ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 553 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 399 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 163 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 553 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 12، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.73‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 14.92‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 157 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 320 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 21 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 553
المشتركون
+724 ساعات
+77 أيام
+1230 أيام
أرشيف المشاركات
ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለ130 ኛው የአድዋ ድል መታሰቢያ በሠላም አደረሳችሁ! ጀግኖች አያት ቅድመ አያቶቻችን ህይወታቸውን ገብረው ነፃነት እንዳቀዳጁንና ጀግንነት እንዳወረሱን ሁሉ ተቋማችን ለሀገራችን እድገት አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ በርካታ መስዋዕትነት የሚጠይቁ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። ከእነዚህም መካከል በመላው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እውን የሆነው የመላ አፍሪካውያን ኩራት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ይጠቀሳል። በህዳሴ ግድብ ላይ የተጀመረውን የድል አድራጊነት ስኬት በሌሎች ፕሮጀክቶቻችንም ላይ በመድገምና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር በማድረግ ለሀገራችንን ዕድገት የበኩላችንን ድርሻ መወጣታችንን እንደምንቀጥል እምነቴ የፀና ነው። በዓሉ በሁሉም ዘርፍ የምናሸንፍበትና የአንድነት እንዲሆንልን ከልብ እመኛለሁ፡፡ አሸብር ባልቻ፣ ዋና ሥራ አስፈፃሚ

image_2026-03-01_14-50-18.png6.10 KB

ዐድዋ እና ሕዳሴ፦ ትናንት በደም፣ ዛሬ በላብ የተገነባ የሉዓላዊነት ድልድይ! 🇪🇹 በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ሁለት ታላላቅ "የማይቻል" የሚመስሉ ድሎች አሉ። አንደኛው በጠመንጃ ወራሪን ድል ያደረግንበት የዐድዋ ድል ሲሆን፤ ሁለተኛው ደግሞ በገንዘባችን፣ በዕውቀታችንና በላባችን ድህነትንና ኢፍትሐዊነትን ድል ለማድረግ በቁርጠኝነት የሰራንበት የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ ያስመዘገብነው ድል ነው። 🇪🇹 አባቶቻችን በዐድዋ ተራሮች ላይ ለዓለም ያስተማሩት ትምህርት "ለነፃነት ዋጋ መክፈል!" የሚል ነበር። ያ ድል ኢትዮጵያን በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በመላው ዓለም የተጨቆኑ ሕዝቦች ተስፋ አደረጋት። ዐድዋ ባይኖር ኖሮ ዛሬ ስለ ሉዓላዊነትና ስለ ኢኮኖሚ ነፃነት የምናወራበት የጸና ሀገር ባልኖረን ነበር። 🇪🇹 የኢኮኖሚ ነፃነት ማማ ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰደው የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ደግሞ የዐድዋ ድል የ21ኛው ክፍለ ዘመን ቀጣይነት ማሳያ ነው። ትናንት "ቅኝ አልገዛም" እንዳልን ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ በሕዳሴው ግድብ አማካኝነት "የተፈጥሮ ሀብቴን በራሴ ፈቃድና ፍላጎት እንጂ በሌሎች ይሁንታ አልጠቀምም" ብለን የመልማት መብታችንን ለዓለም አረጋግጠናል። የግድቡ ኃይል ማመንጨት መጀመር ኢትዮጵያ ከድህነት ቀንበር ለመውጣትና የአፍሪካ የኢኮኖሚ ብርሃን (Economic Beacon) ለመሆን የጀመረችው ጉዞ ስኬት ነው። 🇪🇹 ትናንት አባቶቻችን አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍሰው ይህችን ሀገር አቆይተውልናል፡፡ የዛሬው ትውልድ ደግሞ ላቡን አፍሶ ግድቡን በመገንባት ለኢትዮጵያ ብሩህ የተስፋ አድማስ ፈንጥቋል። የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የዐድዋ ድል ባለቤት የሆነችውን ኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ባለድል እና የመጪው ጊዜ ኃያል የማድረግ ቃል ኪዳን ነው። ስለሆነም ዐድዋን ማክበር ማለት የአባቶችን ጀግንነት ማድነቅ ብቻ አይደለም፤ እንደ አባቶቻችን ለሀገር የሚጠቅም አሻራ ማሳረፍም ጭምር ነው። የሕዳሴው ግድብ የሁላችንም ኩራትና የዐድዋ መንፈስ በተግባር የገለጽንበት የታሪካችን አዲሱ ምዕራፍ ነው! የዐድዋ የድል መንፈስ በሕዳሴው ግድብ ላይ ተደግሟል! 🇪🇹 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት  22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

ከዐድዋ እስከ ህዳሴ - የክብርና የሉዓላዊነት ቀጣይነት! 🇪🇹🛡🌊 "ዐድዋ የአፍሪካ ድል ነው። አፍሪካውያን ቅኝ ግዛት ፈጽሞ እንደማይቀበሉ ያሳዩበት ድል ነው።" (የመደመር መጽሐፍ፣ ገጽ 266) የዘንድሮው የዐድዋ ድል በዓል “ከአኩሪ ታሪክ ወደ ብሩህ አድማስ" በሚል ታላቅ መሪ ቃል ይከበራል። ይህ መሪ ቃል ትናንት በጀግኖች ደምና አጥንት የተጠበቀችውን ሀገር ዛሬ በዘላቂ ሰላምና በልማት ወደ ሁለንተናዊ ሉዓላዊነትና ከፍታ ለማሻገር ያለንን ፅኑ ቁርጠኝነት የሚገልጽ ነው። ዐድዋ እና ህዳሴ፦ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች 📌 የዐድዋ ድል ወታደራዊ ድል ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያውያን ለፍትሕና ለእኩልነት ያላቸውን ጽኑ አቋም ለዓለም ያሳዩበት ነው። ዛሬም ይህ የዐድዋ መንፈስ በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በደመቀ ሁኔታ ተደግሟል። 🇪🇹 አባቶቻችን በዐድዋ ምድር በ"ቅኝ አልገዛም!" ብለው ወራሪን እንዳሳፈሩ ሁሉ፣ ዛሬም የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅና ኃይል ማመንጨት መጀመሩ ኢትዮጵያ በሀብቷ የመጠቀም ተፈጥሯዊ መብቷን ለማስከበር ያሳየችው "የዘመኑ ዐድዋ" ነው። ይህ ግድብ ኢትዮጵያ ኢፍትሐዊነትን እና የኢኮኖሚ የእጅ አዙር ቅኝ አገዛዝን የማትቀበል ሀገር መሆኗን ዳግም ለዓለም ያረጋገጠችበት ትልቅ ሀገራዊ ድል ነው። 🇪🇹 ጀግኖች አባቶቻችን ነፃ ሀገር አውርሰውናል፤ እኛ ደግሞ የበለፀገችና በብርሃን የተሞላች ሀገር ለልጆቻችን ለማውረስ በሕዳሴው ግድብ መሠረት ጥለናል። ይህ ጉዞ ከአኩሪ ታሪክ የተነሳና ወደ ብሩህ አድማስ የሚያመራ የድል ሰንሰለት ነው። ትናንት በጦር ሜዳ ሉዓላዊነታችንን አስከብረን እንዳልተንበረከክን፣ ዛሬ ደግሞ በልማትና በኢኮኖሚ ነፃነታችንን በማረጋገጥ ወደ ሁለንተናዊ ከፍታ እየተጓዝን ነው። የሕዳሴው ግድብ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን፣ ልክ እንደ ዐድዋ ሁሉ የጥቁር ሕዝቦችና የመላው አፍሪካውያን የልማት ተስፋና ኩራት ነው። 🇪🇹 ስለሆነም ዐድዋ የነፃነታችን መጀመሪያ እንደሆነው ሁሉ የታላቁ ኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም የኢኮኖሚ ከፍታችን እና የመቻላችን ማረጋገጫ ነው። ትናንት በጥይት ድል አደረግን፤ ዛሬ በዕውቀትና በሀብታችን ድል እያደረግን ነው! ክብር ለዐድዋ ጀግኖች! ሞገስ ለሕዳሴ ግድብ ገንቢዎች! 🇪🇹 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት  22 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የተግባር ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥ
የተግባር ፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቧንቧ ጥገና ሰራተኛ (Plumber Technician) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱ አሟልታችሁ ከተመዘገባችሁት ተወዳዳሪዎች መካከል የፅሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 19 የስም ዝርዝራችሁ የተገለጸው ተወዳዳሪዎች የካቲት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 የተግባር ፈተና ስለሚሰጥ በሰው ኃይል ቅጥርና ምደባ ቢሮ እንድትገኙ እናሳውቃለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት  19 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒያሽን (Technician-I EV Battery Charger) የስራ መደ
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ አድራጊ ቴክኒያሽን (Technician-I EV Battery Charger) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 08 ቀን 2018 ዓ.ም የውጭ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም

የታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን የሚያስችል የጥናት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከደቡብ ኮሪያ ሪፐብሊክ መንግሥት ጋር የኤሌክትሪክ ታሪፍ ድርድር ማዕቀፍን ለማዘመን የሚያስችል የጥናት ማስጀመሪያ መርሀ ግብር በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡ በጥናት ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ የኃይል ልማት ዘርፍን ለማሳደግና ለማዘመን በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ በትብብር ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ከታዳሽ ኃይል ኤሌክትሪክ ለማመንጨት የሚያስችል ሰፊ ሀብት ቢኖራትም አሁን ላይ የኃይል ተደራሽነት ሽፋኑ 54 በመቶ ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የታሪፍ-ድርድር-ማዕቀፍን-ለማዘመን-የሚያ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+2

photo content
+9

አስቸኳይ የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኞች ማኅበር (የሠራተኞች ክበብ) ባለው ክፍት የሥራ መደብ ላይ ሠራተኞችን አወዳድሮ
አስቸኳይ የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ ..........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ ሠራተኞች ማኅበር (የሠራተኞች ክበብ) ባለው ክፍት የሥራ መደብ ላይ ሠራተኞችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል። ክፍት የሥራ መደቦች፦ 1. የሰው ኃይል አስተዳደር ሠራተኛ 2. የሂሳብ ባለሙያ 3. ረዳት የፅዳት ቁሳቁስ ቤት ሠራተኛ ዝርዝር መረጃውን በዌብሳይታችን ይመልከቱ፦ https://www.eep.com.et/?amh-announcement=የሥራ-ቅጥር-ማስታወቂያ፡-የኢትዮጵያ-ኤሌ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም

የጥበቃ ሠራተኞች ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በተላበሰ መልኩ የተቋሙን ደህንነት ማስጠበቅ እንዳለባቸው ተገለፀ …///….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤጀንሲ በኩል የተቀጠሩ አዳዲስ የጥበቃ ሠራተኞችን አ
+6
የጥበቃ ሠራተኞች ሙያዊ ሥነ-ምግባርን በተላበሰ መልኩ የተቋሙን ደህንነት ማስጠበቅ እንዳለባቸው ተገለፀ …///….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኤጀንሲ በኩል የተቀጠሩ አዳዲስ የጥበቃ ሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ እና የተቋሙን ደህንነት ለማስጠበቅ ያለመ የሥራ ማስጀመሪያ ሥልጠና በዛሬው ዕለት ሰጥቷል። በሥልጠናው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በተቋሙ የዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ሥልጠናው የጥበቃ ሠራተኞቹ ከዚህ ቀደም የሚያውቁትን ልምድ እንዲያሳድጉና አዳዲስ አሰራሮችን እንዲቀስሙ ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡ በተቋሙ የኃይል መሠረተ ልማት ደህንነት፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ እንደገለፁት የተቋሙን ንብረት መጠበቅና መንከባከብ ለድርጅቱ ህልውና ወሳኝ በመሆኑ የጥበቃ ሠራተኞችን በዕውቀት ማብቃት አማራጭ የሌለው ተግባር ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/??amh-news=የጥበቃ-ሠራተኞች-ሙያዊ-ሥነ-ምግባርን-በተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2018 ዓ.ም

‎ኢትዮጵያና ቱርክ በኢነርጅ ዘርፍ ልማት አብሮ ለመስራት ተስማሙ ‎....//.... ‎ኢትዮጵያ እና ቱርክ በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ በታዳሽ ኃይል ኢንቨስትመንት እና በውሃ ኃይል መሠረተ ልማት ዙሪ
‎ኢትዮጵያና ቱርክ በኢነርጅ ዘርፍ ልማት አብሮ ለመስራት ተስማሙ ‎....//.... ‎ኢትዮጵያ እና ቱርክ በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ፣ በታዳሽ ኃይል ኢንቨስትመንት እና በውሃ ኃይል መሠረተ ልማት ዙሪያ አብሮ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል። ‎ ‎የመግባቢያ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሐብታሙ ኢተፋ እና የቱርክ የኢነርጂ እና የተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትር አልፓርስላን ባይራክታር ፈርመዋል። ‎ ‎በስምምነቱ መሠረት ሀገራቱ በታዳሽ ኃይል እና በኢነርጂ ቁጠባ ዘርፎች የጋራ ፕሮጀክቶችን እንደሚያዘጋጁ እንዲሁም የውሃ ኃይል ማመንጫ መሣሪያዎችን እና ተርባይኖችን በማምረትና በመትከል አብረው የሚሰሩ ይሆናል። ‎ ‎በተጨማሪም ቱርክ በኢትዮጵያ የኢነርጂ ዘርፍ ፕሮጀክቶችን እንድታለማ እድል የሚፈጥር ነው። ‎ ‎የልምድ ልውውጥ በማጠናከር እና በተለያዩ ዘርፎች ተጨባጭ ፕሮጀክቶችን በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ሀገራቱ አረጋግጠዋል። ‎ ‎ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ትናንት ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ መምጣታቸው የሚታወስ ነው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 11 ቀን 2018 ዓ.ም

የቀድሞ ተመራቂዎች ልምዳቸውን በመጠቀም ዘርፉን ለማገዝ ዝግጁ ናቸው .........///......... የቀድሞ የኢትዮጵያ መብራትና ኃይል ባለስልጣን የሥልጠና ኢንስቲትዩት ተመራቂዎች የረጅም ጊዜ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን በመጠቀም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልንና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ፡፡ የኢንስቲትዩቱ የኤሌክትሪክ 761 ባች የ1978 ዓ.ም የኤሌክትሮ ሜካኒካል ተመራቂዎች የተመረቁበትን 40ኛ ዓመት በተለያዩ ዝግጅቶች አክብረዋል። የማህበሩ የቦርድ አባልና የዝግጅት ኮሚቴው አስተባባሪ አቶ ለገሰ ዳበሳ እንደገለጹት ፕሮግራሙ በሀገር ውስጥና በውጭ በተለያየ ሁኔታ ላይ የሚገኙ የቀድሞ ተመራቂዎችን የእርስ በእርስ ግንኙነት በማጠናከር ያላቸውን ልምድና እውቀት በመጠቀም በቀጣይ ከተቋማቱ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች አብሮ ለመስራት ያላቸውን ዝግጁነት ለማሳየት ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የቀድሞ-ተመራቂዎች-ልምዳቸውን-በመጠቀም&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 9 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+4

photo content
+9

"ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሁን ቤቶችንና ኢንዱስትሪዎችን በኃይል እያደመቀ ነው፤ ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ይልካል። ይህም እንዴት የጋራ ብልጽግናን እንደሚያመጣ ያሳያል። " ጠቅላይ
"ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሁን ቤቶችንና ኢንዱስትሪዎችን በኃይል እያደመቀ ነው፤ ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል ይልካል። ይህም እንዴት የጋራ ብልጽግናን እንደሚያመጣ ያሳያል። " ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት 39ኛው የመሪዎች ጉባኤ ላይ ካስተላለፉት መልዕክት የተወሰደ። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 7 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ ለጎረቤት ሀገራት ካቀረበው ኃይል ከ67 ሚሊዮን ዶላር በላይ አግኝቷል ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለጎረቤት ሀገራት ካቀ
+6
ተቋሙ ለጎረቤት ሀገራት ካቀረበው ኃይል ከ67 ሚሊዮን ዶላር በላይ አግኝቷል ‎....///.... ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ ስድስት ወራት ለጎረቤት ሀገራት ካቀረበው የኃይል ሽያጭ 67 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዶላር ማግኘቱን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለጹ። ‎ ‎የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎትን የ2018 በጀት የግማሽ ዓመት እቅድ አፈጻጸም በዛሬው ዕለት ገምግሟል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-ለጎረቤት-ሀገራት-ካቀረበው-ኃይል-ከ67&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et የካቲት 6 ቀን 2018 ዓ.ም