en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 696 subscribers, ranking 8 049 in the Technologies & Applications category and 2 173 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 696 subscribers.

According to the latest data from 02 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 141 over the last 30 days and by 0 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 28.59%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 16.37% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 487 views. Within the first day, a publication typically gains 2 569 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 10.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
EEP Communication

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 03 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 696
Subscribers
No data24 hours
+147 days
+14130 days
Posts Archive
photo content

የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን እየተሰራ ነው ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዢ ሂደቶቹን ለማዘመን ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር ያለማው ሲስተም ወ
+9
የተቋሙን የግዥ ሥርዓት ለማዘመን እየተሰራ ነው   ……..///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግዢ ሂደቶቹን ለማዘመን ፔራጎ ኢንፎርሜሽን ሲስተምስ ከተሰኘ ሀገር በቀል ኩባንያ ጋር ያለማው ሲስተም ወደሥራ ሊገባ ነው፡፡  የለማውን የግዢ ሥርዓት ለማስጀመር በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የተቋሙ እና የኩባንያው የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡    በፕሮጀክቱ የማስጀመሪያ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት በተቋሙ የሚከናወኑ የተለያዩ ሥራዎች በወረቀት አልባ መንገድ እንዲመሩ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ይገኛል። ተቋሙ ግዢዎቹን ጨምሮ ሌሎች ሥራዎቹን በዲጂታል ሥርዓት ታግዞ ማከናወኑ በአሰራር ላይ ለሚያጋጥሙ ችግሮች በቀላሉ መፍትሔ ለመስጠት እና ሥራዎቹን ለማቀላጠፍ እንደሚያስችል አንስተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-የግዥ-ሥርዓት-ለማዘመን-እየተሰ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ብክነትን በቴክኖሎጂ መታገል - ለጠንካራ ኢኮኖሚና አስተማማኝ ብርሃን! የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትን መቀነስ የሀገርን ኢኮኖሚ መገንባት ነው! የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት (Power Loss) ከ
+1
የኃይል ብክነትን በቴክኖሎጂ መታገል - ለጠንካራ ኢኮኖሚና አስተማማኝ ብርሃን!   የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነትን መቀነስ የሀገርን ኢኮኖሚ መገንባት ነው!   የኤሌክትሪክ ኃይል ብክነት (Power Loss) ከኢኮኖሚ ጥቅሙ ባለፈ የተቋሙን የፋይናንስ አቅምና የኃይል አቅርቦት አስተማማኝነት የሚፈትን ትልቅ ጉዳይ ነው። ይህ ብክነት በሁለት ዋና ዋና መንገዶች ይከሰታል፡፡     ቴክኒካዊ ብክነት (Technical Loss)፦ ይህ ብክነት የሚከሰተው ኤሌክትሪክ ከማመንጫ ጣቢያው ተነስቶ ለተጠቃሚዎች በሚደርስበት ረጅም መንገድ ላይ በተለያዩ ምክንያቶች የሚባክን ኃይል ሲሆን በኢንጂነሪንግ ሥራዎች የሚፈታ  ነው። ምንጮቹ፦ በዋናነት ያረጁ የማስተላለፊያ እና የሥርጭት መስመሮች እና የትራንስፎርመሮች መጨናነቅ ናቸው።   መፍትሔው፦ መሠረተ-ልማትን ማዘመን! ስማርት ግሪድ (Smart Grid) በመጠቀም ብክነት ያለበትን መስመር ለይቶ ማወቅና ኃይልን በከፍተኛ ቮልቴጅ በማስተላለፍ በመንገድ ላይ የሚጠፋውን ኃይል መቀነስ ይቻላል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ብክነትን-በቴክኖሎጂ-መታገል-ለጠ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት ለህዳሴው ግድብ ደህንነት! 🌱💧 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ9 ወራት ውስጥ 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለኃይል ማመንጨት ተግባር ጥቅም ላይ አውሏል! 🌊⚡️ የ
+2
የአረንጓዴ አሻራ ትሩፋት ለህዳሴው ግድብ ደህንነት! 🌱💧 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በ9 ወራት ውስጥ 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ለኃይል ማመንጨት ተግባር ጥቅም ላይ አውሏል! 🌊⚡️ የግድቡ ሥራ አስኪያጅ አቶ ከማል አሕመድ እንዳስታወቁት ግድቡ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 42.85 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ በመጠቀም 13 ሺህ 778 ነጥብ 37 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ማመንጨት ችሏል። ይህም ለኃይል ማመንጨት የታቀደውን የውሃ አጠቃቀም 84.9 በመቶ አፈጻጸም ላይ አድርሶታል። ታሪካዊው የውሃ ፍሰት እና የወደፊት ተስፋ   • ከታቀደው በላይ የነበረ የውሃ መጠን፦ ወደ ግድቡ ይገባል ተብሎ የታቀደው 46 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ቢሆንም በዓመቱ 57.7 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ውሃ ገብቷል (የ24.4% ብልጫ)። • የክረምት በረከት፦ ከጠቅላላ የውሃ ገቢ ውስጥ 50.5 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ የሚሆነው በሐምሌ፣ ነሐሴ፣ መስከረም እና ጥቅምት ወራት የገባ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የአረንጓዴአሻራትሩፋትለህዳሴውግድብደ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም

የሀገር ሀብትን በመቆጠብ ለቀጣይ ትውልድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረብን ነው! 🇪🇹 ......///...... የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለሙያዎች ባለፉት 9 ወራት በራስ አቅም ባከናወኗ
የሀገር ሀብትን በመቆጠብ ለቀጣይ ትውልድ አስተማማኝ ኃይል እያቀረብን ነው! 🇪🇹  ......///...... የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለሙያዎች ባለፉት 9 ወራት በራስ አቅም ባከናወኗቸው የጥገና ሥራዎች በከ7.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪን አድነዋል!   የአዳማ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ  ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ አይናለም ወ/ሚካኤል አእንዳስታወቁት ይህ ስኬት የተመዘገበው ጣቢያው የቴክኖሎጂ ሽግግርንና የባለሙያዎችን ክህሎት መሠረት በማድረግ በወሰደው እርምጃ ነው።   የተመዘገቡት ዋና ዋና ስኬቶች፦   ✅  ራስን መቻል፦ የስዊችጊር፣ የስዊችያርድ፣ የኮሙዩኒኬሽን መቆጣጠሪያዎች እና የስርጭት መስመሮችን በራስ ባለሙያዎች በመጠገን ከፍተኛ ወጪ ተቆጥቧል።   ✅  የቴክኖሎጂ ሽግግር፦ በካርዶች፣ በስሊፕሪንግ እና በአይ.ጂ.ቢ.ቲ (IGBT) የጥገና ሥራዎች ወቅት የክህሎት ሽግግር በማድረግ አዳዲስ ባለሙያዎችን ማፍራት ተችሏል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የሀገር-ሀብትን-በመቆጠብ-ለቀጣይ-ትውልድ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የገነባው የዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን አሸነፈ ------///------- የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ
+1
ታላቁ  የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን የገነባው የዊቢልድ  ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን አሸነፈ ------///------- የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለዊቢልድ ግሩፕ የሳሞተር 2026 የፈጠራ ሽልማትን  (Samoter 2026 Innovation Award) አስገኝቷል።   በጣሊያን በተካሄደው የሳሞተር ዓለም አቀፍ የግንባታ ማሽነሪዎች ኤግዚቢሽን ላይ የተሰጠው ይህ ሽልማት  የፕሮጀክቱን ከፍተኛ የቴክኖሎጂ ፋይዳ እንዲሁም የኢትዮጵያንና የአፍሪካን የኃይል ዘርፍ ገጽታ በመለወጥ ረገድ ያለውን ጠቀሜታ የሚያሳይ ነው። በ1965 የተመሰረተው የሳሞተር የፈጠራ ሽልማት በአውሮፓ የግንባታ ምህንድስና ዘርፍ ውስጥ ረጅም ዕድሜ ካላቸውና ታዋቂ ከሆኑ የክብር ሽልማቶች አንዱ ሲሆን  ሽልማቱ በኃይል መሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ልማት ውስጥ አነስተኛ የቴክኒክ ችግሮችን ከመፍታት ባለፈ አዲስና አብዮታዊ ለውጥን ያመጡ ፕሮጀክቶችን እውቅና ለመስጠት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ታላቁ-የኢትዮጵያ-ህዳሴ-ግድብን-የገነባው&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥ ስምምነት ተፈራረመ …..///…… የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ዘላቂ አገልግሎትና የኃይል ምርት አስተማማኝ ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ስም
+3
ተቋሙ ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የቴክኒክ ድጋፍ የሚሰጥ ስምምነት ተፈራረመ …..///…… የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ዘላቂ አገልግሎትና የኃይል ምርት አስተማማኝ ለማረጋገጥ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ፡፡ ስምምነቱት የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ግሩፕ የሃይድሮ ሰርቪስ ዳይሬክተር ዋን ጂይ ናቸው፡፡ በቻይና ሻንጋይ በሚገኘው የቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ዋና መሥሪያ ቤት የተከናወነው የመግባቢያ ስምምነት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዓለም አቀፍ የውሃ ኃይል መፍትሔዎች አቅራቢ ከሆነው ቮይት ሃይድሮ ሻንጋይ ኩባንያ የረጅም ጊዜ የጥገና እና የቴክኒክ ድጋፍ አገልግሎት ለማግኘት ያስችለዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለታላቁ-ህዳሴ-ግድብ-የቴክኒክ-ድጋፍ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

"የተቋሙን መሠረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነት እንወጣለን" የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች …......///…….... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን
+9
"የተቋሙን መሠረተ ልማት ደህንነት ለማስጠበቅ የተሰጠንን አደራ በኃላፊነት እንወጣለን" የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች …......///…….... በኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል እና ደህንነታቸውን ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰጣቸውን አደራ በኃላፊነት እንደሚወጡ በሪጅኖች የተመደቡ የፊዚካል ሴኩሪቲ ከፍተኛ መኮንኖች አረጋገጡ። ከፍተኛ መኮንኖች በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚፈጸሙ ጉዳቶችን በመከላከል ረገድ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ያከናወኗቸውን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበዋል። ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተቋሙን ንብረቶች በመጠበቅ እና የሚፈጸሙ ስርቆቶችን በመከላከል እንዲሁም ስርቆት የሚበዛባቸውን የስጋት ቀጣናዎች በመከታተልና በሙከራ ደረጃ በማህበረሰቡ እንዲጠበቁ በማድረግ፣ ከአካባቢ የመስተዳድር አካላትና ከማህበረሰቡ ጋር የቅድመ መከላከል የግንዛቤ ሥራዎችን በማጠናከር የአስተሳሰብ ለውጦች እንዲመጡ ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙን-መሠረተ-ልማት-ደህንነት-ለማስጠ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ጣቢያው አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ነው ‎….....///…..…. ‎የጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚ
+6
ጣቢያው አዲስ ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ ነው ‎….....///…..…. ‎የጎዴ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ በኢትዮጵያ መንግሥት እና በዳንጎቴ ግሩፕ አማካኝነት ለሚገነባው የማዳበሪያ ፋብሪካ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ ዝግጁ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ። ‎ ‎ሥራ አስኪያጁ አቶ ጌዲዮን አበራ እንደገለፁት የጎዴ ማከፋፈያ ጣቢያ ከራይቱ በባለ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል የሚያገኝበት አንድ ገቢ መስመር እንዲሁም በ132 እና 33 ኪሎ ቮልት ለተለያዩ አካባቢዎች ኃይል የሚሰጥበት ሰባት ወጪ መስመሮች አሉት። ‎ ‎ጣቢያው በ132 ኪሎ ቮልት ለቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያ፣ በ33 ኪሎ ቮልት ለጎዴ፣ ሀዳዋይ እና አዳዲሌይ ከተሞች እና በዙሪያው ለሚገኙ አካባቢዎች እንዲሁም ለሁለት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ጠቁመዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጣቢያው-አዲስ-ለሚገነባው-የማዳበሪያ-ፋብ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ ይቀጥላል …......///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በዘላቂነት ለመከ
+9
በተቋሙ ንብረቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን ለመከላከል የሚደረገው ዘመቻ ተጠናክሮ ይቀጥላል …......///……... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ የሚደርሱ ጉዳቶችን በዘላቂነት ለመከላከል የሚደረገውን ዘመቻ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋማዊ ደህንነትና አስተዳደራዊ ጉዳዮች መምሪያ አስታወቀ። መምሪያው ከሪጅን ኃላፊዎችና ከመሠረተ ልማት ደህንነት የጥበቃ ከፍተኛ መኮንኖች ጋር በኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ደህንነት ዙሪያ የተከናወኑ ሥራዎችን አስመልክቶ ለሦስት ቀናት በሀዋሳ ሲያካሂድ የቆየውን ግምገማ አጠናቋል። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሺፋ በሪፖርቱ ማጠቃለያ ላይ እንደገለጹት መምሪያው ከተደራጀ አጭር ጊዜ ቢሆነውም የተቋቋመበትን ተልዕኮ በሚገባ እየተወጣ ይገኛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በተቋሙ-ንብረቶች-ላይ-የሚደርሱ-ጉዳቶችን&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል ….....///….... በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ኦዳ በተባለ አካባቢ ከትናንት በስቲያ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝና
+6
ከባድ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል ….....///….... በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ባሌ ዞን ጊኒር ወረዳ ኦዳ በተባለ አካባቢ ከትናንት በስቲያ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለው ዝናብ ስድስት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች በመጣሉ ኃይል መቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ እንዳስታወቁት ጉዳቱ የደረሰው ከመልካ ዋከና - ራይቱ - ጎዴ በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ ነው። መስመሩ ለጎዴ እና ቀብሪደሃር ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል የሚሰጥ ሲሆን ከእነዚህ ጣቢያዎች ኃይል የሚያገኙ የኦሮሚያና የሶማሌ ክልል አካባቢዎች ሙሉ በሙሉ ኃይል መቋረጡን ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከባድ-ንፋስ-ቀላቅሎ-የጣለ-ዝናብ-ለኃይል-መ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ሥልጠናው የፕሮጀክቶችን አካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ስጋቶችን ለመከላከል ያግዛል ‎…....///.….. በዓለም ባንክ ፋይናንስ በሚደረጉ የፕራይም - 1 ፕሮጀክቶች ላይ ‎በአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ዙሪያ የተሰጠው ሥልጠና የአካባቢያዊና ማህበራዊ ስጋቶችን ለመከላከል እንደሚያግዝ የስልጠናው ተሳታፊ ባለሙያዎች ገለጹ። ‎ ‎የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከዓለም ባንክ የኢትዮጵያ የአካባቢ እና ማህበራዊ ስጋት አስተዳደር ቡድን ጋር በመተባበር በባንኩ ፋይናንስ ተደርገው በሚሰሩ ፕሮጀክት ላይ ለሚሰማሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና እና የደቡብ ሱዳን የአካባቢያዊ፣ የማህበራዊ እና የጤና ባለሙያዎች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቋል፡፡ ‎ ‎በተቋሙ የፕራይም - 1 ፕሮጀክቶች የኢንቫሮሜንታል ባለሙያ የሆነችው ወ/ሪት አዝመራ ተስፋዬ እንደገለጸችው ፕሮጀክቶች በሚተገበሩበት ወቅት ከአካባቢያዊና ማህበራዊ ተጽዕኖዎች ጋር በተያያዘ የተለያዩ ተግዳሮቶች ያጋጥማሉ። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሥልጠናው-የፕሮጀክቶችን-አካባቢያዊና-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

photo content
+9

ጣቢያው ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት በፈረቃ ኃይል መስጠት ጀምሯል ........///........ የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር በመሙላቱ የተነሳ ጣቢያው በአግባቡ አገልግሎት ለመስጠት
+3
ጣቢያው ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት በፈረቃ  ኃይል መስጠት ጀምሯል ........///........ የሰመራ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ትራንስፎርመር በመሙላቱ የተነሳ ጣቢያው  በአግባቡ አገልግሎት ለመስጠት መቸገሩን የሰሜን ምስራቅ 2 ሪጅን አስታወቀ። የሪጅኑ ዳይሬክተር  ሀሰን መሀመድ እንደገለፁት በጣቢያው የተተከለው ባለ 25  ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር መጫን ከሚችለው አቅም በላይ ኃይል እየጫነ ነው። በዚህ የተነሳ ሰመራ፣ ዱብቲ፣ አሳአይታ፣ ሚሌ፣ ሎጊያና በአቅራቢያቸው የሚገኙ ከተሞች ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት በጊዜያዊነት ኃይል በፈረቃ ለመስጠት እየተገደዱ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ጣቢያው-ጭነት-በሚበዛባቸው-ሰዓታት-በፈረ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ግንቦት 1 ቀን 2018 ዓ.ም

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቶት የነበረው ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ምዝገባ በቴክ
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቶት የነበረው ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ምዝገባ በቴክኒክ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረ መሆኑ ይታወቃል፤ አሁን ላይ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተፈቶ ምዝገባ የተጀመረ በመሆኑ ከሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት  10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከታች በተጠቀሰው ሊንክ   መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን። ዝርዝር የስራ መስፈርቶችን መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የወጣውን ማስታወቂያ ወይንም ከላይ የተያያዘውን ምስል መመልከት መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። የምዝገባ ሊንክ፡ https://vacancy.eep.com.et/VacancyList 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቶት የነበረው ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ምዝገባ በቴክ
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አውጥቶት የነበረው ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ምዝገባ በቴክኒክ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረ መሆኑ ይታወቃል፤ አሁን ላይ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተፈቶ ምዝገባ የተጀመረ በመሆኑ ከሚያዝያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት  10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከታች በተጠቀሰው ሊንክ   መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳዉቃለን። ዝርዝር የስራ መስፈርቶችን መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ የወጣውን ማስታወቂያ ወይንም ከላይ የተያያዘውን ምስል መመልከት መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። የምዝገባ ሊንክ፡ https://vacancy.eep.com.et/VacancyList የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

በፕሮጀክቱ ዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ……..///…….. ኢትዮጵያን ብርሃን የማልበስ ዓላማ ያለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀ
+6
በፕሮጀክቱ ዙሪያ የሚገኙ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ነው ……..///…….. ኢትዮጵያን ብርሃን የማልበስ ዓላማ ያለው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኮይሻ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ዙሪያ ለሚገኙ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የተቋሙ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ከኮንታ ዞን እና ኮንታ ኮይሻ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው የፌዴራልና የክልል ምክር ቤት ተወካዮች በተገኙበት በግድቡ አካባቢ የሚገኙ የኮይሻ ወረዳ ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ለማድረግ ስለተጀመሩት ተግባራት አስመልክቶ የምክክር መድረክ ተካሂዷል፡፡ በመድረኩ ላይ የኮንታ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ማርቆስ ወንድሙ እንደገለፁት የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ መጀመር አካባቢው ያለውን አስደናቂ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር እና የተፈጥሮ ሀብት በማስተዋወቅ የቱሪስት መዳረሻ እንዲሆኑ በር ከፍቷል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በፕሮጀክቱ-ዙሪያ-የሚገኙ-ነዋሪዎችን-የኤ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

በሪጅኑ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በተፈጸመ ስርቆት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ደርሷል ….….///……… በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በተፈጸመ ስርቆት 18 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የሚገ
+3
በሪጅኑ በዘጠኝ ወራት ውስጥ በተፈጸመ ስርቆት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ኪሳራ ደርሷል ….….///……… በ2018 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ በተፈጸመ ስርቆት 18 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪሳራ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ኃይሉ በቀለ እንዳስታወቁት በሪጅኑ የሚፈጸሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ስርቆት ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር እየቀነሰ ቢመጣም ከነቀምት - ጊዳ አያና ባለ 132 ኪሎ ቮልት እና ከፊንጫ - ሻምቡ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ በተደጋጋሚ ስርቆት እየተፈፀመ ይገኛል። በሪጅኑ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ሰማኒያ ሁለት የከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በተፈጸመ ስርቆት 3 ሺህ 908 የታወር ብረቶች መሰረቃቸውን ገልጸው በዚህም በስርቆት የደረሰው ጉዳት፣ የተሰረቁ ታወሮችን መልሶ ለመጠገን የወጣውን ወጪ እና ኤሌክትሪክ በመቋረጡ የታጠውን ገቢ ጨምሮ 18 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በሪጅኑ-በዘጠኝ-ወራት-ውስጥ-በተፈጸመ-ስር&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

የግል ባንኮች ከተቋሙ ጋር በጋራ አንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ ......///........ የግል የፋይናንስ ተቋማት በቀጣይ 10 ዓመታት ለሚከናወኑ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ድጋፍ በማድረግ
+6
የግል ባንኮች ከተቋሙ ጋር በጋራ አንዲሰሩ ጥሪ ቀረበ ......///........ የግል የፋይናንስ ተቋማት በቀጣይ 10 ዓመታት ለሚከናወኑ የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ድጋፍ በማድረግ  ከተቋሙ ጋር በጋራ እንዲሰሩ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጥሪ አቀረበ። ተቋሙ ባንኮቹ ለኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች ድጋፍ የሚያደርጉበትን ዕድል ለመፍጠር በሀገሪቱ ከሚገኙ የግል ባንኮች የሥራ ኃላፊዎች ጋር  ውይይት እያካሄደ ይገኛል። በውይይቱ ላይ የመክፈቻ ንግግር  ያደረጉት በተቋሙ  የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደተናገሩት ተቋሙ የተለያዩ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ለሀገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል። ተቋሙ አሁን ላይ ከ900 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት ያለው ሲሆን የተፈቀደ ካፒታሉ ደግሞ 1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን ብር እንደሆነ ገልፀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የግል-ባንኮች-ከተቋሙ-ጋር-በጋራ-አንዲሰሩ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሚያዚያ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

EEP Communication - Statistics & analytics of Telegram channel @eepcommuication