EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 534 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 338,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 534 名订阅者。
根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.10%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.85% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 901 次浏览,首日通常累积 2 619 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 534
订阅者
-124 小时
-167 天
+630 天
帖子存档
15 533
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡
ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡
ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም
ተ.ቁ
የተወዳዳሪዎች ስም
ፆታ
ኮድ
ውጤት ከ 50%
ከ 30%
ከ 70% የቃለመጠይቅ
ውጤት
ከ 100% ድምር
ውጤት
ደረጃ
ምርመራ
1
ፋሲካ በቀለ ተሰማ
ሴ
C/C/G/018
38.5
23.1
65
88.1
1ኛ
አልፈዋል
2
መቅደስ ተካልኝ ወ/አረጋይ
ሴ
C/C/G/011
32
19.2
64
83.2
2ኛ
አልፈዋል
3
ሙላቷ ብርሃኑ እንዳይላሉ
ሴ
C/C/G/046
27
16.2
66
82.2
3ኛ
አልፈዋል
4
ቤተልሔም አባይ ተካ
ሴ
C/C/G/051
34
20.4
61
81.4
4ኛ
ተጠባባቂ
5
ብርቱካን ግርማ ብርሃኑ
ሴ
C/C/G/059
33
19.8
60
79.8
5ኛ
ተጠባባቂ
6
ጥሩሴት አዳሙ መንግስቱ
ሴ
C/C/G/083
32.5
19.5
58
77.5
6ኛ
ተጠባባቂ
7
በፀሎት ደስታ ተፈራ
ሴ
C/C/G/023
44
26.4
50
76.4
7ኛ
ተጠባባቂ
8
ትዕግስት ታደለ ዳባ
ሴ
C/C/G/086
32
19.2
57
76.2
8ኛ
ተጠባባቂ
9
ጥሩነሽ ገለታው ማሞ
ሴ
C/C/G/004
36
21.6
52
73.6
9ኛ
ተጠባባቂ
15 533
ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡
ስለሆነም መስፈርቱን አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች የተገለጸው በተሰጠው የጽሁፍ እና የቃል ፈተና (ኢንተርቪው) ብልጫ ያመጣችሁ ስለሆነ ከህዳር 18 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃችሁን ዋናውን በመያዝ እየቀረባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈፅሙ እናሳውቃለን፡፡
ማሳሰቢያ፡-ስማችሁ ያልተጠቀሰ ተወዳዳሪዎች የማለፊያ ነጥብ ያላገኛችሁ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም
ተ.ቁ
የተወዳዳሪዎች ስም
ፆታ
ኮድ
ውጤት ከ 50%
ከ 30%
ከ 70% የቃለመጠይቅ
ውጤት
ከ 100% ድምር
ውጤት
ደረጃ
ምርመራ
1
ፋሲካ በቀለ ተሰማ
ሴ
C/C/G/018
38.5
23.1
65
88.1
1ኛ
አልፈዋል
2
መቅደስ ተካልኝ ወ/አረጋይ
ሴ
C/C/G/011
32
19.2
64
83.2
2ኛ
አልፈዋል
3
ሙላቷ ብርሃኑ እንዳይላሉ
ሴ
C/C/G/046
27
16.2
66
82.2
3ኛ
አልፈዋል
4
ቤተልሔም አባይ ተካ
ሴ
C/C/G/051
34
20.4
61
81.4
4ኛ
ተጠባባቂ
5
ብርቱካን ግርማ ብርሃኑ
ሴ
C/C/G/059
33
19.8
60
79.8
5ኛ
ተጠባባቂ
6
ጥሩሴት አዳሙ መንግስቱ
ሴ
C/C/G/083
32.5
19.5
58
77.5
6ኛ
ተጠባባቂ
7
በፀሎት ደስታ ተፈራ
ሴ
C/C/G/023
44
26.4
50
76.4
7ኛ
ተጠባባቂ
8
ትዕግስት ታደለ ዳባ
ሴ
C/C/G/086
32
19.2
57
76.2
8ኛ
ተጠባባቂ
9
ጥሩነሽ ገለታው ማሞ
ሴ
C/C/G/004
36
21.6
52
73.6
9ኛ
ተጠባባቂ
15 533
ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ ገቢውን 95 ቢሊዮን ብር ለማድረስ አቅዷል
.........///.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ ዓመታዊ ገቢውን 95 ቢሊዮን ብር ለማድረስ ማቀዱን የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የስትራቴጂና ኢንቨስትመንት ዳይሬክተር አቶ ወንዶሰን ተሾመ የዕቅድ ትግበራውን አስመልክተው ባቀረቡት ሪፖርት እንደገለጹት ተቋሙ የውጭ ምንዛሪ እጥረትና የውጭ ዕዳ ጫና ያለበት በመሆኑ የፋይናንስ አቅሙን ደካማ አድርጎት ቆይቷል።
የተቋሙን ወጪ በመቀነስ እና የውጭ ዕዳ ጫናውን ለማቃለልና ገቢው በማሳደግ ትርፉን ለመጨመር የሚያስችሉ አዳዲስ ሀሳቦች በዕቅዱ ውስጥ መካተቱን ገልፀዋል።
በቀጣይ ሦስት ዓመታት የሀገር ውስጥና የውጭ ደንበኞችን ቁጥር በመጨመር፣ አዳዲስ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በመገንባት፣ የተለያዩ የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በማስፋት እና የተጀመሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን አጠናቆ ወደ ምርት በማስገባት የተቋሙን የፋይናንስ አቅም ጠንካራ ለማድረግ መታሰቡን ዳይሬክተሩ አብራርተዋል።
እንደ ተቋም የተገነቡና ከሌሎች የመንግስት የልማት ተቋማት ጋር በቅንጅት የተሰሩ መሰረተ ልማቶችን በመጠቀም የኢንቨስትመንት ወጪን ለመቀነስ ትኩረት እንደሚደረግም ገልፀዋል።
የሚገነቡ ፕሮጀክቶችን በአነስተኛ ወጪ ለመገንባት በሌሎች ሀገራት የተሞከሩ ቴክኖሎጂዎችን በጥናትና ምርምር ታግዞ የማባዛት ሥራ እንደሚሠራ ተናግረዋል።
ተቋሙ የሚያጋጥመውን የውጭ ምንዛሬ እጥረት ለመቅረፍ የውጭ ሀገር የኃይል ሽያጭን በማስፋት በሚገኘው ገቢ ወጪውን ለመሸፈን መታሰቡን አቶ ወንድወሰን ጠቁመዋል።
ተቋሙ ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በማቅረብ በቀጣይ ሦስት ዓመታት ገቢውን ወደ 330 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከፍ ለማድረግ የታቀደ ሲሆን ይህም ዕዳን በራስ ለመክፈል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
በዘርፉ የኮርፖሬት ሪስክ ማኔጅመንት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ህሊና አለማየሁ በበኩላቸው በኤሌክትሪክ ኃይል ለሚሰሩ ተሸከርካሪዎች የኃይል መሙያ ጣቢያዎችን በማቅረብ ፣ ለማዳበሪያ ምርት ግብአት የሚሆን ንፁህ ሀይድሮጅን በማምረት እና ለሀገር ውስጥ እና ለጎረቤት ሀገራት የቴክኒክ ስልጠና አገልግሎት በመስጠት የገቢ ማስገኛ አማራጮችን ለማስፋት መታቀዱን ገልጸዋል።
እንደ ሥራ አስኪያጇ ገለጻ በሦስት ዓመታት ውስጥ በኤሌክትሪክ ለሚሰሩ ተሽከርካሪዎች ኃይል በማቅረብ ለነዳጅ ከሚወጣው ወጪ 265 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ለማዳን ታቅዷል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
ኢትዮ- ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ ሽንፈቱን አስተናገደ
........///.......
የኢትዮ-ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ቡድን በኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫ በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ከኮልፌ ክፍለ ከተማ ጋር ባካሄደው ጨዋታ አንድ ለባዶ ተረቷል።
በዚህ የውድድር ዓመት አራት ተከታታይ ጨዋታዎችን በማሸነፍ ጥሩ ግስጋሴ ላይ የነበረው ኢትዮ-ኤሌክትሪክ በ51ኛው ደቂቃ በተቆጠረበት ጎል ሽንፈትን አስተናግዷል።
በመከላከል እና መልሶ ማጥቃት የጨዋታ ስልት ወደ ሜዳ የገቡት ኮልፌዎች ዕቅዳቸውን ማሳካት የቻሉ ሲሆን በአንፃሩ ሙሉ በሙሉ በማጥቃት ላይ የተመሠረተ ጨዋታ ይዘው የተጫወቱት ኢትዮ-ኤሌክትሪኮች በተደጋጋሚ በርካታ የጎል ሙከራዎች ቢያደርጉም የኮልፌ ክ/ከተማ ግብ ጠባቂ አምክኖባቸዋል።
ኢትዮ-ኤሌክትሪክ ባሳለፍነው ማክሰኞ ጅማ አባ ጂፍርን 1ለ0 በማሸነፍ በከፍተኛ ሊግ ያከናወናቸውን ሶስት ጨዋታዎች በሙሉ በድል ማጠናቀቅ የቻለ ሲሆን ከሶስት ጨዋታዎች ሙሉ ዘጠኝ ነጥብ በመያዝ ምድቡን በበላይነት እየመራ ነው።
በመጪው ቅዳሜ ህዳር 22 ቀን 2016 ዓ. ም.ከቀኑ 10:00 ሰዓት ከወልዲያ ከተማ ጋር በአበበ ቢቂላ ስቴዲየም ጨዋታውን የሚያከናውን ይሆናል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
በኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌይ ውድድር ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለተኛ ሆኖ አጠናቀቀ
.........///........
በመቀሌ ከተማ በተካሄደው የ19ኛው የኢትዮጵያ ማራቶን ሪሌይ ውድድር የኢትዮ-ኤሌክትሪክ ክለብ አትሌት የሆነችው ፅጌ ገ/ሰላማ ሁለተኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ አግኝታለች።
በውድድሩ ኢትዮ- ኤሌክትሪክን በመወከል አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ፣ በረከት ነጋ፣ ሰለሞን በሪሁን፣ ዓለምፀሐይ ቢምር፣ ፀጋዬ ኪዳኔ እና መዝገቡ ሰማ ተሳታፊ ሆነዋል።
ሴትና ወንድ አትሌቶችን በጋራ በማወዳደር በተካሄደው የማራቶን ሪሌይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአትሌት ታደሰ ታከለ አማካኝነት የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን ችሏል።
በክብር እንግድነት የተገኙት የትግራይ ክልላዊ መንግስት ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ሌተናል ጄነራል ፃድቃን ገ/ተንሳይ፣ የኢፌዲሪ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እንዲሁም የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ ለአሸናፊ ክለቦች እና አትሌቶች የዋንጫ እና የሜዳሊያ ሽልማት አበርክተዋል።
በአጠቃላይ ከስምንት ክለቦች፣ ከስድስት ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች የተውጣጡ 84 አትሌቶች በውድድሩ ተሳትፈዋል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 15 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
20ኛ ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በሚኒስቴሩና በተጠሪ ተቋማት አመራሮች ተከበረ
.......///.......
20ኛውን ዓለም አቀፍ የፀረ ሙስና ቀን "ሙስና የጋራ ጠላታችን ነው በህብረት እንታገል'' በሚል መሪ ቃል የገንዘብ ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማቱ አመራሮች በተገኙበት ተከብሯል።
በገንዘብ ሚኒስቴር የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለግማሽ ቀን በተዘጋጀው መድረክ ላይ ሙስናን በጋራ ስለመከላከል፣ የሙስና ሥጋት ያለባቸው አሠራሮች ላይ ስለሚወሰዱ የመከላከል እርምጃዎች እንዲሁም የሀብት ማሳወቅና ምዝገባ ማካሄድ ሙስናን ለመከላከል ስላለው ሚና በሚሉ ሀሳቦች ላይ ገለፃ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ እንደተናገሩት መንግስት የኢኮኖሚ እድገት ቀጣይነት በማረጋገጥ ለዜጎች ፍትሐዊ የሀብት አጠቃቀም ለማስቻል በረካታ ስራዎች እየሰራ ነው።
በመሆኑም ሙስናን በተቀናጀና በተደራጀ አግባብ መከላከልና ማስቆም ይረዳ ዘንድ በፋይናንስ ዘርፍ ስር ያሉ ሁሉም ተቋማት የበላይ አመራሮች እስከ ቡድን መሪዎች ድረስ የሀብት ምዝገባ ማከናወናቸውን ገልፀዋል፡፡
የፌዴራል ሥነምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ወዶ አጦ በበኩላቸው በከፍተኛ ፣ በመካከለኛና በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ አመራሮች ለሚያገለግሉት ሕዝብ የግልጽነት፣ የተጠያቂነት እና የታማኝነት አሰራርን በመዘርጋት ለፀረ-ሙስና ትግሉ ያላቸውን ቁርጠኝነት ሊያረጋግጡ ይገባል ብለዋል።
የመንግስት ሠራተኞችና ተሿሚዎች ሀብታቸውን ማስመዝገብ በህግ የተጣለባቸው ግዴታ በመሆኑ እስካሁን ሀብታቸውን ያላስመዘገቡ እስከ ህዳር 23 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንዲያስመዘግቡ አቅጣጫ ተቀምጧል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 14 የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶችን ለማስጀመር ታቅዷል
........///..........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የ14 አዳዲስ የማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ ለማስጀመር ማቀዱን በተቋሙ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የኃይል ማመንጫዎች ስትራቴጂና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ማርዓለም አምደብርሃን የተቋሙ ስትራቴጂክ ዕቅድ ይዘት ለተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ለማስተዋውቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ እንደገለፁት በቀጣዮቹ ሦስት የሚገነቡት መሰረተ ልማቶች 227 ነጥብ 64 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ይፈልጋሉ።
ለተቋሙ ሠራተኞች በቨርቹዋል ቴክኖሎጂና በአካል በተደረገው ገለፃ ላይ ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት የፕሮጀክቶቹ ፋይናንስ በዓለም ባንክ የኃይል ልማት ዘርፍ ኢንቨስትመንት እና ማሻሻያ ፕሮጀክት ይሸፈናል።
በአሁኑ ወቅት ተቋሙ በኦፕሬሽን ላይ ከ20 ሺህ 634 ኪሎ ሜትር በላይ የማስተላለፊያ መስመር እና 190 የማከፋፈያ ጣቢያዎች እንዳሉት የገለፁት ሥራ አስኪያጁ በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ የማስተላለፊያ መስመሩን 22 ሺህ 268 ኪሎ ሜትር፤ የማከፋፈያ ጣቢያዎችን ቁጥር ደግም 217 ለማድረስ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
በአሁኑ ወቅት ከ41 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጭ የተለያየ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 17 የማስተላለፊያ መስመሮች እና የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ግንባታ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቁመዋል።
በግንባታ ላይ ከሚገኙት ፕሮጀክቶች መካከል 2 ሺህ 187 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የማስተላለፊያ መስመር እንደሚገኝበት ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት።
እንደ አቶ ማርአለም ገለፃ በግንባታ ላይ ከሚገኙ ፕሮጀክቶች መካከል ሰባቱን በተያዘው በጀት ዓመት እንዲሁም ቀሪ 10 ፕሮጀክቶችን እስከ 2018 ዓ.ም መጨረሻ ባሉት ጊዜያት ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ግሪዱን ለማሳደግ እና አስተማማኝነቱን ለማረጋገጥ በሚጀመሩት ፕሮጀክቶች ላይ 624 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የማስተላለፊያ መስመር እና 14 የማከፋፈያ ጣቢያዎች የግንባታ ሥራን ለመጀመር ዕቅድ መያዙን አቶ ማርአለም ተናግረዋል።
ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የኃይል ተደራሽነትን ከማሳደግ ባለፈ ለሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት የብሔራዊ የኃይል መቆጣጣሪያ ማዕከሉን ሊያዘምኑ የሚችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ገልፀው የግሪድ እና የመቆጣጠሪያ ማዕከሉ የማዘመን ሥራዎች ሲጠናቀቁ የኦፕሬሽን እና የቁጥጥር ሥራውን አመችና በዘመናዊ ቴክኖሎጅ የተደገፈ በማድረግ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያግዝ አስረድተዋል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ጥገና ላይ ለተሳተፉ የተቋሙ ሠራተኞች ዕውቅና ተሰጠ
.........///........
በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የተጎዱ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን እንዲሁም የህዳሴ-ዴዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመርን ጠግኖ ዳግም ሥራ ለማስጀመር በተደረገው የጥገና ሥራ ላይ ተሳትፎ ላደረጉ የተቋሙ ሠራተኞች የዕውቅና የምስክር ወረቀት ተሰጠ።
በዕውቅና መርሃ ግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ የጥገና ሥራውን በፍጥነት በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ እንዲያገኝ ለማድረግ ርብርብ ያደረጉ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎችን አመስግነዋል።
በሁለቱም የጥገና ሥራዎች ላይ የታየው የትብብር አቅም እንደ ተቋም በቀጣይ ለመተግበር በታሰበው የሦስት ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅድ ትግበራ ላይ እንዲደገም አሳስበዋል።
የሰው ኃይል ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው የተከናወነው ሥራ ከዚህ ቀደም ሲል በተቋሙ ሥራ አመራር ቡድን እውቅና ተሰጥቶት እንደነበር አስታውሰው የአሁኑ ዕውቅና ለ426 የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች መሰጠቱን ተናግረዋል።
የዕውቅና መርሀግብሩ መካሄዱ የተቋሙን ሠራተኞች የሥራ ተነሳሽነት እንደሚጨምር ገልፀው መርሃግብሩ እንዲካሄድ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላትም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በህዳሴ-ደዴሳ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ኮሪደር ላይ የነበሩ ዛፎችን በማፅዳት መስመሩ አገልግሎት መስጠት እንዲችል መደረጉ በመርሃ ግብሩ ላይ ተጠቅሷል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 13 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9 ሺህ ሜጋ ዋት ለማድረስ ይሰራል
.......///........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የኃይል ማመንጨት አቅሙን ወደ 8 ሺህ 956 ሜጋ ዋት ለማድረስ እንደሚሰራ የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ አስታወቀ።
በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚገኙ የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት በሚተገበረው ስትራቴጂክ ዕቅድ ዙሪያ በአካልና በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ተሳታፊ በመሆን ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ ላይ የዘርፉ የኢንቨስትመንትና ስትራቴጂ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ተሾመ እንደገለፁት በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የሚተገበረው ዕቅድ በየጊዜው ፈጣን ለውጦችን እያሳየ ከመጣው የሀገሪቱ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ጋር የተጣጣመ እንዲሆን ተደርጓል።
ተቋሙ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተግባራዊ በሚያያደርገው የግሪድ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ የኤሌክትሪክ ማመንጨት አቅምን በ68 በመቶ ከፍ ለማድረግ እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የግንባታ ሥራቸው ከሚጠናቀቁት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ፣ የአሰላ የንፋስ ኃይል፣ የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት እና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ 3 ሺህ 6 መቶ ሜጋ ዋት ኃይል እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
ስትራቴጂክ ዕቅዱ እንደ ሀገር እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ታሳቢ ማድረጉን የገለፁት ዳይሬክተሩ በግንባታ ላይ የሚገኙትን አራት የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ዝግጁ የማድረግ ሥራ ይሰራል ብለዋል።
በአሁኑ ሰዓት ከውሃ 4 ሺህ 820 ሜጋ ዋት፣ ከንፋስ 4 መቶ 4 ሜጋ ዋት እንዲሁም ከቆሻሻ የኃይል ማመንጫ 25 ሜጋ ዋት ሀገራዊ የኃይል ማመንጨት አቅም ላይ መደረሱን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ 90 ከመቶ የሚሆነውን የኃይል አማራጭ የምታገኘው ከውሃ መሆኑን የጠቀሱት አቶ ወንድወሰን ስትራቴጂክ ዕቅዱ ከውሃ ኃይል ማመንጫ ባሻገር ሌሎች የታዳሽ ኃይል ማመንጫ አማራጮችን በስፋት ለመጠቀም የሚያግዝ እንደሆነም ነው ያስታወቁት።
በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት 8 መቶ 25 ሜጋ ዋት ኃይል ማመንጨት የሚያስችሉ ስድስት የንፋስ እንዲሁም 7 መቶ 75 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው አምስት የፀሐይ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ለማስጀመር በዕቅድ መያዙንም አብራርተዋል።
የስትራቴጂክ ዕቅዱ ውጤታማ ሆኖ የታሰበውን ግብ ማሳካት እንዲቻል የአመራሩ እና የሠራተኛው ድጋፍና ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ያነሱት አቶ ወንድወሰን በተቋሙ ስር ያሉ ሁሉም ዘርፎች የልማት ዕቅዱን ማስተገበር የሚያስችል የተቋም አወቃቀርና የአሰራር ሥርዓት ከወዲሁ መዘርጋት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 12 ቀን 2016 ዓ.ም
15 533
ተቋሙ የሦስት ዓመት ስልታዊ ዕቅዱ ላይ ውይይት ማካሄድ ጀምሯል
......///.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በተቋሙ የሦስት ዓመት ስልታዊ ዕቅድ ላይ በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ውይይት ማካሄድ ጀምረዋል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወካይ እና የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዱዓለም ሲዓ መድረኩን በንግግር ሲከፍቱ እንደተናገሩት ስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ተቋሙን የሚያሻግርና እንደሀገር ተጠቃሚ የሚያደርጉ ትሩፋቶች የተካተቱበት ነው።
የሦስት ዓመት መሪ የልማት ዕቅዱ የኤሌክትሪክ ኃይል ለሀገር ዕድገት ያለውን ድርሻ በሚያሳይ መልኩ መዘጋጀቱን አቶ አንዱዓለም ተናግረዋል።
ተቋሙ በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት በሰው ኃይል አደረጃጀት፣ በኃይል ማመንጨት፣ ማስተላለፍ ፣ በኃይል ሽያጭ እንዲሁም ለግንባታ በዕቅድ ለተያዙት ፕሮጀክቶች ምን ያህል ወጪ ያስፈልጋል በሚሉ አበይት ጉዳዮች ላይ ለውይይቱ ተሳታፊዎች ገለፃ መሰጠት ተጀምሯል።
ለአንድ ቀን በሚቆየው የውይይት መርሃ-ግብር ላይ በሁሉም የሃገሪቱ ክፍሎች ላይ የሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች በአካልና በቨርቹዋል ቴክኖሎጂ ተሳታፊ እየሆኑ ይገኛል።
"ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ህዳር 12 ቀን 2016 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
