አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን
Open in Telegram
ፕሮግራሞች 👉🏽እሁድ ከ 3 - 5 ሰዐት የፀሎትና የአምልኮ ኘሮግራም። 👉🏽ማክሰኞ ከ 4 - 8 ሰዐት ፆም አና ፀሎት። 👉🏽እሮብ 12:00 - 1:30ተከታታይ ትምህርት። 👉🏽ቅዳሜ ከ 9 -11 ሰዐት የአዳጊ ወጣቶች ፕሮግራም 👉🏽ቅዳሜ ከ 9 - 12 ሰዐት የወጣቶች ፕሮግራም።
Show more3 619
Subscribers
+824 hours
+467 days
+8730 days
Posts Archive
🔥የጸሎት እና የምስጋና ጊዜ🔥
🗓 ፓጉሜ 4 ፣ 2018 ዓ/ም 11:30 ሰዓት
📍አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ማ/ም
ሁላችሁም ተጋብዛችኃል!! 🙏
ጷጉሜ/1/18
(September/6/26)
የመልዕክት አቅራቢ: ዶ/ር ለማ ደገፋ
የመልዕክት ክፍል: (ራዕይ 2:1-7)
ርዕስ: በኤፌሶን ላለችው ቤ/ክርስቲያን
መግቢያ:የኤፌሶን ከተማ በብዙ ስራና እንቅስቃሴ የምትታወቅ ከተማ ናት። የስራ ባህሏ ከፍተኛ ነው። ሰው ጥሮ ግሮ ካልሆነ ዝምተብሎ አይኖርም። በመንፈሳዊ ነገርም አርጤምስ የምትባል ጣዖት እና የራሷ የሆነ አስተምህሮ ትታወቃለች። እና ከዚህ ህይወት የተለዩ የኤፌሶን አማኞች ከጳውሎስ ደብዳቤ ደርሷቸዋል። በፍቅር ለመኖር እንደተጠሩ ይፅፍላቸዋል። ይህም ምክንያቱ ከብዙ አይነት የኑሮ ዘይቤ ስለመጡ ልዩነት አለ። ጳውሎስ ግን እንዲዋደዱ ይመክራቸዋል።
-የኤፌሶን ቤ/ክርስቲያን መሠረት ፍቅር እንደሆነ ጳውሎስ ያስተምራቸዋል።
በጌታ እይታ ኤፌሶን እንዴት ናት?
1) ንቅናቄ ያላት ነበረች: እጅና እግሯ በጣም የሚሰሩ ናቸው። እረፍት የሌላት ቤ/ክርስቲያን ናት። ለጌታ በጣም ትተጋለች። ነፍሳትን ለመማረክ በጣም ትሰራለች።
2) ፍቅርን ረስታለች: እጅና እግሯ ቢሰራም ልቧ የለም። የቀድሞውን ፍቅር ትታ ነበር። ብዙ ንቅናቄ ቢኖርም ልብ አልነበራትም።
እግዚአብሔር ጉዳዩ ከማን ጋር ነው?
-እግዚአብሔር ከማንነታችን ጉዳይ አለው። ሕይወታችን ዋና ነገራችን ነው። ኢየሱስ ሕይወታችን እስከሆነ ድረስ ማንን እያንፀባረቅን እንደሆነ ልንጠነቀቅ ይገባል።
-ለሰው ትልቁ ስጦታችን እና አገልግሎታችን ማንነታችን ነው። እውነተኛ ልማት የማንነት ልማት ነው።
-የስኬታችን መለኪያ ማንነታችን ነው። የማንነታችን ባለ አደራዎች ነን።
እግዚአብሔር ስለ እኛ ምን ይላል?
-በቃሉ መነፅር ማንነታችንን መፈተሽ ይገባናል።
ማንነት የመፈተሽ ዋጋ
-ማንነታችን፣ ሕይወታችን፣ ዋናውን እንድንጠጋ ከእግዚአብሔር ጋር እየተናበብን ለመጓዝ ይረዳናል።
-ለበለጠ ለማደግ፣ ለመለወጥ በተጠራንበት ለመሠማራት ይረዳናል።
-ራሳችንን (original) እንሆናለን።
ማጠቃለያ
እግዚአብሔር ጉዳዩ ከእኛ ጋር ነው። የህን ማወቅ እንድንችል ጌታ ይርዳን! አሜን
በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው የአምልኮ ምሽት እነሆ የ 1 ቀን እድሜ ብቻ ቀረው!
😊❤️
በሰአቱ የሚኖረን ፕሮግራም :-
* ጸሎት 🙏
* ቃለ እግዚአብሄር
* ረዘም ያለ የአምልኮ ጊዜ
ቀን: ነሃሴ 30/2018
በአያት መካነየሱስ ቅጥር ግቢ ውስጥ
በሮች ከ9:30 ጀምሮ ክፍት እደሚሆኑ ስናሳውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው ☺️🔥
አሄንን ማስታወቂያ ለጓደኞቻቹ በማጋራት ይጋብዟቸው 😉
ተባረኩ ❤️🙏
ደረሰ ደረሰ 🔥🔥🔥
ሃሌሉያ 🙏🔥
መዝሙር 150:6 6 እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን። ሃሌ ሉያ።በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው የአምልኮ ምሽት እነሆ የሳምንታት እድሜ ብቻ ቀርተውታል 😊❤️ በሰአቱ የሚኖረን ፕሮግራም :- * ጸሎት 🙏 * ቃለ እግዚአብሄር * ረዘም ያለ የአምልኮ ጊዜ ቀን: ነሃሴ 30/2018 በአያት መካነየሱስ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሮች ከ9:30 ጀምሮ ክፍት እደሚሆኑ ስናሳውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው ☺️🔥 አሄንን ማስታወቂያ ለጓደኞቻቹ በማጋራት ይጋብዟቸው 😉 ተባረኩ ❤️🙏
🔥የትምህርት እና የአምልኮ ጊዜ🔥
🗓 ነሐሴ 27 ፣ 2018 ዓ/ም 11:30 ሰዓት
📍አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ማ/ም
ሁላችሁም ተጋብዛችኃል!! 🙏
ጾም እና ፀሎት ፕሮግራም
🕝 ጠዋት ከ 4:00 - 9:00 ሰዓት
☀️ ነገ ማክሰኞ 26_2018
ጠዋት ከ 4:00 - 9:00 ሰዓት
📍አያት መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ማ/ም
አድራሻ : አያት ጣፎ መብራት ኅይል
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
ደረሰ ደረሰ 🔥🔥🔥
ሃሌሉያ 🙏🔥
መዝሙር 150:6 6 እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን። ሃሌ ሉያ።በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው የአምልኮ ምሽት እነሆ የሳምንታት እድሜ ብቻ ቀርተውታል 😊❤️ በሰአቱ የሚኖረን ፕሮግራም :- * ጸሎት 🙏 * ቃለ እግዚአብሄር * ረዘም ያለ የአምልኮ ጊዜ ቀን: ነሃሴ 30/2018 በአያት መካነየሱስ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሮች ከ9:30 ጀምሮ ክፍት እደሚሆኑ ስናሳውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው ☺️🔥 አሄንን ማስታወቂያ ለጓደኞቻቹ በማጋራት ይጋብዟቸው 😉 ተባረኩ ❤️🙏
ነሐሴ/24/18
(August/30/26)
የመልዕክት አቅራቢ: ቄስ ትዕግስቱ ሞገስ
የመልዕክት ክፍል: (መዝ 4:1-8)
ርዕስ:የጽሞና አራት በረከቶች
መግቢያ: ይህ መዝሙር የትና መች እንደተዘመረ አውዱ ሲገባን ነው በደንብ የምንረዳው። ዳዊት የተበጠበጠበት ወቅት ነበር። ለሊት እንቅልፍ አይተኛም ነበር። ዳዊት እንደነገ ልጁን ሊዋጋ ዛሬ ላይ እንደዘመረው መዝሙር ነው። ዳዊት አዝኖ ነበር ምክንያቱም አሸናፊም ተሸናፊም የለም። የገዛ ልጁ ነበርና።
-አቤሴሎም እህቱን ስለሚወድ፣ ፍትህም ስለተዛባ እጅግ ተቆጥቶ ነበር። ዳዊት አምኖንን ስላልተቆጣ፣ ስላልገሰጸ አቤሴሎም ተናዶ ነበር። መፈንቅለ መንግስት አደረገበት።
-ዳዊት ከጦርነቱ በፊት ለብቻው የጽሞና ጊዜ ተሰጠው። በራሱ ሳይሆን እግዚአብሔር ሕዝቡን ተውሶ ወደ ጦርነት እንዳይወጣ ነገርግን በፀሎት እንዲቆይ ስለተናገረው ነው።
-በዚህ ዓውድ (መዝሙር 4)ን ስንመለከት ዳዊት ንስሃ ይገባል
አራቱ የጽሞና በረከቶች
1) ራስን ማየት:- ዳዊት በጽሞናው ጊዜ ራሱን ተመልክቶ ነበር። ድሮ እንደሚለው "ማራቸው" ሳይሆን "ማረኝ" ነው ብሎ የፀለየው። ንስሃ ሲገባ ሰላሙ ተመለሰለት። በጦርነት ማግስት እንቅልፍ ከመተኛት አልፎ አንቀላፋ። ለምን? የጦርነቱ ምክንያት እሱ እንደሆነ ስለተረዳ ቶሎ ብሎ ወደ ንስሃ ስለሄደ ነው። በአምላኩ ፊት እውነተኛ ማንነቱን መረመረ፣ ሰላምም አገኘ።
2) ቁጣን መግራት:- ዳዊት ከጽሞናው በፊት ቁጣው አልተገራም ነበር። የዳዊት ቁጣ ወደ ኃጥያት የሚመራ ነበር። ደምን እንዲያፈስ የሚገፋ ነበር። የአቤሴሎምም ቁጣ ወደ ኃጥያት ገፍቶት ነበር። ከዳዊት ቁባቶች ጋር ኃጥያት ሰርቶ ነበር። ስለዚህ ዳዊት በጽሞናው ሰዓት ቁጣውን መግራት እንዳለበት ተምሮ ነበር። የሰው ቁጣ የእግዚአብሔርን ጽድቅ እንደማይሰራ ማወቅ አለብን። ይህ ስለገባው ዳዊት ቁጣን መግራት እንዳለብን ይመክረናል።
3) መከራን መታገስ: መዝ 4:4 ላይ "በመኝታ ሳላችሁ አስቡ ዝም በሉ" የሚል ጥቅስ አለ። ያሰብነው ላይሆን ስለሚችል በሀሳባችንና በድርጊታችን መሀል ጊዜ ልንሰጥ ይገባል። መታገስ በጣም ያስፈልጋል። ትዕግስት ብዙ ማስተዋልን ይሰጣል። በዝምታ ውስጥ የሚገለጡ ብዙ ነገሮች አሉ። መረጃዎች ሁሉ ልክ ቢሆኑም ትንሽ ጊዜ መውሰድ ጥሩ ነው። ምክንያቱም በቁጣ ተነሳስተን ጥሩ ውሳኔ ላንወስን ስለምንችል ጊዜ መውሰድ አለብን።
4) እውነተኛነት:- ዘላቂ መረጋጋት ያለው መንግስት የሚኖረው ለእግዚአብሔር የጽድቅ መስዋት ሲያቀርብ እንደሆነ ዳዊት ለአቤሴሎም ይጽፋል። አቤሴሎም ፀጉሩን አበጥሮ፣ ድምፁን አሳምሮ፣ ሰላምታውን አብዝቶ የሰዎችን ልብ ቢይዝም እሱ ዘላቂ እንዳልሆነ ዳዊት አውቆ ነበር። አስመሳይነት ሳይሆን እውነተኛነት ነው የሚያስፈልገው። አቤሴሎም ስለዳዊት ብዙ ክፉ ተናግሯል፣የሕዝቡን ልብ ለጦርነት አነሳስቷል። ይህ ከእውነተኛነት የመነጨ ወይም ለእግዚአብሔር የጽድቅ መስዋት አልነበረም። ለዛ ነበር አቤሴሎም በጦርነቱ የሞተው፣ የሰዎችም ህይወት ያለፈው።
*ጽሞና የለመደው ዳዊት ግን በህይወት ነበር። ክብሩ ተመለሰለት፣ ብዙ ዓመትም ኖረ።
ማጠቃለያ
ቁጣችንን የምንገራ፣ የምንታገስ፣ ራሳችንን የምናይ እና እውነተኞች እንድንሆን ጌታ ይርዳን! አሜን!
