en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 559 subscribers, ranking 8 384 in the Technologies & Applications category and 2 165 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 559 subscribers.

According to the latest data from 23 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 0 over the last 30 days and by -2 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 25.89%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.48% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 026 views. Within the first day, a publication typically gains 2 408 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 24 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 559
Subscribers
-224 hours
-37 days
No data30 days
Posts Archive
አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ ለዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ተችሏል ……..///……. በአዳማና በሞጆ ከተሞች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን በከተሞቹ በሚገኙ ፋብሪካዎች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሆኑ ሠራተኞች ገለፁ፡፡ በአዳማ ከተማ በሚገኘው አብርሃም አበበ ፒፒ ከረጢት እና ፒፒሲ ኤች ዲፒ ፋብሪካ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሆኑት ወ/ሮ መሰለች ዓሊ ረመዳን እና ወ/ሮ አማከለች መኮንን እንደገለፁት በድርጅቱ በመቀጠር በሚያገኙት ገቢ ራሳቸውና ቤተሰቦቻቸውን እያስተዳደሩ ነው፡፡ ድርጅቱ ካሉት ከ110 በላይ ሠራተኞች አብዛኞቹ ሴቶች መሆናቸውን እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በአካባቢው በመኖሩ በርካታ ሴቶች በተከፈቱ ፋብሪካዎች ከቤተሰብ ሳይርቁ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የኤሌክትሪክ ኃይል ባይኖር ድርጅቱ ስለማይኖር የሥራ እድል ተጠቃሚ አንሆንም ነበር ያሉት ሠራተኞቹ ማህበረሰቡ የኃይል መሰረተ ልማቶችን በእኔነት ስሜት መጠበቅ እንዳለበትም ተናግረዋል፡፡ የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ አለማየሁ አበበ ድርጅቱ ምርቶቹን ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ የሚያቀርብ በመሆኑ የኃይል አቅርቦት ለፋብሪካው የህልውና መሰረት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በሞጆ ከተማ በሚገኘው የሲ ኤንድ ኢ ወንድማማቾች ብረታ ብረት ፋብሪካ ሠራተኛ የሆኑት አቶ ሽመልስ ፍቃዱ እና አቶ ሻረው አለማየሁ በበኩላቸው በድርጅቱ ከአስር ዓመት በላይ መስራታቸውን ይናገራሉ፡፡   በፋብሪካው ከመቀጠራቸው በፊት ትምህርት ጨርሰው ያለሥራ ተቀምጠው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ሽመልስ በድርጅቱ ሥራ ከጀመሩ በኋላ የትምህርት ደረጃቸውን ከዲፒሎማ ወደ ዲግሪ አሻሽለውና ዕድገት አግኝተው ትዳር በመመስረት ቤተሰባቸውን እያስተዳደሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ከ680 በላይ ሠራተኛ በፋብሪካው በቀጥታ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት ባለሙያው በተዘዋዋሪ ግብዓት ለሚያቀርቡና የፋብሪካውን ምርት ለሚወስዱ በርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩን አብራርተዋል፡፡ በአካባቢው ያለው የኃይል አቅርቦት የተሻለ በመሆኑ ብዛት ያላቸው ፋብሪካዎች እንደሚገኙ የጠቆሙት አቶ ሻረው ከሥራ ዕድል ፈጠራው በተጨማሪ የቴክኖሎጂ እና የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ማድረጉንም ገልፀዋል፡፡ የሞጆ ከተማ የሎጅስቲክስና የኢንዱስትሪ ማዕከል በመሆኗ እና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ ፋብሪካው የማስፋፊያ ሥራ እያከናወነ እንደሆነና ማስፋፊያው ሲጠናቀቅ ለበርካታ ዜጎች ተጨማሪ የሥራ ዕድል እንደሚፈጥር ጠቁመዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+8

በአረርቲ የነበረውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽ መቀነስ ተችሏል ........///...... የሞጆ ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በአረርቲ  አካባቢ የነበረውን የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽ በመቀነስ አስተማማኝ ኃይል እያቀረበ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ሥራ አስኪያጁ አቶ ሚናስ ወንድምሞላ እንደገለጹት ጣቢያው በ2013 ዓ.ም 80 ሜጋ ዋት ኃይል የመጫን አቅም ባላቸው ሁለት  ትራንስፎርመሮች ነው ሥራ የጀመረው። ጣቢያው በ15 ኪሎ ቮልት ስድስት ወጭ መስመሮች ሲኖሩት ለሞጆ ከተማ፣ ለኢፌዲሪ አየር ኃይል፣ ለሞጆ ቆዳ ፋብሪካ፣ ለአዳማ ውሃ እና ለደረቅ ወደብ ኃይል እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡ ይሁንና ለአረርቲ ከተማ ኃይል ከጣቢያው ለማቅረብ በተቋሙ የራስ ኃይል አማካኝነት የማስፋፊያ ሥራ በማከናወን 25 ሜጋ ቮልት አምፔር የመጫን አቅም ያለው ባለ 33 ሺ ኪሎ ቮልት ትራንስፎርመር መጨመሩን ተናግረዋል፡፡ ትራንስፎርመሩ ከአረርቲ በተጨማሪ ለኤጀሬ ከተማ፣ ለአንበሳ ቢራ ፋብሪካ እና ለአረርቲ ሴራሚክ ኃይል የሚሰጡ አራት ወጪ መስመሮች እንደተዘጋጁ ገልጸዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ለረጅም ጊዜ የመቆራረጥ ችግር የነበረበት ወደ አረርቲ የሚሄደው መስመር ዋንኛ ችግር ለአረርቲ፣ ለኤጀሬና ለአረርቲ ሴራሚክስ በአንድ ሰርኪዩት ብሬከር ኃይል ይሰጥ ስለነበረ ነው። በዚህ ምክንያት በወር ውስጥ እስከ 234 ጊዜ የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሽ ይመዘገብ እንደነበረ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ይህም ለደንበኞች ቅሬታ እና ብሬከሩን ለብልሽት ዳርጎ ነበር ብለዋል፡፡ አሁን ላይ ሦስቱም መስመሮች በተናጠል በተዘጋጀው ብሬከር አገልግሎት በመስጠቱ የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሹ በከፍተኛ ደረጃ መቀነሱን ተናግረዋል፡፡ ይህም በተደጋጋሚ በሚከሰቱ የኃይል መቋረጦች ምክንያት ብሬከሩ ላይ ያጋጥም የነበረውም የመሳሪያ ብልሽት ከማስቀረቱም ባሻገር ያልተቆራረጠ ኃይል ማቅረብ ማስቻሉን ገልፀዋል፡፡ ለአረርቲና አካባቢው ተብሎ የተተከለው ትራንስፎርመር 20 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ቢሆንም እስከአሁን ጥቅም ላይ የዋለው ግን ከዘጠኝ ሜጋ ዋት ያልበለጠውን ነው ብለዋል። በአካባቢው ከዋናው መስመር ተለይተው ወደ ውስጥ የሚገቡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ንዑስ ጣቢያዎች በመኖራቸው ችግር በሚያጋጥምበት ወቅት ንዑስ ጣቢያዎችን ሄዶ ለመክፈት የሚወስደው ጊዜ ኃይል የመቋረጥ ስዓቱን ያረዝመዋል ነው ያሉት፡፡ ከአገልግሎት መስጫ ማዕከሉ ጋር በመነጋገር የተሻለ መስመር የማፅዳት ሥራ እንዲከናወን ለማድረግ እየተሰራ ነው ያሉት አቶ ሚናስ ከአካባቢው ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ቢመጣ ተቀብሎ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በአካባቢው የነበረው የኃይል መቆራረጥ ድግግሞሹ በከፍተኛ ደረጃ ቢቀንስም ሙሉ በሙሉ ችግሩን ለመቅረፍ ከሞጆ የኤሌክትሪክ አገልግሎት መስጫ ማዕከል ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ጣቢያው ካለው 100 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ውስጥ በአሁኑ ወቅት ጥቅም ላይ የዋለው 25 ሜጋ ዋት አካባቢ ነው ያሉት አቶ ሚናስ የዳታ ማይኒንግ ድርጅት ወደ ሥራ እየገባ በመሆኑ ተጨማሪ ኃይል ጥቅም ላይ ይውላል በሚል እምነት እየሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

ተቋሙ የጣና ነሽ 2 ጀልባ ጉዞ በስኬታማ እንዲጠናቀቅ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ ይገኛል ……///…… የጣና ነሽ 2 ጀልባ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን የበኩሉን አስተዋፅኦ እያበረከተ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ በተቋሙ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይ ዘወልዴ እንደገለፁት በተሸከርካሪ ተጭነው በከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ስር የሚያቋርጡ ከፍታ ያላቸው ብረት ነክ ዕቃዎች ዓለም አቀፍ አሰራሮችን በጠበቀ መልኩ እንዲያልፉ እየተደረገ ነው፡፡ በጣና ሀይቅ ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠትና የቱሪዝም ፍሰቱን ለማሳደግ ታስቦ ከጅቡቲ ዶራሌህ ወደብ ወደ ባህር ዳር እየተጓጓዘች የምትገኘው ጣና ነሽ 2 ጀልባ አዳማ ከተማ እስከምትደርስ ድረስ የኃይል መስመሮች ጉዳት እንዳያደርሱ የመጠበቅ ሥራ መሰራቱን ተናግረዋል፡፡ ጀልባዋ ጉዞ ማድረግ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ  አዳማ ከተማ እስከምትደርስ ድረስ ባለ 230 እና 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉባቸው 53 ቦታዎችን ችግር ሳያጋጥም በተሳካ ሁኔታ ማቋረጧን ገልፀዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮቹን ለአጭር ሰዓት ኤሌክትሪክ በማቋረጥ ለጀልባዋ ጉዞ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር ተችሏል፡፡ የማዕከላዊ 2 ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ባለሙያ አቶ ሙሉቀን ወልደማሪያም በበኩላቸው ከአዋሽ ሰባት ኪሎ እስከ ቆቃ በተዘረጋው መስመር ላይ የጀልባዋን ጉዞ ለማሳለጥ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ተቋሙ ጀልባዋ ጉዞ ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰው በቀጣይም በምታልፍባቸው ቦታዎችም ተመሳሳይ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል፡፡ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ከመሬት ያላቸውን ከፍታ በዘመናዊ መሳሪያ በመለካት መረጃዎችን ማደራጀት መቻሉም ተገልጿል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ተቋማቱ በመቀናጀት ጊዜን የቀደሙ ሥራዎች መስራት አለባቸው - የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ……..///….... አስተማማኝና ተደራሽ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ተናበው ጊዜን የቀደሙ ሥራዎችን ማከናወን እንዳለባቸው የሁለቱ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ገለጹ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ማናጅመንት ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ገበየሁ ሊካሳ እንደገለፁት ሁለቱ ተቋማት እስከ 2006 ዓ.ም ድረስ በአንድ ተቋም ሥር የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ሥራዎችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል፡፡ የኃይል ፍላጎት እያደገ በመምጣቱ እና ዘርፉ ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን በመረዳት ዓለምአቀፋዊ ተሞክሮዎችን በመገምገም አቅርቦቱንና ተደራሽነቱን ለማሳደግ ሲባል በጥናት ላይ በመመስረት ሁለቱ ተቋማት ራሳቸውን ችለው እንዲደራጁ መደረጋቸውን ተናግረዋል። የተቋማቱ ወደ ሁለት መከፈል ትኩረት እንዳይበታተን በማድረግ እንዲሁም የፋይናንስ ጫናዎችን በማቃለል አቅርቦቱን ከማዘመን እና ተደራሽነቱን ከማስፋት አንጻር አበረታች ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን ጠቁመዋል። ዶ/ር ገበየሁ አክለውም የውስጥ አሰራርን በማዘመን የነባር ኔትወርኮችን መልሶ ግንባታ እና የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በማከናወን የኃይል መቆራረጡን በመቀነስ ተደራሽነቱን ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። በዚህም ባለፉት 11 ዓመታት ተቋማቱ ባከናወኗቸው ሥራዎች የደንበኞችን ቁጥር ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ወደ 5 ነጥብ 2 ሚሊዮን እንዲሁም የተደራሽነት ሽፋኑን ከ30 በመቶ ወደ 54 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል፡፡ ተቋማቱ በአደረጃጀት ለሁለት ቢከፈሉም ሥራቸው ተመጋጋቢ እና ኔትወርኩም የተያያዘ በመሆኑ እያደገ የመጣውን የኃይል ፍላጎት ለመመለስና ተደራሽነቱን ለማሳደግ የጋራ የግንኙነት ጊዜ አስቀምጠው እየሰሩ መሆኑን ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን በበኩላቸው 78 ከመቶ ከግሪድ እንዲሁም 22 ከመቶ ከግሪድ ውጭ የኃይል አቅርቦቱን ተደራሽ ለማድረግ የተያዘውን ሀገራዊ ዕቅድ ለማሳካት ሁለቱ ተቋማት ተናበው መስራት እንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡ የኃይል ተደራሽነቱን ከማሳደግ በተጨማሪ ቀደም ሲል የኃይል ተጠቃሚ የነበሩ አካባቢዎች የኃይል ፍላጎት በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መሆኑንና ይሄን ጥያቄ ለመመለስ ሁለቱ ተቋማት ተናበው ጊዜን የቀደሙ ሥራዎች መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ መናበቡን መዋቅራዊ አድርጎ ለመቀጠል በሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የሚመራና ሥራዎችን የሚገመግም ቡድን ተዋቅሮ እየተሰራ ነው። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

ተቋሙ ከኦፕሬሽን ዘርፎች ለተውጣጡ ሠራተኞች የአሰልጣኞች ስልጠና እየሠጠ ነው ….....///…...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኃይል ማመንጫዎች፣ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ዘርፍ ለተውጣጡ ሠራተኞች የአሰልጣኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ። በኢትዮጵያ ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት በሦስት ዙር ተከፋፍሎ ለአስር ቀናት የሚሰጠውን ሥልጠና የመጀመሪያ ዙር ሠልጣኞች ትናንት ሥልጠናቸውን ጀምረዋል። በተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠና እና ልማት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደምስ ሰይፉ በስልጠናው ማስጀመሪያ መርሃግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ እንደገለጹት ሥልጠናው በዋናነት ሰልጣኞች ከሥልጠና በኋላ የስልጠና አሰጣጥ ጥበብ እና ስልቶችን ተከትለው እውቀታቸውን  በተገቢው መንገድ ለሌሎች ማስተላለፍ እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። በተቋሙ የብዙ ልምድ ባለቤት የሆኑ አንጋፋ ሠራተኞች የሚገኙ ቢሆንም ያላቸውን እውቀትና ልምድ ለሌሎች በማካፈል ረገድ ውስንነቶች እንደነበሩ ሥራ አስኪያጁ ገልጸዋል። ሥራ አስኪያጁ በነባር የተቋሙ የሰው ኃይል እና አዲስ በሚቀላቀሉ ሠራተኞች መካከል ከ15 እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የዕድሜ ክፍተት እንዳለ በጥናት መረጋገጡን ጠቅሰው ይህም ሰፊ የእውቀት ክፍተት እና  ልዩነት እንደሚፈጥር አስረድተዋል። ስለሆነም  በተቋሙ የውስጥ አቅም ስልጠናን በማሳደግ እና በሁሉም ዘርፎች ተደራሽ በማድረግ  የእውቀት ክፍተት እንዳይፈጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ነው የገለጹት። የተቋማዊ ትራንስፎርሜሽን ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም ኪዳኔ በበኩላቸው በአስተዳደራዊ እና በቴክኒክ ዘርፉ ላይ ያሉ እውቀቶችን በመጠቀም የተቋሙን ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ማሳካት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። ተቋሙ በስትራቴጂካዊ ዕቅዱ ካስቀመጣቸው ግቦች ለመድረስ የሰው ኃይል አቅም ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ ሁሉም የተቋሙ አመራርና ሠራተኛ የሚሰጡ ስልጠናዎችን በአግባቡ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል። ስልጠናን በተቋሙ የውስጥ አቅም በመስጠት ብቃት ያለው የሰው ሀብት ለመገንባት በኦፕሬሽን ዘርፉ ላይ የተጀመረው  የአሰልጣኞች ስልጠና በቀጣይ በተቋሙ ሁሉም ዘርፎች የሚሰጥ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በማከፋፈያ ጣቢያዎች የትራንስፎመሮችን ደኅንነት ለማስጠበቅ የሚስችል ስልጠና ለማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና ባለሙያዎች እየሰጠ ይገኛል፡፡ በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝንስ ዘርፍ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድርያስ እንደገለፁት ሥልጠናው በየማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚገኙ ትራንስፎርመሮች ከብልሽት የፀዱና ደኅንነታቸው የተጠበቁ እንዲሆኑ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ በመላው ሀገሪቱ ከሚገኙ 154 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውስጥ ከ45 በላይ የሚሆኑት ከአቅም በላይ የኃይል ጭነት የተሸከሙ በመሆናቸው ጥብቅ የደኅንነት ክትትልና የፍተሻ ሥራ ይፈልጋሉ ብለዋል፡፡ በተቋሙ የፓወር ግሪድ ትንተና ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑትና ሥልጠናውን እየሰጡ ያሉት አቶ አበባው ጋሻው በበኩላቸው ሥልጠናው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ትራንስፎርመሮችን የአገልግሎት ዘመናቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ስድስት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በመውደቃቸው ኃይል ተቋርጧል ……..///……. በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ልዩ ስሙ መቃ በተባለ አካባቢ በስርቆት እና ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ዝናብ ምክንያት በከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት በተፈፀመው ስርቆት እና ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ዝናብ ምክንያት ከአዘዞ-ሸኽዲ በተዘረጉ ስድስት ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ በዚህም ምክንያት ከሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በሙሉ የኃይል አቅርቦት በጊዜያዊነት እንደተቋረጠባቸው ተናግረዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የወደቁትን የብረት ምሰሶዎች ለመጠገን የጥገና ባለሙያዎች ወደ ስፍራው ማቅናታቸውንም ነው የጠቆሙት፡፡ የኃይል መቋረጡን በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶዎች ለመተካት  ጥረት መጀመሩን የጠቀሱት አቶ አባይነህ ከተዘጋጁት 84 የእንጨት ምሰሶዎች መካከል በአሁኑ ወቅት የስድስት የእንጨት ምሰሶዎች ተከላ መጠናቀቁን ተናግረዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የወደቁትን የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በአፋጣኝ በመጠገን በአጭር ጊዜ የኃይል አቅርቦቱን ለማስቀጠል ጥረት ተጀምሯል፡፡ በመሆኑም ችግሩ እስኪቀረፍ ድረስ የአካባቢው ነዋሪዎች በትዕግስት እንዲጠብቁ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሪጅኑ ከአንድ ዓመት በላይ የኃይል አቅርቦቱ ተቋርጦ የቆየውን የማርቆስ-ሞጣ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዳግም ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት እየሰራ መሆኑን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

ጉዳት ደርሶበት የነበረው የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ተጠግኗል .....///.....… በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቱሉቦሎ አካባቢ ጉዳት ደርሶበት የነበረው የማስተላለፊያ መስመር እና ለግንኙነት የሚያግዘው ኦፕቲካል ፋይበር (OPGW) ተጠግኖ ወደ ሥራ መግባቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፋይበር ኦፕቲክስ የኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ገለፀ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ኤርሚያስ ገብረ መድህን እንደገለፁት የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮቹ ለኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች መከላከያ ከመስጠት ባለፈ ለቴሌኮሙዩኒኬሽን ሥራዎች እንዲሁም ከኃይል ማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች መረጃዎችን ወደ ብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ለማድረስ ይረዳሉ። ከጊቤ ሁለት - ሰበታ ሁለት ባለው ባለ 400 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ላይ ተዘርግተው በሚገኙ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመሮች በጉዳት ምክንያት አገልግሎቱ ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ ጉዳት በደረሰበት መስመር ኢትዮ ቴሌኮም እና ሳፋሪ ኮም ኢትዮጵያ የፋይበር ኦፕቲክስ ተከራይተው ይጠቀሙ እንደነበር አቶ ኤርሚያስ አስታውሰዋል። በደረሰው ጉዳት የተነሳ አገልግሎቱ ተቋርጦ ጥገና ሳይደረግለት መቆየቱን እና የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከሉ ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች ያሉ መረጃዎችን መሰብሰብና መመልከት አለመቻሉን አብራርተዋል፡፡ የተቋሙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ መስመሩን ጠግኖ ወደ ሥራ ማስገባቱን ተናግረዋል፡፡ የጥገና ሥራው በጥቂት ቀናት እንዲጠናቀቅ እገዛ ያደረገውን ከደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አመስግነዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ሪጅኑ የእንጨት ምሰሶዎችን በብረት ምሰሶ እየቀየረ ነው ……....///…..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን በስርቆት ምክንያት ወድቀው በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በብረት ምሰሶዎች እየቀየረ መሆኑን ገለጸ። በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች እና ኦፕቲካል ፋይበር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሳዬ ደምሴ  እንደገለጹት በሪጅኑ በአዋሽ - አሰላ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ በተፈጸመ ስርቆት ምሰሶው ወድቆ ነበር። ሪጅኑ አገልግሎቱ እንዳይቋረጥ ለማድረግ የወደቁ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን በእንጨት በመተካት በጊዜያዊነት አገልግሎቱን ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል። አሁን ላይ የአዋሽ - አሰላን የእንጨት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎችን በብረት በመቀየር ወንጂ ስኳር ፋብሪካ፣ አሰላ እና አካባቢው የሚገኙ ዞንና ወረዳዎች ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ ያልተቆራረጠና አስተማማኝ ኃይል እንዲያገኙ መደረጉን አስረድተዋል። ሪጅኑ በመቶ ቀን ዕቅዱ የአዋሽ - አሰላ የማስተላለፊያ መስመርን ጨምሮ ሌሎች በጊዜያዊ የእንጨት ምሰሶዎች አገልግሎት እየሰጡ ያሉትን የቆቃ - ቢሾፍቱ- ገላን እና ቃሊቲ ባለ 132 ኪሎ ቮልት እንዲሁም አዳማ ሁለት - አዋሽ 7 ኪሎ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመሮች በብረት ምሰሶ ለመቀየር እየሰራ ነው ብለዋል። በሌላ በኩል ሪጅኑ  የተቋረጡትን የመተሀራ - መልካ ጅሎ የባቡር መስመር እና ቃሊቲ - ቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመሮች  ወደ ኦፕሬሽን እንዲገቡ ለማድረግ  እየሰራ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የይርጋለም ቁጥር ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የምሽት ገጽታ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራ
+6
የይርጋለም ቁጥር ሁለት ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የምሽት ገጽታ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 30 ቀን 2017 ዓ.ም

#EidAlAdha 🕋✨ ለተቋማችን የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የመረዳዳት እንዲሆንላችሁ እ
#EidAlAdha 🕋✨ ለተቋማችን የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የመረዳዳት እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ። አሸብር ባልቻ (ኢንጂነር) ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦቱ ለከተሞች የኢንዱስትሪ  ዕድገት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው ……….///……… የኃይል አቅርቦት አስተማማኝ መሆንና የተደራሽነቱ መስፋት የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት እያፋጠነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 2 ሪጅን መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡ ዳይሬክተሩ አቶ አለማየሁ ዘበርጋ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገነባቸውና የሚያስተዳድራቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች  ለኢንዱስትሪዎች መስፋፋት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙት በአዳማ ፣ በቢሾፍቱ፣ በሞጆና በዱከም ከተሞች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ለሀገር ኢኮኖሚዊ ዕድገት ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ ኢንዱስትሪዎች ቁጥር እንዲጨምር ምክንያት የሆነው የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝነት ማደግ እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡ እንደ አቶ አለማየሁ ገለፃ በሪጅኑ ውስጥ በሚገኙ ከተሞች  አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖር ለበርካታ ዜጎች የሥራ ዕድል እንዲፈጠር እና  የኑሮ ዘይቤ እንዲስተካከል  መነቃቃትን ፈጥሯል፡፡ ለህብረተሰቡና ለኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ ከፍተኛ አቅም ያላቸው ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ከአዲስ አበባ እስከ መተሃራ ድረስ ተገንብተው አስተማማኝ አገልግሎት እየሰጡ ነው ብለዋል፡፡ ዱከም ኢስት ኢንዱስትሪ፣ የሱ ብረታብረት፣ ሲ እና ኢ ብራዘርስ ፣ካኖሪያ ጨርቃ ጨርቅ ፣ ጆርጅ ሹዝ እና ወንጂ ስኳር ፋብሪካ በማዕከላዊ 2 ሪጅን ወስጥ ከሚገኙ ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንደስትሪዎች መካከል እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ የደንበኞችን እርካታ ከማሳደግ ባለፈ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት  የሪጅኑ የአሰራር ጥንካሬዎች መሆናቸውንም ገልፀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ግንቦት 28 ቀን 2017 ዓ.ም