የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
Open in Telegram
5 204
Subscribers
-11024 hours
-1 9137 days
-2 77030 days
Posts Archive
በእስራኤል ጦርና በፍልስጤማውያን ተዋጊዎች መካከል በ7 ግንባሮች ውጊያ እየተደረገ ነው
ሃማስ ባሳለፍነው ቅዳሜ በእስራኤል ላይ ያለተጠበቀ እና ድንገተኛ ጥቃት መሰንዘረሩን ተከትሎ በእስራኤልና በፍልስጤም መካከል የተጀመረው ጦርነት ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል።
በሃማስ ጥቃት እና በእስራዔል የአየር ድብደባ ከሁለቱም ወገኖች የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ11 ሺህ ማለፉ ተነግሯል።
የእስራኤል መከላከከያ ኃይል ዛሬ ባወጣው መረጃ መሰረት በሃማስ ጥቃት የሞቱ እስራኤላውኝ ቁጥር 700 የደረሰ ሲሆን፤ 2 ሸህ 150 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል።
የፍልስጤም ባለስልጣናት በሰጡት መረጃ ደግሞ በእስራኤል የአየር ድብደባ የሞቱ ፍልስጤማውያን ቁጥር 413 መድረሱን እና ከ2 ሺ 300 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን አስታውቀዋል።
ሃማስ ወደ እስራኤል የሚተኩሳቸውን ሮኬቶች ከ36 ሰዓታት በኋላ እንደ አዲስ የጀመረ ሲሆን፤ እስራኤልም በጋዛ የምትፈጽመውን የአየር ድብደባ ቀጥላበታለች።አሁን ላይ ጦርነቱ በ7 ግንባሮች ቀጥሎ የተካሄደ ነው የተባለ ሲሆን፤ 100 ሺህ የእስራኤል ወታደሮች በምድረ ላይ ሊደረግ ለሚችል ዘመቻ በተጠንቀቅ ላይ ናቸው ተብሏል።
እስራኤል ጦር ሰድሮት ፖሊስ ጣቢያን መልሶ መቆጣጠሩን ያስታወቀ ሲሆን፤ አሁንም ቢሆን የጋዛ ግንብን ጨምሮ በርካታ ስፍራዎች በፍልስጤመውያን ተዋጊዎች እጅ ይገኛል።እስራኤል በጋዛ የምትፈጽመውን የአየር ድብደባ የቀጠለች ሲሆን፤ በጋዛ የሚገኙ መኖሪያ ቤቶች በአየር ድብደባው መውደማቸው ተነሯል።የሚባኖሱ ሄዝቦላህ በሼባ ፋርምስ የሚገኝ የእስራኤል ጦር ካምፕ ላይ ለደረሰው ጥቃት ኃፊነቱን እንደሚወስድ አስታውቋል። እስራኤልም ለሄዝቦላህ ጥቃት መልሽ መስጠቷን አስታውቃለች።
የእስራኤል እና ፍልስጥኤም ግጭት ተከትሎ ሀገራት መግለጫን አውጥተዋል
🇺🇸የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ሃገራቸው ለእስራኤል የምታደርገው ድጋፍ ጠንካራ እና የማይናወጥ ነው ብለዋል። ዩናይትድ ስቴትስ መርከቦችን እና አውሮፕላኖችን ወደ አካባቢው በማሰማራት ተጨማሪ የጦር መሳሪያ ወደ እስራኤል እንደምትልክ አስታውቀዋል።
🇬🇧የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪሺ ሱናክ ለቤንጃሚን ኔታንያሁ “ጽኑ ድጋፍ” እንዳላቸው ገልፀዋል። "እኛ የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን። ሽብርተኝነት አያሸንፍም" ሲሉ ተናግረዋል። የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ ኢራን የፍልስጤማውያንን ራስን የመከላከል መብት እንደምትደግፍ ገልጸው እስራኤል ባለፉት ዓመታት አካባቢውን አደጋ ላይ በመጣል ተጠያቂ መሆን አለባት ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ሃማስ በኢራን እንደሚደገፍ ተመላክቷል።
🇱🇧ሄዝቦላህ የተባለው ኃያል የታጠቀ ቡድን ሲሆን በኢራን ይደገፋል።እሁድ ዕለት ከሊባኖስ በመሆን ከእስራኤል ጋር መድፍ እና የሮኬት ተኩስ ልውውጥ አድርጓል። ይህው የተኩስ ልውውጥ በእስራኤል እና በተቃዋሚ ሀገራት መካከል ሰፊ ግጭት እንዳይፈጠር ስጋት ፈጥሯል።
🇨🇳ቻይና በበኩሏ ሁለቱ ወገኖች “ተኩስ በአስቸኳይ እንዲያቆሙ” ጥሪ አቅርባለች። ቻይና የፍልስጤም ነጻ መንግስት መመስረትን ጨምሮ "የሁለት መንግስት መፍትሄ" ሀሳብን በድጋሚ አቅርባለች።
🇷🇺 የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር "አፋጣኝ የተኩስ አቁም" እና "ሁሉን አቀፍ፣ ዘላቂ እና ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው ሰላም" ለማምጣት ድርድር እንዲደረግ ጠይቋል።
ምንጭ፦ ዳጉ ጆርናል
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🏴 የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
10:00 | ብራይተን ከ ሊቨርፑል
10:00 | ዌስትሃም ከ ኒውካስትል
10:00 | ወልቭስ ከ አስቶን ቪላ
12:30 | አርሰናል ከ ማንችስተር ሲቲ
🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
09:00 | ቅዱስ ጊዮርጊስ ከ ወልቂጤ ከነማ
12:00 | ኢትዮጵያ መድን ከ ባህር ዳር ከነማ
🇪🇸በስፔን ላሊጋ
09:00 | ቪላሪያል ከ ላስ ፓልማስ
11:15 | አትሌቲኮ ማድሪድ ከ ሪያል ሶሴዳድ
01:30 | አላቬስ ከ ሪያል ቤቲስ
01:30 | ሴልታ ቪጎ ከ ሄታፌ
04:00 | ግራናዳ ከ ባርሴሎና
🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1
08:00 | ማርሴይ ከ ሌ ሃቨሬ
10:00 | ብረስት ከ ቱሉስ
10:00 | ሊዮን ከ ሎሬንት
10:00 | ሞንፔሌ ከ ክሌርሞንት
12:05 | ሌንስ ከ ሊል
03:45 | ሬንስ ከ ፒኤስጂ
🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ
10:30 | ባየር ሊቨርኩሰን ከ ኮለን
12:30 | ባየር ሙኒክ ከ ፍራይበርግ
02:30 | ፍራንክፈርት ከ ሃይደንሃይም
🇮🇹በጣልያን ሴሪ ኤ
07:30 | ሞንዛ ከ ሳለረንቲና
10:00 | ፍሮሲኖን ከ ቬሮና
10:00 | ላዚዮ ከ አታላንታ
01:00 | ካግላሪ ከ ሮማ
03:45 | ናፖሊ ከ ፊዮረንቲና
©ArdiSport
ሃማስ ከጋዛ ሰርጥ በተለያዩ አቅጣጫዎች እስራኤል ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት የከፈተ ሲሆን፤ እስራኤል ደግሞ በአጸፋው በርካታ የአየር ድብደባዎችን እየፈጸመች ትገኛለች።
የፍልስጤም ታጣቂ ቡድን ሃማስ “ ዘመቻ አል አቅሳ ጎርፍ” የሚል መጠሪያ የተሰጠው ጥቃት በእስራኤል ላይ የከፈተ ሲሆን፤ ይህም ከፈረንጆቹ 2021 ወዲህ በግዙፍነቱ የመጀመሪያው ነው።ሃማስ ወደ እስራኤል 5 ሺህ ሮኬቶችን መተኮሱን የገለፀ ሲሆን፤ እስራኤልም የሃማስ ቡድን ታጣቂዎች ድንበር ጥሰው መግባታቸውን አረጋግጣለች።
ሃማስ ሮኬቶቹን ከንጋቱ 12፤30 ጀምሮ መተኮስ የጀመሩ ሲሆን፤ ሃማስ ሮኬቶቹም ወደ ሩቅ ምስራቅ ቴል አቪቭ ተኩሷል፤ በደቡብ በኩል ደግሞ ታጣቂዎቹን ወደ እስራኤል አስገብቷል።
የእስራኤል አየር ኃይልም በርካታ የጦር ጄቶችን በማሰማራት በጋዛ ሰርጥ ውስጥ በሚገኙ የሃማስ ኢላማዎችን ሲደበድብ ውሏል።
የሃማስ መሪ መሐመድ ዴፍ "ለመጨረሻ ጊዜ በቃን ብለን ተነስተናል" ሲል ተናግሯል።
የሃማስ ቃል አቀባይካሊድ ካዶሚ በበኩሉ፤ ቡድኑ በእስራኤል ላይ የጀመረው ወታደራዊ ዘመቻ ባለፉት አስርት ዓመታት ፍልስጤማውያን ላይ ለተፈጸመው ግፍ ምላሽ ነው ብሏል።
“ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ በጋዛ የሚፈጸመውን ግፍ እንዲያስቆም እንፈልጋለን” ያለው ቃል አቀባዩ፤ “አል ኣቀሳን ጨምሮ ቅዱሳን ስፍራዎቻችን ለዘመቻው መጀመር መነሻ ነው” ብሏል።መሳሪያ የታጠቀ ማንኛውም ፍልስጤማዊ ጦርነቱን እንዲቀላቀል ጥሪ ያቀረበው ሃማስ፤ የዌስት ባንክ ታጣቂዎች፣ የአረብ ማህበረሰብ እና ሙስሊም ሀገራት ዘመቻውን እንዲቀላቀሉ በቴሌግራም በለቀቀው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል።
የእስራኤል ጦር ጋዛ አቅራቢያ የሚኖሩ እስራኤላውያን ከቤታቸው እንዳይወጡ እና ምሽግ ውስጥ እንዲሸሸጉ አሳስቧል።
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ሀገራቸው ጦርነት ውስጥ መሆኗን ጠቅሰው፤ ጦርነቱን ግን ታሸንፋለች ብለዋል።የእስራኤል መከላከያ ሚንስትር ዮአቭ ጋላንት ሃማስ “ከባድ ስህተት ሰርቷል” ሲሉ “የእስራኤል መንግስት በዚህ ጦርነት እንደሚያሸንፍ አስታውቀዋል።
ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🏴በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
10:00 | ኖቲንግሃም ከ ብሬንትፎርድ
🇪🇹በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ(ዛሬ ይጀመራል)
09:00 | አዳማ ከተማ ከ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
12:00 | ሲዳማ ቡና ከ ኢትዮጵያ ቡና
🇪🇸በስፔን ላሊጋ
09:00 | አልሜሪያ ከ ግራናዳ
11:15 | አላቬስ ከ ኦሳሱና
04:00 | አትሌቲኮ ማድሪድ ከ ካዲዝ
04:00 | ሪያል ቤቲስ ከ ቫሌንሲያ
🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ
10:30 | ዳርምስታድት ከ ቨርደር ብሬመን
12:30 | ፍራይበርግ ከ ኦግስበርግ
🇮🇹በጣልያን ሴሪያ
08:30 | ቦሎኛ ከ ኢምፖሊ
10:00 | ዩድኒዜ ከ ጄሮና
01:00 | አትላንታ ከ ጁቨንቱስ
03:45 | ሮማ ከ ፍሮሲኖን
🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1
08:00 | ሬምስ ከ ሊዮን
10:00 | ሌ ሃቭሬ ከ ሊል
10:00 | ኒስ ከ ብረስት
10:00 | ቱሉስ ከ ሜትዝ
12:05 | ሎሬንት ከ ሞንፔሌ
0345 | ሬንስ ከ ናንትስ
ትላንት የተድረጉ ጨዋታዎች
🏴በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
አስቶን ቪላ 6-1 ብራይተን
በርንማውዝ 0-4 አርሰናል
ኤቨርተን 1-2 ሉተን
ማን ዩናይትድ 0-1 ክሪስታል ፓላስ
ኒውካስትል 2-0 በርንሌይ
ዌስትሃም 2-0 ሼፊልድ
ወልቭስ 2-1 ማን ሲቲ
ቶተንሀም 2-1 ሊቨርፑል
🇪🇸በስፔን ላሊጋ
ሄታፈ 0-0 ቪያሪያል
ራዮ ቫልካኖ 2-2 ማሎርካ
ጅሮና 0-3 ሪያል ማድሪድ
ሪያል ሶሴዳድ 3-0 አትሌቲኮ ቢልባዎ
🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ
ቦቹም 1-3 ሞኝቼግላድባህ
ኮለን 0-2 ስቱትጋርት
ሃይደንሃይም 1-0 ዩኒየን በርሊን
ሜንዝ 0-3 ባየር ሌቨርኩሰን
ዎልፍስበርግ 2-0 ፍራንክፈርት
RB ሌብዚንግ 2-2 ባየር ሙኒክ
🇮🇹በጣልያን ሴሪያ
ሊቼ 0-1 ናፖሊ
ኤሲ ሚላን 2-0 ላዚዮ
ሳለርንትና 0-4 ኢንተር ሚላን
🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ 1
ክሎምነት 0-0 ፒኤስጂ
ሞናኮ 3-2 ማርሴ
የመስቀል ደመራ እና የመውሊድ በዓላት በሰላም መጠናቀቃቸው የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል አስታወቀ
በዛሬው ዕለት በመላው ሀገራችን የተከበሩት የመስቀል ደመራ እና የመውሊድ በዓላት በሰላም መጠናቀቃቸውን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ያስታውቃል።
የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ-ኃይል ቅደመ ዝግጅት በማድረግ በዕቅድ እየተመራ ተጋላጭ ቦታዎችንና አካባቢዎችን ለይቶ በቅድመ መከላከል ሥራው ላይ በርካታ የሰው ኃይል በማሰማራት እና ለሥራው አጋዥ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ከህዝቡ፣ ከሁለቱ የእምነት ተቋማት የሃይማኖት አባቶች፣ ከበዓላቱ አዘጋጅ ኮሚቴዎችና ከወጣቶች ጋር ተባብሮ በመስራቱ በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች ሁለቱም በዓላት በሰላም መጠናቀቃቸውን ያስታውቃል፡፡
በዓላቱ በሰላም እንዲጠናቀቁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረገው ህዝባችን እንዲሁም የሀይማኖት አባቶች፣ ለበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴዎች እና ለወጣቶች የጋራ ግብረ ኃይሉ ላቅ ያለ ምስጋና ያቀርባል።
የፀጥታና ደህንነት ኃይሎችም የተሰጣቸውን ግዳጅ በሚገባ ስለተወጡ የጋራ ግብረ-ኃይሉ ላቅ ያለ ምስጋና አቅርቧል፡፡
ህብረተሰቡ እንደተለመደው የአካባቢውን ሰላም በመጠበቅ እያሳየ ያለውን ቀና ትብብር ወደፊት በሚከበሩ ሌሎች ህዝባዊና ሐይማኖታዊ በዓላት ላይም አጠናክሮ እንዲቀጥል የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ- ኃይሉ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
ግብጽ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን ልትገነባ ትችላለች የሚል ስጋቷን ገለፀች
🌹🌹🌹🌷🌷🌷
በግብጽ በተቃዋሚ ፓርቲነት የሚንቀሳቀሰው ፍትህ ፓርቲ "ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ አዳዲስ ግድቦችን ልትገነባ እንደምትችል ጠርጥሬያለሁ" በማለት የግብዕ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ምላሽ እንዲሰጥ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና መስኖ ሚኒስቴርን በድብዳቤ ጠይቋል።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼
በዚህም ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ሌሎች ግድቦችንም የመገንባት ዕቅድ አላት ተብሎ ስለሚሰራጨው መረጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ያላቸው አመለካከት ምን እንደሆነ ተጠይቀዋል።
🌼🌼🌼🌼🌼
የግብጽ የፓርላማ አባል እና የፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር አብደል ሞኒም ኢማም ከዚህ ባለፈም ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ በተመለከተ የግብጽን ጥያቄዎች ችላ በማለቷ የግብጽን የፖለቲካ አማራጮ በሚመለከት ለውጭ ጉዳይ እና ለመስኖ ሚኒስቴር በርከት ያሉ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የግብጽ መንግሥት የኢትዮጵያን የህዳሴው ግድብ የውሃ ሙሌት በመግለጫ ውግዘት ብቻ እያለፈ ቀጣዩን ድርድር መጠበቁን ኮንነው፤ "ኢትዮጵያ የግብጽን ጥያቄዎች ችላ ብላ ከቀጠለች የግብጽ የፖለቲካ አማራጭ ምንድን ነው።" ሲሉ መጠየቃቸውን ኢጂብት ኢንዲፐንደንት ዘግቧል።
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
ግብጽ ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ተጨማሪ ግድቦችን ልትገነባ ትችላለች የሚል ስጋቷን ገለጸች!!
በግብጽ በተቃዋሚ ፓርቲነት የሚንቀሳቀሰው ፍትህ ፓርቲ "ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ አዳዲስ ግድቦችን ልትገነባ እንደምትችል ጠርጥሬያለሁ" በማለት የግብዕ መንግሥት በዚህ ጉዳይ ምላሽ እንዲሰጥ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና መስኖ ሚኒስቴርን በድብዳቤ ጠይቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ በዓባይ ወንዝ ላይ ሌሎች ግድቦችንም የመገንባት ዕቅድ አላት ተብሎ ስለሚሰራጨው መረጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ያላቸው አመለካከት ምን እንደሆነ ተጠይቀዋል።
የግብጽ የፓርላማ አባል እና የፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር አብደል ሞኒም ኢማም ከዚህ ባለፈም ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ በተመለከተ የግብጽን ጥያቄዎች ችላ በማለቷ የግብጽን የፖለቲካ አማራጮ በሚመለከት ለውጭ ጉዳይ እና ለመስኖ ሚኒስቴር በርከት ያሉ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
የግብጽ መንግሥት የኢትዮጵያን የህዳሴው ግድብ የውሃ ሙሌት በመግለጫ ውግዘት ብቻ እያለፈ ቀጣዩን ድርድር መጠበቁን ኮንነው፤ "ኢትዮጵያ የግብጽን ጥያቄዎች ችላ ብላ ከቀጠለች የግብጽ የፖለቲካ አማራጭ ምንድን ነው።" ሲሉ መጠየቃቸውን ኢጂብት ኢንዲፐንደንት ዘግቧል።
በተጨማሪም ግብጽ በቀጣዩ የኢትዮጵያ፣ ግብጽና ሱዳን የሦስትዮሽ ድርድር የተሳካ እንዲሆን ምን ዓይነት ዕቅድና ዝግጅት እንዳላት ለ2ቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በላኩት ጥያቄ አካተዋል። የፓርላማ አባሉ አክለውም፤ የግብጽ መንግሥት የግድቡን ጉዳይ ለመደገፍ የወሰዳቸው ዓለም አቀፍ ዘዴዎች ምን እንደሆኑና ተጽዕኗቸም እንዴት እንደሚለካ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጥያቄ አቅርበዋል።
በዓባይ ወንዝ ላይ የሚገነባውና የአፍሪካ ታላቁ የኃይል ማመንጫ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ 93% መጠናቀቁ ተመላክቷል።
#Earthquake ትግራይ ድረስ ንዝረቱ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ።
ከአንድ ሰዓት በፊት በሬክተር ስኬል 5.0 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ከኤርትራ፣ አስመራ በ59 ኪሎሜትር ርቀት መከሰቱን የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ ሪፖርት አድርጓል።
የመሬት መንቀጥቀጡን የሚመለከት ዝርዝር መረጃዎች በሰዓታት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የመሬት መንቀጥቀጡን በተመለከተ አንድ ኤርትራዊ ፤ " ከደቂቃዎች በፊት እናቴን በስልክ እያነጋገርኳት ነበር (አዲ ቀይኺ) በድንገት ግን ቤት የነበሩ ህፃናት ሲጯጯሁ ሰማሁ ፤ በሁኔታው ተደናግጬ እናቴን ምን እንደተፈጠረ ጠየኳት የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ እንደሆነ ነገረችኝ " ብሏል።
በሌላ በኩል ፤ በትግራይ ክልል መቐለ የሚገኙ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ምሽት 2:52 ደቂቃ ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ እንደተሰማቸው ጠቁመዋል።
በሽረ ፣ ዓዲግራት ፣ ኣክሱም እንዲሁም ዓድዋና ሌሎች አካባቢዎች የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት የተሰማቸው እንዳሉ የትግራይ ቤተሰቦቻችን ገልጻዋል።
ሃምሌ 25 /2015 ዓ.ም ከምሽቱ 2:15 ገደማ ዋና መነሻው (Epicenter) ከምፅዋ ወደብ በ43 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሆነ ከባድና 5.6 ሬክተር ስኬል የሚለካ የመሬት መቀጥቀጥ ተከስቶ ፤ በእንዳስላሰ ሽረ ፣ ሰለኽለኻ ፣ አክሱም ፣ ዓድዋ ፣ ዓዲግራት ፣ ውቕሮ ፣ ሓውዜንና አከባቢው ፣ ኣፅቢ ፣ መቐለና ሌሎች አከባቢዎች ላይ የመሬት መንቀጥቀጡ እንደተሰማ አይዘነጋም።
Via ቲክቫህ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት መስከረም 01 ቀን 2016 ዓ.ም
እንኳን አደረሰህ
በአውደዓመት ምድር....አንተ ስለ ሀገር፣
ስለ ህዝብ ሰላም.........ተኝተህ ማታድር፣
እንቅልፍ አልባው ወቴ...ስለ ኢትዮጵያ ፍቅር፣
የቀን ጸሃይ ሀሩር...........የሌት ብርድና ቁር፣
አቀበት ቁልቁለት.........የጫካ እሾህ ቆንጥር፣
የፈተናን መዓት............በድል ምትሻገር፣
በበዓልም ዕለት...........ወጥተህ የምታድር፣
እንኳን አደረሰህ...........ጀግናው የኛ ወታደር።
የዶሮ ወጥ መዓዛ........የበዓል ዕለት ቃና፣
የአበባየሆሽ...............ወግ ባህል ወዘና፣
የልጆች ሳቅ ሆታ.........የዘመድ አዝማዱ፣
ተሰባስቦ ደስታ............የዓመታት ልማዱ፣
ናፍቆትህን ውጠህ.......ከሞት ጋር ተፋጠህ፣
በቀበሮ ጉድጓድ...........ቆርጠህና ጸንተህ፣
ስለእኛ ኗሪው..............እንኳን አደረሰህ።
እናከብርሃለን..............ከልብ ከውስጣችን፣
ከፈጣሪ በታች.............ዋስ የሰላማችን፣
የኢትዮጵያችን ጋሻ. ......ጽኑ መከታችን፣
መልካም አዲስ ዓመት...መከላከያችን።
በአሥቻለው ሌንጫ
በራሳቸው ቀን አቆጣጠር አዲስ ዓመትን የሚያከብሩ ሀገራት እነማን ናቸው?
ኢትዮጵያን ጨምሮ ጥቂት የዓለማችን ሀገራት ከምዕራባዊያን ዘመን በተለየ አዲስ ዓመታቸውን ያከብራሉ። ኢትዮጵያ፣ ኢራን፣ ቻይና፣ ሰሜን ኮሪያ እና ሌሎችም የራሳቸው ዘመን መቁጠሪያ ስርዓት አላቸው።
ሀገራቱን ዝርዝር በተከታዩ ሊንክ ይመለክቱ፤ https://am.al-ain.com/article/countries-celebrating-new-year-differently
#እንቁጣጣሽ
የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ፤ ከፍተኛ ሽልማቶችን እንደያዘ የገለፀው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ዕጣ ዛሬ ጳጉሜን 6 ቀን 2015 ዓ.ም በህዝብ ፊት መውጣቱን ገልጿል።
በዚህም ፦
- የ1ኛ ዕጣ 20 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 1820259
- የ2ኛ ዕጣ 10 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 1656546
- የ3ኛ ዕጣ 5 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 2118779
- የ4ኛ ዕጣ 3 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 0865504
- የ5ኛ ዕጣ 2 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 1020830
- የ6ኛ ዕጣ 1 ሚሊዮን ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 1317686
- የ7ኛ ዕጣ 500,000 ብር የሚያሸልመው የዕጣ ቁጥር 1903473 ሆኖ የወጣ ሲሆን የማስተዛዘኛ ዕጣ ቁጥርም 6 በመሆን መውጣቱን አሳውቋል።
(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮችን ከላይ ይመልከቱ)
👉 ጀግኖቻችን እንኳን አደረሳችሁ‼️💪💪
ስለ እኛ ሠላም ስትሉ፤ ከቤተሰባችሁ ተነጥላችሁና ኑሯችሁን ትታችሁ፤ በዱር፣ በገደሉ፣ በጥሻ፣ በሸንተረሩ...ለምትዋደቁልን ጀግናው የመከላከያ ሠራዊታችን አባላት በሙሉ እንኳን ለ2016 ዓ.ም አደረሳችሁ‼️
መልካም አዲስ ዓመት ይሁንላችሁ‼️
#የኢትዮጵያ_ክንድ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጳጉሜ 05 ቀን 2015 ዓ.ም
ሞልቶ ፈሷል
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አራተኛው ዙር የውሃ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ታላቁ ወንዛችን ዛሬም ሞልቶ በኩራት ይፈሳል።
የመላው ኢትዮጵያውያን ልፋት ተሳክቷል እሰየው ያሰኛል። ይህ ስኬት የነገይቱ ኢትዮጵያን የማድረግ አቅም ዛሬ ላይ አመላክቷል። አረጋግጧል።
ለዚህ ድል መብቃት የአንድነታችንና የኛነታችን መተባበር እምርታ ስለመሆኑ ታላቁ የህዳሴ ግድባችን እማኝ ሆኖን ገፅታችንን በዓለም ላይ ቀይሮታል።
ይህ ታላቁ ግድባችን ኢትዮጵያ የምትታወቅበትን አልደፈር ባይነትና ጀግንነት በልማቱም እንድንደግም ሁለተኛ ዕድል ሰጥቶናል። እነዚያ የረሃብ ምሳሌ አድርገው በመዝገ-ቃላት ከትበውን የነበሩ ሰዎችን ዛሬ ላይ ከኢትዮጵያ አልፎ ለጎረቤት ብርሃን የሚሰጥ ግድብ የገነባ ትውልድን ተዓምር እንዲመለከቱ አስችሏል።
ይህ ስኬት ከመቀነቷ ፈታ ከሰጠኝ ደሀ እናት ያለውን እስካካፈለው ባለሀብት ድረስ ይዘልቃል። አንድያ ህይወቱን ለሀገሩና ለህዝቡ የሚሰጠው ወታደር ደግሞ የግዳቡ ግንባታ ያለአንዳች የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ለዓመታት ውሎና አዳሩን በበረሃው አድርጓል። ጉባ ላይ ውሎ ጉባ ላይ አድሯል።
በውጪ የሚደገፉ ይሁን በሀገር ውስጥ ያሉ እኩያን የግድቡ ግንባታ እንዲስተጓጎል ያልቆፈሩት ጉድጓድ የለም። ግብዓት የሚያደርሱ ተሽከርካሪዎችን ጉዞ ከማደናቀፍ እስከ ፈንጂ ቀበራ ብዙ ብዙ ጥረዋል።
ሁሉም ሙከራዎቻቸው ግን በጀግናው መከላከያ ሰራዊት የአካልና የሕይወት መስዋዕትነት ከሽፈዋል። ዛሬ ላይ ኢትዮጵያውያንን ያኮራው አራተኛ የውሃ ሙሌት በድል ይጠናቀቅ ዘንድ ሰራዊቱ ከግልገል በለስ እስከ ጉባ ድረስ ግብዐት የሚያመላልሱ ተሽከርካሪዎች እና አሽከርካሪዎችን ደህንነት በአስተማማኝ በመጠበቅ ከቦታው አድርሶ መልሷል።
የውጊያ ምህንድስና ሙያተኞች በየጥርጊያው የተቀበሩ ፀረ-ሰውና ፀረ-ተሽከርካሪ ፈንጂዎችን አምክነዋል። ወታደር መሀንዲሱ አቋራጭ መንገዶችን ሰርቷል። ድንገተኛና የደፈጣ ውጊያዎችንም አክሽፏል። በዚያ በአስቸጋሪ የአየር ፀባይ በርካታ ኪሎሜትሮችን በእግሩ ተጉዟል።
ይህ ታላቅ ማማ ላይ የሚያቆመን የአፍሪካ ትልቁ ግድባችን ስራ በስኬት እንዲጠናቀቅ አጥንቱን ከስክሷል ደሙን አፍስሷል ውድ ህይወቱንም ገብሯል።
ግን ደግሞ ልፋቱ ሁሉ ፍሬ አፍርቷል። አባይ በኩራት ሞልቶ ፈሷልና። ይህ የመላው ኢትዮጵያውያን ግድብ የመላው ኢትዮጵያውያንን የመተባበር እና አንድነት ዳግማዊ አድዋ ማሳያ ነውና ሰራዊቱ ነገም የመጨረሻው ግብ ይሳካ ዘንድ ጉዞውን ይቀጥላል። ሰላም።
በአብዮት ዋሚ
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ የሕዳሴው ግድብ አራተኛ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አበሰሩ
ጳጉሜ 5/2015 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሕዳሴው ግድብ አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አበሰሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልዕክት የሕዳሴው ግድብን አራተኛና የመጨረሻ ሙሌት በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሳበሥር በታላቅ ደስታ ነው ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን ተባብረን በመሥራታችን ፈጣሪ ረድቶናል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህም በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው፣ በጉልበታቸውና በጸሎታቸው በሥራው ውስጥ ለተሳተፉ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ያሉ ሲሆን ይህ ኅብረታችንም በሌሎች ጉዳዮቻችን ሊደገም እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
የሙሊቱ ሂደት ብዙ ፈተና ነበረው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደኋላ እንድንመለስ ብዙ ተጎትተን ነበር ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም በውስጥ ፈተና በውጭ ጫና እንደነበር ገልፀው ከፈጣሪ ጋር የመጣውን ሁሉ ተቋቁመን ለዚህ ደርሰናል ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም ነገር ግን አሁንም የዳገቱ ጫፍ ላይ ደረስን እንጂ ዳገቱን ወጥተን አልጨረስነውም፤ በቀጣዩ ጊዜ ያቀድነውን አጠናቅቀን ፈጣሪን እንደምናመሰግን እምነቴ ነው። ለግድቡ የምናደርገውን ማናቸውንም ድጋፍ እስከ ፍጻሜው እንድንቀጥል በዚሁ አጋጣሚ አደራ እላለሁ ብለዋል።
👉 ታላቅ የምስራች ከጉባ ተራራዎች እምብርት‼️👇👇
የታላቁ የህዳሴ ግድብ 4ኛው የውሐ ሙሌት በስኬት ተጠናቅቋል። ውሐው ሞልቶ በመሀከለኛው የግድቡ ኮሪደር አናት ላይ መፍሰስ ጀምሯል። እንኳን ደስ ያለን፤ እንኳን ደስ ያላችሁ‼
#የኢትዮጵያ_ክንድ
የኛ 👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneCommand
ሰብስክራይብ ያድርጉን
👇
https://www.youtube.com/@theredtigers_4034
