አንድ የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል እና የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያ ስርዓት አሉት፡፡ ፕሮጀክቱን ለመገንባት አራት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ሶስት ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት ሲሆን ከዚህ ውስጥ 85 በመቶው ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር እንዲሁም 15 በመቶው ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡ የቻይናው ሲኖ ሃይድሮ ኩባንያ በዋና ተቋራጭነት፤ ሀገር በቀሉ መላ ኢንጂነሪንግ የሲቪል ሥራውን በንዑስ ተቋራጭነት ሲያከናውኑት የጣሊያኑ ኢ.ኤል.ሲ ኤሌክትሮ ኮንሰልት ደግሞ የማማከር ሥራውን አከናውኗል፡፡ ከአዲስ አበባ በ335 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን፤ በሻንቡ ከተማ የተገነባው የማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢው ማህበረሠብ እና የማምረቻ ፋብሪካዎች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ረገድ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 19 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+2