uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 697 підписників, посідаючи 8 062 місце в категорії Технології та додатки та 2 174 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 697 підписників.

За останніми даними від 01 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 139, а за останні 24 години на 1, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 28.75%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 16.42% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 513 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 578 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 10.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 02 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 697
Підписники
+124 години
+277 днів
+13930 днів
Архів дописів
#Vacancy የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ሠራተኞችን በኮንትራት አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ተፈላጊ የሥራ መደቦች፡- • ሶሺዮሎጂስት • ኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ
#Vacancy የስራ ቅጥር ማስታወቂያ የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ ኃይል የውጭ ሠራተኞችን በኮንትራት አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ተፈላጊ የሥራ መደቦች፡- • ሶሺዮሎጂስት • ኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር • ኦኮፔሽናል ኸልዝ እና ሴፍቲ ኦፊሰር (ዲ1) በመሆኑም ከላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች የሚከተሉትን ሊንኮች መጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። Link 1 👉 https://forms.gle/dHiiFD2w3ubSs3ZK9 18 Link 2፡ 👇 https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSfA1P8Oc9OymnrSYLNUUq2v0ulr_ZgFUth2qBP1WC7DmHo6aQ/viewform?usp=dialog 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም

#Vacancy የቃለ-መጠይቅ ፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በChange Management Officer III (D4) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 06 ቀን 2017 ዓ
#Vacancy የቃለ-መጠይቅ ፈተና ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በChange Management Officer III (D4) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 06 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና መፈተኑ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ 50 እና ከዚያ በላይ ያገኛችሁ ከተ.ቁ 1 እስከ 6 ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች ነሐሴ 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ የቃለ መጠይቅ (Interview) ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም

የኃይል ልማት ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚፈልግ ነው …..///…... የኃይል ልማት ዘርፉ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የሚፈልግ በመሆኑ በተቋሙ አቅም ብቻ ሊሸፈን እንደማይችል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ፡፡ ተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም እና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን አስመልክቶ ዓመታዊ ጋዜጣዊ መግለጫ በስካይ ላይት ሆቴል በሰጠበት ወቅት ከታሪፍ ማሻሽያ እና ከኃይል አቅርቦት ተደራሽነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች ከመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ተነስተዋል፡፡ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተቋሙ ከአስር ዓመታት በላይ የታሪፍ ማሻሽያ ሳያደርግ በከፍተኛ ብድር የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድጉ የኃይል መሰረተ ልማት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡ በዚህም ተቋሙ የህልውና አደጋ ውስጥ በመግባቱ በመንግሥት በኩል የሀገር ውስጥ ዕዳ ጫና ስረዛ እንደተደረገለት አስታውሰዋል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ የፋይናንስ ቁመናውን ለማሻሻል፣ የኃይል ሽፋንን ለማሳደግ እና  የአገልግሎት ጥራትን ለማዘመን እንዲሁም የኦፕሬሽንና የፕሮጀክት ወጪዎችን ለመሸፈን በጥናት ላይ ተመስርቶ የታሪፍ ማሻሻያ መተግበሩን ተናግረዋል፡፡ የታሪፍ ማሻሽያው በየሩብ ዓመቱ ተከፋፍሎ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን ያስታወሱት ኢንጂነር አሸብር የታሪፍ ማሻሻያው ከጎረቤት ሀገራት አንፃር ሲታይ አሁንም እጅግ ዝቅተኛና የተቋሙን ወጪ መሸፈን የማይችል መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በየዓመቱ የሀገሪቱ የኃይል ፍላጎት በአስር በመቶ እያደገ በመሆኑ ከታሪፍ ማሻሽያው ጎን ለጎን በዘርፉ ያለውን የኃይል ስብጥር ለማሳደግና የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋት የግል አልሚዎች እንዲሳተፉ የሚያስችል የሕግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ መገባቱንም ጠቁመዋል፡፡ ይሁን እንጂ በሀገሪቱ ያለው ዝቅተኛ የኤሌክትሪክ የታሪፍ ምጣኔ የግል አልሚዎችን የሚያበረታታ ባለመሆኑ እስከ አሁን የሚፈለገው ውጤት አለመገኘቱን ገልፀዋል፡፡ የተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓ በበኩላቸው በሀገሪቱ አሁን ላይ ከ40 በመቶ በላይ ለሚሆነው የህብረተሰብ ክፍል ኤሌክትሪክ ተደራሽ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡ ያልተቆራረጠ ኃይል ለማህበረሰቡ ለማዳረስ እና የኃይል ሽፋኑን ለማሳደግ ከፍተኛ የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎች የሚጠይቁ በመሆናቸው የታሪፍ ማሻሻያው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ተግባራዊ መደረጉን አንስተዋል፡፡ የታሪፍ ማሻሽያው ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የህብረተሰብ ክፍል ታሳቢ ያደረገ ነው ያሉት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጭማሪው በቀን ሲሰላ ከ55 ሳንቲም ያልበለጠ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ የታሪፍ ማሻሽያውን አስመልክቶ የሚነሱ የተሳሳቱ አመለካከቶችን በማረም በኩል መገናኛ ብዙኃን የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባም ነው ያስረዱት፡፡ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት ተቋሙ ከዓመታዊ በጀቱ አብዛኛውን ለካፒታል ፕሮጀክቶች በመመደብ እየሰራ ይገኛል፡፡ ከአሁን ቀደም ተቋሙ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወስዶት የነበረውና በተቋሙ የፋይናንስ ቁመና ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሮ የቆየውን ብድር መንግሥት ወደ ራሱ መውሰዱን የጠቆሙት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ተቋሙ የመክፈል አቅሙንና ገቢውን ያገናዘበ ብድር ከባንኩ በመውሰድ ፕሮጀክቶችን በራሱ አቅም ለማስፈፀም እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በዚህም በ2017 በጀት ዓመት ብቻ በግንባታ ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች ማስኬጃ ከ261 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከራስ ፋይናንስ መሸፈኑንም ተናግረዋል፡፡ በ2018 በጀት ዓመት ከያዘው 251 ቢሊየን ብር በጀት ውስጥ 71 በመቶ ለፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ እንደሚውል የጠቆሙት አቶ ደመረ በጀቱ ከኃይል ሽያጭ፣ ከመንግሥት ከሚገኝ ድጋፍ፣ ከአገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ከሚገኝ ብድርና ድጋፍ የሚሸፈን መሆኑን አንስተዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 02 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክቶች ላይ የተሻለ አፈጻፀም ተመዝግቧል ........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2017 በጀት ዓመት የፕሮጀክቶች አፈፃፀም የተሻለ እንደነበር የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ። ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀምና የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት እንደገለፁቱ እያደገ ለመጣው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠትና በመላ ሀገሪቱ የኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ የኃይል ማመንጫ፣ ከፍተኛ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እና የማስተላለፊያ መስመሮችን በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ በበጀት ዓመቱ አራት የኃይል ማመንጫ እና 20 የማከፋፈያ ጣቢያ፣ ማስተላለፊያ መስመርና ተያያዥ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ እንደነበሩ ገልፀዋል። የበጀት ዓመቱ አፈጻፀማቸውም የተሻለ እንደነበር ኢንጂነር አሸብር ጠቁመዋል፡፡ በዚህም በበጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ፕሮጀክት ለማጠናቀቅ በተደረገው ርብርብ ለምረቃ ዝግጁ መሆኑን  በመጥቀስ አሁን ላይም በዘጠኝ ተርባይኖች 3 ሺህ 400 ሜጋ ዋት ኃይል እያመነጨ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ በተመሳሳይ በአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የጀት ዓመቱን ዕቅድ በማሳካት በ12 የንፋስ ተርባይኖች 41 ሜጋ ዋት እያመነጨ በመሆኑ በተያዘው በጀት ዓመት ለምረቃ እንደሚበቃም ገልፀዋል፡፡ የአይሻ የንፋስና የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ ተግዳሮት ገጥሟቸው እንደነበር ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው ችግሩን በመንግስት እገዛና በተቋሙ ጥረት በማቃለል የግንባታ ሥራቸው በተሻለ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል፡፡ የፕሮጀክቶቹን የግንባታ አፈጻፀም ለማሻሻል ተቋሙ ለአይሻና ለኮይሻ ጨምሮ ለማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች ከራሱ ፋይናንስ 261 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ መፈፀሙን በመግለጫቸው አመልክተዋል፡፡ በዚህም የኮይሻ ፕሮጀክት 71 ነጥብ 4 በመቶ እንዲሁም የአይሻ ከ85 በመቶ በላይ እንዲደርስ ማስቻሉን በመግለፅ ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ  ከፋይናንስ ጋር በተያያዘ የተስተዋለውን ችግር በዘላቂነት  ለመፍታት እየተሰራ ስለመሆኑም አስታውቀዋል። በበጀት ዓመቱ ከኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ባለፈ የኃይል ተደራሽነትን የሚያሳድጉ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቶች የግንባታ ሥራ ትኩረት ተሰጥቷቸው ሲከናወኑ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ በበጀት ዓመቱ በግንባታ ላይ ከነበሩ የማከፋፈያ ጣቢያ፣ ማስተላለፊያ መስመርና መሰል ፕሮጀክቶች መካከል የአምስት ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ማብቃት ተችሏል፡፡ ከተጠናቀቁት መካከልም የደብረ ታቦርና በቆጂ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ የለገጣፎ-አላማጣ-ኮምቦልቻ ማስተላለፊያ መስመር እና የጫካ ፕሮጀክት የኃይል አቅርቦት ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን እና የደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም በበጀት ዓመቱ  ከ75 በመቶ በላይ ለማድረስ ታቅዶ በቅደም ተከተል 79 እና ከ80 በመቶ በላይ ማድረስ መቻሉንም አመልክተዋል፡፡ በኃይል ልማት ዘርፉ የሚከናወኑ ሥራዎች ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚኖራቸውን ሚና በመገንዘብ ተቋሙ በፕሮጀክት አስተዳደር ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነና በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ ከኃይል ሽያጭና ገቢ ጋር በተያያዘ ያነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች 📌 በ2017 በጀት ዓመት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እንዲሁም ከተለያዩ የገቢ ምንጮች 75 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ገቢ ተገኝቷል። 📌 ከዚህ ውስጥ 74 ነጥብ 05 ቢሊየን ብሩ  ከኃይል ሽያጭ 1 ነጥብ 41 ቢሊየን ብሩ ደግሞ ከተጓዳኝ አገልግሎቶች የተገኘ ነው። 📌 ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ ከተገኘው ገቢ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 35 በመቶ፣ የዳታ ማይኒንግ 39 በመቶ እንዲሁም የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች የ4 በመቶ ድርሻ አላቸው። 📌ለውጭ ሀገራት ከቀረበው የኃይል ሽያጭ የተገኘው ገቢ የኬኒያ የ15 በመቶ እንዲሁም የጅቡቲ  5 በመቶ ድርሻ ያለው ነው ። 📌በበጀት ዓመቱ ለደንበኞች በአጠቃላይ 25 ሺህ 180 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ተሽጧል። 📌ከዚህ ውስጥ 93 በመቶ ለሀገር ውስጥ እንዲሁም 7 በመቶ ለውጭ ሀገራት የቀረበ ነው። ይህም ተቋሙ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ ቅድሚያ እየተሰጠ ለመሆኑ ማሳያ ነው። 📌ከሽያጭ ከቀረበው ኃይል ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 60 በመቶ፣ የዳታ ማይኒንግ 27 በመቶ፣  ከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች 6 በመቶ ፣ ለኬኒያ የ5 በመቶ እንዲሁም ለጅቡቲ  2 በመቶ የቀረበ ነው። 📌የተቋሙ ገቢ ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት እያሳየ ነው።  ለአብነትም በ2015 በጀት ዓመት ከነበረበት 22 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በ2017 በጀት ዓመት 75 ነጥብ 4 ቢሊዮን ደርሷል። 📌የተቋሙ ገቢ እያደገ በመሄዱ ለፕሮጀክቶች የሚያስፈልጉ ወጭወችን በራስ አቅም መሸፈን ተጀምሯል። በዚህም በበጀት ዓመቱ 261 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር በራስ አቅም ለፕሮጀክቶች ውሏል። 📌 በበጀት ዓመቱ ከኤሌክትሪክ የኃይል ሽያጭ 338 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ተገኝቷል። ይህም በ2016 በጀት ዓመት ከተገኘው የ140 ሚሊዮን ዶላር ጋር ሲነፃፀር 135 በመቶ ብልጫ ያለው ነው። 📌በበጀት ዓመቱ ለተገኘው ገቢ እና የውጭ ምንዛራ አፈፃፀም ዕድገት ምክንያቶች:- 📌 የታሪፍ ማሻሻያ መደረጉ፣ 📌የዳታ ማይኒንግና የውጭ የኃይል ሽያጭ ገቢ ማደጉ 📌 በሀገር ውስጥ ለዳታ ማይኒንግ ኃይል በዶላር መሸጡ የ2018 በጀት ዓመት ገቢ ዕቅድ በተመለከተ 📌ተቋሙ በ2018 በጀት ዓመት  ከ109 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማግኘት አቅዷል 📌በተያዘው የበጀት ዓመት ከውጭ ምንዛሪ 420 ሚሊዮን ዶላር  ለማግኘት ዕቅድ ይዟል ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

‎ተቋሙ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት  ከ29 ሺ ጊጋ ዋት ስዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል ‎......///..... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት 29 ሺ 480 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረቱን አስታወቀ። ‎ ‎ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም እና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው። ‎ ‎የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ መግለጫውን በሰጡበት ወቅት እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ 25 ሺ 423 ጊጋ ዋት ሰዓት ለማምረት ታቅዶ 29 ሺ 480 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማምረት ተችሏል። ‎ ‎ይህም ከዓመታዊ ዕቅዱ የ16 በመቶ ወይም 4 ሺ 56 ጊጋ ዋት ሰዓት እንዲሁም በ2016 በጀት ዓመት ከተመረተው 20 ሺ 596 ጊጋ ዋት ሰዓት የ43 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገለጻ በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ውስጥ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት 9 ሺ 798 ጊጋ ዋት ስዓት ወይም የ33 ነጥብ 2 በመቶ እንዲሁም የጊቤ ሦስት የኃይል ማመንጫ ጣቢያ 7 ሺ 148 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ24 ነጥብ 2 በመቶ በማመንጨት ከፍተኛ ድርሻ ነበራቸው። ‎ ‎በበጀት ዓመቱ ከመነጨው ኃይል 28 ሺ 682 ጊጋ ዋት ሰዓቱ ወይም 97 ነጥብ 3 በመቶ ከውኃ እንዲሁም 789 ጊጋ ዋት ሰዓቱ  ወይም 2 ነጥብ 7 በመቶ ከንፋስ የተገኘ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡  ‎ ‎የህዳሴ ግድብ እና የአሰላ ንፋስ የተወሰኑ ተርባይኖች ወደ ኦፕሬሽን መግባት፣ የባለሙያዎችን አቅም በማሳደግ ጠንካራና ቀጣይነት ያላቸው የጥገና ሥራዎች መከናወን፣ የመለዋወጫ ዕቃ አቅርቦቱ መሻሻል ለዕቅድ አፈጻጸሙ ከፍ ማለት በምክንያትነት አንስተዋል። ‎ ‎ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበውን ስኬት እንደመነሻ በመጠቀም በቀጣይ የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ዓለም አቀፍ እውቅና ካላቸው የሲስተም ኦፕሬተሮች ጋር በጥገናና ኦፕሬሽን ሥራዎች ላይ አብሮ በመስራት፣ የማመንጫ ጣቢያዎችን አቅም በማሻሻልና በማዘመን እንዲሁም የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከር እንደሚሰራም ገልጸዋል። ‎ ‎ህዳሴን እና አሰላ ኃይል ማመንጫዎችን ሙሉ በሙሉ ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት በ2018 በጀት ዓመት 38 ሺ 124 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማምረት መታቀዱን ተናግረዋል፡፡  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የተቋሙ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃ
የተቋሙ ለመገናኛ ብዙኃን ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ነው ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ዙሪያ ለመገናኛ ብዙኃን በስካይ ላይት ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። መግለጫውን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እየሰጡ ነው። ጋዜጣዊ መግለጫው በ2017 በጀት ዓመት የኃይል ሽያጭና የገቢ አሰባሰብ፣ በኃይል ማመንጨት የኦፕሬሽን ሥራ አፈፃፀም፣ በማመንጫ፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እንዲሁም በ2018 ዋና ዋና ዕቅዶች ላይ ትኩረት ያደርጋል። እኛም በጋዜጣዊ መግለጫው የሚነሱ ሀሳቦችን እየተከታተልን በሁሉም የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ነሐሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

የችግኝ ተከላ መርሀ ግብሩ ለኃይል ማመንጫ ግድቦች ደህንነት መጠበቅ ሚናው የጎላ ነው .....///..... የኢትዮጵያ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የተቋሙን የኃይል ማመንጫ ግድቦችን ደህንነት ለማስጠበቅ የጎላ ሚና እንዳለው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፓወር ግሪድ ኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ዛሬ የችግኝ ተከላ ሲያከናውኑ የመምሪያው ዳይሬክተር ኢንጂነር ሚኪያስ ወንድሙ እንደገለጹት በየዓመቱ እየተከናወነ ያለው የችግኝ ተከላ መርሀ ግብር ግድቦችን ከደለል በመከላከል ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ የሚያስችል ነው። መርሀ ግብሩ ወቅቱን የጠበቀ ዝናብ እንዲኖር በማድረግ ተቋሙ የታዳሽ ኃይል አማራጮችን በመጠቀም አስተማማኝና ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይልን ለማቅረብ የያዘውን ተልዕኮ ለማሳካት ጉልህ አበርክቶ እንዳለው ገልጸዋል፡፡ የመምሪያው ሠራተኞች የተከሏቸውን ችግኞች በእኔነት ስሜት በመንከባከብ የመጽደቅ ምጣኔያቸውን ለማሳደግ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል። በችግኝ ተከላው ላይ የተገኙት የቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሱራፌል ቢያብል በበኩላቸው በወረዳው በሚገኘው የተቋሙ ግቢ ውስጥ ችግኞች በመተከላቸውና ወረዳውም ተሳታፊ በመሆኑ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ‎መርሀ ግብሩ አካባቢውን ፅዱና አረንጓዴ ከማድረጉ በተጨማሪ እየተተከሉ የሚገኙ ችግኞች ለምግብነት የሚውሉ በመሆኑ የምግብ ዋስትናዋን ያረጋገጠች ሀገር ለትውልድ ለማስተላለፍ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ብለዋል። ‎በቀጣይም በአረንጓዴ ልማት አሻራ መርሀ ግብሩና በሌሎች ጉዳዮች አስተዳደሩ ከተቋሙ ጋር በትብብር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

በበጀት ዓመቱ የሴቶችን የአመራር ሰጪነት ሚና ለማሳደግ እንደሚሰራ ተገለፀ .......///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በበጀት ዓመቱ የሴቶችን የአመራር ሰጪነት ሚና ለማሳደግ እንደሚሰራ አስታወቀ፡፡ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ከፓዎር አካዳሚ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውን የምክክር መድረክ ሲከፍቱ እንደተናገሩት የሴቶችን የአመራር ሰጪነት ሚና የማሳደግ ሥራ በአመራሩ ትኩረት ተሰጥቶታል፡፡ ሴቶች በባለሙያነትም ሆነ በኃላፊነት በተመደቡበት ቦታ ሁሉ የተሰጣቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ብለዋል። በመድረኩ ላይ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓዎር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ ( ዶ/ር) የተቋሙን የሴቶች አቅም እና የአመራር ሰጭነት ሚና ለማሳደግ በሚያስችሉ ሀገራዊ እና ዓለምቀፋዊ አሰራሮች ላይ ያተኮረ የመወያያ ጽሁፍ አቅርበዋል፡፡  ምንም እንኳን ሴቶች በአመራር ሰጭነት እና በተቋማዊ የሥራ አፈፃፀም ክንውን ጉልህ ድርሻ ቢኖራቸውም በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ ሀገራት ተሳትፏቸው አነስተኛ መሆኑ በቀረበው ጽሁፍ ተገልጿል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሴቶችን ተሳታፊ የሚያደረግ ፖሊሲ እና የአሰራር ማዕቀፎችን ቀርፆ ቢንቀሳቀስም ተሳትፎአቸው ከ18 በመቶ እንዳልዘለለ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ በተቋሙ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ በበኩላቸው ሴቶችን ለማብቃት እና ተሳትፏቸውን ለማሳደግ የተቋሙ የሥራ መሪዎች ትኩረት እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡   ሴቶችም ተጠቃሚነታቸውን እና ተሳትፎኣቸውን ለማሳደግ የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በመድረኩ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ መካከለኛ እና የበላይ አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን ሴቶች ለራሳቸው እና ሌሎች ለሴቶች የሚሰጡት የተሳሳተ ግምት እንዲሁም ሴቶችን ማዕከል ያላደረጉ ፖሊሲ እና የሥራ አካባቢዎች እንዲስተካከሉ፤  ለሴቶች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በልዩ ሁኔታ እንዲዘጋጁ፣ የሴቶችን ተጠቃሚነት እና አካታችነት የሚያረጋግጡ አስራሮች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጠይቀዋል፡፡‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+6

የግድቡ መጠናቀቅ ባለመጨረስ የባሕል ልምምድ ላይ የተሰነዘረ መዶሻ ነው ‎....///..... ‎የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ ለምርቃት ዝግጁ መሆን ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ ያለመጨረስ የባሕል ልምምድ ላይ የተሰነዘረ መዶሻ መሆኑን የአፍሪካ ሥራ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ዛዲግ አብርሃ ተናገሩ። ‎ ‎ፕሬዚደንቱ ይህን የተናገሩት ለሕዳሴ ግድብ ምክር ቤት ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች  በሰጡት ስልጠና ላይ ነው። ‎ ‎እንደ አቶ ዛዲግ ገለጻ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ፉክክርን ወደ ትብብር በመቀየር ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ጀምሮ የመፈጸም ሀገራዊ መሰረት የተጣለበት እንዲሁም ብሔራዊ ማንነታችንንና የፍላጎታችንን አዋጅ የተነገረበት ነጋሪት ጋዜጣ ነው። ‎ ‎የግድብ ግንባታው የመሰረት ድንጋይ ሲቀመጥ ቦንድ የገዛውና ገንዘብ የለገሰው ሕዝብ በወቅቱ ይታየው የነበረው የመሰረት ድንጋይ ሳይሆን የመነጨ የኤሌክትሪክ ኃይል እና ብርሃን ነበር ብለዋል። ‎ ‎ሕዝቡ ከመንግስት ጋር በመተባበር በጨለማ እየኖረ በቅርብ ላላየው ብርሃን ታጋይ ሆኖ የዘመኑ አደዋ የሆነውን የሕዳሴ ግድብ ግንባታን የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ እንዲደርስ ማድረጉን ገልጸዋል። ‎ ‎የፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ መጠናቀቅ የአባይ ምንጭ የነበረችዋን ኢትዮጵያ 5 ሺ 150 ሜጋ ዋት ኃይል በማመንጨት የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል እንድትሆን መደላድል የሚፈጥር መሆኑን አብራርተዋል። ‎ ‎እንደ አቶ ዛዲግ ገለፃ ግድቡ አፍሪካ ያላትን ፀጋ በራሷ ልጆች ዕውቀት፣ ጉልበትና ገንዘብ ወደ ሀብት በመቀየር መልማት እንደምትችል ለዓለም ያሳየ የአደባባይ ትዕምርት ነው። ‎ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ....///.... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ Junior Electrical Engineer እና በ Junior Mechanical Engineer የስራ መደቦች ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ሚያዚያ 09 ቀን 2017 ዓ.ም  የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸ አመልካቾች በJunior Electrical Engineer ነሐሴ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት  በJunior Mechanical Engineer ነሐሴ 07 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ  ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በዋናው መ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

photo content
+9