es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 695 suscriptores, ocupando la posición 8 017 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 152 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 695 suscriptores.

Según los últimos datos del 31 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 142, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 30.85%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 16.42% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 842 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 578 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 10.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 695
Suscriptores
+224 horas
+237 días
+14230 días
Archivo de publicaciones
photo content
+4

ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ፣ በጀት እና ጥራት እንዲጠናቀቁ ማድረግ ይገባል ‎........///....... በ2018 በጀት ዓመት በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ እና በጀት በጥራት ማጠናቀቅ እንደሚገባ የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ፡፡ ዘርፉ በ2018 በጀት ዓመት የታቀዱ ሥራዎች በሚከናወኑበት አግባብ በሥሩ ከሚገኙ የመምሪያ ኃላፊዎች እና የፕሮጀክት ሥራ አስኪያጆች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ የዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በውይይቱ ላይ እንደገለፁት በመዋቅራዊ ለውጡ ዘርፉ እንደ አዲስ ከተደራጀ በኋላ በዲዛይን፣ ፕሮጀክት ትግበራ፣ ኮንትራት አስተዳደር፣ ግዥና ፋይናንስ አፈፃፀም ላይ ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት እና የኢንጂነሪንግ የሥራ ክፍሎችን በማዋሃድ ቀጣይነት ያለው የሥራ ባህል ለመፍጠር እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡ እንደ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ዘርፉ በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ላይ የፋይናንስ ወጪን ያገናዘበ የሥራ ጥራት እና ቅልጥፍና መለያዎቹ እንዲሆኑ በትኩረት ይሰራል፡፡ ዘርፉ ለተቋሙ የሚያስፈልገው አዋጪ ሥራዎችን ማከናወን እስከቻለ ድረስ ብቻ ነው ያሉት ኢንጂነር ውድነህ ለዚህም በተያዘው በጀት ዓመት የፕሮጀክቶችን የፋይናንስ ቁመና በማስተካከል በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ የውስጥ አቅምን በማጠናከር በአጭር ጊዜ ውስጥ ከሀገር ውጭ በሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ ለመሆን የያዘውን ግብ ለማሳካት አመራሩና ሠራተኛው በቁርጠኝነት ሊሰሩ እንደሚገባም ነው የተናገሩት፡፡ ሙያዊነት ለሥራ ጥራትና ለጋራ መግባባት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ የሥራ ላይ ሥነ-ምግባርን ማሳደግ ጠቃሚ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የሠራተኛውን የሥራ ላይ ደህንነት በማስጠበቅና ከተቋሙ የአሰራር ባህል ጋር እንዲዋሃድ በማድረግ ምቹ የሥራ ከባቢ መፍጠር እንደሚያስፈልግም ነው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚው የጠቆሙት፡፡ በፕሮጀክቶች ግንባታ ዙሪያ ለሚነሱ የአፈፃፀም ክፍተቶች ተጠያቂነትን ለማስፈን እንዲሁም ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሔ ሰጪ ለመሆን አመራሩ ቁርጠኛ ሊሆን እንደሚገባም ነው የገለፁት፡፡ በውይይቱ ላይ ከዲዛይን፣ ከኮንትራት አስተዳደር፣ ከሥራ ላይ ግንኙነት፣ ከፋይናንስና ግዥ፣ ከዘርፉ አወቃቀር፣ ከአሰራር ሥርዓት እና ከበጀት አቅርቦት እንዲሁም ከፕሮጀክቶች አፈፃፀም ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች ቀርበው ምላሽ ተሰጦባቸዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 13 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+5

#Vacancy የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ሠራተኞችን በኮንትራት አወዳድሮ ለኮይሻ ፕሮጀክት ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች የሚከተሉትን
#Vacancy የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ሠራተኞችን በኮንትራት አወዳድሮ ለኮይሻ ፕሮጀክት ለመቅጠር ይፈልጋል። በመሆኑም መስፈርቶቹን የምታሟሉ አመልካቾች የሚከተሉትን ሊንኮች በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። Link 1 👉 https://forms.gle/NbERitgfmi49iRf1A Link 2፡ 👇 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSdirS8H4d3BJU0WgHBMat5IeRjZ5qr_iyRbYlq3gY7w2DD8wg/viewform?usp=dialog 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 12 ቀን 2018 ዓ.ም

#update በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች በከፊል የተቋረጠው ኃይል ከጥቂት ቦታዎች ውጪ ከ95 በመቶ በላይ ተመልሷል። ቀሪዎቹንም አካባቢዎች በተወሰኑ ደቂቃዎች ውስጥ ለማገናኘት እየተሰራ ይገኛል። መደበኛ ጥገና  በሚከናወንበት ሰዓት እና በፍተሻ ወቅት የተፈጠረው ችግር እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁን ደንበኞቻችን ምስጋናችንን እናቀርባለን። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 11 ቀን 2018 ዓ.ም

በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ተከስቷል ……..///……. ከሰበታ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ ጥቁር አንበሳ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ፤ ከጥቁር አንበሳ ኃይ
በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ተከስቷል ……..///……. ከሰበታ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ ጥቁር አንበሳ  ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ፤  ከጥቁር አንበሳ  ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ አዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ማከፋፈያ ጣቢያ  በተዘረጋዉ 132 ኪ.ቮ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ መደበኛ የጥገና ሥራ ሲከናወን ውሏል፡፡ ይሁንና ጥገናው ተጠናቆ መስመር በሚሞከርበት ጊዜ በተፈጠረ የመስመሮች መነካካት በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡   የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ በመሆኑ መስመር በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 11 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ተቋሙ ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ በማውጣት በመቄዶኒያ የማዕድ ማጋራት አደረገ ...‎….///…..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅና መመረቅን ምክንያት በማድረግ ከ2 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ በማድረግ በመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማዕከል በመገኘት ማዕድ አጋርቷል፡፡ ‎ ‎በፕሮግራሙ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ የሥራ አመራር አባላት እና የመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል መስራች ቢኒያም በለጠ ተገኝተዋል። ‎ ‎በፕሮግራሙ ላይ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሀገርና ማህበረሰብን የሚያሻግሩ ትልልቅ የኃይል መሰረተ ልማቶችን ከመገንባት ባሻገር በተለያዩ መስኮች የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራትን በዕቅድ ይዞ በመላ ሀገሪቱ እየሰራ ይገኛል፡፡ ‎ ‎ተቋሙ ቀደም ሲል ለማዕከሉ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡ በዛሬው ዕለት የህዳሴ ግድብ ምረቃ በዓልን በማስመልከት ያከናወነው የማዕድ ማጋራት ተቋሙ የሚያከናውናቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎች አካል መሆኑን የጠቆሙት ዋና ሥራ አስፈፃሚው በቀጣይም ሠራተኞቹን በማስተባበር ጭምር ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ ‎ ‎መቄዶንያ ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማንን ወገኖች የተስፋ ብርሃንና ሕይወትን የሠጠ ተቋም በመሆኑ ይሄን በጎ ተግባር መደገፍ ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የበኩሉን ኃላፊነት ሊወጣ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡ ‎የመቂዶኒያ መሥራች ቢኒያም በለጠ በበኩላቸው ድርጅቱ ካለምንም የውጭ ሀገር የገንዘብ ድጋፍ በየቀኑ ከ2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ በማድረግ በ52 ቅርንጫፎች የሚገኙ ከ8 ሺህ 500 በላይ ከጎዳና ያነሳቸውን አረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማንን በመደገፍ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ ‎ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በራሱ ከሚያደርገው ድጋፍ በተጨማሪ ፕሮጀክቶችን የሚገነቡ ዊ ቢውልድን የመሰሉ የሥራ ተቋራጮችን በማስተባበር ጭምር ለማዕከሉ ትልቅ እገዛ እያደረገ መሆኑንም አስታውሰዋል፡፡ ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ከ15 በላይ ህንጻዎችን በመገንባት ላይ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ ቢኒያም የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 250 በማሳደግ በርካታ አረጋውያንንና የአዕምሮ ህሙማንን ለመደገፍ የያዘውን እቅድ ለማሳካት ተቋሙ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል፡፡ በማዕከሉ የሚኖሩ አረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማኑ በበኩላቸው ተቋሙ ላደረገላቸው የማዕድ ማጋራት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ ለማዕከሉ የሚደርገው ድጋፍ በትክክለኛ ቦታ ላይ ስለሚውል ተቋሙ በቀጣይም ከጎናቸው እንዳይለይ ጠይቀዋል፡፡ የተቋሙ የሥራ አመራር አባላት በማዕከሉ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በየዓመቱ “መስከረም 8 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመቄዶኒያ ለሰብዓዊ ድጋፍ” በሚል መሰየሙም ተገልጿል። ‎“ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው” በሚል መሪ ቃል የአዕምሮ ህሙማንና አረጋውያንን ከጎዳና በማንሳት እየደገፈ የሚገኘው መቂዶኒያ በአዲስ አበባ ማዕከሉ ባለ 15 ወለል ዘመናዊ ሆስፒታል እና መኖሪያ እየገነባ ይገኛል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

photo content
+9

የተሽከርካሪ ስምሪት እና ቁጥጥርን ለማዘመን እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ውጤት እየተገኘባቸው ነው ………///………. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሸከርካሪ ስምሪት እና ቁጥጥርን ለማዘመን የተገበራቸው የአሰራር ስርዓቶች ውጤት እየተገኘባቸው መሆኑን በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ ገለፀ። የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ተቋሙ የተሸከርካሪዎችን ስምሪት ለማሳለጥ እና የቁጥጥር ስርዓቱን ለማዘመን የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፡፡ የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ተሽከርካሪዎች የመስክ ሥራቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ያለ ሥራ የሚቀመጡበት ጊዜ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ይህም የተሸከርካሪ እጥረት እንዲከሰት በማድረግ የሥራ ክፍሎች  ሥራቸውን በዕቅዳቸው መሰረት እንዳያከናውኑ እንቅፋት ሆኖ እንደነበር አቶ ዋለ ተናግረዋል፡፡ በተሸከርካሪ ስምሪት እና ቁጥጥርን ላይ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በአሁኑ ወቅት በተቋሙ ካሉ 1 ሺህ 40 ተሸከርካሪዎች መካከል 500 በሚሆኑት ላይ ጂ.ፒ.ኤስ መገጠሙንም ነው ያስታወቁት፡፡ ተሸከርካሪዎችን በቴክኖሎጂ በመከታተል ሥራቸውን ጨርሰው ሲመለሱ ለሌላ ስምሪት ዝግጁ በማድረግ እና የተቋሙን ሥራ ውጤታማ ለማድረግ የራሱ የሆና አስተዋጽዖ እንዳለው አስረድተዋል፡፡ የጂፒኤስ ቴክኖሎጂው ሥራን ከማቀላጠፍ በተጨማሪ ከዚህ በፊት ከነዳጅ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የነበሩ ችግሮችን በማቃለል ተቋሙን ከተጨማሪ ወጭ እየታደገው ይገኛል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ዋለ ገለፃ ማሻሻያው በአሃዝ የተደገፈ ግልጽ መረጃ ለማግኘት ከማስቻሉም ባለፈ ተሸከርካሪዎች ከተመደቡበት መስመር ሲወጡና ከፍጥነት ወሰን በላይ ሲጓዙ መልዕክት ወደ ማዕከል ያደርሳል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 7 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

#vacancy የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀማሪ ኤሌክትሪካል መሐንዲስ እና በጀማሪ መካኒካል መሐንዲስ የስራ መደብ ለመቅጠር ነሐሴ 07 እና ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም
+2
#vacancy የፈተና ውጤት ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጀማሪ ኤሌክትሪካል መሐንዲስ እና በጀማሪ መካኒካል መሐንዲስ የስራ መደብ ለመቅጠር ነሐሴ 07 እና ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና መስጠቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም በጀማሪ ኤሌክትሪካል መሐንዲስ የስራ መደብ የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 15 እንዲሁም በጀማሪ መካኒካል መሐንዲስ የስራ መደብ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 4 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በተሰጠው የፅሁፍ ፈተና አብላጫ ውጤት ያመጣችሁ በመሆኑ ከመስከረም 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 (አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ኮተቤ በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ በመገኘት የትምህርት ማስረጃ ዋናውን እና ኮፒ በመያዝ ቀርባችሁ የቅጥር ሂደት እንድትፈጽሙ እያሳወቅን፤ ስማችሁ ያልተገለጸው አመልካቾች የማለፊያ ውጤት ያላመጣችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication to 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et መስከረም 5 ቀን 2017 ዓ.ም

እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ በኩር ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ወደፊት እንድናስብ የሚያደርግ ከመሆኑ
እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሠላም አደረሳችሁ! አዲስ ዓመት ሁሌም ተስፋ ይዞ የሚመጣ የበዓላት ሁሉ በኩር ነው፡፡ የዘመን መቀየር ተስፋችንን የሚያለመልም እና ወደፊት እንድናስብ የሚያደርግ ከመሆኑም ባሻገር በአዲስ ዓመት ዋዜማ ለምርቃት የበቃው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ደግሞ ተስፋችንን ምሉዕ ያደርገዋል፡፡ እንደ ተቋም ብቻ ሳይሆን እንደሀገር ለምናቅዳቸው ሥራዎች መሳካት ትልቅ አቅም እንደሚሆን እምነቴ የፀና ነው፡፡ ስለሆነም በአዲሱ ዓመት "የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል" የመሆን ራዕያችንን እውን ለማድረግ የምንሠራበት፣ ሁለንተናዊ ተቋማዊ ስኬት የምናስመዘግብበት እንዲሁም በግል ያቀድናቸውን ውጥኖች ከግብ የምናደርስበት የሠላም፣ የደስታና የስኬት ዘመን እንዲሆን እመኛለሁ!! መልካም አዲስ ዓመት! አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) ዋና ሥራ አስፈፃሚ

በቅርቡ የኃይል ትስስር ሊፈረም ይችላል ........///....... ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመውሰድ የሚያስችላትን ስምምነት በቅርቡ እንደምትፈጽም ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት አስታወቁ ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደተናገሩት ግድቡ ከኢትዮጵያ አልፎ የቀጣናውን ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘት የሚያስችላትን ስምምነት በቅርቡ እንደምትፈፅም ገልፀዋል፡፡ ሁለቱ ሀገራት የኃይል ሽያጭ ለማከናወን የመግባቢያ ስምምነት መፈራረማቸውና ባለሙያዎቻቸው አስፈላጊውን ጥናት እያካሄዱ መቆየታቸው ይታወሳል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ግድቡ አፍሪካዊ አጀንዳዎችን ለማሳካትና ቀጣናዊ ትስስርን ለማሳደግ የሚያስችል ነው …....///…...... ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካዊ አጀንዳዎችን ለማሳካት እና ቀጣናዊ ትስስርን ለማሳደግ እንደሚያስችል የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ገለፁ፡፡ ሊቀመንበሩ ሙሐሙድ አሊ ዩሱፍ በግድቡ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ግድቡ በትውልድ ቅብብሎሽ ተገንብቶ ለምረቃ በመብቃቱ ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። ግድቡ የሀገር ውስጥን ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር ቀጣናውን በኃይል ልማት ዘርፍ ለማስተሳሰር የጎላ ሚና እንዳለው ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ለአየር ንብረት የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ በመገንባት ኢትዮጵያንና ቀጣናውን ተጠቃሚ የሚያደርግና ከአህጉራዊ አጀንዳዎች ጋር የሚጣጣም መሆኑንም ጠቅሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ ግድቡን በራስ አቅም ገንብታ ማጠናቀቋ ለአህጉሩ መነሳሳትን የሚፈጥርና የሕብረቱን 2063 አጀንዳን ለማሳካት የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ከሴኔጋል ወንዝ ጋር በተያያዘ በሴኔጋል፣ ማሊ እና ሞሪታኒያ መካከል የተደረገውን የሦስትዮሽ ትብብር የጠቀሱት ሊቀመንበሩ ድንበር ተሸጋሪ ወንዞችን በጋራ ተጠቃሚነት ላይ በተመሰረተ መርህ በሰላማዊ መንገድ የመጠቀም ልምምድ መጎልበት እንደሚገባው ገልፀዋል፡፡ የጅቡቲ ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የኢትጵያውያን ብቻ ሳይሆን የዓለምን ሕዝብ ያስደነቀ የመላ አፍሪካውያን የጋራ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡፡ የግድቡ መሳካት ለኢትዮጵያ ወዳጆች ሁሉ ድል በመሆኑ የከበረ አድናቆት አለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ የግድቡ ግንባታ በኢትዮጵያውያን ሙያተኞች ለፍጻሜ በመብቃቱ እጅግ የተለየ አድናቆት የሚቸረው መሆኑንም ተናግረዋል፡፡ የግድብ ግንባታውን በራስ አቅም በማጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን እንደገና አፍሪካን የሚያኮራ ሥራ መስራታቸውን የተናገሩት ደግሞ የኢስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ሚሶ ድላሚኒ ናቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ሀገራቸው ኢስዋቲኒን ጨምሮ በርካታ የምዕራብ አፍሪካና በጥቅሉ አፍሪካውያን መሪዎች ህዳሴን መሰል ትውልድ ተሸጋሪ ሥራዎችን እንዴት መስራት እንደሚቻል የሚያስተምር ነው ብለዋል፡፡ የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ በበኩላቸው የግድቡ መመረቅ ለቀጣናው ኩራት እንዲሁም ለጋራ ዕድገትና ቀጣናዊ ትብብር ወሳኝ ስለመሆኑም ገልፀዋል፡፡ የግድቡ መጠናቀቅ ኢትዮጵያ በራሷ አቅም ያከናወነችው ትልቅ ታሪክ እና የብልጽግናዋ ጉዞ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑንም አንስተዋል። ፕሮጀክቱ ከአንድ ግድብነት ያለፈ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ በትብብር ለመልማትና ለማደግ የሶማሊያ ሕዝብና መንግስት ዝግጁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

የግድቡ ግንባታ ጠንካራ የሥራ ባህል እና ጽናት የታየበት ነው- ፔትሮ ሳሊኒ …....///….. የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ጠንካራ የሥራ ባህል እና ጽናት የታየበት እንደሆነ የፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ የጣሊያኑ ዊ ቢውልድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፔትሮ ሳሊኒ ተናገሩ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው በግድቡ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ የግድብ ግንባታው ተጠናቆ ሲታይ ቀላል ቢመስልም በርካታ ፈተናዎችን እና ውጣ ውረዶችን በጽናት ማለፉን ተናግረዋል፡፡ ግድቡ አሁን ላይ የሚያስፈልገውን ውሃ መያዙን እና የሀገሪቱን የማመንጨት አቅም በከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ በርካታ ኢትዮጵያውያን የኃይል ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለጎረቤቶቿ በመሸጥ ትብብሯን ለማጠናከር ጉልህ ሚና እንደሚጫወት አስገንዝበዋል:: የህዳሴ ግድብ በዓለማችን ደህንነታቸው ከተጠበቁ ፕሮጀክቶች አንዱ ነው ያሉት ሥራ አስፈጻሚው በግንባታው ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በጽናትና በቁርጠኝነት የተሳተፉበት እንዲሁም የእውቀት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ያገኙበት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ የግድብ ግንባታው መጠናቀቅ የኔ እና የኢትዮጵያ ህልም እውን የሆነበት ነውም ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያውያን በፈተናዎችና በችግሮች ሳይበገሩ ግድቡ እንዲጠናቀቅ ትልቅ ሚና መጫወታቸውን የጠቆሙት ፔትሮ ሳሊኒ ለግድብ ግንባታው እውን መሆን አሻራቸውን ላሳረፉ ሠራተኞችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በግድቡ ግንባታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ በነበረበት ወቅት በተለያዩ አደጋዎች ሕይወታቸውን ላጡ ሠራተኞች ክብር እንደሚሰጡ እና በኅሊና እንደሚያስቧቸው ተናግረዋል። የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ጆርጂያ ሜሎኒ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ለመንግሥታቸው የላኩትን የደስታ መግለጫ መልዕክትም አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content