ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 554 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 399,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 163

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 554 名订阅者。

根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 12,过去 24 小时变化为 7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.73%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.92% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 157 次浏览,首日通常累积 2 320 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 554
订阅者
+724 小时
+77
+1230
帖子存档
በኢትዮጵያ በመንግስት እና የግል አጋርነት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሊገነቡ ነው …...///…... በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግሥትና የግል አጋርነት ዘርፍ (Public- Private Par
በኢትዮጵያ በመንግስት እና የግል አጋርነት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሊገነቡ ነው …...///…... በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግሥትና የግል አጋርነት ዘርፍ (Public- Private Partnership) የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ሊከናወን ነው። ‎የኢትዮጵያ መንግስት ከዩናይትድ ኪንግደም መንግሥት ጋር ሁለት የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ለመገንባት የ400 ሚሊዮን ዶላር ሥምምነት ተፈራርሟል። ‎ሥምምነቱ 198 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የሁርሶ- አይሻ ባለ 400 ኪሎ ቮልት እና 206 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍን የደገሃቡር- ቀብሪድሃር ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ለመገንባት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በኢትዮጵያ-በመንግስት-እና-የግል-አጋርነ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም

ከማከፋፈያ ጣቢያው የሚፈልገውን ኃይል እያገኘ መሆኑን ፋብሪካው ገለፀ .......///........ ከኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለምርት ሂደቱ የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑ
+9
ከማከፋፈያ ጣቢያው የሚፈልገውን ኃይል እያገኘ መሆኑን ፋብሪካው ገለፀ .......///........ ከኮምቦልቻ ቁጥር 1 ማከፋፈያ ጣቢያ ለምርት ሂደቱ የሚያስፈልገውን የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን የአማር ቁጥር አንድ የከረጢትና ፕላስቲክ ማምረቻ ፋብሪካ አስታወቀ፡፡ የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ እንየው ጌትነት (ዶ/ር) እንደተናገሩት ፋብሪካው የፕላስቲክና የአግሮ ባግ ከረጢቶችን እያመረተ ይገኛል፡፡ ፋብሪካው ለብቻው በተዘረጋለት መስመር በቀጥታ ከማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሪክ ኃይል እያገኘ መሆኑን በመግለጽ አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ እንደተቀረፈ ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… ‎https://www.eep.com.et/?amh-news=ከማከፋፈያ-ጣቢያው-የሚፈልገውን-ኃይል-እ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዕድገት በጋራ ማደግ መርህ ላይ የተመሰረተ ነው _ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ....///.... የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዕድገት ጎረቤት ሀገራትን የሚጎዳ ሳይሆን በጋራ የማደግ መርህ ላይ የተመሠረተ መሆኑን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒሰትር  ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍን በመረቁበት ወቅት እንደተናገሩት ኢትዮጵያ  የምትገነባው የአረንጓዴ ኢነርጂ አካባቢን የማይጎዳ እና ለመላው አፍሪካ የመጣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ብስራት ነው። ከ21ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ በኋላ የኤሌክትሪክ  ኃይል ዕድገትን  ያረጋገጡ ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ቢያመጡም በነበረው የኢነርጂ አመራረት ችግር ምክንያት በተፈጥሮ ላይ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ ያለፈ ዕድገት እንደነበራቸው አንስተዋል። በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ ዕድገት እንዲመጣ ከተፈጥሮ ጋር የተስማማ ንጹህ ኢነርጂ ማምረት እንደሚገባ በአፅንኦት ተናግረዋል። ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ ግርማ ሞገስና የመቻል ተምሳሌት መሆኑን የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአፍሪካ ህዝቦች ከፈለጉና ከወደዱ እንዲሁም ከተደመሩ ግዙፍ ሥራ ጀምረው መጨረስ እንደሚችሉ ያሳየ የንፁህ ኢነርጂ ፕሮጀክት ነው ብለዋል ። ግድቡ በኢትዮጵያውያን ታስቦ በኢትዮጵያውያን ሀብት ብቻ የተገነባ ለመላው አፍሪካ የምሳሌነት ምልክት እንደሆነም ነው የገለጹት  ። ኢትዮጵያ ከተለያዩ የታዳሽ ኃይል ምንጮች የምትገነባቸው ፕሮጀክቶች የወደፊቱን የአፍሪካ ዘመን ዕድገት ለማረጋገጥ አብዛኛው በንጹህ ኢነርጂ ላይ ያተኮረ መሆን እንዳለበት ያላትን ቁርጠኝነት እንደሚያሳይ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የምታካሂዳቸው የንጹህ ኢነርጂ ኢንቨስትመንቶች ኮፕ 2032 በኢትዮጵያ እንዲዘጋጅና ዓለም አቀፍ እውቅና እንድታገኝ መታሰቡ በአረንጓዴ አሻራ እና በአካባቢ ደህንነት በምትከተለው ፖሊሲ የተገኘ ውጤት መሆኑን አመልክተዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 24 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

‎የኢነርጂ ደህንነት የሀገር ደህንነት ጉዳይ ነው!  ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ‎....///..... ‎የኢነርጂ ደህንነት የሀገር ደህንነት ጉዳይ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። ‎ ‎የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በዛሬው ዕለት በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ተመርቋል፡፡ ‎ ‎በዚህ ወቅት ኢንጂነር አሸብር እንደገለጹት ባለፉት ሰባት የለውጥ ዓመታት እንደ ሀገር የነበረውን 4 ሺህ ሜጋ ዋት ከእጥፍ በላይ በማሳደግ ከ9 ሺህ 700 ሜጋ ዋት በላይ ማድረስ ተችሏል። ‎ ‎ለዚህም የለውጡ መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረትና የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ ድርሻቸው ከፍተኛ ነበር ብለዋል። ‎ ‎የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ መጠናቀቅ እንደ ሀገር የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል በመሆን ቀጣናውን በኤሌክትሪክ ለማስተሳሰር የተያዘውን ግብ አመላካች መሆኑን ገልፀዋል። ‎ ‎ከአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ በተጨማሪ 350 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የሚያስችል ፕሮጀክት ለመገንባት እየተሰራ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር በመንግሥትና በግል አጋርነት 300 ሜጋ ዋት ለማመንጨት ውል ተፈርሞ ለግንባታ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል። ‎ ‎በምስራቁ የአይሻ ኮሪደር ከንፋስ እስከ 9 ሺ ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም መኖሩንም አስገንዝበዋል። ‎ ‎በአሁኑ ወቅት ለኬኒያ፣ ጅቡቲና ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል እየቀረበ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈጻሚው በቀጣይ ከደቡብ ሱዳንና ከሶማሊያ ጋር የኃይል ትስስር ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ‎ ‎ተቋሙ እንደ አዲስ ከተቋቋመ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፉት 6 ወራት ብቻ ከ7 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱንና የውጭ ምንዛሬ ግኝቱም 247 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን ተናግረዋል። ‎ ‎ይህም የአይሻ ሁለት የንፋስ እና የኮይሻ የውሃ የኃይል ማመንጫ ግንባታዎችን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በፋይናንስ ለመደገፍ እንዳስቻለው ጠቁመዋል። ‎ ‎ክቡር ጠ/ሚኒስትሩ የኢነርጂ ሴክተሩን በማሳደግ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማማ ለማድረግ ለሚሰጡት ቆራጥ አመራር፣ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም በፕሮጀክቱ ግንባታ ላይ ለተሳተፉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

በዛሬው እለት ታሪካዊ የሆነውን የአይሻ-2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በይፋ መርቀን ለአገልግሎት አብቅተናል። በሶማሌ ክልል የሚገኘው ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት የኃይል ዋስትና የማረጋገጥ ስትራቴጂያችን አንድ የማዕዘን ድንጋይ ነው። ፕሮጀክቱ ዓመታዊ ኃይል የማመንጨት አቅሙ 467 ጊጋ ዋት በሰዓት (GWh) ሲሆን፤ ዘመናዊ የSCADA እና SVG ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለተረጋጋ የኃይል አቅርቦት እና ለቴክኖሎጂ-መራሽ ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል፡፡ የአይሻ ስትራቴጄያዊ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ ከምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የንፋስ ኮሪደርነቱ ያለፈ ጠቀሜታ አስገኝቶለታል። ለጎረቤት ሀገራት ያለው ቅርበት ኢትዮጵያን የምስራቅ አፍሪካ የኃይል ንግድ ማዕከል ለማድረግ ለተቀመጠው ግብ መሳካት በተግባር የተረጋገጠ ትልቅ እመርታ ነው። በመደመር መርህ የኢትዮጵያን ሰፊ የተፈጥሮ ጸጋ ወደ የጋራ ሐብት በመለወጥ የአፍሪካ ቀንድን  በአካል እና በኢኮኖሚ ይበልጥ ለማስተሳሰር ቁርጠኞች ነን። "ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)"

‎የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ ‎…...///….... ‎ከአዲስ አበባ በ700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሶማሌ ክልል አይሻ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በይፋ ተመረቀ፡፡ ‎ ‎በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣የጅቡቱ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የፌደራል መንግስትና የክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ከ257 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በ2009 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን በፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የ32 ተርባይኖች ተከላ፣  30 የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶችና የስዊች ያርድ እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። ‎ ‎በዛሬው ዕለት የተመረቀው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በ32 ተርባይን 80 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ‎ ‎የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ሲጠናቀቅ  የዛሬውን ጨምሮ 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል። ‎ ‎በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ታሪክ የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዩኒት በአማካሪነት ለመጀመሪያ ጊዜ በአይሻ ቁጥር 2 የንፋስኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ ተሳትፎ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

‎የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ተመረቀ ‎…...///….... ‎ከአዲስ አበባ በ700 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሶማሌ ክልል አይሻ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ በይፋ ተመረቀ፡፡ ‎ ‎በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣የጅቡቱ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የፌደራል መንግስትና የክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ ‎ ‎የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ ከ257 ሚሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ በ2009 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን በፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ የ32 ተርባይኖች ተከላ፣  30 የሠራተኛ መኖሪያ ቤቶችና የስዊች ያርድ እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመር የግንባታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ ተጠናቀዋል። ‎ ‎በዛሬው ዕለት የተመረቀው የአይሻ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ በ32 ተርባይን 80 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ‎ ‎የሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ ሲጠናቀቅ  የዛሬውን ጨምሮ 120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ይኖረዋል። ‎ ‎በኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ታሪክ የተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዩኒት በአማካሪነት ለመጀመሪያ ጊዜ በአይሻ ቁጥር 2 የንፋስኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ ተሳትፎ አድርጓል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ የዓመቱ ምርጥ የኢነርጂ ፕሮጀክት ተብሎ ተመረጠ .......///........ ‎ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በአፍሪካ የንግድ ምክር ቤት የ2026 የዓመቱ "የኢንዱስትሪ ኢነርጂ ፕሮጀክት" (Industrial Energy Project of the Year) ተብሎ ተመረጠ።  ‎ የዕውቅና ሥነ-ሥርዓቱ ጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም ማታ በጋና አክራ ኬምፐንስኪ ጎልድ ኮስት ሆቴል ተካሂዷል። ‎ ዕውቅናው የታላቁ ህዳሴ ግድብ አህጉራዊ ፋይዳ ያለው ታላቅ የኢንዱስትሪ ኢነርጂ ፕሮጀክት መሆኑን ለመመስከር ያለመ ነው። የዕውቅና ሽልማቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን በመወከል በጋና የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተጠባባቂ የሚሲዮን መሪ  የሆኑት ክቡር                                                                                       አምባሳደር አሣየ ዓለማየሁ (ዶ/ር) ተቀብለዋል። በእውቅና ሽልማቱ ፕሮግራም ላይ የተለያዩ ሀገራት መሪዎች፣ ሚኒስትሮች፣ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎችና ተቋማት ኃላፊዎች፣ ኣምባሳደሮች እና ሌሎች ታዋቂ ሰዎች ተገኝተዋል፡፡ ‎በአፍሪካ የንግድ ምክር ቤት የአፍሪካ የንግድ ሽልማት ዳይሬክተር መሀሙዱ ሃያቱ እንደገለፁት ምክር ቤቱ ፕሮጀክቱን ለመሸለም የወሰነው ግድቡ ለአፍሪካ የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ ለቀጣናዊ የንግድና የኤሌክትሪክ ትስስር እያበረከተ ያለውን የጎላ አስተዋጽኦ እና የፕሮጀክት አመራር ሚና ዕውቅና ለመስጠት ነው። ‎ ግድቡ በኃይል ማመንጨት አቅምና ዋስትና እንዲሁም በረጅም ጊዜ የኢንዱስትሪ ሽግግር ላይ የተደረገ ትልቅ ኢንቨስትመንት መሆኑን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ‎ ግድቡ ለከፍተኛ ማኑፋክቸሪንግ፣ ለግብርና ማቀነባበሪያ እና ለኢንዱስትሪ የእሴት ሰንሰለቶች መሠረት የጣለ መሆኑን የጠቆሙት ሚስተር መሀሙዱ ለቀጣናዊ የኃይል ትስስር እና ለዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል። ‎ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ዕውቅናው በአፍሪካ ንግድ ሽልማት ቋሚ ተቋማዊ መዝገብ ላይ የሚሰፍር ይሆናል። ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በኤምባሲው በኩል ዕውቅናውን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት ሽልማቱ የአፍሪካን የወደፊት ዕጣ ፈንታ ሀገራት በራሳችን ሀብትና ጥረት ለመገንባት ያለንን የጋራ ምኞት የሚያሳይ ነው ብለዋል።‎ ‎ግድቡ ግዙፍ፣ ውስብስብ እና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች በአፍሪካውያን ታስበው፣ ተገንብተው እና ተመርተው ለአፍሪካውያን የጋራ ብልፅግና ሊውሉ እንደሚችሉ ማረጋገጫ የሰጠ ነው። ‎ ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ ወደ አረንጓዴ ኢነርጂ-መር የልማት ጎዳና የምታደርገውን ስልታዊ ሽግግር የሚያሳይ ህያው ምስክር  ነው ብለዋል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በመልዕክታቸው። ኢትዮጵያ ታዳሽ የውሃ ኃይልን በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ ዕድገት፣ የኢንዱስትሪ መስፋፋት እና የአካባቢ ጥበቃ ተደጋግፈው የሚሄዱ ጉዳዮች መሆናቸውን እያስመሰከረች እንደምትገኝ አብራርተዋል። ‎ግድቡ በአሁኑ ወቅት ፋብሪካዎችን በማንቀሳቀስ፣ የዲጂታል ሽግግርን በማገዝ እና በምስራቅ አፍሪካ የኃይል ገንዳ (Eastern Africa Power Pool) በኩል ድንበር ተሻጋሪ የኃይል ትስስርን በማጠናከር እንደ አህጉራዊ የኃይል ማዕከል እያገለገለ መሆኑን ጠቅሰዋል። ‎ ዕውቅናው ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ህብረት የ2063 አጀንዳ ስኬት ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን በማንሳት ፕሮጀክቱ አፍሪካ በራሷ ኃይል ኢንዱስትሪዎቿን የማንቀሳቀስ አቅም እንዳላት ለዓለም ያበሰረ ክስተት ሆኖ መመዝገቡን በመልዕክታቸው ጠቅሰዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

መኾኒ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ   ከ500 በላይ የታወር ብረቶች ተያዙ …///… በሰሜን ሪጅን ከአላማጣ – መኾኒ – መቐለ አቅጣጫ በተዘረጋው የ230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት መምሰሶዎች ላይ ተሰርቀው የተደበቁ ከ500 በላይ ብረቶች መያዙን የሰሜን ሪጅን ፊዚካል ሴኩሪቲ አስታወቀ፡፡  በሪጅኑ የመሰረተ ልማት ደህንነት ፊዚካል ሴኩሪቲ አባል ኮሎኔል ማዕረግ አሰፋ እንዳስታወቁት በሪጅኑ ከአላማጣ – መኾኒ – መቐለ አቅጣጫ በተዘረጋው የ230 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር በሚያጋጥመው ተደጋጋሚ ስርቆት ከፍተኛ ውድመት የሚደርስበት አካባቢ ነው፡፡ በተለይም በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን፣ ራያ ዓዘቦ ወረዳ፣ መኾኒ ከተማና አካባቢው ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ በመሆኑ ከመደበኛ የጥገና ሥራዎች ጎን ለጎን የኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ደህንነትን ለማስጠበቅ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡ የአካባቢውን ማህበረሰብ በማወያየት የቅድመ መከላከል ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የጠቀሱት ኮሌኔሉ በሥጋት ቀጠናዎች ላይ ክትትል እና ድንገተኛ ፍተሻ በማድረግ  ተጠርጣሪዎችን በህግ ቁጥጥር ሥር እያዋሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ እንደ ኮሌኔሉ ገለጻ በመኾኒ ከተማ በተደረገ ድንገተኛ ፍተሻ ለጊዜው ግምታዊ ዋጋቸው ያልታወቀ ከ500 በላይ የታወር ብረቶች የተያዙ ሲሆን በጉዳዩ ላይ አንድ ባጃጅ እና አምስት ተጠርጣሪ ግለሰቦች በሕግ ቁጥጥር ሥር ውለው ክስ ተመስርቶባቸዋል። በሪጅኑ የሚገኙ የተቋሙን መሰረተ ልማቶች ደህንነት የመጠበቅ ሥራ ከሪጅኑ አመራርና ሠራተኛ እንዲሁም ከአካባቢው የመስተዳደር አካላትና ከመላው ማህበረሰብ ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 20  ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+3

🌍 Today is World Clean Energy Day! (January 26) Did you know that Ethiopia is one of the greenest countries in the world whe
🌍 Today is World Clean Energy Day! (January 26) Did you know that Ethiopia is one of the greenest countries in the world when it comes to energy? 🇪🇹 Here are 4 reasons why today matters: 1️⃣ Climate Protection: Renewable energy is helping us fight the 1.5°C global warming limit. 2️⃣ Affordability: Solar energy is now the cheapest source of electricity in history! 3️⃣ National Success: 98% of our electricity comes from clean sources like the sun, wind, and water. 4️⃣ Regional Leadership: With a capacity of over 9,700 MW, Ethiopia is becoming the clean energy hub for all of East Africa. Let’s celebrate a cleaner, brighter future for our children. Happy World Clean Energy Day! #CleanEnergy #Ethiopia #GreenEnergy #WorldCleanEnergyDay #Sustainability

🌍 የዓለም የንፁህ ኢነርጂ ቀን (ጥር 18) የንፁህ ኢነርጂ ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ ጥር 18 ወይም እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ጃንዋሪ 26 ቀን ይከበራል። ዋነኛ ዓላማው፦ ✅ አካባቢን የማይበክሉ የንፁህ ኢነርጂ ምንጮችን (ፀሃይ፣ ንፋስ፣ ሃይድሮ፣ ጂኦተርማል፣ ባዮማስ) ማስተዋወቅ እና ጥቅም ላይ ማዋል ✅ የነዳጅ ጥገኛነት መቀነስ ✅ ርካሽ ኢነርጂን ለተጠቃሚው ማቅረብ ✅ የማህበረሰብ ግንዛቤ ማሳደግ የኢነርጂ ዘርፍ በየጊዜው በርካታ ታሪካዊ ስኬቶችን አስመዝግቧል። 1. የአቅም እድገት 💡 30%፦ በዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ምርት ውስጥ የታዳሽ ኃይል ግምታዊ ድርሻ። o በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በበርካታ ታላላቅ ኢኮኖሚዎች ውስጥ የንፋስ እና የፀሐይ ኃይል ከድንጋይ ከሰል (Coal) የተሻለ ውጤት እያስመዘገቡ ነው። 💡 510 ጊጋ ዋት (GW)፦ ባለፈው ዓመት ብቻ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጨመረው የታዳሽ ኃይል መጠን ሲሆን፣ ይህም ካለፉት ዓመታት የ50% እድገት አሳይቷል። 💡 $1.8 ትሪሊዮን ዶላር፦ ባለፈው ዓመት ለንፁህ ኢነርጂ ቴክኖሎጂዎች (የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች፣ ለኃይል ማመንጫዎች እና ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ) ኢንቨስት የተደረገው ግምታዊ ዓለም አቀፍ በጀት ነው። ይህም ለነዳጅ እና ጋዝ ከሚወጣው መዋዕለ ንዋይ በእጅጉ ይበልጣል። 2. የፀሐይ እና የንፋስ ኃይል የበላይነት 🎯 ከ$0.02 – $0.05 ዶላር በኪሎዋት ሰዓት (kWh)፦ በትላልቅ የፀሐይ ኃይል ማመንጫዎች የሚመረት የኤሌክትሪክ አማካኝ ዋጋ ሲሆን ይህም በታሪክ ውስጥ በብዙ የዓለም ክፍሎች የፀሐይ ኃይልን ርካሹ የኤሌክትሪክ ምንጭ አድርጎታል። 🎯 1 ቴራዋት (TW)፦ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተተከለው የፀሐይ ኃይል አቅም ነው፤ ይህም ታሪካዊ ዕድገት ተብሎ ተመዝግቧል። 🎯 11%፦ በአሁኑ ወቅት ከንፋስ ኃይል የሚገኘው የዓለም አቀፍ የኤሌክትሪክ ድርሻ ሲሆን በተለይም በባህር ላይ የሚገነቡ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ፈጣን እድገት እያሳዩ ነው። 3. የአፍሪካ ሁኔታ (በተለይ የኢትዮጵያ ሁኔታ) 🇪🇹 98%፦ በዜና ዘገባዎች እንደተጠቀሰው፣ ይህ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ከታዳሽ ምንጮች (በዋነኝነት ከውሃ፣ ከንፋስ እና ከጂኦተርማል) የሚመረትበት መቶኛ ነው። 📊 600 ሚሊዮን፦ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት የኤሌክትሪክ አገልግሎት የማያገኙ ሰዎች ቁጥር ነው። ይህም እንደ IRENA እና COP32 ያሉ ጉባኤዎች ችግሩን ለመፍታት መስራት ያለባቸው ን ሰፊ የ"ንፁህ ኢነርጂ ክፍተት" እንዳለ ያሳያል። 📊 5,150 ሜጋዋት (MW)፦ የምስራቅ አፍሪካ የንፁህ ኢነርጂ የጀርባ አጥንት የሆነው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) የኃይል ማመንጨት አቅም ነው። ኢትዮጵያ እንደሀገር ከ9 ሺህ 7 መቶ ሜጋ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም ፈጥራለች፡፡ 4. የአካባቢ ተፅዕኖ 🌱 1.50C፦ ዓለም የሙቀት መጠኗ ከዚህ እንዳያልፍ እየታገለች ያለችበት ገደብ ነው። ይህንን ለማሳካት የታዳሽ ኃይል አቅም እስከ 2030 ድረስ በሶስት እጥፍ ማደግ ይኖርበታል። 🌱 12 ጊጋ ቶን፦ በአሁኑ የታዳሽ ኃይል አጠቃቀም እና የኢነርጂ ብክነትን በመቀነስ እርምጃዎች አማካኝነት በየዓመቱ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ የተደረገ የCO2 መጠን ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደብ መረጃ የሥራ መደብ መጠሪያ፦ ቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የሥራ ደረጃ፦ ጂኤስ4 ደመወዝ፦ በድርጅቱ ስኬል መሰረት ብዛት፦ እንደ አስ
የክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የሥራ መደብ መረጃ የሥራ መደብ መጠሪያ፦ ቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የሥራ ደረጃ፦ ጂኤስ4 ደመወዝ፦ በድርጅቱ ስኬል መሰረት ብዛት፦ እንደ አስፈላጊነቱ የሥራ ቦታ፦ ዋናው መ/ቤት የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት የመመዝገቢያ ቀን፦ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ብቻ ይሆናል ። የምዝገባ ቦታ፦ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው በድርጅቱ ዋና መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በአካል በመገኘት መመዝገብ ይቻላል ። ለተጨማሪ መረጃ ከላይ የተያያዘዉን ፎቶ ይመልከቱ! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም

መምሪያው የተቋሙን የአሠራር ስርዓት ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገለፀ …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮሰስ፣ ፖሊሲና የለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ ቀልጣፍ እና ውጤትን መሠረት ያደረገ
+3
መምሪያው የተቋሙን የአሠራር ስርዓት ለማዘመን እየሰራ መሆኑን ገለፀ …….///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮሰስ፣ ፖሊሲና የለውጥ ሥራ አመራር መምሪያ ቀልጣፍ እና ውጤትን መሠረት ያደረገ የአሠራር ስርዓት ለመዘርጋት የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ አንዷለም ኪዳኔ እንደተናገሩት የአሰራርና የዶክመንቴሽን ስርዓቶችን በማዕከል ለማደራጀት፣ ደህንነታችውን ለመጠበቅና ለተጠቃሚዎች ምቹ ለማድረግ የሚያስችል ሲስተም የማበልጸግ ስራ ተከናውኗል። የተቋሙን የመፈፀም አቅም የሚያጎለብቱ የፖሊሲ ዝግጅት፣ መመሪያ፥ ማጣቀሻ ሰነዶች እና ቴምፕሌቶች ተዘጋጅተው ወደ ስራ መገባቱን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=መምሪያው-የተቋሙን-የአሠራር-ስርዓት-ለማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም