Goqa-ጎቃ (Ethio-news)
Open in Telegram
All about Ethiopia!!! ሁሌም ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም አለም-አቀፍ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበረሰባዊ ዜና ከትንተና ጋር።
Show more4 151
Subscribers
No data24 hours
-127 days
-8130 days
Posts Archive
4 151
#በሱዳን ጦርነት የሞቱ ንጹሀን በጋዛ ከተገደሉት እንደሚበልጥ ጥናት አረጋገጠ
⚡️በ14 ወራቱ ጦርነት 61 ሺህ የሚጠጉ ንጹሀን መሞታቸውን የብሪታንያ እና ሱዳን አጥኚዎች ገልጸዋል
በርካቶቹ ሟቾች ከጦርነቱ ባለፈ በርሀብ እና በበሽታ ህይወታቸው ማለፉ ነው የተነገረው::
⚡️በሱዳን ጀነራሎች ጦርነት የሟቾች ቁጥር አሁን ላይ ተመዝግቦ ከሚገኘው ሊበልጥ እንደሚችል ጥናት አመላከተ፡፡
⚡️የተባበሩት መንግስታት እና ሱዳን በጦርነቱ 26 ሺ ሰዎች መሞታቸውን በተለያየ ጊዜ ባወጡት መግለጫ መግለጻቸው ይታወሳል። አዲሱ ጥናት አሃዙን ወደ 61 ሺህ ከፍ ያደረገው ሲሆን፥ ይህም መጠን በሱዳን የሚገኘውን አሳሳቢ ሰብአዊ ሁኔታ አመለካች ነው ተብሏል፡፡
©AL-Ain
Join us
4 151
#ሩስያ በኩርስክ ግዛት 50,000 ወታደሮችን ልታሰማራ መሆኑን ተነገረ!!!
⚡️#የዩክሬን ኃይል ወደ #ሩስያ ምድር ገብቶ የተቆጣጠረው የመጀመርያዎ ግዛት ማለትም ኩርስክ ላይ #ሩስያ 50,000 ወታደሮቿን ልትልክ መሆኑን #የዩክሬን ጠቅላይ ሚኒስቴር ቭላድሚር ዝሌንስኪ ገለፀ
⚡️#የዩክሬን የኩርስክ ዘመቻ #የሩስያ ኃይሎች ወደ #ዩክሬን ግዛት ዘልቀው እንዳይገቡ ለመከላከል የተደረገ ከመሆኑም በላይ በምስራቅ #ዩክሬን እየተዋጉ ያሉ #የሩስያ ወታደሮች የውግያ ጣብያቸውን ለቀው ወደ ኩርስክ አንድያመሩ ያደርጋል ተብሎ የታሰበ ቢሆንም #አሜሪካ ባላት መረጃ መሰረት አስካሁን ድረስ የውግያ ጣቢያውን አንዲለቅ የተደረገ አንድም #የሩስያ ወታደር የለም
⚡️ይልቁንም #ሩስያ #ከሰሜን ኮሪያ ጋር ከወራት በፊት በተፈራረመቺው ስምምነት መሰረት በኩርስክ ግዛቱ ውግያ በሺህዎች የሚቆጠሩ የሰሜን ኮሪያ ወታደሮችን ስትጠቀም ቆይታለች።
#ዩክሬን #ጦርነት #ሩስያ #ሰሜንኮሪያ #ኩርስክ
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
በትግራይ መፈንቅለ መንግሥት እና ሥርዓት አልበኝነት የተባሉት ክስተቶች ምንድን ናቸው?
በትግራይ የተካሄደውን ጦርነት ያበቃውን የፕሪቶሪያ ስምምነትን ተከትሎ በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ በመሄድ እርስ በርስ ሲካሰሱ ቆይተዋል።
በተለይ ባለፈው ዓመት ማብቂያ ላይ በኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ እውቅናን ያላገኘው የህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ከተካሄደ በኋላ በድርጅቱ ሊቀመንበር እና በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት መካከል ያለው ውዝግብ እየተባባሰ ቀጥሎ ነበር።
ይህንንም ለማርገብ በክልሉ ያሉ ሲቪል ማኅበራት፣ የአገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት አባቶች ጥረት ሲያደርጉ ቆይተው ፍሬ ሳያፈራ ቢቆይም ከአንድ ሳምንት በፊት የሃይማኖት መሪዎች ዶክተር ደብረ ጽዮንን እና አቶ ጌታቸውን በማቀራረብ እንዲነጋገሩ እና አለመግባባቱን እንዲፈቱ መንገድ ከፍተው ነበር።
ሁለቱ የህወሓት ዋነኛ ሰዎች እየተካረረ እና ጋብ እያለ የቆየውን አለመግባባታቸውን ለመፍታት የሚያስችሉ ውይይቶችን ያደርጋሉ ተብሎ በሚጠበቅበት ወቅት ባለፈው ሳምንት ማብቂያ ላይ በአቶ ጌታቸው የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደር ተቀናቃኙ የህወሓት ቡድን “በይፋ መፈንቅለ መንግሥትን ወደ መፈጸም ተሸጋግሯል” ሲል ከሷል።
4 151
#Update
ፑቲን የአፍሪካ ሃገራት የሩስያ ሙሉ ድጋፍ አንዳላቸው ተናገረ!!!
⚡️#በሩስያ ሶቺ ከተማ ውስጥ በተደረገው ስብሰባ የተነበበው የፑቲን መግለቻ የአፍሪካ ሃገራት በሁሉም ዘርፎች #የሩስያ ድጋፍ አንደሚኖራቸው ገልጿል።
⚡️በቦታው የተገኙት የአፍሪካ ሃገራት ወኪሎች #የሩሲያን የእኩል ተጠቃሚነት ፖሊሲ በማድነቅ በቴክኖሎጂ በመሰረተ ልማት አንዲሁም የኃይል ማመንጨት ዘርፎች አብሮ ለመስራት ያላቸውን ፍቃደኝነት ገልፀዋል።
⚡️አንደ #ቡርኪና ፋሶ ያሉ ከምዕራብ ሃገራት ጋር ባላቸው ቅኝ-ግዛት መሰል ግንኙነት የተማረሩ የአፍሪካ ሃገራት #ከሩስያ ጋር ለመተባበር የተፈጠረው እድል አንዳስደሰታቸው ተናግረዋል።
#ሩስያ #አፍሪካ #ፑቲን
©BBC
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+1
"#ኢትዮጵያ በመጪው የአፍሪካ ህብረት ሰላም የማስከበር ተልዕኮ ቦታ አይኖራትም!!"
- የሶማሊያ መንግስት
⚡️#ኢትዮጵያ #ከሶማሌላንድ ጋር ባደረገችው ሁለትዮሽ ስምምነት ሉዐላዊነቴ ተጥሷል የምትለው #ሶማሊያ በሀገሪቷ ለአመታት ሰላም ሲያስከብር የቆየውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ግዛቷን ለቆ እንዲወጣ ደጋግማ መጠየቋ ይታወሳል።
⚡️ሆኖም #የኢትዮጵያ ሰራዊት በስሩ ሲያገለግል የቆየበት የአፍሪካ ህብረት ATMIS ተልዕኮ በመጪው ወራት የሚያበቃ ሲሆን በቦታው የአፍሪካ ህብረት በሶማሊያ የድጋፍ እና የማረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ይተካል።
⚡️እናም ባለፉት ወራት አየሻከረ በመጣው #የኢትዮ-ሶማሌ ግንኙነት ምክንያት በተተኪው የAUSSOM ተልዕኮ #የአትዮጵያ ሰራዊት ቦታ አንደማይኖረው #የሶማልያ መንግስት አሳወቀ።
#ሶማልያ #ኢትዮጵያ #AU #ሶማሌላንድ
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+1
#Update
- #እስራኤል በዛሬው እለት #በጋዛ አና በሰሜን #ሌባነን ባደረሰችው ጥቃት የበርካታ ዜጎች ህይወት አለፈ!!!
⚡️ሰሜን #ሌባነን ውስጥ በደረሰው ጥቃት በትንሹ 23 ሰዎች መሞታቸውን የተናገረው የሀገሪቷ የጤና ሚኒስቴር 7ቱ ህፃናት መሆናቸውንም ገልፃል።
⚡️#የጋዛው የድሮን ጥቃት ሁለት መኖርያ ቤቶች ላይ የተደረገ ሲሆን በጥቃቱ የ 30 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ከዛ ውስጥ 13ቱ ህፃናት ነበሩ።
#እስራኤል #ጋዛ #ሌባነን #ሄዝቦላ
Join us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+1
#Update
#ኳታር አራሷን #ከእስራኤል እና ሐማስ አደራዳሪነት ሚናዋ አሸሸች!!!
⚡️#ኳታር ከብዙ ወራት ተደጋጋሚ ጥረት ቡሃላ ለተለያዩ የተኩስ አቁም ስምምነቶች ከሁለቱም ተደራዳሪዎች ፍቃደኝነትን ስላላገኘች ለጊዜው የአደራዳሪነት ስራዎን ማቆሟን ገለፀች።
⚡️ሐማስ ሁሌም ለተኩስ አቁም ስምምነት የጦርነቱን ማብቃት አና #የእስራኤል ወታደሮች ሙሉ ለሙሉ #ከጋዛ መልቀቅን አንደ ቅድመ ሁኔታ ሲያነሳ #እስራኤል ደግሞ ከጦርነቱ ማብቂያ ይልቅ የሀማስን መጥፋት በመፈለግ ትወቀሳለች።
⚡️#የኳታር ውሳኔ የተሰማው ከፍተኛ የዋሺንግተን ባለስልጣናት በተደጋጋሚ የተኩስ አቁም ስምምነቶችን የማይቀበለው ሐማስ በኳታር : ዶሃ ያለው ቢሮ ከአሁን ወዲ ተቀባይነት እንደሌለው ተናገሩ ከተባለ በኋላ ነው።
#ሃማስ #ጋዛ #እስራኤል #ኳታር
Join us https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+2
#Update
"የኛ እጆች በጭቃ የእናንተ ደግሞ በደም ተጨማልቀዋል!!!!" - #የቫሌንሽያ ህዝብ
⚡️ከ100,000 በላይ ሰዎች የአስተዳደሩን የጎርፍ አያያዝ ተቃውመው #በቫሌንሺያ ጎዳናዎች ሰላማዊ ሰልፍ ወተዋል።
⚡️ጎርፉ ከጀመረ ሰዓታት ቡሃላ የአደጋ ማስጠንቀቅያ የደረሳቸው #የቫሌንሽያ ነዋሪዎች ለሟቾቹ አንዲሁም ለወደሙባቸው ቤቶች የክልል አስተዳደሩን ቸልተኝነት ሲወቅሱ በዋነኝነት የክልሉ መሪ ካርሎስ ማዞን ስልጣኑን አንዲለቅ ጠይቀዋል።
⚡️አስካሁን በጎርፍ አደጋው የ200 ሰዎች ሂወት ማለፉ ሲረጋገጥ 80 የሚደርሱ ሰዎች አሁንም ቢሆን መገኛቸው አልታወቀም።
#ቫሌንሽያ #ጎርፍ #ስፔን
Join us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+1
#ፓኪስታን ውስጥ በደረሰ የቦምብ ጥቃት የ25 ሰዎች ህይወት አለፈ!!!
⚡️#በፓኪስታን ደቡብ ምዕራብ ክፍል በሚገኘው የባሎቺስታን ግዛት ውስጥ ባለ የባቡር ጣቢያ ላይ በደረሰ የቦምብ ፍንዳታ 25 ሰዎች ሲሞቱ ከ50 በላይ ሰዎች ቆስለዋል።
⚡️#ፓኪስታን ውስጥ የሚንቀሳቀሰው የባሎቺስታን ነፃ አውጪ ሀይል (BLA) ለጥቃቱ ኃላፊነትን ሲወሰድ ጥቃቱ ያነጣጠረው ከክዌታ አየተመለሱ የነበሩ #የፓኪስታን ሰልጣኝ ወታደሮችን ነው ብሏል። ፖሊስ ከሟቾቹ መሃል 14ቱ ወታደሮች መሆናቸውንም አረጋግጧል።
⚡️ባሎቺስታን #የፓኪስታን ትልቁ ግዛት ስትሆን ባላት የተፈጥሮ መአድን ሃብት ምክንያት ጎሮቤቶቿ ኢራንና አፍጋኒስታንን ጨምሮ አንደ BLA ያሉ በርካታ ኃይሎች ሊቆጣጠሯት ይሞክራሉ።
#ፓኪስታን #ጥቃት #ባሎቺስታን
Join Us
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
በጋዛ ከ70% በላይ የሚጠጉት ማቾች ሴቶችና ህፃናት መሆናቸውን union nation ባወጣው መረጃ አስታወቀ
⚡️አመት ባለፈው የእስራኤል በጋዛ እየወሰደች ባለችው እርምጃ ንፁሃንን ብቻ ኢላማ እያደረገች መሆኑ UN ያስታወቀው
⚡️የUnited nation ሰብዓዊ መብቶች ዋና #volker turks እንዳለው በነዚህ 6 ወራት ብቻ ከተገደሉት ሰዎች ብዙሃኑ ሴቶች ሲሆኑ የተቀሩት ደግሞ ከ14 አመት በታች መሆናቸውን አስታውቀዋል::
‼️አክለውም ይህ ኢ ሰብዓዊ ተግባራት በፍጥነት በቃ መባል አለባቸው ብለዋል!
Join us ; @Goqaeth
4 151
+1
#በሰሜን ጎጃም በድሮን ጥቃት ነፍሰ ጡር ሴቶችን ጨምሮ 50 የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ
⚡️በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ደቡብ አቸፈር ወረዳ በተፈጸመ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ህጻናትን እና ነፍሰ ጡር ሴቶችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች እና የዓይን እማኞች ለቢቢሲ ተናገሩ።
⚡️ጥቃቱ ማክሰኞ ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም. ከወረዳው ዋና ከተማ ዱርቤቴ 40 ኪሎ ሜትር ገደማ በምትርቀው አርጌ (ዝብስት) በተባለች ታዳጊ ከተማ በተከታታይ ሦስት ጊዜ መፈጸሙን እማኞች እና ነዋሪዎች ገልጸዋል።
‼️ጠዋት 1፡10 አካባቢ በከተማዋ ገበያ አካባቢ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት እና ጤና ጣቢያ ላይ ጥቃቱ እንደተፈጸመ እማኝነታቸውን ለቢቢሲ የተናገሩ የአካባቢው ነዋሪዎች፤ “ከልጅ እስከ አዋቂ ያለቀበት” ነው ብለውታል።
4 151
+2
#Update
የ ዶናልድ ትራምፕ ወደ ነጩ ቤተ መንግሥት መመለስ እና የመጀመሪያ የቤት ስራቸው
⚡️ሚድል ኢስት ላይ; የእስሬእሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ የእንኳን ደስ አሎት ምልክታቸውን መላካቸውን የድሮ ጠንከር ያለ ግንኙነታቸውን ከማደስ ባሻገር ስለ ሌሎችም ጉዳዮች ተነጋግረዋል:: ታዲያ ይህ ልክ እንደነ ኢራን ላሉ ሃገራት ስጋታቸውን እየገለፁ ነው በአሜሪካ እስራኤል ላይ ባላት ምልከታ ማለት ነው:: ሃማስ ራሱ ይህ ለፍልስጤማዊያን ስጋት ነው ብሏል::
⚡️ራሺያ ና ዩክሬን; በትራምፕ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ መሰረት በራሺያ ላይ የጣልቃ ገብነትን ሳይሆን ለዩክሬን የሚሰጣትን እርዳታ ላይ ማቆምን ይከተላል ምንአልባትም ይህን አካሄድ ኮንግረሱ እስካልተቃወመ ድረስ:: የ Putin አጋር በመሆን የሚታወቀው #ዲሜትሪ ሜድቪድቭ እንዳስታወቀው የትራምፕ የቢዝነስ መር አስተሳሰብ ለራሺያ ይጠቅማል ሲል የዩክሬኑ መሪ ቭላድሚር ዜለንስኪ በበኩሉ ትራምፕ ለአለም ሰላም ሲባል ወራሪውን የራሺያን ሃይል መዋጋትን ማስቀጠል አለበት ብላል:: ትራምፕ በበኩሉ ነጩ ቤተመንግሥት በገባው በመጀመሪያው ቀን ጦርነቱን አስቆመዋለው ማለቱ አይረሳም::
⚡️ቻይናም የትራምፕ አልገምትም ባይነት በታይዋን ጉዳይ ላይ ስጋት ይፈጥርባታል ለዚህም ቤጂንግ ለመጪው ችግሮች ራሷን ያዘጋጀች
ትራምፕ ታይዋን ለአሜሪካ የደህንነት ዋስትና ክፍያ የመክፈል ግዴታ አልባት ሲል መናገሩ ይታወሳል አሁንም ይህን ነገር ያጠናክረዋል ሲሉ የውጭ ሚዲያዎች እየዘገቡ ይገኛሉ
⚡️ስደተኞችን በተመለከተ ትራምፕ ፕሬዚዳንት ሆኖ በተመረጡበት እለት ከተናገረው መረዳት እንደሚቻለው በቅርቡ ብዙ ሚሊየን ህገወጥ ስደተኞችን ወደሃገራቸው እንመልሳለን ሲል ተናግሯል:: ታዲያ በቅርቡ mass deportation የሚያካሂድ መሆኑን ተናግሯል::
ለበለጠ መረጃ ይቀላቀሉን ሼር አርጉት
4 151
+1
#Update
ኔታንያሁ ጋላንትን ማባረሩ በሙሉ እስራኤል ሰላማዊ ሰልፎችን አስነሳ!!!
⚡️#እስራኤል አንድ አንድ ሃሳቦች ላይ ለመደራደር ፍቃደኛ አስከሆነች ድረስ ታጋቾችን ማስመለስ ይቻላል የሚለው ጋላንት የጦርነቱን ማብቂያ ለናፈቁ እስራኤላውያን የተስፋ ድምፅ ሆኖ ቆይቷል።
⚡️በዚህም ምክንያት መባረሩ ብዙሃኑን ያስቆጣ ውሳኔ ሲሆን ህዝቡ የጋላንትን መመለስ ከመጠየቅ አልፎ ኔታንያሁ ስልጣኑን አንዲለቅ አየጠየቀ ይገኛል::
⚡️ኔታንያሁ ለጋላንት መባረር አንደምክንያት ያቀረበው በመሪዎቹ መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲ የተፈጠረው አለመተማመን ሲሆን ከመቼውም ጊዜ በላይ በጦርነት ወቅት በመሪዎች መካከል መተማመን አንደሚያስፈልግም ተናግሯል ::
#እስራኤል #ጋላንት #ፖለስታይን #ኔታንያሁ
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+1
#Update
ቤንያሚን ኔታንያሁ የሀገሪቷን የጦር ሚንስቴር ዮአቭ ጋላንትን ከስራ አባረረ!!!
⚡️ከድሮም ቢሆን እምብዛም ያልነበሩት ሁለቱ መሪዎች የነበራቸው ሸካራ ግንኙነት በስተመጨረሻ አብቅቷል። ቤንያሚን አና ጋላንት ከሚለያዩበት ነጥቦች መሃል ዋነኛው ቤንያሚን የሃማስ መደምሰስ ላይ ሲያተኩር ጋላንት ደግሞ በቅድምያ የታጋቾቹ መመለስ ላይ መሰራት አለበት ብሎ ያምናል።
⚡️በተጨማሪም ጋላንት #እስራኤል በመስከረም 27ቱ ለደረሰባት ጥቃት ያን ያህል ተጋላጭ ያደርጋት የመረጃ፣ የወታደር አንዲሁም የጥበቃ ድክመት ላይ ምርመራ ይካሄድ ሲል ቤንያሚን ግን አሁን ለዛ ጊዜው አይደለም ይላል።
⚡️ከዚህ በፊትም በየካቲት 2016 ከሥራው ተባሮ የነበረው ዮአቭ ጋላንት የእስራኤል ህዝብ አደባባይ ወጥቶ ወደ ስልጣኑ ይመለስ ባለው መሰረት መመለሱ ይታወሳል።
#እስራኤል #ፖለስታይን #ኔታንያሁ
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
+3
#update
ጠቅላይ ሚኒስትር #አብይ አህመድ ለአሜሪካው 47ኛ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደስ አሎት መልክታቸውን አስተላልፈዋል
⚡️የሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ጄ ትራምፕ በሰፊ ልዩነት ተቀናቃኙን ካማላ ሀሪስን ከረቱ ቡሃላ ከመላው አለም የእንካን ደስ አሎት መልክት አየተበረከተላቸው ይገኛል
⚡️በተጨማሪም የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያሚን ኔታንያሁ ከነ ባለቤታቸው እንኳን ደስ አሎት ምልክታቸውን ልከዋል
4 151
#Update
አሸናፊው ዶንልድ ትራምፕ አሁን ላይ የመጀመሪያ ፕሬዝዳንታዊ ንግግራቸውን እያደረጉ ነው!!!
ተፎካካሪው የነበረችው ካምላ ሀሪስ እስካሁን ድረስ ስለደረሰባት ሽንፈት ሆነም ስለአዱሱ ፕሬዝዳንት ምንም አልተናገረችም።
https://t.me/+b9wXeMwslWU3MTU0
4 151
#update
ዶናልድ ትራምፕ ዊስኮነስን ላይ በማሸነፋቸው ከ270 ድምፅ በላይ ማለፋቸው ተረጋግጧል::
⚡️ዶናልድ ትራምፕ 2016 ዙር ምርጫ በማሸነፍ ለ4 አመት ማገልገላቸው ይታወሳል ቢሆንም በ 2020 ላይ በ ጆይ ባይደን ተሸንፈው ከነጩ ቤተ መንግሥት መባባረራቻው ይታወሳል ይህው ዛሬ ከ 4 አመታት ቆይታ ቡሃላ የዴሞክራቷ እጩ ካማላ በማሸነፍ የፕለቲካ come back አድርጓል ይህም በታሪክ ሁለተኛው ፕሬዚዳንት በመሆን በ አሜሪካ ታሪክ ላይ መስፈር ችለዋል::
⚡️በተጨማሪም የኤል ሳልቫዶሩ መሪ የእንኳን አደረሶት መልክት በመላክ የመጀመሪያው መሆን ችለዋል
4 151
#Update
47ተኛው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ጄ ትራምፕ መሆናቸው ተረጋግጧል!!!
ምርጫውን ከሚያስፈልገዉ 270 ድምጾች 267ቱን በማግኘት አሸንፏል!!!!
4 151
ዶናልድ ጄ ትራምፕ 47 ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው መመረጣቸውን በfox news ተረጋግጧል ከተከታያቸው ካማላ ሀሪስ በሰፊ ርቅት ሲመሩ የነበሩት የሪፐብሊካኑ እጩ ትራምፕ አሁን ላይ ለሁለትኛ ጊዜ አሜሪካን እንደሚመሩ ተረጋግጧል
መረጃው የ fox news ነው
