en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 691 subscribers, ranking 8 014 in the Technologies & Applications category and 2 155 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 691 subscribers.

According to the latest data from 29 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 137 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 34.17%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 17.11% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 5 362 views. Within the first day, a publication typically gains 2 685 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 11.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 30 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 691
Subscribers
+524 hours
+77 days
+13730 days
Posts Archive
ፓርኩ ያልተቆራረጠ ኃይል እያገኘ መሆኑን ገለፀ ………///……… የደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያልተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን አስታወቀ። የፓርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ የሺጥላ ሙሉጌታ እ
+5
ፓርኩ ያልተቆራረጠ ኃይል እያገኘ መሆኑን ገለፀ ………///……… የደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ያልተቆራረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን አስታወቀ። የፓርኩ ስራ አስኪያጅ አቶ የሺጥላ ሙሉጌታ እንደገለፁት ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርታቸውን ለተጠቃሚው ለማቅረብ በእጅጉ አግዟቸዋል። በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ የሚገኘው የሶላር ፓነል አምራች ኩባንያ በደብረብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥራ ለመጀመር የቦታ መረጣ ማከናወኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ ኩባንያው እስከ 40 ሜጋ ዋት ኃይል ሊጠቀም እንደሚችል ጠቁመዋል። በቀጣይም በርካታ አምራች ኩባንያዎች በኢንዱስትሪ ፓርኩ ሥራ ለመጀመር ፍላጎት እያሳዩ መሆኑን ገልፀው ለዚህም በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። የደብረብርሃን ቁጥር 2 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዳኜ ይታገሱ በበኩላቸው ጣቢያው 33 እና 15 ኪሎ ቮልት አቅም ባላቸው 15 ወጪ መስመሮች ለኢንዱስትሪዎች፣ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ፓርኩ-ያልተቆራረጠ-ኃይል-እያገኘ-መሆኑን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 20 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን እየተከበረ ይገኛል …….///……… የዘንድሮው የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረ
+5
በተቋሙ የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን እየተከበረ ይገኛል …….///……… የዘንድሮው የዓለም አቀፍ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤና ቀን "ጤናማ የሥነ-ልቦናና ማህበራዊ የሥራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል በተቋም ደረጃ እየተከበረ ይገኛል። በተቋሙ ዋና መስሪያ ቤት በውይይት እየተከበረ በሚገኘው የሥራ ደህንነትና ጤና ቀን በዋናነት በሥራ ገበታ ላይ እያሉ በተለያዩ አደጋዎች ሕይወታቸውን ላጡና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሠራተኞች መታሰቢያ እንዲሆን ታስቦ የተሰናዳ ነው። ማንኛውም ሠራተኛ የዕለት ተግባሩን አከናውኖ ወደ ቤቱ በሠላምና በጤና የመመለስ ሙሉ መብት ቢኖረውም አሁንም ድረስ የሥራ ቦታዎች ላይ ተግዳሮቶች እንደሚታዩ በመድረኩ ተገልጿል። በተለይም ደህንነቱና ጤንነቱ ያልተጠበቀ የሥራ አካባቢ፣ የእውቀትና የክህሎት ክፍተት እንዲሁም ደካማ የሙያ ደህንነት አጠባበቅ ባህል ለሠራተኞች ጤና ጉድለት፣ ለአካል ጉዳትና ለሞት መጋለጥ በምክንያትነት ተጠቃሽ ናቸው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-የዓለም-አቀፍ-የሥራ-ላይ-ደህንነት&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

ከሚያዚያ 30 በፊት ሀብታቸውን ያላስመዘግቡ የተቋሙ ሠራተኞች ቅጣት ይጠብቃቸዋል ‎........///…….. ‎እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የተቋሙ ሠራተኞች ለቅ
ከሚያዚያ 30 በፊት ሀብታቸውን ያላስመዘግቡ የተቋሙ ሠራተኞች ቅጣት ይጠብቃቸዋል ‎........///…….. ‎እስከ ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ የተቋሙ ሠራተኞች ለቅጣት የሚዳረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታትያ መምሪያ ገለጸ። ‎ ‎በመምሪያው የሙስና ተጋላጭነትና ሥልጠና ሥራ አስኪያጅ አቶ መንግሥቱ አባይነህ እንደገለጹት በሀብት ማሳወቂያና ማስመዝገቢያ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሠረት ሁሉም የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ሀብታቸውን የማስመዝገብ ግዴታ አለባቸው። ‎ ‎ሠራተኛው የራሱን እና የትዳር ጓደኛውን እንዲሁም ከ18 ዓመት በታች የሆነ ልጁን ጨምሮ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት፣ የገቢ ምንጭና ዕዳ ማስመዝገብ ይኖርበታል ብለዋል። ‎ ‎ሆኖም በውርስ የተገኘ የጋራ ንብረት፣ የቤት ዕቃዎች፣ የግል መገልገያዎችና የጡረታ ገቢ በአዋጁ ከምዝገባ ነጻ መሆናቸውን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከሚያዚያ-30-በፊት-ሀብታቸውን-ያላስመዘግቡ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ በተቋሙ የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀም ግምገማ መድረክ ላይ ከተናገሯቸው ታሪካዊ ስኬቶችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል:- ዋና ዋና ስኬቶች 1. የኃይል ማመንጨት አቅም ዕድገት፦ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ኩራት የሆነው ታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የአይሻ 2 እና የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች በስኬት ተጠናቅቀው ወደ ሥራ በመግባታቸው የሀገሪቱ የኃይል ማምረት አቅም ከ 9,730 ሜጋዋት በላይ ደርሷል። 2. የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫፕሮጀክት፦ ግዙፉ የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል። 3. የፋይናንስ ስኬታማነት፦ ተቋሙ ካለበት ከፍተኛ የዕዳ ጫና ወጥቶ ወደ "ምንዳ" ተሸጋግሯል። የሀገር ውስጥ ዕዳ ወደ መንግሥት መዛወሩ፣ አዳዲስ ማመንጫዎች ሥራ መጀመራቸውና የኢነርጂ ምርት መጨመሩ፣ የታሪፍ ማሻሻያ መደረጉ እና የዳታ ማይኒንግ ሽያጭ በዶላር መከናወኑ የተቋሙን ገቢ አሳድጎታል። ይህም ደግሞ እንደ ኮይሻ እና አይሻ ያሉ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በራስ የፋይናንስ አቅም እንዲገነቡ አስችሏል። የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች 1. የፕሮጀክት መዘግየት ባህልን መቅረፍ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜና ጥራት ማጠናቀቅ የተቋሙ ዋነኛ ባህል ሊሆን ይገባል። አላስፈላጊ ወጪንና የሥራ መጓተትን ለማስቀረት፣ በአሠራርና በአመለካከት ረገድ ራስን ወደ ውስጥ መመልከትና መለወጥ ያስፈልጋል። 2. የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞ "የተቋሙ አምባሳደሮች ሆኖ መስራት ይጠበቃል በየክልሉ (ሪጅን) የምትገኙ አመራሮችና ሠራተኞች የተቋሙ አምባሳደሮች ናችሁ። በተለይ ከመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት የተቋሙን መሠረተ ልማት ከጥቃት የመከላከልና የተቋሙን ጥቅም የማስከበር ኃላፊነታችሁን በላቀ ሁኔታ እንድትወጡ አደራ እላለሁ። 3. የስትራቴጂካዊ ዕቅድ ቀጣይነት ከ2016-2018 ዓ.ም በመተግበር ላይ ያለው የሦስት ዓመት የግሪድ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ በዚህ ዓመት ቢጠናቀቅም የጎደሉትን በመሙላትና አዳዲስ ዓለም አቀፋዊና ሀገራዊ እንዲሁም ተቋማዊ ሁኔታዎችን በማካተት በቀጣይም መሪ ዕቅድ ሆኖ ያገለግላል። 4. የኢነርጂ ሽግግርና የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች (EV) ዓለም አቀፍ የነዳጅ እጥረት ተፅዕኖ ለመቋቋም ነዳጅን በቁጠባ መጠቀምና ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መሸጋገር አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። በተለይ ተቋማችን የኃይል አምራች እንደመሆኑ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በስፋት በመጠቀም ለሌሎች ተቋማት አርአያ መሆን ይጠበቅበታል። በዚህ ጉዳይ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ። 5. ለብሔራዊና ዓለም አቀፋዊ ኩነቶች ዝግጁ መሆን ሀገራዊ ምርጫ፦ በቴክኖሎጂ ለሚደገፈው ምርጫ አስተማማኝና ያልተቋረጠ የኃይል አቅርቦት ማረጋገጥ፣ ኮፕ 32 (COP32)፦ በ2020 ዓ.ም እስከ 100 ሺህ ሰዎች ይታደሙበታል ተብሎ በሚጠበቀውና ሀገራችን በምታስተናግደው ዓለም አቀፍ ጉባዔ ላይ የተቋማችን አረንጓዴ ኢነርጂ አሻራችን የማሳየት ከፍተኛ ኃላፊነት አለበት። ለእነዚህ ሥራዎች ከወዲሁ አሮጌ መስመሮችን የማደስና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም የማሳደግ ሥራ በከፍተኛ ፍጥነት መከናወን ይኖርበታል። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030፦ መንግሥት ላቀደው የዲጂታል ኢትዮጵያ ስኬት ተቋማችን የጀርባ አጥንት በመሆኑ ሌት ተቀን መስራት ይጠበቅብናል። 6. የእውቅናና ሽልማት ሥርዓት በበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ላይ በሥራቸው የተሻለ አፈጻጸም ላሳዩ የተቋማችን አመራሮችና ሠራተኞች ተገቢው የእውቅናና የሽልማት ሥርዓት ተግባራዊ ይደረጋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የፕሮጀክት ክትትል የሚታይ ለውጥ ሊያመጣ ይገባል - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.......///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቶች ክትትል የሚታይ የአፈፃፀም ለውጥ እንዲኖራቸው የክትትል ሥርዓቱን ማጠናከር እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። ‎ ‎ዋና ሥራ አስፈጻሚው በተቋሙ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት በፕሮጀክት ክትትል ረገድ ከሪፖርት ያለፈ ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ክትትልና ድጋፍ የሚደረግላቸው ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ፣ በጀትና የጥራት ደረጃ እንደሚጠናቀቁ ሁሉ የተቋሙ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ወደዚህ ደረጃ ማምጣት እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡ ‎ ‎የተቋሙ ከፍተኛው በጀት የሚውለው ለፕሮጀክቶች በመሆኑ የኃይል መሠረተ ልማቶች ፕሮጀክቶች ላይ የሚታይ ለውጥ ለማስመዝገብ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር ሁሉም ኃላፊነቱን በእኔነት ስሜት መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+1

‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተገኙት ውጤቶች ተቋሙን ከዕዳ ወደ ምንዳ ያሸጋገሩ ናቸው - ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎.......///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ሥራዎች እና የተገኙት ውጤቶች ተቋሙን ከዕዳ ወደ ምንዳ ያሸጋገሩ መሆናቸውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ገለጹ። ‎ ‎ዋና ሥራ አስፈጻሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በተቋሙ የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት የተቋሙ ቦርድና ሥራ አመራር ባደረገው ስትራቴጂካዊ አመራርና መንግስት በሰጠው ትኩረት በበጀት ዓመቱ የተሻለ ውጤት ተመዝግቧል። ‎ ‎በዚህም የተቋሙ የፋይናንስ ቁመና ላይ መሠረታዊ በሆነ መልኩ አዎንታዊ ለውጥ መታየቱን አብራርተዋል። ‎ ‎ይህም በፋይናንስ እጥረት ምክንያት የቆሙ ፕሮጀክቶችን ግንባታ በራስ አቅም ወደ ሥራ ለማስገባት የጎላ ሚና እየተጫወተ ነው ብለዋል። ‎ ‎የኦፕሬሽን ባለሙያዎች በማይመችና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው እንደሚሰሩ ያስታወሱት ኢንጂነር አሸብር ሥራዎችን ይበልጥ ማዘመንና ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር እንደሚገባም ተናግረዋል። ‎ ‎ሆኖም ከፕሮጀክት አፈጻጸም ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮች በሌሎች ተቋሚዊ ሥራዎች ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድሩ ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚገባ አንስተዋል። ‎ ‎የተቋሙ ትልቁ በጀት የሚውለው ለፕሮጀክቶች በመሆኑ የኃይል መሠረተ ልማቶች ፕሮጀክቶች ላይ የሚታይ ለውጥ ለማስመዝገብ የክትትልና የድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር ሁሉም ኃላፊነቱን በእኔነት ስሜት መወጣት አለበት ብለዋል። ‎ ‎ባለፉት ሦስት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የተቋሙ የግሪድ ስትራቴጅ በዚህ በጀት ዓመት የሚጠናቀቅ በመሆኑ አፈጻጸሙን በመገምገም ለአዲሱ ስትራቴጂ እንደ ግብዓት መጠቀም እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ‎ ‎ተቋማዊ ሥራዎች ወጪን በቀነሰ እንዲሁም ከሙስናና ብልሹ አሰራር በጸዳ መልኩ ሊከናወኑ ይገባል ብለዋል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ለተመዘገበው ውጤት የበኩላቸውን ሚና ለተወጡ የተቋሙ የሥራ መሪዎች እና ሠራተኞችም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ‎ ‎በቀሪ ሦስት ወራት በበጀት ዓመቱ ያልተከናወኑ ተግባራትን በመለየት እንዲሁም የነበሩ እጥረቶችን በማስወገድ እና ቅንጅታዊ አሠራርን በማጎልበት በተለዬ እይታ ለተሻለ ውጤት ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ‎ የኮፕ 32 ዝግጅት እና 7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ በተሳካ መልኩ የሀገርን ሁለንተናዊ ገጽታ በሚገነባ መልኩ እንዲከናወን እንዲሁም ዲጅታል 2030 እንዲሳለጥ እንደ ተቋም የሚጠበቁ ኃላፊነቶችን በአግባቡ ለመወጣት ሁሉም በትኩረት መስራት እንዳለበትም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋሙ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 92 ቢሊዮን ብር ገቢ አግኝቷል ‎........///....... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እና ተጓዳኝ አገልግሎቶች 92 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ፡፡ ‎ ‌‎በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 24 ሺህ 970 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ለሀገር ውስጥና ለጎረቤት ሀገራት በመሸጥ 90 ነጥብ 16 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል። በበጀት ዓመቱ ለውጭ ሀገራት እና ለቴክኖሎጂ ካምፓኒዎች ከቀረበ የኃይል ሽያጭ 366 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መገኘቱንና ይህም ካለፈው በጀት ዓመት የ138 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ብልጫ እንዳለው ገልፀዋል፡፡ ‎ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ የተሻለ ውጤት መመዝገቡን የተናገሩት አቶ ያለውአይቀር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጨምሮ የአሰላና አይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ወደ ኦፕሬሽን መግባታቸውን አስታውሰዋል፡፡ በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ በበኩላቸው እንደገለፁት ገቢው ከኃይል ሽያጭ፣ ከኦፕቲካል ፋይበር ኪራይ፣ ከማማከር እና ካለፈው በጀት ዓመት ከዞረ ተሰብሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ለገቢው ከፍ ማለት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ወደ ኦፕሬሽን መግባቱ፣ የኃይል ምርት እና አቅርቦት መጠን ማደጉ፣ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የኃይል ሽያጭ በውጭ ምንዛሪ መከናወኑ፣ የብር ከዶላር ጋር ያለው ምንዛሪ ማደጉ፣ መንግስት ለተቋሙ ያደረገው የእዳ ሽግሽግ፣ የታሪፍ ማሻሻያ እና የተቋሙ የገቢ አሰባሰብ ማደግን አንስተዋል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞች እና የሥራ መሪዎችም በቀረበው ሪፖርት እና አፈፃፀም ላይ ጥያቄዎች አቅርበው በሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ ቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል ተመርቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት ከ27 ሺህ በላይ ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል መመረቱን አስታወቀ። ‎ ‎የኮርፖሬት ፕላኒግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 29 ሺህ 381 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 27 ሺህ 105 ነጥብ 6 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም የዕቅዱ 92 ነጥብ 4 በመቶ መሳካቱን የሚያሳይ ሲሆን በ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ከተመረተው ኃይል የ27 ነጥብ 3 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከመነጨው ኃይል ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 50 ነጥብ 8 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስትና የበለስ የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የ18 ነጥብ 3 በመቶ እና የ6 ነጥብ 9 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ እንደነበራቸው ተጠቅሷል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጨምሮ የአይሻና የአሰላ ንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው ወደ ኦፕሬሽን በመግባታቸው የማመንጨት አፈጻጸሙ የተሻለ እንዲሆን ማድረጉን ጠቅሰዋል። ‎ ‎የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች ሲከናወኑ እንዲሁም በማዕቀፍ ግዥ ጭምር የመለዋወጫ ዕቃዎች ሲቀርቡ መቆየታቸውን አንስተዋል።  ‎ ‎በቀሪ ሦስት ወራት የግድቦችን ደህንነት በማረጋገጥ እና የነበሩ ክፍተቶችን በማረም እንዲሁም አማካይ የኃይል ጭነትን በማሻሻል የታቀደውን ዓመታዊ የኃይል ምርት ግብ ለማሳካት እንደሚሰራ አቶ ያለው አይቀር ተናግረዋል:: ‎ ‎ከመነጨው ኃይል ውስጥ 24 ሺህ 970 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል መሸጡንም ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+8

‎ተቋሙ የበጀት ዓመቱን የ9 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እየገመገመ ነው ‎.....///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የተቋሙ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ ሁሉም ሥራ መሪዎችና የዋና መ/ቤት ሠራተኞች በተገኙበት በተቋሙ የመሰብሰቢያ አዳራሽ መገምገም ጀምሯል። ‎ ‎የግምገማ መድረኩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ የኦፕሬሽን፣ የፕሮጀክትና ሌሎች ተቋማዊ ሥራዎች እንዲሁም የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ያለፉት ዘጠኝ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የአይሻና የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን አስመርቆ ወደ ሥራ በማስገባት ትልቅ ታሪክ የተመዘገበበት መሆኑን ተገልጿል። ‎ ‎በተለያየ የግንባታ ሂደት ላይ በሚገኙ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ላይ ቀጣይነት ያለው መሻሻል መመዝገቡንም በመድረኩ ላይ ተብራርቷል። ‎ ‎ተቋሙ አዳዲስ ፕሮጀክቶችን ከመገንባት ባሻገር ነባር የኃይል መሠረተ ልማቶችን በማዘመንና አቅማቸውን በማሳደግ በኩልም ቁልፍ ሥራዎች መከናዎናቸውም ተነግሯል። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ተቋሙ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ከኪሳራ ወጥቶ ትርፍ የተመዘገበ ሲሆን ለዚህ ስኬት የመንግስት ድጋፍ እንደተጠበቀ ሆኖ የተቋሙ ሠራተኞችና አመራሮች የራሳቸው ድርሻ እንደነበራቸው ተገልጿል። ‎ ‎በግምገማ መድረኩ የተቋሙን የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም የኮርፖሬት ፕላኒንግ ተወካይ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ያለውአይቀር ማንደፍሮ እየቀረበ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ብርሃን የሚፈነጥቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ! 🇪🇹⚡️🌍 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD) የሀገራችንን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለምሥራቅ አፍሪካ አ
ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ ብርሃን የሚፈነጥቀው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ! 🇪🇹⚡️🌍 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD) የሀገራችንን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለምሥራቅ አፍሪካ አዲስ የኢኮኖሚና የኢነርጂ ትስስር ምዕራፍ እየከፈተ ይገኛል። ኢትዮጵያ ያላትን የታዳሽ ኃይል ፀጋ ወደ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ በመለወጥ ቀጣናዊ ውህደትን የምታፋጥንበት ስትራቴጂካዊ መሣሪያም ሆኖ እያገለገለ ነው። የግድቡ ስትራቴጂካዊ ሚና በሦስት ዋና ዋና ዘርፎች ይገለፃል፡፡ 1. የአፍሪካ የኃይል ቋት ማዕከልነት 🔋 ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ቋት ማዕከል በመሆን ለጎረቤት ሀገራት አስተማማኝና በዋጋ ተወዳዳሪ የሆነ ኃይል ታቀርባለች። ይህ ኃይል ለኢትዮጵያም ሆነ ኃይል ከኢትዮጵያ ለሚገዙ ወገኖች ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡ • ለኢትዮጵያ፦ ከግድቡ የሚመነጨው ኃይል ሙሉ በሙሉ ቢሸጥ በዓመት እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ይገኛል። ይህም ከቡና ቀጥሎ ትልቁ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ የመሆንዕድል እንዳለው ያሳያል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከኢትዮጵያ-አልፎ-ለአፍሪካ-ብርሃን-የሚፈ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም

ጤናማ አዕምሮ ለተሻለ የሥራ ውጤት! 👷♂️🛡🧠 በየዓመቱ በሚያዝያ ወር የሚታሰበው የዓለም የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት ቀን ዘንድሮ "ጤናማ የስነ-ልቦናና ማህበራዊ የስራ አካባቢን እናረጋግጥ" በ
ጤናማ አዕምሮ ለተሻለ የሥራ ውጤት! 👷♂️🛡🧠 በየዓመቱ በሚያዝያ ወር የሚታሰበው የዓለም የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት ቀን ዘንድሮ "ጤናማ የስነ-ልቦናና ማህበራዊ የስራ አካባቢን እናረጋግጥ" በሚል መሪ ቃል ይከበራል። ስለ ሥራ ቦታ ደህንነት ስናስብ መጀመሪያ ወደ አእምሮአችን የሚመጣው የአካል ጉዳትን መከላከል ቢሆንም የዘንድሮው መሪ ቃል ትኩረት ግን ከዚያም ያለፈ ነው። አንድ ሠራተኛ ውጤታማ እንዲሆን ከአካላዊ ደህንነት በተጨማሪ የተረጋጋ ሥነ-ልቦና እና ጤናማ ማህበራዊ ግንኙነት ያለው የሥራ ድባብ ያስፈልገዋል። ለምን ንቁ ተሳትፎ ያስፈልገናል? ✅ ደህንነት የጋራ እሴት ስለሆነ፤ የአደጋ መከላከያ መመሪያዎችን መተግበር የአንድ ክፍል ኃላፊነት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ሠራተኛና አመራር የዕለት ተዕለት ተግባር መሆን አለበት። ✅ የአእምሮ ጤና ለውጤታማነት አጋዥ ስለሆነ፤ ጭንቀትና ጫና የበዛበት የሥራ አካባቢ ለአደጋዎች መከሰት ዋነኛ መንስኤ ነው። የተረጋጋ ሥነ-ልቦና ሲኖር ግን ፈጠራና ጥራት ይጨምራል። ✅ መከላከል ቀዳሚ ትኩረት መሆን ስላለበት፤ የሥራ ላይ አደጋዎችን ቀድሞ በመለየትና ሪፖርት በማድረግ የራሳችንንና የባልደረቦቻችንን ሕይወት መታደግ ይኖርብናል። በመሆኑም በተቋማችን ውስጥ ማንም ሠራተኛ በአካልም ሆነ በሥነ-ልቦና ሳይሰጋ በደስታና በሙሉ አቅሙ የሚሠራበትን አካባቢ ለመፍጠር በጋራ መቆም ይጠበቅብናል። የሥራ ላይ ደህንነት ደንቦችን እናክብር፤ አንዳችን ለሌላችን ደህንነት ዘብ እንቁም! ጤናማ የሥራ አካባቢ ለሁሉም! 🇪🇹⚙️

🇪🇹⚡️ ኢትዮጵያ የኃይል ማማ (Power Hub) የመሆን ጉዞዋን አፋጥናለች! 🇪🇹 🇪🇹🏗⚡️ ሀገራችን ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኃይል ማመንጨት ዘርፍ አስደናቂ ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች። አጠቃላይ ሀገራዊ የማመንጨት አቅማችን አሁን ላይ 9,760 ሜጋ ዋት (MW) ደርሷል፤ ይህም ለኢንዱስትሪዎቻችን ዕድገትና ለቀጣናዊ ትስስር ትልቅ ግብዓት እንደሚሆን ይታመናል፡፡ 🇪🇹 የውሃ ኃይል ማመንጫዎቻችን ድርሻ በኃይል ማመንጨት ሂደት ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ የሚይዙት የውሃ ኃይል ማመንጫዎቻችን ሲሆን ከሚመነጨው 96% አስተዋጽዖ አላቸው፡፡ 🇪🇹🌊🏗⚡️ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ (GERD)፦ በ 5,150 MW ግዙፍ አቅሙ የኃይል ማመንጫችን በመሆን በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ውስጥ ከመነጨው የ51% ድርሻ ነበረው፡፡ 🇪🇹🌊🏗⚡️ ጊቤ III (1,870 MW)፣ በለስ (460 MW) እና ሌሎችም የኃይል ማመንጫዎች እንደ ማመንጨት አቅማቸው ለኃይል አቅርቦቱ የራሳቸውን አስተዋጽዖ በማበርከት ላይ ይገኛሉ። 🇪🇹 እያደገ የመጣው የንፋስ እና የሌሎች ታዳሽ ኃይሎች ድርሻ 💧 🌊 የንፋስ ኃይል (~504 MW)፦ በአዳማ፣ በአሸጎዳ፣ በአይሻ እና በአሰላ የሚገኙ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ኢትዮጵያን በአፍሪካ የንፋስ ኃይል ቀዳሚ እያደረጓት ይገኛሉ። ♻️ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ፡- በረጲ የተገነባው ከደረቅ ቆሻሻ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአፍሪካ የመጀመሪያው ጣቢያ ሲሆን ከኃይል ማመንጨት በተጓዳኝ የከተማዋን ቆሻሻ በማስወገድ ረገድ አርአያ የሆነ ተግባር እያከናወነ ነው፡፡ ♨️🌋 ጂኦተርማል፦ በአሉቶ ላንጋኖ፡- በቱሉ ሞዬና በኮርቤቲ የሚከናወኑ የከርሰ-ምድር እንፋሎት ፍለጋዎች አዲስ የኃይል አማራጭና ስብጥሩን የሚያሰፉ ዕድሎችን ይዘውልን እየመጡ ነው። 🇪🇹 ቀጣይ ግባችን - የማመንጨት አቅምን 17,000 ሜጋ ዋት ማድረስ! 🏗 የሀገራችንን የኃይል አቅርቦት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ግዙፍ ፕሮጀክቶች በግንባታና በሂደት ላይ ይገኛሉ፡፡ 💧 ኮይሻ (1,800 MW) የውሃ ኃይል ማመንጫ፤ 🌬 አይሻ I እና III የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች፤ ♨️🌋 ቱሉ ሞዬ እና ኮርቤቲ የግል ባለሀብቶች (IPPs) የሚሳተፉባቸው ግዙፍ የጂኦተርማል ፕሮጀክቶች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ 🇪🇹 ኢትዮጵያ የራሷን የኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባለፈ ለጎረቤት ሀገራት አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ የቀጣናው የኢኮኖሚ ትስስር ማዕከል እየሆነች ነው። ይህ የሁላችንም ኩራትና የብልጽግናችን መሠረት ነው! 🇪🇹🌊🏗⚡️

photo content