en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 534 subscribers, ranking 8 338 in the Technologies & Applications category and 2 162 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 534 subscribers.

According to the latest data from 29 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 6 over the last 30 days and by -1 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.10%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.85% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 901 views. Within the first day, a publication typically gains 2 619 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 8.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 30 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 534
Subscribers
-124 hours
-167 days
+630 days
Posts Archive
photo content

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡-ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡-ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ተ.ቁ የተወዳዳሪዎች ስም ፆታ ኮድ ውጤት ከ 50% ከ 30% ከ 70% የቃለመጠይቅ ውጤት ከ 100% ድምር ውጤት ደረጃ ምርመራ 1 ፋሲካ በቀለ ተሰማ ሴ C/C/G/018 38.5 23.1 65 88.1 1ኛ አልፈዋል 2 መቅደስ ተካልኝ ወ/አረጋይ ሴ C/C/G/011 32 19.2 64 83.2 2ኛ አልፈዋል 3 ሙላቷ ብርሃኑ እንዳይላሉ ሴ C/C/G/046 27 16.2 66 82.2 3ኛ አልፈዋል 4 ቤተልሔም አባይ ተካ ሴ C/C/G/051 34 20.4 61 81.4 4ኛ ተጠባባቂ 5 ብርቱካን ግርማ ብርሃኑ ሴ C/C/G/059 33 19.8 60 79.8 5ኛ ተጠባባቂ 6 ጥሩሴት አዳሙ መንግስቱ ሴ C/C/G/083 32.5 19.5 58 77.5 6ኛ ተጠባባቂ 7 በፀሎት ደስታ ተፈራ ሴ C/C/G/023 44 26.4 50 76.4 7ኛ ተጠባባቂ 8 ትዕግስት ታደለ ዳባ ሴ C/C/G/086 32 19.2 57 76.2 8ኛ ተጠባባቂ 9 ጥሩነሽ ገለታው ማሞ ሴ C/C/G/004 36 21.6 52 73.6 9ኛ ተጠባባቂ

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡ ማሳሰቢያ፡-ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ተ.ቁ የተወዳዳሪዎች ስም ፆታ ኮድ ውጤት ከ 50% ከ 30% ከ 70% የቃለመጠይቅ ውጤት ከ 100% ድምር ውጤት ደረጃ ምርመራ 1 ፋሲካ በቀለ ተሰማ ሴ C/C/G/018 38.5 23.1 65 88.1 1ኛ አልፈዋል 2 መቅደስ ተካልኝ ወ/አረጋይ ሴ C/C/G/011 32 19.2 64 83.2 2ኛ አልፈዋል 3 ሙላቷ ብርሃኑ እንዳይላሉ ሴ C/C/G/046 27 16.2 66 82.2 3ኛ አልፈዋል 4 ቤተልሔም አባይ ተካ ሴ C/C/G/051 34 20.4 61 81.4 4ኛ ተጠባባቂ 5 ብርቱካን ግርማ ብርሃኑ ሴ C/C/G/059 33 19.8 60 79.8 5ኛ ተጠባባቂ 6 ጥሩሴት አዳሙ መንግስቱ ሴ C/C/G/083 32.5 19.5 58 77.5 6ኛ ተጠባባቂ 7 በፀሎት ደስታ ተፈራ ሴ C/C/G/023 44 26.4 50 76.4 7ኛ ተጠባባቂ 8 ትዕግስት ታደለ ዳባ ሴ C/C/G/086 32 19.2 57 76.2 8ኛ ተጠባባቂ 9 ጥሩነሽ ገለታው ማሞ ሴ C/C/G/004 36 21.6 52 73.6 9ኛ ተጠባባቂ

photo content
+1

ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ ገቢውን 95 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዷል .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ ዓመታዊ ገቢውን 95 ቢሊዮን ብር ለማድረስ ማቀዱን የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የስትራቴጂና ኢንቨስትመንት ዳይሬክተር አቶ ወንዶሰን ተሾመ የዕቅድ  ትግበራውን አስመልክተው ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት ተቋሙ የውጭ ምንዛሪ እጥረትና የውጭ ዕዳ ጫና ያለበት በመሆኑ የፋይናንስ አቅሙን ደካማ አድርጎት ቆይቷል። የተቋሙን ወጪ በመቀነስ እና የውጭ ዕዳ ጫናውን ለማቃለልና ገቢው በማሳደግ ትርፉን ለመጨመር የሚያስችሉ አዳዲስ ሀሳቦች በዕቅዱ ውስጥ መካተቱን ገልፀዋል። በቀጣይ ሦስት ዓመታት የሀገር ውስጥና የውጭ ደንበኞችን ቁጥር በመጨመር፣ አዳዲስ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት፣ የተለያዩ  የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በማስፋት  እና የተጀመሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ምርት በማስገባት የተቋሙን የፋይናንስ አቅም ጠንካራ ለማድረግ መታሰቡን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። እንደ ተቋም የተገነቡና ከሌሎች የመንግስት የልማት ተቋማት ጋር በቅንጅት የተሰሩ መሰረተ ልማቶችን በመጠቀም የኢንቨስትመንት ወጪን ለመቀነስ ትኩረት  እንደሚደረግም ገልፀዋል። የሚገነቡ ፕሮጀክቶችን በአነስተኛ ወጪ ለመገንባት በሌሎች ሀገራት የተሞከሩ ቴክኖሎጂዎችን በጥናትና ምርምር ታግዞ የማባዛት ሥራ እንደሚሠራ ተናግረዋል። ተቋሙ የሚያጋጥመውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ የውጭ ሀገር የኃይል ሽያጭን በማስፋት በሚገኘው ገቢ ወጪውን ለመሸፈን መታሰቡን አቶ ወንድወሰን ጠቁመዋል። ተቋሙ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በማቅረብ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ገቢውን ወደ 330 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን ይህም ዕዳን በራስ ለመክፈል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። በዘርፉ የኮርፖሬት ሪስክ ማኔጅመንት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ህሊና አለማየሁ በበኩላቸው በኤሌክትሪክ ኃይል ለሚሰሩ ተሸከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን በማቅረብ ፣ ለማዳበሪያ ምርት ግብአት የሚሆን ንፁህ ሀይድሮጅን በማምረት እና ለሀገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት የቴክኒክ ስልጠና አገልግሎት በመስጠት የገቢ ማስገኛ አማራጮችን ለማስፋት መታቀዱን ገልጸዋል። እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ በሦስት ዓመታት ውስጥ በኤሌክትሪክ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ኃይል በማቅረብ ለነዳጅ ከሚወጣው ወጪ 265 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማዳን ታቅዷል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

ኢትዮ- ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናገደ ........///....... የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከኮልፌ ክፍለ ከተማ ጋር ባካሄደው ጨዋታ አንድ ለባዶ ተረቷል። በዚህ የውድድር ዓመት አራት ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ ጥሩ ግስጋሴ ላይ የነበረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ51ኛው ደቂቃ በተቆጠረበት ጎል ሽንፈትን አስተናግዷል። በመከላከል እና መልሶ ማጥቃት የጨዋታ ስልት ወደ ሜዳ የገቡት ኮልፌዎች ዕቅዳቸውን ማሳካት የቻሉ ሲሆን በአንፃሩ ሙሉ በሙሉ በማጥቃት ላይ የተመሠረተ ጨዋታ ይዘው የተጫወቱት ኢትዮ-ኤሌክትሪኮች በተደጋጋሚ በርካታ የጎል ሙከራዎች ቢያደርጉም የኮልፌ ክ/ከተማ ግብ ጠባቂ አምክኖባቸዋል። ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ባሳለፍነው ማክሰኞ ጅማ አባ ጂፍርን 1ለ0 በማሸነፍ በከፍተኛ ሊግ ያከናወናቸውን ሶስት ጨዋታዎች በሙሉ በድል ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን ከሶስት ጨዋታዎች ሙሉ ዘጠኝ ነጥብ በመያዝ ምድቡን በበላይነት እየመራ ነው። በመጪው ቅዳሜ ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ. ም.ከቀኑ 10:00 ሰዓት ከወልዲያ ከተማ ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

በኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌይ ውድድር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለተኛ ሆኖ አጠናቀቀ .........///........ በመቀሌ ከተማ በተካሄደው የ19ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌይ ውድድር የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ክለብ አትሌት የሆነችው ፅጌ ገ/ሰላማ ሁለተኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ አግኝታለች። በውድድሩ ኢትዮ- ኤሌክትሪክን በመወከል አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ፣ በረከት ነጋ፣ ሰለሞን በሪሁን፣ ዓለምፀሐይ ቢምር፣ ፀጋዬ ኪዳኔ እና መዝገቡ ሰማ ተሳታፊ ሆነዋል። ሴትና ወንድ አትሌቶችን በጋራ በማወዳደር በተካሄደው የማራቶን ሪሌይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአትሌት ታደሰ ታከለ አማካኝነት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን ችሏል። በክብር እንግድነት የተገኙት የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሌተናል ጄነራል ፃድቃን ገ/ተንሳይ፣ የኢፌዲሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እንዲሁም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ለአሸናፊ ክለቦች እና አትሌቶች የዋንጫ እና የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል። በአጠቃላይ ከስምንት ክለቦች፣ ከስድስት ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የተውጣጡ 84 አትሌቶች በውድድሩ ተሳትፈዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

20ኛ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በሚኒስቴሩና በተጠሪ ተቋማት አመራሮች ተከበረ .......///....... 20ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል'' በሚል መሪ ቃል የገንዘብ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማቱ አመራሮች በተገኙበት ተከብሯል። በገንዘብ ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለግማሽ ቀን በተዘጋጀው መድረክ ላይ ሙስናን በጋራ ስለመከላከል፣  የሙስና ሥጋት ያለባቸው አሠራሮች ላይ ስለሚወሰዱ የመከላከል እርምጃዎች እንዲሁም የሀብት  ማሳወቅና  ምዝገባ ማካሄድ ሙስናን ለመከላከል ስላለው ሚና በሚሉ ሀሳቦች ላይ ገለፃ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንደተናገሩት መንግስት የኢኮኖሚ እድገት ቀጣይነት በማረጋገጥ ለዜጎች ፍትሐዊ የሀብት አጠቃቀም ለማስቻል በረካታ ስራዎች እየሰራ ነው። በመሆኑም ሙስናን በተቀናጀና በተደራጀ አግባብ መከላከልና ማስቆም ይረዳ ዘንድ በፋይናንስ ዘርፍ ስር ያሉ ሁሉም ተቋማት የበላይ አመራሮች እስከ ቡድን መሪዎች ድረስ የሀብት ምዝገባ ማከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡ የፌዴራል ሥነምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ወዶ አጦ በበኩላቸው በከፍተኛ ፣ በመካከለኛና  በዝቅተኛ  ደረጃ ላይ የሚገኙ አመራሮች ለሚያገለግሉት ሕዝብ የግልጽነት፣ የተጠያቂነት እና የታማኝነት አሰራርን በመዘርጋት ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት ሊያረጋግጡ ይገባል ብለዋል። የመንግስት ሠራተኞችና ተሿሚዎች ሀብታቸውን ማስመዝገብ በህግ የተጣለባቸው ግዴታ በመሆኑ እስካሁን  ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ እስከ ህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ  እንዲያስመዘግቡ  አቅጣጫ ተቀምጧል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 14 የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር ታቅዷል ........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የ14 አዳዲስ  የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ለማስጀመር ማቀዱን በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የኃይል ማመንጫዎች ስትራቴጂና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ማርዓለም አምደብርሃን የተቋሙ  ስትራቴጂክ ዕቅድ ይዘት ለተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ለማስተዋውቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ እንደገለፁት በቀጣዮቹ ሦስት የሚገነቡት መሰረተ ልማቶች 227 ነጥብ 64 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ይፈልጋሉ። ለተቋሙ ሠራተኞች በቨርቹዋል ቴክኖሎጂና በአካል በተደረገው ገለፃ ላይ ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የፕሮጀክቶቹ ፋይናንስ በዓለም ባንክ የኃይል ልማት ዘርፍ ኢንቨስትመንት እና ማሻሻያ ፕሮጀክት ይሸፈናል። በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በኦፕሬሽን ላይ ከ20 ሺህ 634 ኪሎ ሜትር በላይ የማስተላለፊያ መስመር  እና 190 የማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዳሉት የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ የማስተላለፊያ መስመሩን 22 ሺህ 268 ኪሎ ሜትር፤ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ቁጥር ደግም 217 ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ከ41 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 17 የማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። በግንባታ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል 2 ሺህ 187 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የማስተላለፊያ መስመር እንደሚገኝበት ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት። እንደ አቶ ማርአለም ገለፃ በግንባታ ላይ ከሚገኙ ፕሮጀክቶች መካከል ሰባቱን በተያዘው በጀት ዓመት እንዲሁም ቀሪ 10 ፕሮጀክቶችን እስከ 2018 ዓ.ም መጨረሻ ባሉት ጊዜያት  ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል። በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ግሪዱን ለማሳደግ እና አስተማማኝነቱን ለማረጋገጥ በሚጀመሩት ፕሮጀክቶች ላይ 624 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የማስተላለፊያ መስመር እና 14 የማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ሥራን ለመጀመር ዕቅድ መያዙን አቶ ማርአለም ተናግረዋል። ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የኃይል ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ገልፀዋል። በአሁኑ ወቅት የብሔራዊ የኃይል መቆጣጣሪያ ማዕከሉን ሊያዘምኑ የሚችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ገልፀው የግሪድ እና የመቆጣጠሪያ ማዕከሉ የማዘመን ሥራዎች ሲጠናቀቁ የኦፕሬሽን እና የቁጥጥር ሥራውን አመችና በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የተደገፈ በማድረግ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያግዝ አስረድተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ጥገና ላይ ለተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞች ዕውቅና ተሰጠ .........///........ በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የተጎዱ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን እንዲሁም የህዳሴ-ዴዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርን ጠግኖ ዳግም ሥራ ለማስጀመር በተደረገው የጥገና ሥራ ላይ ተሳትፎ ላደረጉ የተቋሙ ሠራተኞች የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጠ። በዕውቅና መርሃ ግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ የጥገና ሥራውን በፍጥነት በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ለማድረግ ርብርብ ያደረጉ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎችን አመስግነዋል። በሁለቱም የጥገና ሥራዎች ላይ የታየው የትብብር አቅም እንደ ተቋም በቀጣይ ለመተግበር በታሰበው የሦስት ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ ትግበራ ላይ እንዲደገም አሳስበዋል። የሰው ኃይል ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው የተከናወነው ሥራ ከዚህ ቀደም ሲል በተቋሙ ሥራ አመራር ቡድን እውቅና ተሰጥቶት እንደነበር አስታውሰው የአሁኑ ዕውቅና ለ426 የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች መሰጠቱን ተናግረዋል። የዕውቅና መርሀግብሩ መካሄዱ  የተቋሙን ሠራተኞች የሥራ ተነሳሽነት እንደሚጨምር ገልፀው መርሃግብሩ እንዲካሄድ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በህዳሴ-ደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኮሪደር ላይ የነበሩ ዛፎችን በማፅዳት መስመሩ አገልግሎት መስጠት እንዲችል መደረጉ በመርሃ ግብሩ ላይ ተጠቅሷል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”     የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric     ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower     ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ   www.eep.com.et     ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9 ሺህ ሜጋ ዋት ለማድረስ ይሰራል .......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የኃይል ማመንጨት አቅሙን ወደ 8 ሺህ 956 ሜጋ ዋት ለማድረስ እንደሚሰራ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ። በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚገኙ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በሚተገበረው ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያ በአካልና በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ተሳታፊ በመሆን  ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱ ላይ የዘርፉ የኢንቨስትመንትና ስትራቴጂ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ተሾመ እንደገለፁት በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የሚተገበረው ዕቅድ በየጊዜው ፈጣን ለውጦችን እያሳየ ከመጣው የሀገሪቱ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጓል። ተቋሙ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተግባራዊ በሚያያደርገው የግሪድ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ የኤሌክትሪክ ማመንጨት አቅምን በ68 በመቶ ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልፀዋል። በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የግንባታ ሥራቸው ከሚጠናቀቁት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ የአሰላ የንፋስ ኃይል፣ የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት  እና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ 3 ሺህ 6 መቶ ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። ስትራቴጂክ ዕቅዱ እንደ ሀገር እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ማድረጉን የገለፁት ዳይሬክተሩ በግንባታ ላይ የሚገኙትን አራት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ሥራ ይሰራል ብለዋል። በአሁኑ ሰዓት ከውሃ 4 ሺህ 820 ሜጋ ዋት፣ ከንፋስ 4 መቶ 4 ሜጋ ዋት እንዲሁም ከቆሻሻ የኃይል ማመንጫ 25 ሜጋ ዋት  ሀገራዊ የኃይል ማመንጨት አቅም ላይ መደረሱን ተናግረዋል። ኢትዮጵያ 90 ከመቶ የሚሆነውን የኃይል አማራጭ የምታገኘው ከውሃ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ወንድወሰን ስትራቴጂክ ዕቅዱ ከውሃ ኃይል ማመንጫ ባሻገር ሌሎች የታዳሽ ኃይል ማመንጫ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም የሚያግዝ እንደሆነም ነው ያስታወቁት። በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 8 መቶ 25 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚያስችሉ ስድስት የንፋስ እንዲሁም 7 መቶ 75 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አምስት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስጀመር በዕቅድ መያዙንም አብራርተዋል። የስትራቴጂክ ዕቅዱ ውጤታማ ሆኖ የታሰበውን ግብ ማሳካት እንዲቻል የአመራሩ እና የሠራተኛው ድጋፍና ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ያነሱት አቶ ወንድወሰን በተቋሙ ስር ያሉ ሁሉም ዘርፎች የልማት ዕቅዱን ማስተገበር የሚያስችል የተቋም አወቃቀርና የአሰራር ሥርዓት ከወዲሁ መዘርጋት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

ተቋሙ የሦስት ዓመት ስልታዊ ዕቅዱ ላይ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል ......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተቋሙ የሦስት ዓመት ስልታዊ ዕቅድ ላይ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ውይይት ማካሄድ ጀምረዋል። የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ተቋሙን የሚያሻግርና እንደሀገር ተጠቃሚ የሚያደርጉ ትሩፋቶች የተካተቱበት ነው። የሦስት ዓመት መሪ የልማት ዕቅዱ የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ዕድገት ያለውን ድርሻ በሚያሳይ መልኩ መዘጋጀቱን አቶ አንዱዓለም ተናግረዋል። ተቋሙ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በሰው ኃይል አደረጃጀት፣  በኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍ ፣ በኃይል ሽያጭ እንዲሁም ለግንባታ በዕቅድ ለተያዙት ፕሮጀክቶች ምን ያህል ወጪ ያስፈልጋል በሚሉ አበይት ጉዳዮች ላይ ለውይይቱ ተሳታፊዎች ገለፃ መሰጠት ተጀምሯል። ለአንድ ቀን በሚቆየው የውይይት መርሃ-ግብር ላይ በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች በአካልና በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ተሳታፊ  እየሆኑ ይገኛል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ህዳር 12 ቀን 2016 ዓ.ም