EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 538 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 326,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 176 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 538 名订阅者。
根据 04 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 26,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.64%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 139 次浏览,首日通常累积 2 395 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 05 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 538
订阅者
-724 小时
-77 天
+2630 天
帖子存档
15 538
በስማርት ሜትር ቆጣሪ አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና በመሰጠት ላይ ነው
………..///………..
ከኢትየጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተውጣጡ ሠራተኞች በስማርት ሜትር ቆጣሪ አጠቃቀም ዙሪያ ላይ ያተኮረ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡
ስልጠናው በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተተከሉትን ስማርት ሜትሮች አገልግሎት ላይ ለማዋል እና እንዴት መጠቀም እንደሚቻል እንደሚረዳ በተቋሙ የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ ገልፀዋል፡፡
ስልጠናው ስማርት ሜትሮች እንዴት መጠቀም እንደሚቻል፣ የቆጣሪ ንባብ እንዴትና መቼ መውሰድ እንደሚቻል፣ ቢል እንዴት መስራትና መውሰድ እንደሚቻል፣ ከሜትሮች ጋር አብሮ የመጣውን ሶፍትዌር እንዴት መሞላት (configure) መደረግ እንዳለበት፣ በስማርት ሜትሩ ላይ ያሉ መመሪያዎችን (parameters) እንዴት ማስተካከል እና መሙላት (configure) እንደሚቻል እንዲሁም ኢነርጂ ሜትሮች እንዴት መስራት (install) መደረግ እንዳለባቸው በሚሉ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንደሚያደርግ ሥራ አስኪያጇ ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው ላይ ከጀኔሬሽን ኦፕሬሽን፣ ከትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሪጅኖች፣ ከኤል ዲ ሲ (load dispatch center) ከማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ፣ ከኤሲቲ፣ ከሳይበር ሴኩሪቲ እና ከኢንጅነሪንግ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ 39 ባለሙያዎች በመሳተፍ ላይ እንደሚገኙም ወ/ሮ ሃይማኖት ጠቁመዋል፡፡
ሠራተኞች ከስልጠናው ያገኙትን ዕውቀት ወደ ሥራ ገበታቸው ሲመለሱ በተግባር ላይ ማዋል እና ለሌሎች የስራ ባልደረቦቻቸው ግንዛቤ መፍጠር እንዳለባቸው ኃላፊዋ አሳስበዋል፡፡
የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው የስማርት ሜትር ቴክኖሎጂ አዲስ በመሆኑ ስልጠናው ቴክኖሎጂውን በመረዳት ሥራቸውን በቀላሉና በአጭር ጊዜ ለማከናወን ዕድል እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል፡፡
ስልጠናው ከመስከረም 24 እስከ ጥቅምት 2 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን የገጠማ ስራ ባከናወነው "Siemens Proprietary Limited" በተሰኘ ኩባንያ አማካኝነት እየተሰጠ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 25 ቀን 2014 ዓ.ም
15 538
የመልካም ምኞት መግለጫ
************
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዐቢይ አህመድ አሊ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመሰየማቸው ለኢትዮጵያ ህዝብና መንግስት እንኳን ደስ አለን እያለ መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንልንላቸው መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡
መስከረም 24 ቀን 2014
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
15 538
ተፈናቅለው በተለያዩ አካባቢዎች ለተጠለሉ ዜጎች የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ያደረጉትን ድጋፍ አመስግነዋል፡፡
ሁሉም አካል ችግሩን በመገንዘብ ለተፈናቃዮች የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ጠይቀዋል።
ድጋፉን የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ቢሮ ከኮርፖሬት ኮሙኙኒኬሽን ቢሮ ጋር በመተባበር የተሰበሰበ ነው፡፡
መስከረም 14 ቀን 2014
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
15 538
ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ46 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
…….//…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአሁኑ ሠዓት በተለያዩ አካባቢዎች እያደረገ ባለው ጦርነት ምክንያት ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች በ46 ሺህ 5 መቶ ብር የተገዛ የዕለት ደራሽ ምግብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ድጋፉን በተቋሙ የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዛሬው ዕለት አስረክበዋል፡፡
ወ/ሮ ሌንሴ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ወገኖች የእለት ምግብና አልባሳት እንደሚስፈልጋቸው በመረዳት የተቋሙን ሠራተኞች በማስተባበር ድጋፉ መደረጉንም አንስተዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ላደረጉት ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተደረገው ድጋፍ 125 ኪሎ ግራም ሩዝ፣ 125 ኪሎ ግራም ማካሮኒ፣ 15 ካርቶን ፓስታ፣ 7 ካርቶን የተለያዩ የህጻናት ምግቦች፣ የንጽሕና መጠበቂያ ዕቃዎች፣ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶች እንዲሁም የተለያዩ አልባሳት እና ጫማዎች መሆናቸውን ተነግሯል፡፡
እንደ ወ/ሮ ሌንሴ ገለፃ ከዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሠራተኞችም በአካባቢያቸው ለሚገኙ አቅመ ደካሞች የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ለእለት ምግብ የሚሆኑ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ሁሉም ከጎናቸው በመሆን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም ወ/ሮ ሌንሴ አሳስበዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት "የዕኔ እያለሁ ወገኔ አይራብም" በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ኑረዲን ነስሮ ማህበሩ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር አብሮ እንደሚሰራ ገልፀው በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው
15 538
ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች ከ46 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገ
…….//…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አመራሮችና ሠራተኞች አሸባሪው የህወሓት ቡድን በአሁኑ ሠዓት በተለያዩ አካባቢዎች እያደረገ ባለው ጦርነት ምክንያት ከተለያዩ አካባቢዎች ለተፈናቀሉ ወገኖች በ46 ሺህ 5 መቶ ብር የተገዛ የዕለት ደራሽ ምግብ ድጋፍ አድርገዋል፡፡
ድጋፉን በተቋሙ የሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ መምሪያ ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዛሬው ዕለት አስረክበዋል፡፡
ወ/ሮ ሌንሴ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት የተፈናቀሉ ወገኖች የእለት ምግብና አልባሳት እንደሚስፈልጋቸው በመረዳት የተቋሙን ሠራተኞች በማስተባበር ድጋፉ መደረጉንም አንስተዋል፡፡ የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ላደረጉት ድጋፍም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
በዛሬው ዕለት የተደረገው ድጋፍ 125 ኪሎ ግራም ሩዝ፣ 125 ኪሎ ግራም ማካሮኒ፣ 15 ካርቶን ፓስታ፣ 7 ካርቶን የተለያዩ የህጻናት ምግቦች፣ የንጽሕና መጠበቂያ ዕቃዎች፣ የትምህርት መማሪያ ቁሳቁሶች እንዲሁም የተለያዩ አልባሳት እና ጫማዎች መሆናቸውን ተነግሯል፡፡
እንደ ወ/ሮ ሌንሴ ገለፃ ከዋና መስሪያ ቤት በተጨማሪ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገኙ ሠራተኞችም በአካባቢያቸው ለሚገኙ አቅመ ደካሞች የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ላይ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ለእለት ምግብ የሚሆኑ የተለያዩ ድጋፎችን በማድረግ ሁሉም ከጎናቸው በመሆን ማህበራዊ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባም ወ/ሮ ሌንሴ አሳስበዋል፡፡
ድጋፉን የተረከቡት "የዕኔ እያለሁ ወገኔ አይራብም" በጎ አድራጎት ማህበር መስራች አቶ ኑረዲን ነስሮ ማህበሩ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ጋር አብሮ እንደሚሰራ ገልፀው በጦርነት ምክንያት ከቤት ንብረታቸው
15 538
ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ 45 % ላይ ደርሷል
.........///.......
ኤን ኤስ ኢነርጂ ድረገፅ https://www.nsenergybusiness.com/projects/koysha-hydroelectric-power-project ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ የሚገኘው በኦሮሚያ ክልል ነው በሚል ያወጣው ዘገባ በትክክለኛ መረጃ ያልተመሰረተ ነው።
ድረገፁ በኦሞ ጊቤ ተፋሰስ ላይ እየተገነባ የሚገኘው ግድብ በኦሮሚያ ክልል እንደሚገኝ የዘገበ ቢሆንም የፕሮጀክቱ ትክክለኛ መገኛ በደቡብ ብሔሮችና ብሔረሰቦች ክልላዊ መንግስት በኮንታ ልዩ ወረዳ ኮይሻ ቀበሌ ነው።
ስህተቱ ሆን ተብሎ ያልተፈፀመና በስራ አጋጣሚ ሊከሰት የሚችል መሆኑን በቀናነት በመውሰድ ድረገፁ ዘገባውን እንዲያርም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጠየቀ ሲሆን ይስተካከላል ብሎ ያምናል።
ግድቡ በዓመት በአማካይ 6460 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ የሚያመነጭ ሲሆን በዓመት እስከ አንድ ሚሊየን ቶን የካርበን ልቀት የመቆጣጠር አቅም አለው።
ኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአሁኑ ሰዓት 45 % ደርሷል።
የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ 180 ሜትር ቁመት፣ 250 ሜትር ርዝመትና 41 ሜትር ስፋት ይኖረዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 12 ቀን 2014
15 538
የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" ዘመቻን ተቀላቀሉ
………..//…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" በሚል ርዕሰ ጉዳይ በሃገር ዓቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ህዝባዊ ንቅናቄ በዛሬው ዕለት በይፋ ተቀላቅለዋል፡፡
የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች በሃገራዊ ዘመቻው ላይ በመሳተፋና በደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን በማኖር የኢትዮጵያን የተደበቀ እውነታ ለአለም ዓቀፉ ማህበረሰብ እንዲታወቅ ለማድረግ ኃላፊነታቸውን ተወጥተዋል፡፡
በንቅናቄ ዘመቻው ላይ የተሳተፉት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ቴክኒካል አማካሪ አቶ አንዳርጌ እሸቴ እንደተናገሩት የንቅናቄ ዘመቻው አሸባሪው የህወሓት ቡድን በኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎች እያደረሰ ያለውን ዘግናኝ ጭፍጨፋ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ያግዛል ብለዋል፡፡
"የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" የንቅናቄ ዘመቻ ህብረተሰቡ የሃገሩን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ያለውን ቁርጠኝነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየት እድል እንደሚሰጥም ጠቁመዋል፡፡
እንደ አቶ አንዳርጌ ገለፃ ዘመቻው ኢትዮጵያ ተበዳይ ሆና ሳለ በተቃራኒው በሃገሪቱ ያለውን እውነታ በማዛባት ጫና ለማሳደር የሚፈልጉ የተለያዩ ኃይሎችን በመታገል የሃገሪቱን መፃኢ ዕድል ለመወሰን ፋይዳው የጎላ ነው፡፡
የንቅናቄ መድረኩ በኢትዮጵያ ላይ ያለውን ተጨባጭ መረጃ ለነጩ ቤተ መንግስት ብቻ ሳይሆን መላው ዓለም እውነቱን እንዲገነዘብ ለማድረግ እንደሚረዳም የተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ተናግረዋል፡፡
የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር ከመሯሯጥ ይልቅ የህወሓትን ሴራ በማጋለጥ ከህዝባችን ጎን ሊቆም እንደሚገባም ነው ሠራተኞቹ የጠቆሙት፡፡
የወገኑን ሞትና መፈናቀል የማይፈልግ ኢትዮጵያ የሆነ ሁሉ የንቅናቄ ዘመቻውን በመቀላቀል ኢትዮጵያን የመበተን ፍላጎት ያለው የህወሓት ቡድን በሃገሪቱ ላይ እየፈጸመ ያለውን ተግባር ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስረዳት እንደሚገባ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች አሳስበዋል፡፡
መስከረም 3 ቀን 2014 ዓ.ም በይፋ የተጀመረው "የነጩ ፖስት ጎርፍ ለነጩ ቤተ መንግስት" ሃገራዊ ዘመቻ እስከ መስከረም 15 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 11 ቀን 2014
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
