en
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

Open in Telegram

Addis abeba Ethiopia

Show more
5 204
Subscribers
-11024 hours
-1 9137 days
-2 77030 days
Posts Archive
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇪🇺 በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ 01:00 | አዘርባጃን ከ ኦስትሪያ 03:45 | ቤልጅየም ከ ስዊድን 03:45 | ቦስኒያ ከ ፖርቹጋል 03:45 | ግብራልታር ከ አይርላንድ 0
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇪🇺 በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ 01:00 | አዘርባጃን ከ ኦስትሪያ 03:45 | ቤልጅየም ከ ስዊድን 03:45 | ቦስኒያ ከ ፖርቹጋል 03:45 | ግብራልታር ከ አይርላንድ 03:45 | ግሪክ ከ ኔዘርላንድ 03:45 | አይስላንድ ከ ሌችንስታይን 03:45 | ሉክዘምበርግ ከ ስሎቫኪያ 🤝በአቋም መለኪያ 12:00 | ናይጄሪያ ከ ሞዛምቢክ 01:00 | ሩስያ ከ ኬንያ 01:00 | አልጄሪያ ከ ግብፅ 03:30 | ሴኔጋል ከ ካሜሮን ©ArdiSport

ቱርክ የጦር መርከቧን ወደ መካከለኛው ምስራቅ አንቀሳቀሰች ! ወደ ቦታው የሚንቀሳቀሱት የቱርክ ጦር መርከቦችም እዚያው ወታደራዊ ልምምድ የሚያደርጉ ሲሆን አካባቢውን ይቃኛሉ መረጃም ይሰበስባሉ ተብሏል
ቱርክ የጦር መርከቧን ወደ መካከለኛው ምስራቅ አንቀሳቀሰች ! ወደ ቦታው የሚንቀሳቀሱት የቱርክ ጦር መርከቦችም እዚያው ወታደራዊ ልምምድ የሚያደርጉ ሲሆን አካባቢውን ይቃኛሉ መረጃም ይሰበስባሉ ተብሏል ። አሜሪካ የጦር መርከቦቿን ወደ ቀጠናው ማንቀሳቀሷን ተከትሎ ነው ቱርክ መርከቦቿ ወደዚያው እንዲያመሩ ትእዛዝ የሰጠቺው ። ይህም በአሜሪካና በቱርክ መካከል ያለውን ውጥረት አባብሶታል ። ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን አሜሪካ ጦሯን ወደ ቀጠናው መላኳን በማውገዝ የአሜሪካ ድርጊት አደገኛ ውጤትን ያመጣ እንደሆነ እንጅ ለቀጠናው ሰላም ምንም የሚፈይደው ነገር የለም ብለዋል ። አሜሪካ የቱርክ ጠላቶችን እየደገፈች ነው ያሉት ኤርዶጋን ቱርክ በአስፈላጊው ጊዜ አፀፋውን ትመልሳለች ብለዋል ። የእስራኤል እና ሀማስ ጦርነት ሰፍቶ ከፍተኛ የአለም ቀውስ እንዳይፈጥር ባሰጋበት በአሁኑ ወቅት ቱርክም እየተሳበች መሆኑ ነገሮችን የበለጠ አወሳስቧቸዋል ። መረጃው የቱርኩ Daily sabah ነው ።

የእስራኤል ድርጊት ራስን ከመከላከልም ያለፈ እንደሆነ ቻይና ገለጸች ለፍልስጤም ነጻነት እየተዋጋ መሆኑን የሚገልጸው ሀማስ ከስምንት ቀን በፊት በእስራኤል ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በመካከለኛው ምስ
የእስራኤል ድርጊት ራስን ከመከላከልም ያለፈ እንደሆነ ቻይና ገለጸች ለፍልስጤም ነጻነት እየተዋጋ መሆኑን የሚገልጸው ሀማስ ከስምንት ቀን በፊት በእስራኤል ላይ ጥቃት መክፈቱን ተከትሎ በመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ጦርነት ተቀስቅሷል። እስራኤል ራሴን እየተከላከልኩ ነው በሚል የሀማስ ይዞታዎች ናቸው ባለቻቸው ቦታዎች ላይ የመልሶ ማጥቃት ዘመቻዋን ቀጥላለች።የእስራኤልን ጥቃት ተከትሎ ንጹሀን ዜጎች እና አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች የጥቃቱ ዋና ኢላማ ሆነዋል የሚሉ ትችቶች በተመድ እና የተለያዩ ሀገራት እየተነሳ ይገኛል። የቻይና ውጪ ጉዳይ ሚንስትር ዋንግ ዪ ከሳውዲ አቻቸው ፈይሰል ቢን ፋርሀን አል ሳውዲ ጋር በስልክ ስለ እስራኤል-ሀማስ/ፍልስጤም ጦርነት ዙሪያ መወያየታቸውን ሲጂቲኤን እና አርቲ ዘግበዋል። እንደዘገባው ከሆነ ቻይና የእስራኤል ድርጊት ራስን ከመከላከል ያለፈ እንደሆነ ታምናለች ተብሏል። በመሆኑም እስራኤል በሀማስ ጥቃት ምክንያት መላው ፍልስጤማዊያንን ከመጉዳት እንድትታቀብ ዋንግ ዩ አስጠንቅቀዋል ተብሏል። ሚንስትሩ አክለውም ቻይና የንጹሀንን ጉዳት በጽኑ ታወግዛለች ያሉ ሲሆን ጦርነቱ ቆሞ አለመግባባቱ በድርድር እንዲፈታም ትፈልጋለች ተብሏል። ኢራን በበኩሏ እስራኤል በሀማስ ስም በመላው ፍልስጤማዊያን ላይ እያደረሰች ያለውን የከፋ ጥቃት እንድታቆም አሳስባለች። የኢራን ውጪ ጉዳይ ሚንስትር ሁሴን አሚራብዶልሀሚን ለተመድ የመካከለኛው ምስራቅ አምባሳደር እንዳሉት "እስራኤል በጋዛ ንጹሀን ላይ የምታደርገውን የንጹሀን ግድያ ካላቆመች ኢራን ጦሯን ወደ ጋዛ ልትልክ ትችላለች" ሲሉ ተናግረዋል ተብሏል።በእስራኤል-ፍልስጤም ጦርነት እስካሁን የተገደሉ ዜጎች ቁጥር 5 ሺህ ማለፉ ሲገለጽ የቆሰሉ ሰዎች ደግሞ ከ15 ሺህ በላይ መድረሱ ተገልጿል።   

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት እሁድ ጥቅምት 04 ቀን 2016 ዓ.ም ሠንደቅ ዓላማ እና ኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ የአንድ ሀገር የሉዓላዊነት መገለጫና የህዝቦቿ ማንነት መለያ ምልክት ነው። ሀገራት ከራሳቸው ምክንያታዊ አሥተምህሮ ተነስተው ይገልፀኛል የሚሉትን ቀለማት በመምረጥ የሠንደቅ ዓላማቸውን ትርጉም ይሠይማሉ። ሀገራችን  ኢትዮጵያም ከቀደመው ጊዜ ጀምሮ በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ህብረ ቀለማት ስትሰየም መሃል ላይ ያለው ዓርማ ግን እንደየመንግስታቱ አስተሳሰብና የፖለቲካ ስርዓት መፈራረቅ በየተለያዬ ምሥል ሲወከል ቆይቷል። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ አረንጓዴ፤ ቢጫና ቀይ እንዲሁም በመሃሉ ሙሉ ክብ ሰማያዊ መደብ ላይ በቢጫ የተሰመረ ኮከብ ቀለማት አሉት። የቀለማቱ ስያሜም አረንጓዴው ተስፋ፣ ልምላሜና ሀብት፤ ቢጫው ፣አበባና ፍሬ፤ ቀዩ ፣ መሥዋዕትነትና ጀግንነት ሰማያዊ መደብና ኮከቡ የህዝቦቿና የሀይማኖት እኩልነትን የሚያመለክት ነው። የኢትዮጵያ ሠንደቅ ዓላማ አንዳንዴ መንፈሳዊ ሌላ ጊዜ ደግሞ ፖለቲካዊ ትርጓሜ እየተሠጠው ከ1890ዎቹ ጀምሮ ዛሬ ላይ እንደደረሰ ቢታወቅም እስካሁን የሀገራችን ሠንደቅ ዓላማ የአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ይዘቱን ሳይለቅ መሀል ላይ የሚያርፈውን ዓርማ ብቻ በመቀያየር በስምንት አይነት ምልክቶች እንደተወከለ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ያም ሆነ ይህ ኢትዮጵያዊያን ለሠንደቅ ዓላማቸው ያላቸው ክብር ለየት ያለና ሠፊ ትርጉም የሚሠጠው ነው። ይህም የሆነው ያለምክንያት አይደለም። ቀደምት ኢትዮጵያዊያን ጀግኖች ወደ ጦር ሜዳ ሲተሙ ሠንደቅ ዓላማቸውን ከፍ አድርገው ነው። ተዋግተው አሸንፈው በድል ሲመለሱም ሠንደቅ አላማቸው አይለያቸውም ። ይህ ማለት ለሠንደቅ ዓላማቸው ያላቸውን ክብር ያሳያል። የረጅም ዘመን የጀግንነት ታሪክ ያላቸው ኢትዮጵያዊያን ለሠንደቅ ዓላማ ያላቸው ክብር ለየት ያለ ነው የሚለው እውነታ ሁሉን የሚያሥማማ ቢሆንም በተለይ ደግሞ ለመከላከያ ሠራዊታችን እና ለአትሌቶቻችን ልዩ ትርጉም ሥለመኖሩ በተደጋጋሚ በማይፋቅ የታሪክ መዝገብ ተከትቦ በማህደር ሲሰፍር ተመልክተናል። መከላከያ ሠራዊቱ ከጅምሩ ተልዕኮውን በታማኝነት ለመፈፀም ቃለ መሀላ የሚፈፅመው በሠንደቅ ዓላማው ፊት ነው። ሥለሆነም ሠንደቅ ዓላማው በልቦናው ታትሟል። በዓውደ ውጊያ ፣በሠላም ማሥከበር ተልዕኮ ፣ግዳጅ በሚፈፅምባቸው ቦታዎች፣ ብቻ ሠንደቅ ዓላማው ሠራዊቱ ጋር ሁሌም አብሮት አለ። የሚታገለው የሚዋደቀው መተኪያ የሌላትን ህይወቱን መሥዋዕት የሚያደርገው ለሠንደቅ ዓላማው ክብር ሲል ነውና። ሠንደቅ ዓላማ ከአትሌቶቻችን ጋር ያለው መሥተጋብርም  ከፍ ያለ ነው። የመወዳደሪያ አልባሳታቸው  ኢትዮጵያዊነታቸውን የሚገልፅ ነው።  አትሌቶች አሸንፈው ሰንደቅ ዓላማቸውን ከፍ አድርገው ደሥታቸውን ለመግለፅ በእጅጉ ይጓጓሉ። ይሳካላቸዋልም። እያነቡ በደስታ ስሜት ተውጠው አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሠንደቃቸውን ከፍ ሲያደርጉ በቴሌቪዥን መሥኮት የተመለከተ ሁሉ ውስጡ ላይ የተለዬ ስሜት ይፈጠራል ። እናም የሠንደቅ ዓላማ ቀን መከበሩ ታሪክን ለትውልድ ለማቀበል አሥፈላጊም ክብርም  ነው። በሀገራችን የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል መከበር የጀመረው በአዲሱ ሚሊኒየም መጀመሪያ ላይ ነው ። ሥለሆነም የሰንደቅ ዓላማ ቀን የፊታችን ሰኞ ማለትም ነገ ጥቅምት 05 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚከበር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስታውቋል፡፡ ቀኑ “የሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችንና ለሉዓላዊነታችን ዋስትና ነው” በሚል መሪ ሃሳብ ለ16ኛ ጊዜ ይከበራል፡፡ ክብር ለሠንደቅ ዓላማችን !! በውብሸት ቸኮል

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇪🇹 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ባህር ዳር ከተማ ከ መቻል 12:00 | ሻሸመኔ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ 🇪🇺 በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ 10:00 | ጂዮርጅያ ከ ቆ
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች 🇪🇹 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ባህር ዳር ከተማ ከ መቻል 12:00 | ሻሸመኔ ከተማ ከ ሀዋሳ ከተማ 🇪🇺 በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ 10:00 | ጂዮርጅያ ከ ቆጵሮስ 01:00 | ቼክ ሪፐብሊክ ከ ፋሮ አይስላንድ 01:00 | ስዊዘርላንድ ከ ቤላሩስ 03:45 | ኖርዌይ ከ ስፔን 03:45 | ፖላንድ ከ ሞልዶቫ 03:45 | ሮማኒያ ከ አንዶራ 03:45 | ቱርክ ከ ላቲቪያ 03:45 | ዌልስ ከ ክሮሺያ 🌍 የሴቶች ከ 20 ዓመት በታች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ 09:30 | ኢትዮጵያ ከ ኢኳቶርያል ጊኒ ©Skysport_Ethiopia

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቅዳሜ ጥቅምት 03 ቀን 2016 ዓ.ም የማትላላ እምነታችን የማትዘነጋ ጉዳያችን ሠፊዋን ሀገር ፣በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎቿን የሚያሰባስበው ፣የሚያስተሳሰብ የሚያጋምድ፣ የሚያዋህድ ከእሷ በላይ የለም። የአንድነት ቁልፍ የአብሮነት ምስጢር ተነባ የማታልቅ ምዕራፍ ናት ሠንደቅ ዓላማችን። ለኛ ለኢትዮጵያውያን ሠንደቅ ዓላማች የፅናታችን ምንጭ፣ የጀግንነታችን መሠረት ፣በወል ለማሰለፍ ፣በጋራ ለማለፍ አብሮ ለመግዘፍ የምታስችለን ያስቻለችን ጉልበትና እምነት ናት። ሠንደቅ ዓላማችን ለክብሯ ደም ፈሶላታል ።ሥጋ ተቆርሶላታል።አጥንት ተከስክሶለታል።አካል ጎድሎላታል። ደስታችንም ሆነ በሐዘናችን ከደጃችንም  ከልባችንም የማትጠፋው በበጎ ፍካታችን በክፉ አጥናኛችን ናት። ሠንደቅ ዓላማችን  በማህበረሰባችን የህግ ያህል የምትከበር በእናት ልጅ ሚስት እህት ልክ የምትወደድና የምትፈቀር ናት። በፊት በፊት በባንዲራ አምላክ ማለት ትልቅ አመፀኛን ማስታገሻ ክፉ ለመሥራት የተነሳን መመለሻ እንደነበረ አመዛኙ ህዝቧ ያውቃል። በዓለም አደባባይ ከፍ ስትል ሳናስበው የምናፈሰው እንባ የፍቅራችንን ልክ ያላትን ታሪክ አመላክች ነፃነት ምን ማለት እንደሆነ ምስሉን አእምሯችን ውስጥ ስለሆነች።በማንኛውም ሁኔታ ድል ስናደርግ የጋራችን ሆኖ የሚታየው በታሪክ ተሰንዶ ለትውልድ የሚቆየው እና የሚያንፀው ድሉ በሠንደቅ ዓለማ ሲታጀብ አንደ ቀስተ ዳመና ከላይ ሆኖ ሲነበብ ነው። ሠንደቅ ዓላማችን ለኛ ጌጥ ውበታች ከፍታ ልካችን ፣መጠጊያ ጥላችን፣ ብትሆንም የኛ ብቻ ግን  አይደለችም። የመላው ጥቁር ህዝቦች፣ በግፍ ስር የነበሩ የሰውነት ክብር የተነፈጉ በራስ አቅም አቅም አለኝ ቅኝ ልግዛው ባዩን  ሁሉ ድል ማድረግ የሚፈልጉ ግን ደግሞ ያልቻሉ በእብሪተኞች ከማንነታቸው ልክ የጎደሉ እንዲሁም ጉልበተኛውን በኛ ድል የተበቀሉ ሁሉ ናት። ቁጥራቸው ቀላል ያልሆነ  የአፍሪካ ሀገራት አረንጓዴ ህልማችንን የዕድገት ትልማችንን የራሳቸው አድርገው ተቀብለውታል። ተስፋችንን ተስፋቸው ፍላጎታችን የኛው ነው ብለውታል። በፈይሳ ናኔቻ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ቀዳሚውን ስፍራ ይዟል ! ፖርቹጋላዊው የአል ናስር የፊት መስመር ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ260 ሚልዮን ዶላር የ 2023 የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ እግር ኳስ ተጫዋች መሆኑ ተ
ክርስቲያኖ ሮናልዶ ቀዳሚውን ስፍራ ይዟል ! ፖርቹጋላዊው የአል ናስር የፊት መስመር ተጫዋች ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ260 ሚልዮን ዶላር የ 2023 የአለማችን ከፍተኛ ተከፋይ እግር ኳስ ተጫዋች መሆኑ ተገልጿል። አርጀንቲናዊው የኢንተር ሚያሚ የፊት መስመር ተጨዋች ሊዮኔል ሜሲ በበኩሉ በ135 ሚልዮን ዶላር ተከታዩን ደረጃ መያዝ ችሏል። ከፍተኛ ተካፋይ እግር ኳስ ተጫዋቾች እነማን ናቸው ? 1️⃣ ክርስቲያኖ ሮናልዶ :- 260 ሚልዮን ዶላር 2️⃣ ሊዮኔል ሜሲ :- 135 ሚልዮን ዶላር 3️⃣ ኔይማር :- 112 ሚልዮን ዶላር 4️⃣ ኪሊያን ምባፔ :- 110 ሚልዮን ዶላር 5️⃣ ካሪም ቤንዜማ :- 106 ሚልዮን ዶላር 6️⃣ ኤርሊንግ ሀላንድ :- 58 ሚልዮን ዶላር 7️⃣ ሞሐመድ ሳላህ :- 53 ሚልዮን ዶላር 8️⃣ ሳዲዮ ማኔ :- 52 ሚልዮን ዶላር 9️⃣ ኬቨን ዴብሮይን :- 39 ሚልዮን ዶላር 1️⃣0️⃣ ሀሪ ኬን :- 36 ሚልዮን ዶላር ©tikvahethsport

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ! 🇪🇹 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ሀምበሪቾ ዱራሜ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ 12:00 | ፋሲል ከነማ ከ ኢትዮጵያ መድን 🇪🇺 በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ 01:45 | ኢ
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች ! 🇪🇹 በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ሀምበሪቾ ዱራሜ ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ 12:00 | ፋሲል ከነማ ከ ኢትዮጵያ መድን 🇪🇺 በአውሮፓ ዋንጫ ማጣሪያ 01:45 | ኢስቶኒያ ከ አዘርባጃን 03:45 | ኦስትሪያ ከ ቤልጀም 03:45 | አይስላንድ ከ ሉክዘምበርግ 03:45 | አየርላንድ ከ ግሪክ 03:45 | ሌችንስታይን ከ ቦሲኒያ 03:45 | ኔዘርላንድ ከ ፈረንሳይ 03:45 | ፖርቹጋል ከ ስሎቫኪያ 🌍 በአቋም መለኪያ 01:00 | ሳውድ አረቢያ ከ ናይጄሪያ 03:45 | እንግሊዝ ከ አውስትራሊያ ©ArdiSport

ስድስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የእስራኤል-ሃማስ ጦርነት የተከናወኑ ቁልፍ ክስተቶች • በእስራኤል እና በፍልስጤም ታጣቂዎች መካከል የተከሰተው ግጭት ስድስተኛ ቀኑን አስቆጥሯል፡፡ • የእስራኤል ጦር በዛሬ
ስድስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የእስራኤል-ሃማስ ጦርነት የተከናወኑ ቁልፍ ክስተቶች  • በእስራኤል እና በፍልስጤም ታጣቂዎች መካከል የተከሰተው ግጭት ስድስተኛ ቀኑን አስቆጥሯል፡፡   • የእስራኤል ጦር በዛሬው ዕለት በጋዛ የሃማስ ንብረት በሆኑ ኢላማዎች ላይ ጥቃት እየሰነዘረ መሆኑን ገልጿል።  • ምግብ እና ነዳጅ 2.3 ሚሊዮን ህዝብ መኖሪያ ወደ ሆነችው ጋዛ እንዳይደርስ በመደረጉ ብዙዎች በረሃብ አለንጋ እየተገረፉ ናቸው፡፡ • የሐማስ መገናኛ ብዙሃን እንደዘገበው በጋዛ ያለው ብቸኛ የመብራት ማስተላለፊያ  ስራ ካቆመ በኋላ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል ብሏል። • የእስራኤል ወታደሮችን እና ሲቪሎችን አግተው የያዙት የሃማስ ተዋጊዎች በጋዛ ለሚደረግ እያንዳንዱ ጥቃት ያለማስጠንቀቂያ ምርኮኞችን እንደሚገድሉ ዝተዋል። ሃማስ ዛቻውን እንደፈፀመ የሚጠቁም ነገር የለም። • የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮአቭ ጋላንት ለወታደሮች እንደተናገሩት ጥቃቱን ከአየር ጀምረናል በየብስም እንቀጥላለን በማለት በጋዛ የመሬት ጥቃት እንደሚጀምሩ ዝተዋል፡፡ • እስራኤል የአስቸኳይ ጊዜ የአንድነት መንግስት መስርታለች፡፡ • የፍልስጤም የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በጋዛ እስካሁን የሟቾች ቁጥር ወደ 1ሺህ 200 ከፍ ማለቱን እና 5ሺህ 600 ሰዎች መቁሰላቸውን አስታውቋል። • በእስራኤል በግጭቱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች ቁጥር ወደ 1ሺህ 300 ከፍ ሲል ከ3ሺህ 300 በላይ ሰዎችም መቁሰላቸው ተዘግቧል። • የእስራኤል እና የሐማስ ግጭትን ተከትሎ ህይወታቸው ያለፈ የታይላንድ ዜጎች ቁጥር 21 አድርሶታል። • ጥቃቱን ተከትሎ አለም አቀፍ አየር መንገዶች ወደ ቴል አቪቭ የሚያደርጉትን በመቶዎች የሚቆጠሩ በረራዎች ሰርዘዋል።

ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች! 🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ድሬደዋ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ቡና 12:00 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ሀዲያ ሆሳዕና 🇪🇺በዩሮ 2024 ማጣሪያ 01:00 | ላቲ
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች! 🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ 09:00 | ድሬደዋ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ቡና 12:00 | ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ ሀዲያ ሆሳዕና 🇪🇺በዩሮ 2024 ማጣሪያ 01:00 | ላቲቪያ ከ አርሜኒያ 03:45 | አልባኒያ ከ ቼክ ሪፐብሊክ 03:45 | አንዶራ ከ ኮሶቮ 03:45 | ቤላሩስ ከ ሮማኒያ 03:45 | ክሮሺያ ከ ቱርክ 03:45 | ቆጵሮስ ከ ኖርዌይ 03:45 | ፋሮ አይስላንድ ከ ፖላንድ 03:45 | ስፔን ከ ስኮትላንድ 🌎 በደቡብ አሜሪካ ሀገራት የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ለሊት 05:30 | ኮሎምቢያ ከ ዩራጋይ ለሊት 08:00 | አርጀንቲና ከ ፓራጓይ ለሊት 09:00 | ቺሊ ከ ፔሩ ለሊት 09:30 | ብራዚል ከ ቬንዙዌላ

ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ (Two-Step verification ) ይጠቀማሉ? የተለያዩ የዲጂታል መተግበሪያዎችንና አገልግሎቶችን ስንጠቀም ቀዳሚው ነገር ደኅንነቱን የተጠበቀ መሆኑን ማረጋገጥ ነው። ይህም በሁለት አይነት መልኩ መመልከት ይቻላል። የመጀመሪያው የምንጠቀመው መተግበሪያም ይሁን ድረ-ገጽ ደኅንነቱ የተጠበቀ መሆኑን ማረጋገጥ መቻል ሲሆን ሁለተኛው በራሳችን የምናደርገው የደኅንነት ማረጋገጫ ሂደቶችን ማጠንከር ነው። 💻 የደኅንነት ማረጋገጫ ሂደቶችን እንዴት ማጠንከር ይቻላል? - የምንጠቀመው የይለፍ ቃል (Password) በቀላሉ ተገማች መሆን የለበትም። በተቻለ መጠን ጠንካራ የይለፍ ቃል [ ፊደል፣ ቁጥርና ምልክቶችን ያካተተ] ቢጠቀሙ ይመከራል። - ተጨማሪ የደኅንነት መጠበቂያ ሥርዓቶችን መጠቀም ያስፈልጋል። ይህም ድንገት እንኳን ሰዎች የይለፍ ቃላችንን (Password ) ቢያገኙት በዚህኛው በሁለተኛው የደኅንነት መጠበቂያ መያዝ እንችላለን። ይህም በአብዛኛው ጊዜ ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ (Two-Step verification ) በመባል ይታወቃል። - ስልክ ቁጥራችን በዚህ ሰዓት አንዱ ትልቁ የደኅንነት ማረጋገጫ ብቻ ሳይሆን የሂሳብ አካውንት ቁጥራችን ጭምር ነው። በመሆኑም በመጀመሪያ ደረጃ የምንጠቀመው ሲም ካርድ በስማችን መውጣቱን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፤ ይህ ካልሆነም ሲም ካርዱ በእጃችን እያለ በስማችን ማዞር ይጠበቅብናል። በአንጻሩ በስማችን ተከፍቶ የነበረ ሲም ካርድ ካለ አሁን የሚገለገለው ግለሰብ ስሙን ወደ ራሱ እንዲያዞርም ማድረግ ይጠበቃል። - የበመልዕክት ሚላኩልንን የማረጋገጫ ቁጥሮች (OTP) በምንም መልኩ ለሌሎች አሳልፈን መስጠት አይጠበቅብንም። በተመሳሳይ የትኛውም አካል የሚስጢር ቁጥራችንን ቢጠይቀን መናገርም ሆነ መላክ አይኖርብንም። 💻 ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ (Two-Step verification ) ባልጠቀምስ? - የይለፍ ቃል (Password) የሚያገኝ/ የሚያቅ ሰው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ግል አካውንቶ ይገባል። - ተሳስተው በተለያዩ መንገዶች የሚላኩ ሊንኮችን ቢከፍቱና ስልክና የይለፍ ቃል እንዲያስገቡ ተጠይቀው ቢያስገቡ ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ የማይጠቀሙ ከሆነ የግል አካውንቶ የሌሎች መጠቀሚያ ይሆናል። 💻 ቴሌግራም ላይ ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ (Two-Step verification ) እንዴት መጠቀም እችላለሁ? በቴሌግራሞት ላይ Setting የሚለው ላይ ገብተው Privecy and Security በመጫን  Two-Step verification የሚለውን ON በማድረግ የይለፍ ቃል መፍጠር እንዲሁም የይለፍ ቃሉን ቢረሱት መልሰው የሚያገኙበትን ኢሜይል አስገብተው የደኅንነቶን ደረጃ ከፍ ማድረግ ይችላሉ። [ ሙሉ ሂደቱ ከላይ በምስሉ ተያይዟል።] 🙏

የአፍሪካ አገራት በእስራኤል እና ሐማስ ግጭት የተለያየ አቋም ይዘዋል! የአፍሪካ መሪዎች የፍልስጥኤም ታጣቂ ቡድን ሐማስ በሰነዘረው ድንገተኛ ጥቃት ምክንያት የተቀሰቀሰውን ግጭት እንዲያቆሙ ሁሉንም ተፋላሚ ወገኖች ጠይቀዋል።የአገራቱ አቋም ግን ሙሉ ለሙሉ ተመሳሳይ አልነበረም። ዛምቢያ፣ ኬንያ እና ጋና ሐማስን በግልጽ አውግዘዋል።እስራኤልን እንደሚደግፉም አስታውቀዋል።ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ደቡብ አፍሪካ ለፍልስጥኤማውያን ያላቸውን ድጋፍ በይፋ ገልጸዋል።እስራኤል ባለፉት አስር ዓመታት በአህጉሪቱ ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ተሳትፎ አሳድጋለች።በርካታ የአፍሪካ አገራትም ኤምባሲዎቻቸውን ከቴል አቪቭ ወደ እየሩሳሌም ለማዛወር አቅደዋል። ይህ ግን እስራኤል በዚህ ግጭት ከአፍሪካ የምትጠብቀውን ድጋፍ ሙሉ በሙሉ አላስገኘላትም። የአፍሪካ ህብረት በፈረንሳይኛ እና በእንግሊዘኛ መግለጫ አውጥቷል። የግጭቶቹ መነሻ "የፍልስጥኤም ህዝብ በተለይም ነፃ እና ሉዓላዊ መንግስት የመመስረት መሠረታዊ መብቶች መነፈግ" መሆኑን ገልጿል። “ሊቀመንበሩ ሁለቱ ወገኖች ወታደራዊ ግጭቶችን እንዲያቆሙ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ድርድር ጠረጴዛው እንዲመለሱ ጠይቀዋል። የፍልስጥኤምን ህዝብ እና የእስራኤላውያንን ጥቅም ለማስጠበቅ የሁለት መንግስታትን መርህ ተግባራዊ እንዲደረግም በአስቸኳይ ጥሪ አቅርበዋል” ሲሉ የህብረቱ ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ አክለዋል። እስራኤል ቀደም ሲል በአፍሪካ ህብረት ስብሰባዎች ላይ በታዛቢነት ለመሳተፍ የነበራት ፍላጎት በአንዳንድ አገራት ዘንድ ተቃውሞ ገጥሞታል።የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ተፋላሚ ወገኖች ወደ "ሁለት አገራት መፍትሔ" እንዲመለሱ ጥሪ አቅርበዋል። በተከሰተው ግጭት ማዘናቸውን በመግለጫቸውም አስታውቀዋል። የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ለማሻሻል በሚደረገው ጥረትም ሙሴቬኒ የእስራኤሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ በአውሮፓውያኑ 2016 እና 2020 አቀባበል አድርገውላቸዋል። የኡጋንዳው ፕሬዝዳንት እአአ በ2020 በእስራኤል እና በሱዳን መካከል ያለውን ግንኙነት ለማሻሻል ሠርተዋል። ድጋሚ የተከሰተውን ግጭት ተከትሎ ግን የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለፍልስጥኤማውያን ድጋፍ ሰጥተዋል። "በአሁኑ ጊዜ በፍልስጥኤም እየተከሰተ ያለውን አደገኛ እና አሳሳቢ ሁኔታ ሱዳን በቅርበት እየተከታተለችው ነው። የፍልስጥኤም ህዝቦች ነፃ አገር እና ህጋዊ መብት እንዲኖራቸው ሱዳን ድጋፏን በድጋሚ ትገልጻለች።ዓለም አቀፍ የግጭት አፈታቶች እንዲተገበሩ እና ንፁሃን ዜጎችን ከጥቃት እንዲጠብቁ ትጠይቃለች" ሲል በመንግስታዊው የዜና ወኪል ሱና በፌስቡክ ገጹ መግለጫውን አስነብቧል። ደቡብ አፍሪካ "አፋጣኝ የተኩስ አቁም" እንዲደረስ ጥሪ አቅርባለች።የአገሪቱ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ቢሮ "ቀጠናው በተባበሩት መንግስታት የሁለት መንግሥታት መፍትሔ እና በእስራኤል እና በፍልስጥኤም መካከል ፍትሐዊ እና ሁሉን አቀፍ ሠላም እንዲሰፍን ቀደም ሲል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች የሚተገብር የሠላም ሂደት ይፈልጋል" ሲል አስታውቋል። ናይጄሪያ በበኩሏ “አሁን ያለው የተባባሰው የብጥብጥ እና የበቀል አዙሪት በህዝብ ላይ የማያቋርጥ የስቃይ አዙሪት እንዲኖር ያደርጋል” በማለት አስጠንቅቃለች።የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ “የጉዳቱ መጠን እየጨመረ በመምጣቱ ተፋላሚዎቹ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል። "ኬንያ ለዓለም አቀፍ ሰላምና ደህንነት ከፍተኛ ስጋት ለሆነ ሽብርተኝነት ምንም አይነት ምክንያት ሊኖር እንደማይገባ አጥብቃ ታምናለች። ወንጀለኛው ማንም ይሁን ማን፤ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ሁሉም የሽብርተኝነት፣ የአመጽና የጽንፈኝነት ድርጊቶች አስጸያፊ፣ ህገወጥ እና ኢፍትሐዊ ነው" ሲሉ ኤክስ ላይ ጽፈዋል።የዛምቢያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስታንሊ ካኩቦ የሐማስን ጥቃት በማውገዝ እስራኤልን ደግፈዋል። "በሚያሳዝን ሁኔታ ለሰው ህይወት መጥፋት ምክንያት በሆነው እና በእስራኤል ላይ በቅርቡ የተፈጸመውን ጥቃት አጥብቀን እናወግዛለን። ሁሉንም ጥቃት እና የጥቃት ድርጊቶች በማያሻማ ሁኔታ እናወግዛለን። ዓለም አቀፍ ግጭቶችን ለመፍታት ዲፕሎማሲያዊ መንገዶችን መከተል አስፈላጊ መሆኑንም አበክረን እናሳውቃለን" ብለዋል። Via BBC

#Result የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ማክሰኞ በ29/01/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ ብሏል። ተፈታኞች የሚከተሉትን 3 አማራጭ አድራሻዎችን #ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ ሲል ገልጿል።      👉 በዌብ ሳይት፡- eaes.et 👉 በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡- 6284 👉 ቴሌግራም አድራሻ፡- @eaesbot አገልግሎቱ ከላይ ከተገለጹት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌላ የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን አሳውቋል። ተማሪዎች በማመሳሰል " ውጤት እንገልጻለን " ከሚሉ ከማንኛውም አጭበርባሪዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት ተላልፏል። በተጨማሪ ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ምንም ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑን አስገንዝቧል። እንዴት ውጤት ልመልከት ? በዌብ ሳይት ለማየት ፦ 1. eaes.et ብለው ብሮውዘር ላይ ይጻፉ 2. በመቀጠልም በሚመጣው ገጽ ላይ የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) እና የመጀመሪያ ስም ይጻፉ 3. Check Result የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማግኘት ይችላሉ። በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ፦ 1. 6284 የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ብቻ ጽፎ አንዴ ብቻ በመላክ መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ። በቴሌግራም ቦት ፦ 1. @eaesbot ይፈልጉ 2. የሚመጡ አማራጮችን በመከተል የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ያስገቡ በመቀጠልም መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኞ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ በቀጠናው ተገኝተው የሠራዊቱን የግዳጅ አፈፃፀም ጎበኙ፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል
+4
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሰኞ መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ.ም የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ በቀጠናው ተገኝተው የሠራዊቱን የግዳጅ አፈፃፀም ጎበኙ፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ በሰሜን ሸዋ ዞን በግዳጅ ላይ የሚገኙትን  የሠራዊት አባላት የግዳጅ አፈፃፀም እና ቀጠናውን ጎብኝተዋል፡፡ አዛዡ የክፍሉ የሠራዊት አባላት ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለህዝቦች ሰላም በፍፁም ጀግንነት የፈፀሟቸውን ግዳጆች በማወደስ ለህዝባችሁና ለሀገራችሁ ሰላምና ደህንነት ፅንፈኛ ኃይሉን ተጋፍጣችሁ ለፈፀማችሁት ገድል ክብርና ምስጋና ይገባችኋል በማለት ሠራዊቱን አበረታትተዋል፡፡ ሌተናል ጄኔራል ሹማ የክፍሉ አባላት የኢትዮጵያን አንድነት ከነ ህዝቦቿ ለማስቀጠል በፅናት ቆሞ በመፋለም ለትውልድ የሚሻገር ታላላቅ ድሎች ማስመዝገባቸውን አስታውሰው ይህ ተግባርም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የሠራዊቱ አባላት በገለፁት መሰረት ዛሬም ቢሆን የሀገራቸውንና የህዝባቸውን ክብር ለተቀጣሪ ባንዳዎች አሳልፈው እንዳማይሰጡ በመናገር ከአባቶቻቸው የተቀበሏትን አንድነቷ የተጠበቀች ኢትዮጵያን ከነ ህዝቦቿ ለትውልድ እንደሚያሸጋግሩ አረጋግጠዋል፡፡ ከፅንፈኛ ሃይሉ ዲሽቃን ጨምሮ በርካታ መሳሪያዎች የተማረኩ መሆኑ ለዕዙ አዛዥ ተገልፆላቸዋል።