en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 544 subscribers, ranking 8 357 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 544 subscribers.

According to the latest data from 01 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 22 over the last 30 days and by 4 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.24%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.50% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 921 views. Within the first day, a publication typically gains 2 563 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 544
Subscribers
+424 hours
-357 days
+2230 days
Posts Archive
በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን በአንድ ሳምንት ብቻ ስድስት የብረት ማማዎች በዘራፊዎች ተቆርጠው ወድቀዋል ……….///………. በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ከቆቃ - አዋሽ 2 - ወንጂ እንዲሁም ለኢትዮ -ጂቡቲ የባቡር መስመር ኃይል እንዲያቀርብ በተዘረጋው የአዋሽ - መልካሳ - ወለንጪቲ የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሶሶዎች ላይ ስርቆትና ውድመት መፈፀሙን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ፡፡ በዘርፉ የመካከለኛ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ጎሳዬ ደምሴ እንዳስታወቁት ከቆቃ - አዋሽ 2 - ወንጂ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተተከሉ አራት ምሶሶች ላይ ታህሳስ 15 ቀን 2015 ዓ.ም የስርቆት ወንጀል ተፈጽሟል፡፡ ስርቆት ከተፈጸመባቸው ምሶሶዎች ከእያንዳንዳቸው ከ60-100 የሚደርሱ ብረቶች መሰረቃቸውን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ የወደቁትን ምስሶዎች መልሶ ለማቆም ለመሰረት ሥራው ብቻ ለእያንዳንዱ አምስት መቶ ሺህ ብር እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል ፡፡ በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ በፍቃዱ በቀለ በበኩላቸው ከአዋሽ - መልካሳ - ወለንጪቲ በተዘረጋው መስመር ላይ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በሁለት የብረት ምሶሶዎች ላይ ልዩ ተልዕኮ ያለው የሚመስል ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ እንዳሉት የብረት ምሶሶዎችን ከመጣልና መስመሩ አገልግሎት እንዳይሰጥ ከማድረግ ውጪ ምንም ዓይነት የሥርቆት ወንጀል አለመፈፀሙ ጉዳት አድራሾቹ የተለየ ዓላማ እንደነበራቸው ማሳያ ነው፡፡ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ማማዎቹ ላይ በተፈፀመው ዝርፊያ ወንጂና አካባቢው ኃይል ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም አካባቢዎቹን በጊዜያዊነት ከቆቃ ኃይል እንዲያገኝ ተደርገዋል፡፡ ውድመት እና ስርቆት የተፈጸመባቸውን የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን የወንጂ ከተማ ከንቲባ እና የከተማዋ ፖሊስ እንዲሁም የአዳማ ወረዳ ፖሊስና የፀጥታ ኃይል ኃላፊዎች በቦታው በመገኘት እንደተመለከቱ ሥራ አስኪያጆቹ ተናግረዋል፡፡ ወንጀል ፈጻሚዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል የጸጥታ ኃይሎች በትኩረት ለመስራት ቃል መግባታቸውም ተገልጿል፡፡። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 18 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ተቋማችን በአዲሰ ዘመን ጋዜጣ ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በተለያዩ የስራ መደቦች ባለው ክፍት ቦታ ያወጣው የሥራ ዝርዝር ማስታወቂያ እነሆ! መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ደግሞ ከታች ባለው ሊንክ እንድታመለክቱ ተጋብዛችኋል፡፡ https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSc47Xii6GSMi4AaSyI3_vyX2syzj9OEVLhQkRCaP4eE5h2MlQ/viewform?usp=sf_link OR https://forms.gle/HodKpyec65qUFJ9e7

photo content
+6

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ጥገና ላይ ለተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞች የምስጋና መርሐግብር ተካሔደ …......///……... በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የተጎዱ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን ጠግኖ ዳግም ሥራ ለማስጀመር በተደረገው የጥገና ሥራ ላይ ተሳትፎ ላደረጉ የተቋሙ ሠራተኞች በባህርዳር ከተማ የምስጋና መርሐግብር ተካሔደ። በመርሐግብሩ ላይ ለተገኙት ሠራተኞቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የሰሜን ምዕራብ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ የጥገና ሥራውን በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ በአፋጣኝ እንዲያገኝ ሲደረግ የቆየው ርብርብ የሚደነቅ መሆኑን ገልፀው የጥገና ሥራውን ላከናወኑ ሠራተኞች እና ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና እና የቴክኒክ ድጋፍ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ እንደገለፁት ከሁመራ - ተከዜ - ሽሬ እንዲሁም ከአቢአዲ - አድዋ ድረስ የተዘረጉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ ሲካሄድ የቆየው የጥገና ሥራ በስኬት ተጠናቋል። የጥገና ሥራውን በዕቅድ ከተያዘው ጊዜ ባነሰ ለማጠናቀቅ የጥገና ሠራተኞቹ ያሳዩት ቁርጠኝነት አክብሮት የሚቸረው መሆኑን በመግለጽ በሥራው ላይ የተሳተፉትን በሙሉ አመስግነዋል። በቀጣይም አገልግሎት መስጠት በጀመሩት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የቅርብ ክትትል ማድረግ እንደሚያስፈልግም አሳስበዋል። በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የርዕሰ- መስተዳድሩ የመሠረተ ልማት አማካሪ አቶ ደሴ አሰሜ በላኩት መልዕክት ከሁለት ዓመት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦባቸው የቆዩት የሁመራ ከተማና አጎራባች ወረዳዎች ዳግም ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ መደረጉ እንዳስደሰታቸው ገልፀው ተቋሙን እና በጥገና ሥራው ላይ ተሳትፎ ያደረጉትን ሠራተኞች በክልሉ መንግሥት ስም አመስግነዋል። ተቋሙ በክልሉ እያከናወናቸው ለሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ጥገና እና ግንባታ ሥራዎች የክልሉ መንግሥት አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ ባስተላለፉት መልዕክት የጥገና ሥራዎቹ እንዲሳኩ ርብርብ ሲያደርጉ ለቆዩ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች፣ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ መስተዳደር አመራሮች እንዲሁም የፀጥታ አካላት ምስጋቸውን አቅርበዋል፡፡ በባህርዳር ከተማ በተካሄደው የምስጋና መርሀ-ግብር ላይ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች፣ በጥገና ሥራው ላይ ተሳትፎ የነበራቸው ሠራተኞች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተግኝተዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 14 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

በተቋሙ ያለውን እውቀት በአግባቡ ለመጠቀም እየተሰራ ነው ........///.......... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያለውን እውቀት በመሠብሰብ በአግባቡ ጥቅም ላይ ለማዋል እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የመረጃ እና እውቀት ሥራ አመራር ቢሮ ገለፀ። በተቋሙ ያለውን እውቀት በማደራጀት ጥቅም ላይ ለማዋል እንዲቻል በእውቀት ሥራ አመራር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ስልጠና ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሠራተኞች እየተሰጠ ይገኛል። በተቋሙ የመረጃ እና እውቀት ሥራ አመራር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጌታቸው ከበደ እንደገለጹት በተቋሙ ውስጥ ያለውን የተበታተነ እውቀት ወደ አንድ በመሠብሠብ ጥቅም ላይ ለማዋል የተለያዩ የአሠራር ሥርዓቶች፣ ፖሊሲዎችና ማኑዋሎች ተዘጋጅተዋል። የእውቀት ሥራ አመራርን በተቋሙ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰሩ ላሉ ሥራዎች ስልጠናው ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ገልፀዋል። እንደ አቶ ጌታቸው ገለፃ ከስልጠናው በኋላ፤ ተበታትነው የሚገኙ የሚታዩና የማይታዩ እውቀቶችን (tacit and explicit knowledge)የመለየት፣ የመሰብሰብና የማደራጀት እንዲሁም ለሌሎች የማስተላላፍ ሥራ ይሠራል። የእውቀት ሥራ አመራር በተቋሙ ወጥነት ባለው መልኩ ተግባራዊ ሲደረግ ልምድ ያላቸው ሠራተኞች እውቀታቸውን ለተተኪዎች ለማስተላለፍ እና ከዚህ በፊት ተቋሙን በሚመለከት የተከናወኑ የተለያዩ ጥናቶችንና መረጃዎችን ለአዳዲስ ሠራተኞች ለማሳወቅ እንደሚያግዝ አቶ ጌታቸው ተናግረዋል። በተቋሙ ያሉ እውቀቶች ከተሠበሰቡና ከተደራጁ በኋላ ለአገልግሎት ምቹ በሆነ ቦታና ሁሉም ሠራተኛ ሊያገኛቸው በሚችለው መልኩ እንደሚቀመጡ ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። ስልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የልማት ሥራ አመራርና የህዝብ አስተዳደር ትምህርት ክፍል መምህር ደስታ ሙሉጌታ (ዶ/ር) በበኩላቸው ተቋማት ውጤታማና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚታዩና የማይታዩ የእውቀት ዓይነቶችን በማስተሳሰር ተግባራዊ ማድረግ ይኖርባቸዋል ብለዋል። በተቋም ውስጥ የሚገኝ እውቀትን ወጥነት ባለው መልኩ ለመተግበርና ጥቅም ላይ ለማዋል በየሥራ ክፍሎች ያሉ የተለያዩ እውቀቶችን እና የሚከናወኑ ተግባራትን ማሰባሰብና ማደራጀት ያስፈልጋልም ነው ያሉት። የእውቀት ሥራ አመራርን በተቋም ላይ ተግባራዊ ለማድረግ እውቀት የት እንዳለ፣ ሠራተኛው ተቋሙን ምን ያህል እንደሚያውቀው፣ እውቀቱ በምን መልኩ እንደተቀመጠ እንዲሁም ያለው እውቀት ለሌሎች እንዴት መተላለፍ አለበት የሚለውን ማወቅና መገንዘብ እንደሚገባ አስረድተዋል። የእውቀት አመራርን ለመተግበርና በአግባቡ ለመምራት የሁሉም ሠራተኛ ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባም ተናግረዋል። ከታህሳስ 13 እስከ 15 ቀን 2015 ዓ.ም በሚቆየው ስልጠና ላይ ስለ እውቀት ሥራ አመራር ጽንሰ ሃሳብ፤ የእውቀት ሥራ አመራር ሞደሎችና ሂደቶች፤ የእውቀት ሥራ አመራር ትግበራ ደረጃዎች፣ ተግዳሮቶችና መልካም አጋጣሚዎች እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ የሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተው ውይይት ይደረግባቸዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 13 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ምስጋና አቀረበ .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የወልቃይትና ሁመራ አካባቢ ህዝብ ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ላደረገው ጥረት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ምስጋና አቀረበ። የዞኑ ምክትል አስተዳዳሪና የሰላምና ፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እንደገለፁት ተቋሙ በቸልተኝነት ከሁለት ዓመት ለሚበልጥ ጊዜ አካባቢው ኤሌክትሪክ እንዳያገኝ አድርጓል በሚል ቅሬታ አድሮብን ነበር። ይሁንና የተሰራውን ሥራ ከተመለከትን በኋላ እንደተቋም ኃይል ለማገናኘት የተቸገረበት ነገር እንዳለ ተረድተናል ብለዋል። እንደ ኮሎኔል ደመቀ ገለፃ የዞኑ ህዝብና መስተዳደር የተቋሙን ነባራዊ ሁኔታ በመረዳት አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ለጥገናው መጠናቀቅ የበኩሉን ድጋፍ አድርጓል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአካባቢውን ባህርይ ታሳቢ ያደረገ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያበጅም ምክትል አስተዳዳሪው ጠይቀዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 12 ቀን 2015 ዓ.ም

ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች የቀረበ የጥናትና ምርምር ፕሮፖዛል ጥሪ የተቋማችን ምርምርና ልማት መምሪያ የተቋሙን ችግሮች ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማጥናት ለመተንተንና ምላሽ ለመስጠት አምስት
+4
ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች የቀረበ የጥናትና ምርምር ፕሮፖዛል ጥሪ የተቋማችን ምርምርና ልማት መምሪያ የተቋሙን ችግሮች ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በማጥናት ለመተንተንና ምላሽ ለመስጠት አምስት የጥናትና ምርምር ርዕሶች መርጦ ወደሥራ ገብቷል፡፡ በመሆኑም ፍላጎትና ችሎታው ያላችሁ የተቋሙ ሠራተኞች እንድትሳተፉበት ዝርዝር መሥፈርቱን ከሥር ያያያዝን መሆኑን እናስታውቃለን፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!”

photo content

የአድዋ እና አክሱም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ወይም ግሪድ ጋር ተገናኝተዋል ……....//.......... ከመቀሌ - አቢአዲ - አድዋ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና በመጠናቀቁ የአድዋና አክሱም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ወይም ግሪድ ጋር መገናኘታቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና እና ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቴ እንደገለፁት ትናንት ከሽሬ አድዋ በ66 ኪሎ ቮልት የሥርጭት አድዋ ከተማ ኃይል ካገኘ በኋላ የአክሱም ከተማ ደግሞ በ132 ኪሎ ቮልት ኃይል እንዲያገኝ ተደርጎ ነበር። ዛሬ በተከናወነው የጥገና ሥራ ከመቀሌ - አቢአዲ - አድዋ የተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና በመጠናቀቁ ከተሞቹ ሙሉ በሙሉ ከ132 ኪሎ ቮልት ኃይል አግኝተዋል። ይህም ሁሉም የማከፋፈያ ጣቢያዎች ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ጋር እንዲገናኝ ማስቻሉን ሥራአስኪያጁ ገልፀዋል። በጦርነት የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመጠገን የተጀመረው ሥራ በአብዛኛው የተጠናቀቀ ሲሆን በወልዲያ ዶሮ ግብር አካባቢ የተጀመረው የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታም በመገባደድ ላይ ይገኛል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ በጥገና ሥራው ላይ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁመው ውጤት ላመጡ የተቋሙ ሠራተኞች ምስጋና አቅርበዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+5

የረጲ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ጥገና እየተደረገለት ነው ……..///………. የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የቆሻሻ ማጣሪያ (leachate treatment plant)፣ የስቲም ተርባይንና ጀነሬተር ጥገና እየተከናወነ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ብሩክ ኤባ እንዳስታወቁት ከጥቅምት ወር መጨረሻ ጀምሮ እየተከናወነ ያለውን ጥገና ሥራ እስከ ታህሳስ መጨረሻ ባሉት ጊዜያት ውስጥ በማጠናቀቅ ጣቢያውን ኃይል ወደ ማምረት ለመመለስ እየተሠራ ነው፡፡ ወደ ኃይል ማመንጫ ጣቢያው የሚመጣው የቆሻሻ ጥራት ከሚጠበቀው ደረጃ በታች መሆኑ፣ ማመንጫ ጣቢያው በባህሪዩ የተለየ በመሆኑና በየሲስተሞቹ የሠለጠነ ባለሙያ እጥረት በመኖሩ ብልሽት እንደሚያጋጥም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ጣቢያው ለጊዜው ኃይል ማምረት ቢያቋርጥም በአሁኑ ወቅት በቀን በአማካይ 600 ቶን ቆሻሻ በማቃጠል ላይ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ጣቢያው ኃይል ወደ ማምረት ሲመለስ ቆሻሻ የመቀበል እና የማቃጠል አቅሙን በመጨመር ለአካባቢ ጥበቃና ለዘመናዊ የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓቱ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ጠቁመዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ የጥገና ሥራው የጣቢያው ባለሙያዎችን ጨምሮ ከኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ በተውጣጡ የተለያዩ ባለሙያዎች እየተከናወነ ነው፡፡ የጥገና ሥራው በራስ አቅም መከናወኑ ለውጭ ሥራ ተቋራጭ ለጥገና ሥራ የሚወጣውን ወጪ ከመቀነስ በተጨማሪ የባለሙያዎችን በራስ የመተማመን አቅም ለማሳደግ እና ወደ ፊት የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ችግሮችን በአጭር ጊዜ ለመፍታት ዕድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡ የጥገና ሥራው በውጭ ሥራ ተቋራጭ ይከናወን ቢባል አንድ ተርባይን ከነጀኔረተሩ ከፍተሻ ጀምሮ ለመጠገን 75 ሚሊዮን ብር ወጪ እንደሚጠይቅም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ለጣቢያው የጥገና ሥራ የሚያገለግሉ የመለዋወጫ ዕቃዎችን ለማቅረብ ተቋሙ "China National Electric Engineering Co.LTD" ከተሰኘ የቻይና ኩባንያ ጋር የማዕቀፍ ግዥ የውል ስምምነት በማድረግ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 10 ቀን 2015 ዓ.ም

ከአቢአዲ - አድዋ የተዘረጋው የባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና 90 በመቶ ተጠናቀቀ ……....//.......... ከአቢአዲ- አድዋ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት
ከአቢአዲ - አድዋ የተዘረጋው የባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጥገና 90 በመቶ ተጠናቀቀ ……....//.......... ከአቢአዲ- አድዋ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተጀመረው የጥገና ሥራ 90 በመቶ መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና እና ቴክኒካል ድጋፍ ቢሮ አስታወቀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቴ እንደገለፁት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ጥገና በአብዛኛው በመጠናቀቁ የአድዋና አክሱም ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እንዲያገኙ ለማድረግ ነገ የሙከራ ይሰራል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአድዋ - ሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ የተዘረጋው የ66 ኪሎ ቮልት የሥርጭት መስመር በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠግኖ የተጠናቀቀ ቢሆንም ከሽሬ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ለመስጠት የሙከራ ሥራ ሲከናወን በብሬከሩ ላይ ችግር ማጋጠሙን ገልፀዋል። የብሬከሩን ብልሽት በመጠገን ከመስመሩ ኃይል የሚያገኙ አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ እንደሚደረግም ተናግረዋል። “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 08 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+4

ለስድስት የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች ዓለማቀፍ የፕሮጀክት ሥራ አመራር ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ተሰጠ .........///........... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ለሚመሩ ስድስት የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች ዓለምአቀፍ የፕሮጀክት ሥራ አመራር ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ተሰጠ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ዘርፍ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር አሜሪካ ሀገር ከሚገኘው የፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት በተሰጠው ዓለምአቀፍ ፕሮጀክት ሥልጠና ላይ 11 የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች ተሳትፈዋል፡፡ በሥልጠናው ከተሳተፉት መካከል ስድስቱ ሥልጠናውን በብቃት በማጠናቀቅ ዓለምአቀፍ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ከፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት አግኝተዋል። የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለሰልጣኞቹ የሰጡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ እንደገለፁት ዓለምአቀፍ የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማግኘታችሁ ተቋሙንና ሀገርን የሚያኮራ ነው። ይህም ተቋሙ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት እንደሚያግዘው በመጠቆም ሌሎች የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችን ብቃት በየደረጃው የማሳደግና የማረጋገጥ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ሰልጣኞችም በስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ለሌሎች የተቋሙ ሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በማካፈል የተሰጣቸውን ተልዕኮ በብቃትና በጥራት እንዲፈጽሙና የተቋሙን የፕሮጀክት ሥራ አመራር በማዘመን የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et ታህሳስ 07 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+3

ለፕሮጀክቱ ከአንድ በላይ የኃይል አማራጭ እንዲኖር ተደርጎ እየተገነባ ነው ……....///……... ለአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር ከአንድ በላይ የኃይል አማራጭ እንዲኖር ተደርጎ እየተገነባ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ፕሮግራም-2 የፕሮጀክት አስተዳደር-1 ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ አባዲ እንደገለፁት የአማራ፣ አፋር እና ኦሮሚያ ክልሎችን የሚያዋስነውን ፕሮጀክት በተያዘው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለአዋሽ- ወልዲያ- ሀራ ገበያ የባቡር መስመር ኃይል ለማቅረብ ከኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ጋር በመሆን የወሰን ማስከበር ሥራዎች ማጠናቀቁን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በአሁኑ ሰዓት ፕሮጀክቱ በሚያልፍባቸው አካባቢዎች ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የካሳ ክፍያ እየተፈፀመ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በኃይል ማስተላለፊያ ግንባታው ላይ የመሰረት ቁፋሮና የአርማታ ሙሌት ሥራዎች በመከናወን ላይ የሚገኙ ሲሆን በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ደግሞ አብዛኛው የሲቪል ሥራዎች ተጠናቀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀምም 60 ነጥብ 43 በመቶ ላይ ደርሷል፡፡ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎች የኤሌክትሮ-ሜካኒካል ዕቃዎች ተከላ መከናወኑን የገለፁት ሥራ አስኪያጁ የትራክሽን ጣቢያዎችን ከተቋሙ የብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር በኮሙዩኒኬሽን መሳሪያዎች ለማገናኘት የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ፈቃድ እየተጠበቀ እንደሚገኝ ጨምረው አብራርተዋል፡፡ በፕሮጀክቱ ለሚገነቡት ስምንት የትራክሽን ጣቢያዎች አስተማማኝ የሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ከአንድ በላይ የኃይል አማራጭ እንዲኖር ተደርጎ እየተገነባ እንደሚገኝ ነው አቶ ዮናስ የተናገሩት፡፡ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉትን ዕቃዎች የመፈተሽ፣ የማምረት እና የማጓጓዝ ሥራዎች በጊዜው ማከናወን ባለመቻሉ ግንባታው መዘግየቱን አስታውሰዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በሚከናወንባቸው አንዳንድ አካባቢዎች ይፈጠሩ በነበሩ የፀጥታ ችግሮች ምክንያት የግንባታ ሥራው ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳድር መቆየቱን ያነሱት አቶ ዮናስ ችግሩን ለመቅረፍም ለአካባቢዎቹ የሀገር ሽማግሌዎች እና የአስተዳደር አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቱን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ ፒንጋኦ ግሩፕ (Pinggao Group) እንዲሁም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የማስፋፊያ ሥራን ቲ.ቢ.ኤ (TBEA,Co.Ltd) የተሰኙ ሁለት የቻይና ኩባንያዎች እያከናወኑት የሚገኝ ሲሆን የተቋሙ የኢንጅነሪንግ የሥራ ክፍል ደግሞ የማማከር ሥራውን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ የፋይናንስ ወጪ ከ16 ነጥብ 85 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር እና ከ174 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ሲሆን የፋይናንስ ወጪው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የሚሸፈን ነው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 07 ቀን 2015 ዓ.ም

በተቋሙ የሚቀርቡ ቅሬታዎች እየቀነሱ ነው ………///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከህግና አሰራር ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ ቅሬታዎች እየቀነሱ መምጣታቸውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወ
በተቋሙ የሚቀርቡ ቅሬታዎች እየቀነሱ ነው ………///…….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከህግና አሰራር ጋር ተያይዞ የሚቀርቡ ቅሬታዎች እየቀነሱ መምጣታቸውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት አስታወቀ፡፡ የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት ህግና አሰራርን እንዲሁም የኅብረት ስምምነቱንና ሌሎች ውሳኔዎችን መሰረት በማድረግ የሚቀርቡ ቅሬታዎችን ለመፍታት በተቋም ደረጃ የቅሬታ አቀራረብና የአቤቱታ ማስተናገጃ ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡ ቅሬታ ማቅረብ ተፈጥሮአዊ የሆነና ሊቆም የማይችል ቢሆንም የሚቀርቡ ቅሬታዎች ግን እየቀነሱ መምጣታቸውን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡ በተዘረጋው የአሰራር ሥርዓት መሰረት የሚቀርቡ ጥያቄዎች ተለይተው ፈጣን ውሳኔ እንዲያገኙ የቅሬታው መነሻና የውሳኔ ሀሳቦች ለተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እየቀረበ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በስራ ዘርፎች ውስጥ በሚሰጡ ውሳኔዎች አልረካንም የሚሉ ሠራተኞችና ደንበኞች የሚቀርቧቸውን ቅሬታዎችን ተቀብሎ በፍጥነት በመመርመር ተገቢው መልስ እየተሰጠ ነው ብለዋል፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ በተቋሙ ሠራተኞች ለሚቀርቡ ልዩ ልዩ ጥያቄዎች ከመሠረታዊ የሠራተኛ ማህበሩ ጋር በመሆን መፍትሔ እና ምላሽ እየተሰጠ ነው፡፡ “ከካርቦን ልቀት የፀዳ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ታህሳስ 06 ቀን 2015 ዓ.ም