en
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Open in Telegram

📈 Analytical overview of Telegram channel EEP Communication

Channel EEP Communication (@eepcommuication) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 537 subscribers, ranking 8 326 in the Technologies & Applications category and 2 176 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 537 subscribers.

According to the latest data from 04 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 26 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 26.64%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 15.41% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 139 views. Within the first day, a publication typically gains 2 395 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“EEP Communication”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 05 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Technologies & Applications category.

15 537
Subscribers
-724 hours
-77 days
+2630 days
Posts Archive
በስማርት ሜትር ቆጣሪ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና በመሰጠት ላይ ነው ………..///……….. ከኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሠራተኞች በስማርት ሜትር ቆጣሪ አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ያተኮረ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ ስልጠናው በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተተከሉትን ስማርት ሜትሮች አገልግሎት ላይ ለማዋል እና እንዴት መጠቀም እንደሚቻል እንደሚረዳ በተቋሙ የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ ገልፀዋል፡፡ ስልጠናው ስማርት ሜትሮች እንዴት መጠቀም እንደሚቻል፣ የቆጣሪ ንባብ እንዴትና መቼ መውሰድ እንደሚቻል፣ ቢል እንዴት መስራትና መውሰድ እንደሚቻል፣ ከሜትሮች ጋር አብሮ የመጣውን ሶፍትዌር እንዴት መሞላት (configure) መደረግ እንዳለበት፣ በስማርት ሜትሩ ላይ ያሉ መመሪያዎችን (parameters) እንዴት ማስተካከል እና መሙላት (configure) እንደሚቻል እንዲሁም ኢነርጂ ሜትሮች እንዴት መስራት (install) መደረግ እንዳለባቸው በሚሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ሥራ አስኪያጇ ተናግረዋል፡፡ በስልጠናው ላይ ከጀኔሬሽን ኦፕሬሽን፣ ከትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሪጅኖች፣ ከኤል ዲ ሲ (load dispatch center) ከማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ፣ ከኤሲቲ፣ ከሳይበር ሴኩሪቲ እና ከኢንጅነሪንግ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ 39 ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙም ወ/ሮ ሃይማኖት ጠቁመዋል፡፡ ሠራተኞች ከስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ሥራ ገበታቸው ሲመለሱ በተግባር ላይ ማዋል እና ለሌሎች የስራ ባልደረቦቻቸው ግንዛቤ መፍጠር እንዳለባቸው ኃላፊዋ አሳስበዋል፡፡ የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የስማርት ሜትር ቴክኖሎጂ አዲስ በመሆኑ ስልጠናው ቴክኖሎጂውን በመረዳት ሥራቸውን በቀላሉና በአጭር ጊዜ ለማከናወን ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል፡፡ ስልጠናው ከመስከረም 24 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን የገጠማ ስራ ባከናወነው "Siemens Proprietary Limited" በተሰኘ ኩባንያ አማካኝነት እየተሰጠ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 25 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+4

የመልካም ምኞት መግለጫ ************ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዐቢይ አህመድ አሊ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመሰየማቸው ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት እንኳን ደስ አለን እያለ መልካም
የመልካም ምኞት መግለጫ ************ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዐቢይ አህመድ አሊ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመሰየማቸው ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት እንኳን ደስ አለን እያለ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንልንላቸው መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ መስከረም 24 ቀን 2014 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et

IMG_20210927_091108_686.mp4197.91 MB

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ! !

photo content

ተፈናቅለው በተለያዩ አካባቢዎች ለተጠለሉ ዜጎች የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ያደረጉትን ድጋፍ አመስግነዋል፡፡ ሁሉም አካል ችግሩን በመገንዘብ ለተፈናቃዮች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል። ድጋፉን የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ከኮርፖሬት ኮሙኙኒኬሽን ቢሮ ጋር በመተባበር የተሰበሰበ ነው፡፡ መስከረም 14 ቀን 2014 የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et

ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ46 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ …….//……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአሁኑ ሠዓት
+2
ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ46 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ …….//……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአሁኑ ሠዓት በተለያዩ አካባቢዎች እያደረገ ባለው ጦርነት ምክንያት ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች በ46 ሺህ 5 መቶ ብር የተገዛ የዕለት ደራሽ ምግብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ድጋፉን በተቋሙ የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዛሬው ዕለት አስረክበዋል፡፡ ወ/ሮ ሌንሴ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ወገኖች የእለት ምግብና አልባሳት እንደሚስፈልጋቸው በመረዳት የተቋሙን ሠራተኞች በማስተባበር ድጋፉ መደረጉንም አንስተዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ላደረጉት ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በዛሬው ዕለት የተደረገው ድጋፍ 125 ኪሎ ግራም ሩዝ፣ 125 ኪሎ ግራም ማካሮኒ፣ 15 ካርቶን ፓስታ፣ 7 ካርቶን የተለያዩ የህጻናት ምግቦች፣ የንጽሕና መጠበቂያ ዕቃዎች፣ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶች እንዲሁም የተለያዩ አልባሳት እና ጫማዎች መሆናቸውን ተነግሯል፡፡ እንደ ወ/ሮ ሌንሴ ገለፃ ከዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሠራተኞችም በአካባቢያቸው ለሚገኙ አቅመ ደካሞች የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ለእለት ምግብ የሚሆኑ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ሁሉም ከጎናቸው በመሆን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም ወ/ሮ ሌንሴ አሳስበዋል፡፡ ድጋፉን የተረከቡት "የዕኔ እያለሁ ወገኔ አይራብም" በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ኑረዲን ነስሮ ማህበሩ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር አብሮ እንደሚሰራ ገልፀው በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው

ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ46 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ …….//……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአሁኑ ሠዓት
+3
ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ46 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ …….//……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአሁኑ ሠዓት በተለያዩ አካባቢዎች እያደረገ ባለው ጦርነት ምክንያት ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች በ46 ሺህ 5 መቶ ብር የተገዛ የዕለት ደራሽ ምግብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ድጋፉን በተቋሙ የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዛሬው ዕለት አስረክበዋል፡፡ ወ/ሮ ሌንሴ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ወገኖች የእለት ምግብና አልባሳት እንደሚስፈልጋቸው በመረዳት የተቋሙን ሠራተኞች በማስተባበር ድጋፉ መደረጉንም አንስተዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ላደረጉት ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ በዛሬው ዕለት የተደረገው ድጋፍ 125 ኪሎ ግራም ሩዝ፣ 125 ኪሎ ግራም ማካሮኒ፣ 15 ካርቶን ፓስታ፣ 7 ካርቶን የተለያዩ የህጻናት ምግቦች፣ የንጽሕና መጠበቂያ ዕቃዎች፣ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶች እንዲሁም የተለያዩ አልባሳት እና ጫማዎች መሆናቸውን ተነግሯል፡፡ እንደ ወ/ሮ ሌንሴ ገለፃ ከዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሠራተኞችም በአካባቢያቸው ለሚገኙ አቅመ ደካሞች የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ለእለት ምግብ የሚሆኑ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ሁሉም ከጎናቸው በመሆን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም ወ/ሮ ሌንሴ አሳስበዋል፡፡ ድጋፉን የተረከቡት "የዕኔ እያለሁ ወገኔ አይራብም" በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ኑረዲን ነስሮ ማህበሩ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር አብሮ እንደሚሰራ ገልፀው በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው

ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ 45 % ላይ ደርሷል .........///....... ኤን ኤስ ኢነርጂ ድረገፅ https://www.nsenergybusiness.com/projects/koysha-hydroelectric-power-project ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ የሚገኘው በኦሮሚያ ክልል ነው በሚል ያወጣው ዘገባ በትክክለኛ መረጃ ያልተመሰረተ ነው። ድረገፁ በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ እየተገነባ የሚገኘው ግድብ በኦሮሚያ ክልል እንደሚገኝ የዘገበ ቢሆንም የፕሮጀክቱ ትክክለኛ መገኛ በደቡብ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት በኮንታ ልዩ ወረዳ ኮይሻ ቀበሌ ነው። ስህተቱ ሆን ተብሎ ያልተፈፀመና በስራ አጋጣሚ ሊከሰት የሚችል መሆኑን በቀናነት በመውሰድ ድረገፁ ዘገባውን እንዲያርም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጠየቀ ሲሆን ይስተካከላል ብሎ ያምናል። ግድቡ በዓመት በአማካይ 6460 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ሲሆን በዓመት እስከ አንድ ሚሊየን ቶን የካርበን ልቀት የመቆጣጠር አቅም አለው። ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአሁኑ ሰዓት 45 % ደርሷል። የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ 180 ሜትር ቁመት፣ 250 ሜትር ርዝመትና 41 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 12 ቀን 2014

የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" ዘመቻን ተቀላቀሉ ………..//……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በሃገር ዓቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ህዝባዊ ንቅናቄ በዛሬው ዕለት በይፋ ተቀላቅለዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በሃገራዊ ዘመቻው ላይ በመሳተፋና በደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን በማኖር የኢትዮጵያን የተደበቀ እውነታ ለአለም ዓቀፉ ማህበረሰብ እንዲታወቅ ለማድረግ ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡ በንቅናቄ ዘመቻው ላይ የተሳተፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴክኒካል አማካሪ አቶ አንዳርጌ እሸቴ እንደተናገሩት የንቅናቄ ዘመቻው አሸባሪው የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች እያደረሰ ያለውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ያግዛል ብለዋል፡፡ "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" የንቅናቄ ዘመቻ ህብረተሰቡ የሃገሩን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ያለውን ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት እድል እንደሚሰጥም ጠቁመዋል፡፡ እንደ አቶ አንዳርጌ ገለፃ ዘመቻው ኢትዮጵያ ተበዳይ ሆና ሳለ በተቃራኒው በሃገሪቱ ያለውን እውነታ በማዛባት ጫና ለማሳደር የሚፈልጉ የተለያዩ ኃይሎችን በመታገል የሃገሪቱን መፃኢ ዕድል ለመወሰን ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ የንቅናቄ መድረኩ በኢትዮጵያ ላይ ያለውን ተጨባጭ መረጃ ለነጩ ቤተ መንግስት ብቻ ሳይሆን መላው ዓለም እውነቱን እንዲገነዘብ ለማድረግ እንደሚረዳም የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ተናግረዋል፡፡ የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር ከመሯሯጥ ይልቅ የህወሓትን ሴራ በማጋለጥ ከህዝባችን ጎን ሊቆም እንደሚገባም ነው ሠራተኞቹ የጠቆሙት፡፡ የወገኑን ሞትና መፈናቀል የማይፈልግ ኢትዮጵያ የሆነ ሁሉ የንቅናቄ ዘመቻውን በመቀላቀል ኢትዮጵያን የመበተን ፍላጎት ያለው የህወሓት ቡድን በሃገሪቱ ላይ እየፈጸመ ያለውን ተግባር ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስረዳት እንደሚገባ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች አሳስበዋል፡፡ መስከረም 3 ቀን 2014 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" ሃገራዊ ዘመቻ እስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 11 ቀን 2014

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content