403
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
በወንድ ለተጎዳች ሴት . . .
/// ይቆጨኝ ነበረ \\\
ከፍቅርክ ከፍታ ላፍቃሪ ከራቀው
ኩራት ከውበት ጋር ከተደባለቀው
ከሚታየው ርቆ የዝናህ ቅርንጫፍ
ከጥላቻህ አናት ከመፈቀርህ ጫፍ
አላፈቅርም ብለህ
አልወድሽም ብለህ
እንኩዋን ገፈተርከው
እንኩዋን መሬት ጣልከው
እንኩዋንም ባንተ እጅ ልቤ ተሰበረ
ባላፈቅርህ ኑሮ ይቆጨኝ ነበረ
@eiduka
https://t.me/eiduka
❣️#ናፈከኝ💓
♥️ያልዋልንበት ጊዜ ውሎዬ ሲመስለኝ
ያላለፍነው መንገድ መንገዴን ሲመራኝ❤️🩹
ያላየነው ሁሉ ትውስታ ሲሆነኝ
ባልኖርኩት ትላንት ውስጥ ኖሬ ተገኘሁኝ💕
💗የኖርኩት ካልኖርኩት ገጥሞልኝ ባየው
ያልነበረው ሁሉ ተፈጥሮ ባገኘው
በልቤ መዝገብ ውስጥ ሰፍሮ ብመለከት
ያበድኩ መሰለኝ እራሴን ፈራሁት❤️🔥
💗ውስጤ ሰላም ሆኖ አይኔ ቢያማትር💞
ያልነበረን ሊያይ በስሜት ቢታትር
የሰፈነን ሰላም ሊያሸብር ቢጥር
አልገለጥ አለኝ የብዥታው ሚስጥር❣️
ባልሄድኩት ጎዳና ሄጄ 💖ባስተውለው
ባልኖርኩት ህይወት ውስጥ ህይወቴን ባኖረው
ባላሰብኩት ማእበል ሰምጦ ቢገኝ ነፍሴ❤️
ሊቋረጥ ቢጣጣር ትንሹ እስትንፋሴ
አየሁት እራሴን የኖርኩት መሰለኝ
ባልኖርኩት ትላንት ውስጥ ትዝታህ መለሰኝ
የህይወቴ ዋሻ አንተን አስታወሰኝ💞
ዛሬ ሀቁን ላውራ በብዙ ናፈከኝ💖💔💞
@eiduka23🥀
@eiduka🦋
https://t.me/eiduka
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 43
🔥የመጨረሻው ክፍል
ሄዋን ለአዳም ደወለች አዳም ወዲያው አነሳው። "ሄሎ አለሜ"
አላት። ሄዋን በጩከት "ውዴ ለምድነው ቆይ እስካሁን
እወስድሻለው ብለክ ያልመጣከው" አለችው። ጩከቷ የጆሮ
ታንብር ያሳምማል። አዳም "ፍቅሬ አትጨነቂ እሺ በቃ እሺ
አመጣሻለው" አላት።
ማዋለጃ ክፍል የዲና ጩከት ፣ለቅሶ እና ሲቃ ጠፈቶ በህፃን
ለቅሶ ተተካ። አዳም በደስታ እና በእረጋታ "ሄዋኔ" አላት። ሄዋን
በጩከት "ወዬ ፍቅረ" አለችው። "ዲና በሰላም ተገላግላለች"
አላት። ሄዋን "የምርክን ነው ኡፍፍፍፍፍ እንዴት ደስ ይላል በቃ
የሚያስፈልጋትን ነገረ ላዘጋጅና እመጣለው" አለች። አዳም "እሺ
ተጠንቀቄ ለሲራቅ እደውልለታለው እሱ ያመጣሻል በቃ ስልኩን
ልዘጋው ነው እራስሽን ጠብቂ እወድሻለው" አላት። ሄዋንም
"እኔም እኔም በጣም እወድሀለው እራስክን ጠብቅ" አለችና
ስልኩን ዘጋችው እና የሁለቱንም ሰራተኞች ስም በጩከት ጠራች
ሁለቱም ተክተልትለው እና ተጣድፈው መጡ።
ሄዋን ኑኑ ኑ እቀፉኝ አለቻቸው "ምን ተገኘ?" አሉዋት። "ዲና
በሰላም ተገላገለች ደስ አይልም?" አለቻቸው። ሁለቱም
እልልታቸውን አቀለጡት ሄዋንንም አቅፋት ዘበኛው ሮጦ መጣ
"ምን ተገኘ" አለ።አንዷ ሰራተኛ "ዲና ወለደች" አለችው። ዘበኛው
"እና ለእዚህ እማ እልልታም ያንሳላ" አለና ተሳሳቁ።
፨ ሄዋን "በሉ በሉ የኔ ውዶች አሁን ለዲና የምወስድላትን ነገር
አዘጋጁልኝ" አለች። ሰራተኞቹ "እሺ እሺ" አሉና ሊሄዱ ሲሉ ሲራቅ
ደወለላት ሰላምታ ከተለዋወጡ በኋላ ሲራቅ ሄዋንን "ይሄዉልሽ
አሁን እነ ዲና ቤት ለዲና የሚያስፈልጋትን ላመጣ ልሄድ ነው
በዛው እመጣለው" አላት። ሄዋንም "እንዴ እዚህ ልናዘጋጅ እኮ
ነው" አለችው። ሲራቅም አይ ዲና ያዘጋጀችው አለ። አላት "ሄዋን
እሺ በቃ እንዳልክ ይሁን በቃ ቶሎ ና" አለችና ስልኩን ዘጋችው።
፨ ሄዋን ስልኩን ከዘጋች በኋላ ሰራተኞቹን "በቃ የኔ ውዶች ተውት
ዲና እራሷ ያዘጋጀችው አላት። በቃ እኔ ልብሴን ቀይሬ ሲራቅን
ልጠብቀው" አለችና ወደ መኝታ ቤት ገባችና ልብሷን ቀይራ
ሲራቅን መጠበቅ ጀመረች። ከቆይታ በኋላ መጣና ይዞት ወደ
ሀኪም ቤት ሄዱ። ልክ የሀኪም ቤት በር ላይ ሲደረሱ ሄዋን
ለአዳም ደዉላ "የት ነው ያላችሁት መግቢያ በር ላይ ነን"
አለችው። አዳም "መጣው ቆይ እኔ" አለና ዲናን እና የዲናን ልጅ
ማየቱን አቆርጦ ወደነ ሲራቅ እና ሄዋን ሄደ። ቦስ የዲናን እጅ ይዞ
እያገላበጠ እየሳማት ዲናዬ የኔ ፍቅር አመሰግናለው" አላት
ዲናም "ቦስዬ የምን ምስጋና ነው ይልቅ ፈጣሪን በጋራ
እናመስግን" አለችው። ቦስ ፈገግ ብሎ ልክ ነሽ ውዴ አሁን በቃ
አባት ሆንኩኝ አደል?" አላት። ዲና ከልቧ ሳቀች በጣም ሳቀች።
፨አዳም ወደ በሩ በፍጥነት ሄዶ በሩ ላይ ቦስ እና ሄዋንን
አግኝቷቸው ወደ ዲና ክፍል ወሰዳቸው። ዲና ልጇን እያጠባች
ነበረ።ሄዋን በፍጥነት ሄዳ ዲናና ልጆን ሳመቻቸው።ዲና
በወለደችበት ክፍል ውስጥ ሁሉም ተደሰቱ ቦስ ዲናን እንኳን ደስ
አለሽ አንኳን ለእዚህ አበቃሽ" አላት እና ሰማያዊ የፀጉረ እሪቫን
ካመጣላት የስጦታ እቃ አውጥቶ አረገላት።
፨ከሰአታት በኋላ ዲናን ይዘዋት ቤት ተመለሱ ሁሉም ዲና ቤት
ተስብስበው ተደሰቱ። አመሻሽ ላይ ዶክተር ሉሊት እና ዶክተር ወደ
ደቡብ አፈሪካ ለስልጠና ስለሚሄዱ በረራ አለብን ብለው ሄዱ።
ዲናንን ከወለደች በኋላ በደንብ አረሷት በጣም አምሮባት
የአራስነት ጊዜዋን ጨረሰች።
፨ ዶክተር ሉሊት እና ዶክተር ለክረስትናው እንደርሳለን አሉት።
ዲና የአራስነት ጊዜዋን እንክብካቤ በተሞላበት መለኩ
አላሳለፈችው። እጅግ በጣም ተውባ ነበር። የልጆን የክረስትና
ድግስ እቤቷ አረገች።ድግሱ በጣም የሚገረም ነበረ። ከሰአት
ዶክተር እና ዶክተር ሉሊት መጡ። በድምቀት ተከበረ ዶክተር
የልጃቸው ክርስትና አባት ሆኑ። ዲና በአራስነት ጊዜዋም ዲያሪዋን
መፃፈ ሰላላቆመች እስከ ልጇ ክርስትና ድረስ ያለውን ፅፋዋለች።
፨ የዲና ልጅ ክረስትና ካለፈ ከ 3 ወረ በኋላ አዳም የጠበቃ
ኤረሚያስን መፅሀፈን አሳትሞታል።እና ለመፅሀፉ ምረቃት
ስነስረአት የድግስ አዳራሹ ላየ ቆሞ ስለ ጠበቃ ኤረሚያስ ጥሩነት
አውረቶ የማይጠግበው ሲራቅ መድረክ ላይ ቆሞ እየተናገረ ነው።
፨አዳምም ሲራቅ ሲጨረስ የተሰማውን እየተናገረ ሄዋን ምጧ
መጥቶ መጫክ ጀመረች። ሁሉም ተደናግጠው በጥድፊያ ወደ
ሀኪም ቤት ሄዱ። ሄዋን ጩከቷ በረታ ስቃይዋ በረታ በጣም
ተስቃየች በጣም ሁሉም በጣም ተጨነቁ ዲናም ከእነ ልጆን
ሀኪም ቤት ናት። ሄዋን ለሊቱን በሙሉ ስታምጥ ቆይታ ሊነጋጋ
ሲል አንድ ወንድ ልጅ ወለጀች በድጋሜ ምጧ በረታ በ5
ደቂቃዎች አማጠች ሁለተኛ ልጆን መጣች። ሄዋን የመንታ ልጆች
እናት ሆነች። አዳምንም የሴትና ወንድ መንትያ አባት አረገችው።
ምሳ ሰአት ላይ ወደ ቤት አመጧት።
ሄዋን መንታ እንደመውለዷ አምሮባት እና ሙሽራ መስላ ታረሳ
ወጣች የሁለቱንም ልጆቿን ክረስትና ደገሱ። ስማቸው ያው
የታወቀ ነዉ ሴቷን ሄአድ ወንዱን አድሄ ብለው ሰየሙት ሴቷን ዲና
ክረስትና አነሳቻት ወንዱን ደሞ ልክ እንደ ዲና ልጅ ሲራቅ
አነሳው። የዲና ልጅ ስም ደሞ ፊሊያ ነው።ፊሊያ ማለት የቤተሰብ
ፍቅር ማለት ነው።
፨ "የሆነው ሆኖ ሁሉም አስለቅሶን እና አስቆን እዚህ ደረሰናል"
አለች ዲና መድረክ ላይ ቆማ ሰለ ፃፈችው መፅሀፍ ማብራሪያ
እየሰጠች "በህይወት ውስጥ ስንኖር መልካምነት እና ጥሩነት
በምንም አይተመኑም "ዲና ወደአዳም እያየች ንግግሯን
ቀጠለች"ታውቃላችሁ የህይወት ረቡኒ በመካከላችሁ አለ
ስለህይወት የሚያስተምራችሁ ፈልጉት ተማሪ ካለ አስተማሪ የትም
አለ አይደል የሚባለው አንዳድ አስተማሪዎች እያወሩ ብቻ ሳይሆን
እየኖሩ ያስተምሯቸዋል ፍቅርን በጎነትን መልካምነትን
ያስተምሯቸዋል ከሁሉም ደስ የሚለው ነገ ግን መልካምነት
ለጊዜው ያሳዝነናል ለሰው ጥሩ ስንሆን ያ ሰው የእኛን ጥሩነት
እንደ ሞኝነትም ይወስደዋል ነገር ግን " አለች ዳና ንግግሯን ገታ
አርጋ " ነገር ግን መልካምነት ሲከፍል በብዙ በረከት ነው
መልካምነት መልሶ ሲከፍል ክፉ ሰው አያቆመውም መጥፎ ሰው
ቢመጣም አያቆመውም ምክንያቱም የሚከፍለው ፈጣሪ ስለሆነ
"ዲና ያቀረረውን እንባዋን ገታ አርጋ ንግግሯን ጨረሳ ከመድረክ
ልትወረድ ስትል የ1 አመት ከ 2 ወሩ የሆነው ልጇን አቅፋ 11ወረ
የሆናቸውን መንቶች ተከፈፋለው የያዙትን አዳምና ሄዋንን
እንዲሁም ሲራቅ ፣ዶክተር ፣ዶክተር ሉሊት እና ቦስን ወደ መድረክ
እንዲወጡ ጋበዘቻው። እነሱም መጡ።
፨ዲና እንዲህ አለች "ለሰው ዋጋ መስጠትን ያስተማሩኝ ስዎች
እኒ" ናቸው አለች። ይህንን ተናግራ ስትጨረስ ታዳሚው በሙሉ
ከመቀመጫው ተነስቷ አጨበጨበላት ዲና ደስ አላት። አዳም
ዲናን ከማይኩ አቅፎ ገለል ካረጋት በኋላ "አመስግናለው ጀረባ
መቺዬ" አላት።ከዛ ወደ ማይኩ መለሳት ዲናም "ይህንን መፅሀፈ
መምህሬ ብዬ የሰየምኩት በእዚህ ሰው ምክያት ነው" አለች
በድጋሜ ጭብጨባ አጀባት።
፨ ከዛን ቀን ጀምሮ ሁሉም ጣቢያዎች ዲናን ቃለ መጠየቅ
አረጉላት መፅሀፈም የፍቅር አስተማሪ ነው እና ብዙ ሺ ህዝብ
"ኦኦኦኦ" አለ።
፨ሄዋን ዲናንን ፈገግ ብላ "ተቀላቀይሻለው" አለቻት። ዶክተር
ሉሊት "ዋው እንዴት ደስ ይላል"አለች ዶክተርም ተከትለዋት
"በጣም" አሉ።ሄዋን "ሰዎች ምነው አታቅፋኝም እንዴ" አለች።
አጆን ከአዳም አላቃ ወደነሱ እየዘረጋች። ከዛም ተነስተው አቀፏት።
ደስታ በደስታ ሆኑ ፌሽታ በፌሽታ ዲና ከፀነሰች 5ወረ ከ 25ቀኞ
ነው። ሄዋን ደሞ 25 ቀን ልጆቻቸው በ5 ወር ይበላለጣሉ።
፨ አዳም ሙሉ ለሙሉ ስራውን ለተወሰነ ጊዜ አቅረጦ ሄዋንን
መንከባከብ እና የቀረውን የጊዲዮን ታሪክን ሲፅፍ ቆየ ስራ
ባቆረጠ በ 3 ወሩ መፅሀፉን ጨርሶ ወደ ስራው ተመለሰ።"ታሪኩ
በጠበቃ ኤረሚያስ ተጀምሮ በጠበቃ አዳም ተጨረሰ ይህ መፅሀፍ
እንዲጠናቀቅ ለለፈው ወዳጆችን ሲራቅ ምስጋና ይድረሰው ከዛ
በፊት ግን ፈጣሪ ይመስገን" ብሎ አዳም የመፅሀፉ መደምደሚያ
ይህንን ቃል አረገ።
፨አዳም እና ሲራቅ ለሂሱ መፅሀፈን ሰጡት። ከ15 ቀን በኋላ ቦስ
ስራ ለመሄድ ጠዋት ሲዘጋጅ ዲና መጮክ ጀመረች። ቦስ ዲና 5
ወሯ ሲገባ ገና ነው ስራውን ትቶ እንደ አዳም ሚስቱን ሲንከባከብ
የነበረው ዛሬ ግን በጣም አስፈላጊ ሰለሆነበት ነበረ። ሊሄድ
የነበረው። ቦስ ሮጦ መኝታ ቤት ገባ ዲና የእንሽረት ውሀዋ ፈሶ
ትጮካለች።
፨ አዲሷ ሰራተኛቸው በፍጥነት አዳም ጋራ ደውላ ነገረችው።
አዳም ሄዋንን ቁረስ እያጎረሰ እያበላት ነበረ።ትቶ ሮጠ ሄዋን
"ምነው?" ስትለው "ዲና ምጧ መጣ"አላት "እኔም እሄዳለው"
አለች ሄዋን አዳምም "በኋላ እወስድሻለው በቃ እደውልልሻለው
እወድሻለው" ብሏት ወጣ። መንገድ ላይ ለቦስ ደወለ። ቦስ
ስልኩን አስቶ "ሀኪም ቤት ነን" አለው። አዳም ከመቅፅፈት ደረስ።
ዲና እየጮከች ነው በጣም እየጮከች ስለሆነ ቦስ በጣም
ተጨነቀ የሚያረገው ሁሉ ጠፈበት። ጭንቀቱ አቁነጠነጠው።
✨ይቀጥላል.....
@eiduka
@eiduka
አይቻልም ለሰረጉ ቀን ነው የምታይው" አላት። ዲና እንዴ ግን እኮ
አምሮኝ ነው አለች። ሄዋን"እንዴት እንዴት አልገባኝም"አለች። ዲና
ሳቅ ብላ የሆነ ነገረ ልነግራቹ ነበረ።"እኔ የ3ወረ እረጉዝ ነኝ"ዛሬ
ነው ያወኩት"።አለች ቦስ ምን የምረሽን ነው?"አላት።ሲራቅና
ሊሎች ዋው ደስ ይላል አሉ።ሁሉም ዲናን አቅፏት ቦስ አንስቶ
አቅፎ አሽከረከራት "ደስታም ሀዘንም ሲመጣ አንዴ ነው"አለ
አዳም።በጣም ተደስተዋል ቦስ ከአሁኑ ዲና መንከባከብ ጀምሯል።
፨ ዛሬ አሁን ላይ በአንድ ትልቅ አዳራሽ ውስጥ ነጭ እና ጥቁር
የለበሱ የተሟሸሩ ሙሽሮች ይያያሉ። በሴቷ ጎን 3 በጣም
የተቆነጁ ሴቶች አሉ ሚዜዎች ማለት ነው። በወንዱ ጎን ዝንጥ
ብለው ያማረባቸው ወንዶች አሉ እነዚህም ሚዜዎች ናቸው።
ከአዳራሹ ፊት ለፊት ለእነዚህ መድረክ ላይ ላሉ ሰዎች ደስታ
የተረባረብ ስዎች ተቀምጠዋል ደስታን ለእራሳቸው እና ለሊላው
እያስተገቡ ያሉት ሙሽሮች ሄዋን እና አዳም እንኳን ደስ አላቹ አለ
ዲጄው።
፨ ታዳሚዎች አጨበጨቡ።ከዛም ወደ እራት ስነስረአት ሄዱ
ተበላ፤ተጠጣ ከዛማ ፌሽታ፣ጭፈራ፤ዳንስ፣ጨዋታ፣የደስታ ለቅሶ፣
የፍቅር ህብረት ሁሉም በአንድ አዳራሽ ውስጥ ተከናወነ።ደስስስስ
የሚል ስረግ፤ደስ የሚሉ ጥንዶች፤የሚያስደምም ታሪክ ያላቸው
ታሪከኞች፤ ዝግጅቱ አልቆ ሁሉም ወደየ መኖሬያቸው ሄዱ። ሄዋን
እና አዳምም ወደ ቤታቸው ሄዱ።
፨ዛሬ የኖሩበት ቤት ሲገቡ ሌላ ድባብ አለው። ዛሬ ይህ ቤት የባለ
ትዳሮች ቤት ነው። በፊት ልባቸው አንድ ሆኖ የተለያየ ክፍል
ለሊቱን ያሳልፈ ነበረ። ዛሬ ልባቸው እንደ በፊቱ አንድ ሆኖ በአንድ
አልጋ ላይ ለሊቱን ሊያሳልፉ ነው። የህይወት ሁለተኛ ምእራፋ
ተጀመረ።
፨ አዳም ሄዋንን ወደ ጋራ መኝታ ቤታቸው ከበሩ ጀምሮ ተሸክሞት
ገቦ። ሄዋን የአዳምን አይን ከአይኖቿ ተክላ እያየችው ነው።
አዳምም እንደዛው በፍቅረ እየተያዩ ነው። አዳም በቀስታ እንደ
እንቁላል ይዞ ሄዋንን አልጋው ላይ አጋደማት እሱም አብሯት
ተጋደመ ተጠጋጉ ተጠጋጉ በጣምም ተጠጋጉ የአዳም እና የሄዋን
ከንፈሮች ተነካኩ።የመጀመሪያ ጊዜ ለመጀመሪያ ቀን ሄዋንም ካለ
አዳም አዳምም ያለ ሄዋን ፍቅረን አያውቁም ፍቅረኛም ይዘው
አያውቁም። ከዛማ ጨዋታ ተጀመረ የአልጋ ጨዋታ እፍረት ቀረ
ትግል፣ ፍቅረ፣ ህመም ፣ጩከት እረካታ ፣መነካካት መሳሳም
ድካም የአንሶላ መቆሸሽ እረፈት ለሊቱ በፍቅር ጨዋታ
ተገባደደ።ድካሙ ፀንቶ እንቅልፍ ጣላቸው።
፨ከትግል ሁሉ ትግል ይህ ትግል ደስታ አለው። ፈጣሪ ለምን
ከትዳረ በፊት የአልጋ ጨዋታን እንደከለከለ አሁን ገባኝ። ይህንን
ደስታ መስዋት አረገው ለትዳረ ቀን ድል ማድረግ ለምን ፅድቅ
እንደሆነ አሁን ገባኝ። የሚያፈቅሩትን ሰው ያለ ማንም ከልካይ
መንካት አለም ከምታስተናግዳቸው ደስታዎች ዋነኛው ነው እንኳን
ያለማቋረጥ ሙሉ አካል ከሙሉ አካል ጋራ መነካካት ቀረቶ
መተቃቀፈም ደስታ ነው"።አለ አዳም በውስጡ ይህንን ደሰታ
ስለስጠው አምላክም ምስጋና አቀረበ። አምላኩን በማያስቀይም
መልኩ ለተደሰተው ደስታ እራሱ አምላክን ደጋግሞ አመሰገነ።
፨ሄዋን ስትነቃ አዳም በትዝታ ተውጧል። ተንጠራረታ ሳመችው።
አዳምም ሳማት ዛሬ ሄዋን አዳምን አንገቱን አልያም ጉንጩን
ወይም ደሞ ግንባሩን ሳይሆን ከንፈሩን ነው የሳመችው እሱም
እንደዛው። አልጋቸው ላይ ሰአት ካስቆጠሩ በኋላ ተነስተው
መጀመሪያ አዳም ከዛ ሄዋን በተራ ሻውረ ወሰዱ። በጣም
ደስተኞች ናቸው።
፨ አዳምና ሄዋን ከእዛ ቀን በኋላ ደስተኛ ባለ ትዳሮች ሆኑ ከተጋቡ
4 ወረ ከ 25 ቀን ሆናቸው። ሄዋን አሟኛል ብላ ተኛች። አዳም
ተጨንቆል ለሊቱን ወደላይ ሲላት ስላደረ።ዲናና ቦስን በጠዋት
ነው ደውሎ የጠራቸው። ከዛ ሀኪም ቤት ይዘዋት ሄዱ። ሄዋን
እንዴት እንደሚያረጋት ዶክተሩ ጠየቃት ምልክቶቹን በሙሉ
ነገረችው። ዶክተሩ አስፈላጊውን ምረመራ ካረገላት በኋላ ለነገ
ነይ እና ውጤት እንነግረሻለን አላት።
፨ሄዋን ቤት ከተመለሰች በኋላም አልተሻላትም በነጋታው በጠዋት
አዳም ይዞት ሀኪም ቤት ሄደ። የበሽታዋን ውጤት ለመስማት ወደ
ዶክተሩ ገብ። ዶክተር እና ዶክተር ሉሊት ለስልጠና ወደ ውጪ
ሀገረ ተልከዋል።ከዛም ዶክተሩ እንኳን ደስ አላቹ።"ወይዘሮ ሄዋን
እረጉዝ ነሽ" አላት። ሄዋን በደስታ ህመሟን እረሳችው በጣም
ተደስቱ አዳም አለቀስ ሄዋንን አቅፋውፈ አለቀስች። ከውጤት
መስጫው ክፍል እንደወጡ ሄዋን ለዲና ልደውል ስትል ስልኳን
ስታወጣ አዳም እጆን ያዛት ምነው አለችው ቆይ ለማንም አትናገሪ
ዛሬ እኮ እራት ጠሪዎች እኛ ነን ስለዚህ ያኔ እንነግራቸዋለን
አላት። ሄዋን "እሺ"አለች። ተቃቅፈው ከሀኪም ቤቱ ወጡ።
፨ ማታ ሁሉም ተሰብስበው እራት በልተው ሲጨረሰሱ በሩ ተንኳኳ
ሰራተኛዋ ከፈተችው ዶክተር ሉሊት እና ዶክተር ነበሩ። ሁሉም
ሲያዩዋቸው ደስ አላቸው። ጨዋታ ያዙ ሄዋን በድንገት ብድግ ብላ
ቆመችና "ቆይ ስሙኝ የምነግራቹ ነገረ አለ" አለች። ሁሉም
"ምንድነው?" ብለው በጉጉት አስተያየት ያይዋት ጀመረ። ሄዋን
አለቀስች ሁለት እጆቿን ወደ አዳም ዘረጋች አዳምም
ከመቀመጫው ተነቶ የዘረጋችለትን እጆች ያዛቸው።
፨ዲና "ኧረ በጉጉት ልትገይኝ ነው እንዴ እኔስ ልሙት ልጄ
አያሳዝንሽም?" ብላ ፈገግ አለች።ሄዋንም ለዲናን ፈገግታ
አፀፋውን ከመለሰች በኋላ አይ ዲናዬ ሁሌ ለወሬ እንደቸኮልሽ
አታስቢ አሁን ልነግራቹ ስለሆነ ልጅሽም አንቺም ምንም አትሆኑም
ወረኚት ይልቅ ለልጅሽ አጫዋች አግኝተንለታል" አለቻት። ዲና
"ምን እያልሽ ነው?" ስትላት ሆዶን መነካካት ጀመረች ሲራቅ
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 42
ለአዳም የተደወለለት ከ ጣቢያ ነበረ።ዜናው የጌዲዮንን ሞት
ያበሰረ ነበረ። አዳም ደስም አለው ተናደደም። ደስ ያለው አፈረ
ስለሚገባው ሲሆን የተናደደው ደሞ መሞቱ እረፈት ስለመሰለው
ነው። አዳም የደወለለትን ሰው "ቆይ እንዴት እንዲህ ሆነ?"
አለው። በጥድፊያ ወደ በረንዳ እየወጣ።ኮንስታብሉም "እኛም ዛሬ
ነው ያወቅነው ምግብ ስለማልፈልግ ጭራሽ እንዳታመጡልኝ
ስላለ እኛ የምንስጠውን ምግብ እየደፋ ስላስቸገረ ለእኔ ሪፓሪት
አረጉ ከዛም እኔ ካልጠየቀ እንዳይሰጡት አዘዝኩ በ3ተኛው ቀን
እስረኛ ጌዲዮን የታስረበት ክፍል ሲሸት ጓዶዎች ገብተው አዩት
ተበላሽቶ ነው ያገኘት"አለው።አዳምም"ስለነገረከኝ አመሰግናለው
አለና ወደ ዝግጀቱ ተመልሶ"አንዴ እባካቹ የምነግራቹ ነገረ
አለ"አላቸው አዳም።
ሁሉም ፀጥ አሉ ዲና"ምንድንነው?"አለች።አዳም"እየውላቹ ዛሬ
በዲና መልስ ቀን ጠላታችንጌዲዮን አፈር ሊመለስበት
ነው"አላቸው።የገባቸው ይመስላልግን አስተያየታቸው ዝረዝሩን
ለማወቅ የጎጉ ይመስላል።አዳምም ይህ ስለገባው ወሬውን ቀጠለ
ከዛም ነገራቸው በመቀጠል።"ዛሬ ጠዋት ነው ያየነው ብሎኛል
ኮንስታብሉ" አለ።
ሁሉም የደስታ ፊት እያሳዩ ተቃቀፉ ዲና ጮክ ብላ"ከእዚህ በኋላ
ሀዘን የለምም" አለችና ጮከች።ሁሉም እረስ በእረሳቸው ተቃቀፉ
ሲራቅም ወደ አዳም ሄዶ አቅፎ"በቃ አትናደድ ዋናው ያ ሰይጣን
መቀጨቱ ነው"አለዉ።ሲራቅ ይህንን ይበል እንጂ እሱም ከአዳም
በበለጠ ተናዶል የዲናና የቦስ የመልስ ስነስረአት ደስታን ያረገዘ
ሆነ።እስከ ምሽቱ 4:20 ድረስ ሲጨፈሩ አመሹ።ሲዝናኑ፣ሲደሰቱ
አመሹ ከዛም ሁሉም ወደየ ቤታቸው ሄዱ።አዳም ሄዋን እና
ሰራተኞቹ።ዲናና ቦስን እንዲሁም ሲራቅን፣ዶክተርን፣ዶክተር
ሉሊትን፣የዲና ጓደኞችን፣ባለጌው ዶክተረን በክብር ሸኞቸው።ዲናና
ቦስ በነጋታው ወደ ለንደን የጫጉላ ሽርሽር ሄዱ።
ተዝናንተው በሳምንታቸው ተመለሱ።በሳምንትጊዜ ውስጥ
ሁሉም ተነፋፈቀው ነበረ።ከጫጉላው ሲመለሱ መመለሳቸውን
በማስመልከት አከበሩላቸው።በእዚህ እራት ግብዣ ላይ ዲና አንድ
ሀሳብ አመጣች።ሁሌም በእየ 15 ቀኑ ይህንን ነገረ ለማከናወን
ማለትም በ15 ቀን አንድ ጊዜ የደመቀ እራት በእየተራ ሊያዘጋጁ
ሁሉም ተስማሙ በዲና ሀሳብ ተደሰቱ ሄዋንም እጣ ይውጣ
አለች እና እስኪብረቶ እና ወረቀት አምጥታ እጣ ፃፈችእና
ደበላልቃ ለሁሉም አስያዘች።
አንደኛ የደረሳቸው ዶክተር ነበሩ በመቀጠል ሲራቅ ከዛ ዶክተር
ሉሊት ከዛም ዲናና ቦስ መጨረሻ ላይ ሄዋን እና አዳም። ይህንን
ስምምነት ለማረግ ወሰኑ።ዲና ወደ አዳም ሄዳ "ስማ አዳምዬ
ዲያሬዬስ ግን?" አለችው።አለ ልስጥሽ? አላት እሷም "አዎ ገና
እኮ አልጨረስኩም" አለችው። አዳም እሺ መጣው አለና ከመኝታ
ቤቱ ያዞላት መጣ።
አዳም ዲያሬዋን ብቻ አደለም ይዞላት የመጣው ያኔ ዲና
ኦፕራሲዮን ክፍል ስትገባ ዶክተሩ ለአዳም የሰጠውን የዲና
የአንገት ጌጥ እና ቀለበቶቾን ጨምሮ ነበረ። ዲና "ውይይ አዳምዬ
የጠፋ መስሎኝ ነበረ አመሰግናለው" አለችና ጀረባውን መታ
አረገችው። ሄዋን ፈገግ ብላ እያየቻት እንኳንም ተረፈሽልን
አለቻት።አመሻሽ ላይ ሁሉም ወደየ ቤታቸው ሄዱ።ይህንን
ፕሮግራም ሁሉም በእየ15 ቀኑ እያከበሩ ቆዮ በጣም ደስተኛም
ሆኑ።የሚያስቀና ህብረት ያላቸው ቤተስቦች ሰይጣን እንኳን
ሊያጠቃቸው ቢመጣ አዝኖ የሚተዋቸው አይነት ሆኑ።
ዛሬ የካቲት1 ነው። ይህ ሳምንት የፍቅረኛ ሳምንት ነው ዛሬ
ደሞ የወዳጆች ቀን ብለው ፈረንጆች የሚያከብሩበት ቀን ነው።
አዳም ይህንን ለማክበረ ተዘጋጅቷል ቀኑ እሁድ ነው።rose dey
ተብሎ ቀኑ ተሰይሞል ለምንወዳቸው ሰዎች ለምናፈቅረው ሰው
አበባ የምንሰጥበት ቀን ነው። አዳም ለሁሉም አበባ ገዝቶ ባሉበት
እየሄደ ሰጣቸው።ለሄዋን፣ለዲና፣ ለቦስ ፣ለሲራቅ እና ለእነ ዶክተር
ሁሉም በአዳም ሁኔታ ተገረመዋል ከአበባው ጋራ ስለ ቀኑ
የሚገልፅ አጭር ፁፋ የያዘ ወረቀት አለው። በእየ ስራ ቦታቸው
መሄዱ ደሞ በጣም ገረሞቸዋል።
በነጋታው ምሽት1 ስአት ላይ የተለመደውን በእየ15 ቀን
የሚያዘጋጁት ዝግጅት ቀን ነው።የዛሬ ተረኛ ደሞ ዶክተር ሉሊት
ናት። አዳም ሁላችሁም ዛሬ ዘንጣቹ ማየት እፈልጋለው ብሎቸው
በጣም ዘንጠዋል ምክንያቱ ግን አልገባቸውም እና ሁሉም ዶክተር
ሉሊት ቤት ተሰብስበው እየተጫወቱ አዳም ሆዴን ወጋኝ አለ።
ማቃሰት ጀመረ ከዛም ሁሉም በጋራ አዳምን ይዘው 6 ሰው
የሚይዝ መኪና ተጠቅጥቀው ቦስ እየነዳ እየሄዱ።በድንገት አዳም
ለቦስ "ቦስ እዚህ ጋራ አቁመው አለ እያቃሰተ ቦስ"እንዴ
ለምን?"አለ።አዳም "አየር ማግኘት እፈልጋለው"አለው። ቦስ "እንዴ
እዚህ እንዴት ነው አየረ የምታገኘው ሰውና መኪና በተጨናነቀበት
ቦታ ባይሆን መስኮቱን ክፈቱት" አለ። ዶክተረ መስኮቱን ከፈቱት
ዶክተር ሉሊትም በእሷ በኩል ያለውን መስኮት ከፈተችው ሄዋን
አዳምን ደገፋ እያለቀስች ነው።ዲና የአዳምን እጅ ይዛ አይዞክ
እያለችው ነው።
አዳም"ካልተከፈተ እና ካልወረድኩ"አለ።ስአቱ1:45 ሆነ እሺ
አለና ቦስ መኪናውን አቆመለት። አዳም"ማንም እንዳይነካኝ"ብሎ
በእራሱ ወረደ ሁሉም ተክተልትለው አብረውት ወረዱ። አዳም
ጎዳናው መሀል ተንበረክኮ አንገቱን አቀረቀረ። ሄዋን እና ዲና
በፈጥነት ወደሱ ቀረበው ደገፈት። አዳም አትንኩኝኝ ብሎ ጮከ።
ሁለቱም በድንጋጤ ሸሹት ጥቂት ደቂቃ ካቀረቀረ በኋላ አዳም
ፈገግ ብሎ ቀና አለ።
መንገደኛው እና አሽከረካሪው ተሰብስበው ማየት ጀመሩ።
አዳም በእንብረክክ ወደ ሄዋን ጠጋ እና"አለሜ"አላት ሄዋን"ወዬ
አለችው"የዛሬው ቀን ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?"አላት በፍቅረ
አይን እያያት።ሄዋን ግራ በመጋባት "አይ
አላውቅም"አለችው።አዳም"ዛሬ propose day ነው።ይህ የጋብቻ
ጥያቄ የሚቀረብበት ቀን ነው።እና ደሞ ልክ የዛሬ 5 አመት እኔ
ላንቺ ፍቅረኛዬ እንደትሆኒ የጠየኩበት ቀን ነው አለሜ የእኔ
ህይወት የእኔ ሁሉ ነገረ አንቺ እኔን ታገቢኛለሽ?" አላት።
የተሰበሰበው ሰው ከድንጋጤው መለስ ብሎ ስልኩን አውጥቶ
መቅረፅ ጀመረ ሄዋን በደስታ አለቀሰች
"አዎ አገባካለው አዲ"አለችው።
ከዛማ ተላቀሱ ተደሰቱ ተቃቀፉ።ዲና በደስታ ጮከች ወደ አዳም
ጠጋ ብላ"አንተ እብድ አፍቃሪ"አለችና ጀረባውን መታ አድረጋ
አቀፈችው።የተሰበሰበው ሰው ሁሉ አጨበጨቡ።ህዝቡ ስልኩን
አውጥቶ ቀረፆቸው ፊልም የመሰለውም አለ።ያ ምሽት የማይረሳ
ሆኖ አለፈ።ሄዋን የሚሰጣትን ፍቅር እና ደስታ አይታም አታውቅም።
ወደፊትም እንደማታይ እረግጠኛ ናት።
ይህ ቀን ካለፈ ከ አመት በኋላ አዳምና ሄዋን የሰረጋቸውን ቀን
ቆርጠው በትዛዝ ያሰፉትን የሙሽራ ልብሳቸውን አስፈተዋል ።ዲና፣
ዶክተር ሉሊት እና ኬብሮን ደሞ የሚዜ ልብሳቸውን ይዘው ሄዋን
እና አዳም ቤት መጥተዋል ሁሉም ለብስውት አዩት። የሄዋን
ውበት በጭራሽ በቃል የሚነገረ አደለም ሴቶቹ ልብሳቸውን
ቀይረው አዳምን፣ቦስን ፣ሲራቅን እና ያ ቦለጌ ዶክተረን እየጠበቁ
ነው ከብዙ ጥበቃ ኋላ መጡ። ዲና ገና ተረጋግተው ሳይቀመጡ
"እስቲ ያሰራችውትን ልብስ አሳዩኝ" አለች። ቦስ "አይ ፍቅር
የደስታዬ ምንጭ የህሊና እረፈቴ
የኔ ምንትዋብ የልብ ምቴ
አንቺ ሆንሽ እና ሁሉ ነገሬ
መኖረ ተሳነኝ ብትለይኝ ዛሬ"........
የሚለው የዳንኤል አሽናፊ ዘፈን ነበረ። ዘፈኑ የ90ዎቹ ዘፈን ነው።
ዲና አለቀሰች። ወደ ሳሎን ሄደች። ቦስ የተደወለለትን ስልክ
አንስቶ እያወራ ነው። ዲና ከኋላው ወጥታ አቀፈችው። ቦስ
ደነገጠ እስካሁን የተፈጠረውን አላመነም። በዝምታ ያያት ጀመረ።
ሰራተኞቹ ምግብ ለማቅረብ እና ለማዘጋጀት ሲመጡ ዲናን
አዩዋት።አንዶ ጩከቷን ለቀቀችው አንዶ ደረቃ ቀረች። አዳም እና
ሄዋን በጥድፊያ ከመኝታቸው ተነስተው እየተሯሯጡ መጡ። ሄዋን
"ምንድነው?" አለች። ሁኔታውን አይታ ከማንም መልስ ሳታገኝ
የሰራተኛዋ ጩከት ገባት። ቦስም ዝም አላት። ሄዋን ተረጋጉ ዲና
በህይወት አለች። ቆይ ተቀመጡ አለችና አዳም እና እሷ
የተፈጠረውን ሁሉ አስረዶቸው።
ሁለቱ ስራተኞች ድንጋጤው ሲለቃቸው ዲናን አቅፈው አለቀሱ።
ዲናም አለቀስች ዲና ከተመለስች በኋላ ለሳምንት ሲያዩዋት
መንፈስ እየመሰለቻቸው ሁሉም እየደነገጡ ነበረ ግን ለመዱት።
ዛሬ አዳም ጌዲዮንን እስር ቤት ሙሉ ለሙሉ የሚያስገባበት ቀን
ነው። ጠዋት ዲና እንደተለመደው ውሀ እረጭታ ሳቀሰቅሰው
በጉጉት ስላልተኛ በለሊት ነው የተነሳው።
በሳሎን ቁጭ ብሎ ምን ማለት እንዳለበት እየተለማመደ ነው።
ዲና አጠገብ ተቀምጣ "ይቅናህ" ብላ ጀረባውን ደለቅ አረገችው።
አዳም ፈገግ ብሎ አሜን አሜን ዲናዬ ይቀናኛል ተስፋ አረጋለው"
አለ። ሄዋን እና ቦስ ስራ ለመሄድ ተነስተው ሳሎን ሲገቡ አዳምና
ዲና ተቀምጠው አገኛቸው። እነሱም ተቀላቀሏቸው። ፈጣሪ
አዳምን እንዲቀናው ስራተኞች እና ዘበኛውም ተጠሩ። ሁሉንም
የጠራቻቸው ሄዋን ነበረች። ሁሉም የጋራ ፀሎት አረጉ።
ቁርሳቸውን በሉ። አዳም ወደ ጥብቅና ስራው ሄደ። ጌዲዮንን
ገደል ለማስገባት ቸኩሏል። ሄዋን እና ቦስ "ዛሬ ስራ አንሄድም
ዳኝነቱን አናየዋለን" አሉ። ዲናም ከእቤት ወጥታ ስለማታውቅ
ሁሉም ሰው እንደሞተች ነው የሚያውቀው። አዳም እና ሲራቅ
ናቸው ዲና ከቤት እንዳትወጣ የፈለጉት በተለይ አዳም ነው ዲና
ከእቤት እንድትወጣ ያልፈለገው። ጓደኞቾም አያውቁም ለዳኝነቱ
ጊዜ ነው ሁሉም ዲና በህይወት እንዳለች እንዲያውቁ
የፈለገው።ምክንያቱም ወሬው ጊዲዮን ጋረ ከደረሰ ጥሩ
አይሆንም።
አዳም ለቦስ እና ለሄዋን እሱ ከሄደ በኋላ ዲናን ይዘዋት
እንዲመጡ ነግሯቸዋል ከእናም በእዚህ ተስማምተው ነው አዳም
የሄደው ።አዳም ከሄደ ከ 1 ሰአት በኋላ ዳኝነቱ ላይ ተገኝቷል፤
ዳኞቹ፣የፈረድ ታዳሚዎች ፣ መሀላ አስፈፃሚዎች ብቻ ሁሉም
መገኘት ያለባቸው ተገኝተዋል። እናም አዳም ጌዲዮን ላይ ያለውን
መረጃ በሙሉ ዶኞች ፊት አቀረበ።
፨የጌዲዮን ጠበቃ ምንም ማለት አልቻለም ጌዲዮንም እንደዛው።
ዳኞች ጊዲዮን ላይ ቅጣት ማስተላለፊያ ቀጠሮ እንደሌለበት
ተናግረው ጨርሰው። ውሳኔያቸውን ሊያስተላልፉ ሲል በሩ ተንኳኳ
ቦስ እና ሄዋን ገቡ እነሱን ተከትላ ደሞ ዲና ገባች ጌዲዮን ደረቆ
ቀረ። ቦሰ እድል ከተስጠው ስለ ጊዲዮን ሌላ ወንጀል እንዲናገረ
ጠየቀ። ዳኞች ፈቀዱለት። ቦስ ወደ ዲና እየጠቆመ "ይህቺ ሴት
ዲና ትባላለች ጊዲዮን ሊገላት የቻለውን ሁሉ አረጎ ነበረ
አልተሳካለትም አለ የሰራውን ወንጀሎች አንድ በአንድ በማስረጃ
በቪዲዮ በምስክር አቀረበ የጊዲዮን ጊዲዮን ወደራሱ ጠበቆች
ተመለከተ የሆነ ነገር ከእነሱ ጠብቋል ጠበቆቹ አንዴ ጊዲዮንን
አንዴ ዳኛውን እያፈራረቁ አፋቸው ተሳስሮ ባሉበት ደረቁ ዳኞቹ
የቀረበው መረጃ ማስሰጃ ምስክሮችን ተመለከቱ ረጆም ሰአት
የፈጀው የፍርድ ቤት ውሎ በመጨረሻም እልባት ተሰጠበት ።
ዳኞቹ ያለምንም ቀጠሮ ጊዲዮን ላይ የዘላለም እስራት ፈረዱበት
በተጨማሪም ከማንም ሳይገናኝ አኖድ ክፍል እንዲቆይ
ውሳኔያቸውን አስተላለፉ።
ጌዲዮን ጨለማ ቤት ተወረወረ። አዳም ድል አደረገ "ስቃይ
አበቃ የንፁህ ሰዎች ደም ታፈሰ ስላም አገኘ እንባቸው ተጠረገ"
አለ።
ማታ የአዳምን እና የሲራቅን ስራ ድል በማረጉ ሁሉም ተስብስበው
አከበሩ። በስብስባው ላይ ቦሰ እና ዲና ልንናገረው የምንፈልገው
ነገረ አለ አሉ።
ቦስ "ምን መሰላቹ እስካሁንም አዳም እዚህ ድል ላይ እስኪደረስ
እየጠበቅን ነው የቆየነው እኔ ካሁን በኋላ በጭራሽ ከዲና
መነጠል አልፈልግም ልክ የዛሬ 15 ቀን የእኔ እና የዲና ሰሰርግ
ይደገሳል ተዘጋጁ አለ።ሁሉም "በጣም ደስ ይላል እንዘጋጃለን አዎ"
አሉ። ሁሉም እንኳን ደስ አላቹ ብለው አቀፍቸው።
ዛሬ የታሰበው ቀን ደርሶ ዲናና ቦስ ሊሞሸሩ ነው። የዲና ስራ
ሚዜ ሄዋን ነች ሌላኛዋ እና ሁለተኛዋ ዶክተር ሉሊት ስትሆን
የመጨረሻዋ ደሞ የዲና ደራሲዋ ጓደኛዋ ናት። የቦስ ደሞ
የመጀመሪያ ሚዜ አዳም ነው። ሁለተኛው ሲራቅ ሲሆን ሶስተኛው
ደሞ ያ ባለጌ ዶክተር ነው። ብልግናውን ትቶ ፀባዩን
አስተካክሏል። ሰረጉ አለ የተባለ አዳራሽ ተከራይተው ደገሱት።
በጣም ደስ ይል ነበረ ሁሉም ተደስተዋል።
ምሽት ላይ ቦስ እና ዲና ወደ ቤታቸው ተመለሱ። አዳም ፣ ሄዋን
እና ሰራተኞች ዘበኛው እንዲሁም ዶክተር ፣ ዶክተር ሉሊት ፣ሲራቅ
የሰርጉ ታዳሚዎችም ወደየ ቤታቸው ሄዱ። ቦስ እጅግ በጣም
የሚያምረ ቤት ገዝቶ እቃ አሞልቶ ቢጨርስም ዲናን ግን
ለሰርጋችን ቀን ነው የማሳይሽ ብሏት አላሳያትም እና ዲና ቤቱን
ስታየው ደነገጠች። ውበቱ አስደመማት። ለሊቱን በፍቅር አሳለፉ።
በሳምንቱ አዳም መልስ ጠራቸው።በጣም የሚገርም ድግስ
አዘጋጅቶ እየተደሰቱ አዳም ስልክ ተደወለለት በስልኩ የሰማውን
እውነት ነው ለማለት ተቸግሮ ደነዘዘ፡፡
✨ይቀጥላል.....
@eiduka 🦋🦋
😘አለሜ ነሽ😘
✍ እድል
🔥ክፍል 41
ከድንጋጤአቸው የተነሳ ደረቀው ያዩት ያዩት በአይናቸው ያዩት
እነሱ በአይናቸው ያዩት ህልም ይመስላል ያዩዩዩዩዩትትትትትትት
በአይናቸው ያዩት ዲ ና ን ነበረረረረ። ሄዋን ተንቀጠቀጠች እራሷን
ችላ መቆም አቃታት።ያየችው ጣረ ሞት ይሁን መንፈሰ ይሁን
አላወቀችም። ህልምም መሰላት። ቦስ እያያት ክትክት ብሎ
ሳቀ በጣም ሳቀ በጣም አዳም ዲና ብሎ በፍጥነት ሄዶ
ተጠጋት ግን ሊነካት ቢፈልግም እጁ አልታዘዝለት አለ። እጁን
እንደምንም አስነስቶ ሊነካት ደረሶ ተመለሰ። ዶክተረ ሉሊት ደረቃ
ቀረች። ዶክተረ ግን ባዩት ነገረ አልተገረሙም አልተደናገጡም።
ምክንያቱም እዚህ ነገረ ውስጥ አሉበት። ዶክተረ ሉሊት ፈዛ
ቀረታለች ቃልም ትንፋሽም አልወጣትም።
ዲና በዝምታ እንባዋን ከማፍሰስ ውጪ ቃል ልታወጣ
አልቻለችም። ሲራክ በአትኩሮት ሁሉንም እያያቸው ነው። ረዥም
ደቂቃዎች ተቆጠሩ። በመጨረሻም የዲና የሲቃ ድምፅ ተሰማ።
ዲና ከአፍዋ ቃል ወጣ "የኔ ውዶች" አለች። ማንም መልስ
አልሰጣትም። አዳም ወደ ሲራቅ እያየ "ሲራቅ ምንድነው?"አለው።
ሲራቅ ጉሮሮውን ለወሬ ካመቻቸ በኋላ "እስቲ ቁጭ በሉ" አለ።
ሁሉም ባሉበት ቁጭ አሉ። "እየውላቹ ጌዲዮንን በመረጃ ለመያዝ
ሀሳብ ሳመቻች ቆየው በጣም ብዙ ጊዜ ነው የፈጀብኝ። ከዛም
ስለ አዳም ሰማው ስለ እሱ መረጃ መሰብሰብ ጀመረኩኝ። የእኔ
እና የአዳም ፍላጎት አንድ ነው። ስለዚህ ይረዳኛል ብዬ አሰብኩኝ
እና የሆነ ቀን ባለ ላዳ መስዬ የኤረሚያስን ፅሁፍ ሰጠውት። ያ
ሰይጣን እኔን እንደ ኤርሚያስ የሆነ ነገረ ካረገኝ እንኳን ሌላ ሰው
ያስጨረሰዋል አልኩኝ።
ያው አዳምን ማለቴ ነው። ከዛ ቀን በኋላ የጌዲዮን አሽከሮችን
በሙሉ አስማምቼ እንዲክዱት አረኩኝ ቀላል አልነበረም ብዙ ጊዜ
ፈጅቶብኛል። በመቀጠል ለጌዲዮን አይነት ሰዎች ሰራተኞች
የሚያቀረበውን ሰው ጌዲዮን ስራተኛ ሲፈልግ እነዚህን ቅጠረለት
ብዬ ነገረኩት። ለምን? አለኝ ሰውየው ብር ስለሚወድ ብር ብቻ
ሰጥቼ አፉን አስያዝኩት።
የእራሴ ሰዎችን የጌዲዮን ስራተኞች እንዲሆኑ እና እያንዳንዱን
እንቅስቃሴ እንዲነግሩኝ አመቻቸው። ጌዲዮን በተደስታችሁበት ቀን
በሙሉ ሊያጠቃቹ ሞክሯል ለዲና ምረቃት ፣ ለሁለቱም የቀለበት
ስነስረአት ሌላም ሌላም ጊዜ ግን አልተሳካለትም ምክንያቱም
ሰዎቹ የኔ ስለሆኑ ነው። የእቅዴ መደምደሚያ ዲና ነበረች።
ሰዎቼ 'ዛሬ ጌዲዬን ዲናን ሊገላት አቅዶል' ብለው ነገሩኝ በምን
ስል በመኪና አደጋ አሉኝ እና ዲናን ሊገላት ሲሞክረ
አልተሳካለትም ከዲና ጋረ ያኔ ነው የተገናኘው። ከቀናት በኋላ
ቀጥሬያት አገኘዋት እና የምትወጃቸውን ሸዎች ማትረፍ ከፈለግሽ
ጌዲዮን ባለፈው በመኪና አደጋ ሊያስገድልሽ ባለመቻሉ በአሁኑ
ሊገልሽ ይቀጥረሻ ይህንን እንደምታውቂ አያውቅም ግን
ሲደውልልሸ ለእኔ ደውይልኝ አልኳት። እና እሷም 'የምወዳቸው
ሰዎች ምንም እስካልሆኑ እኔ ምንም ላረግ ዝግጁ ነኝ' አለችኝ።
እኔም 'ሲቀጥረሽ ለእኔ ንገሪኝ ምንም ነገረ ሳያረግሽ
እደረስልሻለው ብዬ አስባለው ግን ካልደረስኩልሽ ሊገልሽ
ይችላል' አልኳት። እሷ 'ይሁን' አለች። እንዳልኩት 'ጌዲዮን
ደወለልኝ' አለችኝ።
ዲና ጊዲዮንን እንድታናድደው አዝዣት ስታበሽቀው ቆይታለች።
እንደቀጠራት ስትነግረኝ እንድትሄድ ነገረኳት። ግን በቃ ላተረፋት
አልቻልኩም ነገሮች በፍጥነት ነበር የሆነው። ዲና ላይ አስተኩሶ
ሀኪም ቤት በር ላይ እንደጣላት ስሰማ በፍጥነት ወደ ሀኪም ቤት
ሄዱኩኝ። ነርስ መስዬ ዲና የምትታከምበት ጋራ ገባው።
ኦፕራሲዮን ከተደረች በኋላ ለአንዱ ዶክተር አስጊ ደረጃ ላይ
እንደሆነች እንዲነግራቹ አረኩኝ።
፨ዶክተሩ የኔ ጓደኛ ነበረ እና ስለችግራችን ሁሉንም ስለነገረኩት
ተባበረኝ። ከዛ ዶክተረ ጋረ ሄጄ አዳም እና ሄዋን ከመጡ
እንደምንም ወደ ካፌ እንዲሄዱ አረጉልኝ አልኳቸው። ቀጥታዊ
ጥያቄዬ ግራ አጋብቷቸው ማንነቴን ጠየቁኝ። እኔም አጠረ አረጌ
ነገረኳቸው በሀሳቤ ተስማሙ።
ከዛም እናንተ ሻይ ቤት ስትሄዱ ዶክተሩ ጎደኛዬ ከ5ደቂቃ በኋላ
ለ3ቀን በድን የሚያረግ እና ከ3ቀን በኋላ የሚያነቃ መድሀኒት
ከማቃቸው የባህል መዳኒት የሚያዘጋጁ ወዳጄ አምጥቼ
ሰጠውት። እሱም ዲናን ወጋት ከዛም ሊሎች ዶክተሮችን ጠረቶ
ታካሚ ዲና ሞታለች አለ።
፨ሁሉም ተሰበሰብ ያው የቀረውን ታውቁታላቹ ዲና ያንን ለ3 ቀን
በድን የሚያረገውን ነገረ ከተወጋጅ በኋላ የእሬሳ ሳጥን አዘጋጀን
እንተ ከገዛችሁት ተመሳሳይ ገዛው። ዲናን እደሞተች ይበልጥ
እንድታምኑ እራሳቹ ገንዛቹ የእሬሳ ሳጥን ውስጥ እንድትከቷት
አረግን ከከተታችዋት በኋላ መኝታ ቤታቹ አሰቀመጣችዋት።
ሁላችሁም እንቅልፍ እንዲጥላቹ የእንቅልፍ መዳኒት በሀይላድ
ውሀ ውስጥ በሲሪግ ጨምረን ከመጣው ውሀ ጋራ ቀላቅለን
አሰገባነው የዲና ጓደኞች ነን ብለው ሲያስተናግዱ የነበት የኔ
ሰዎች ነበሩ። ሁላችሁም እንቅልፍ ሲጥላቹ ሳጥኑን ቀያይረን ዲናን
ከእነ ሳጥኑ ይዘናት ሄድ።
፨የቀየረነውን ሳጥን በጥንቃቄ ሰው ያለው ስላስመሰልነው
ማንም አላወቀም።ይህንን ከረዳቶቼ ጋረ ባረገውም ከባድ ነበረ።
ዲና ከ3 ቀን በኋላ ነቃች በጣም ስቃይ አይታ ሙሉ ተንቆራጣ
በባህል መዳኒት ታግዛ ዳነች። ግን ላትድንም ትችላለች ብለውኝ
ነበረ የባህል ሀኪሙ።
ዲን ያስቀመጥኳት የባህል ሀኪሙ ጋር ነበረ። ትናንት ነው
ያመጣዋት " አለ። ሁሉም የሰሙትን ማመን ተሳናቸው። ቦስ ሳቅ
እና እንባ በእኩል እያስተናገደ "እና ይህቺ ዲና ናት?። ህልምስ
አደለም?" አለ። አዳም አለቀሰ ዲና በባስ እና በአዳም መሀል
ገብታ አቀፈቻቸው ተቃቅፈው አለቀሱ።
ሄዋን አሁንም እየተንቀጠቀጠች ነው። ዲና ከ አዳም እና ከቦስ
መሀል መጥታ ሄዋን ጋራ ሄደች። ሄዋን ሸሸቻት ዲና ተጠጋቻት
ሄዋን ሸሸቻት ዲና ተጠግታ አቅፈት አለቀሰች ሄዋንም አለቀሰች
ተላቀሱ። ዲና ሁሉንም ዞራ አቀፈቻቸው። ስታቅፍቸው
ድንጋጤያቸው ቀነሰ።
ከዛ ሲራቅ አዳምን "አየክ መፅሀፉ አይታተም ያልኩክ ለእዚህ
ነው ያልተጨረስ ታሪክ ስላለው" አለው። ከዛ እራት በሉ ሲጨረሱ
ዲናን ወደ ቤት ይዘዋት ተመለሱ ዘበኛው በሩን ከፈተላቸው ዲና
ከመኪና ወርዳ ስትገባ ማን ናት እያለ ነበር። ምክንያቱም ዲና
መንምናለች። የቤቱን በረ በቁልፍ ከፈተው ገቡ። አዳም ዲናዬ
ክፍልሽን ማንም አልነካውም በቃ እረፍት አረጊ አላት። ዲና እሺ
ብላ ክፍሏ ገባች።
ዲና ክፈሏ ስትገባ ጥላው እንደሄደችው ነው። አልጋዋ ላይ
ስትተኛ የምትለብሰው ብርድ እና አልጋ ልብስ ተነቷል። ቁም
ሳጥኗን ከፈተችው የታጠበ አልጋ ልብስ እና ብረድ ልብስ
አገኘች። ዲና እንባዋ መጣ እያለቀስች አንሷላዋን አንጥፋ አልጋ
ልብሷን ለብሳ ቢጃማ ለብሳ ተኛች።ቢጆማዋ ታፋኖ የቆየ ልብስ
ልብስ ይላል። ጠዋት የቀስቀሳት የቦስ ስልክ ሲጮህ ነው። የቦስ
የስልክ ጥሪ
"የመጀመሪያ ፍቅረን ሀሁ ያልኩት
ባንቺ ነበረ ፍቅሬ ሁሉንም ያየውት
ዘላለም ሄወቴ ካንቺ ጋረ ልትኖር
ነበረ የኔ ሀሳብ ልናዜም በፍቅር
አሁን ይሄ ሁሉ ቀረና
ሁለታችን ተለያየን እና
አንቺም እርቀሽኝ ሄደሻል ዳግም ላንተያይ እንደገና
😘አለሜ ነሽ😘
✍️ እድል
🔥ክፍል 40
ዛሬ ጌዲዮን ዲና ጋራ ሲያስተኩስ የሚያሳይ ቪዲዮ ተገኝቶበታል።
ይህንን ስራውን ያጋለጠው የጌዲዮን ቀኝ እጅ በጠመደው ድብቅ
ካሜራ ነው። የደሮ የእሱ አሸረጋጅ የህግ ባለሙያዎች ወደ ሌላ
ክልል ሄደው አዲስ ለህግ ሟች ሰዎች ተቀይረዋል ጌድዮን አሉ
የተባሉትን ጠበቆች እሱ ጋር ነው ያሉት
ዛሬ አዳም የጠበቃ ኤረሚያስ መፅሀፍ ላይ ያላሟላውን አጣረቶ
ጨረሷል። ጠበቃ ኤረሚያስ ስለፃፋቸው ባለታሪኮች ትክክለኛ
አድራሻ ያልተጠቀስባቸው መረጃዎችን ፤ ተፅፈው ያላለቁ ታሪኮቹን
ከባለ ላዳው ጋራ በጋራ ሰረተው ጨረሰዋል። አዳም ከባለ ላዳው
ጋራ በግልፅ ጌዲዮንን ለማጋለጥ የተነጋገሩት ዲና በሞተች
በሳምንቱ ባለ ላዳው አዳም ጋራ በመደወል "በር ላይ ነኝ ውጣ"
አለው። አዳም ማነክም ሳይል "እሺ" ብሎ ወጣ። ወጥቶ ሲያየው
ያ ባለ ላዳው ነው። ከዛም እንዲገባ ምልክት ሰጠው አዳምም
ገባ። ባለ ላዳው የቀረውን መረጃ ለማሟላት ለ3 ቀናት በጋራ
ባለታሪኮች ባሉበት ቦታ ሄደን ስለላ ማድረግ አለብን አለው።
አዳም ተስማማ እና ከ ባለ ላዳው ጋራ ለ1 ወረ ያክል በጋራ
ስላቸውን ሰሩ የሰሩት ስለላ በጋራ ሁለቱም ጊዲዮንን ለማጋለጥ
ምን ያህል እንደቸኮሉ ሁለቱ ነው የሚያውቁት ሁለቱም ህመም
አለባቸው የትዝታ ህመም የቁጭት ህመም የንዴት ህመም። ነገር
ግን ታመው ብቻ አልተኙም ባላቸው አቅም ባላቸው ጉልበት
እየሰሩ ነው ስለላቸውን ጨረሰው የኤረሚያስ መፅሀፍ ላይ
ያልተመለሱ መልሶችን አግኝተው ተመለሱ አዳም የባለላደው
አስተዋይነት ጉብዝና ተመልክቷል ባለላዳውም የአዳምን ቆራጥነት
አስተዋይነት ታዝቧል ሁለቱም ለአንድ አቋም ስለቆሙ ስራቸው
ቀሎላችዋል ። በእዚህ ሁኔታ አዳም መፅሀፉን ፆፎ አጠናቆል።
ሌላው ደሞ ሙሉ ለሙሉ ወደ ስራው ተመልሶ እየሰራ ነው።
ሄዋንም እንደዛው። ቦስ እና አዳም ከሀገረ ውጪ ያላቸውን ንብረት
ሽጠው የበጎ አድራጎት ድረጅት ከፈተው ወላጅ አልባ ህፆናትን
እያሳደጉ ነው። ቦስ ከሀገር ሀገረ እየተመላለሰ መስራቱን እረግፍ
አድረጎ ትቶ በበጎ አድራጎት በደረጅቱ ላይ እየሰራ ነው። ሄዋን
አዳም እና ቦስ ሀዘኑ በጭራሽ አልተዋቸውም ከውስጣቸው
በቀላሉ የሚፋቅ ህመም አይደለም መቼም የሚጠፋ አይደለም።
ከዝግጅቱ በኋላ የዲና መቃብረን ለማየት ሄዱ። መቃብሯን ሲያዩ
ሁሌም ሆድ ይብሳቸዋል። አዳም በትዝታ ጭልጥ ሲል እና
ከሀሳቡ ሲነቃ "ምን አለበት ዲዬ ጀረባዬን መጥታ መታ አድረጋ
ሁሉም ቅዠት ነው ብትለኝ" ብሎ ይመኛል። ግን አይሆንም።ዲና
መቃብር ፈንቅላ መነሳት አትችልም።
አዳም ዲና የፃፈችውን እና የጠበቃ ኤረሚያስን መፅሀፈ
ሊያሳትም ይፈልጋል ግን ባለ ላዳው አልፈቀደለትም አዳም ከባለ
ላዳው ጋረ በጣም ተቀራረቦ ጓደኛ ሆነዋል። የተቀራረብት ስለ
ኤረሚያስ መፅሀፋ ያልተሞላ ታሪክ ለማሟላት ሲጣጣሩ ነው
በጣም ጓደኞች የሆኑት።
ዛሬ ባለ ላዳው አዳምን ፣ሄዋንን፣ ቦስን እና ዶክተርና ዶክተር
ሉሊትን "እራት ቤቴ ልጋብዛቹ" ብሎ ጠራቸው።
ሁሉም በሀሳቡ ተስማምተው ምሽት 2:30 ላይ ቤቱ እራት እየበሉ
አዳም ስለ ባለ ላዳው እውነተኛ ታሪክ ሲያውቅ ገረሟታል።
ይህ ባለ ላዳ ኮልታፋው ሰውዬ ኮልታፈም ባለ ላዳም አደለም።
ማሪኪ ድምፅ ያለው እጅግ በጣም ሀብታም ሰው ነው። ስሙ
ሲራቅ ይባላል። ሲራቅ ከጌዲዮን ጋራ በቢዝነስ ጉዳይ በጣም
የሚፎካሩ ነበሩ።
ጠበቃ ኤረሚያስ የሲራቅ የግል ጠበቃ ነው። ጌዲዮን
ኤረሚያስን ከሲራቅ በተሻለ እከፍልካለው ቢለውም "ለክፋት ሰረቼ
ከማገኘው ብር በነፃ ሰረቼ የማገኘው የህሊና እረካታ ይበልጣል"
ብሎ መልሷለት አናዶታል። ለዛም ነው ያጠቃው።
ሲራቅ ከእራት መብላት ስረአት ተነስቶ "ዛሬ እራታችውን በደስታ
እንድትበሉ አንድ ነገረ ላሳያቹ እፉልጋለው" አላቸው ሁሉም እሺ
እሺ አሉ።ተዘጋጁ አይናችሁን ጨፈኑ አለ። ግራ ተገቡ ጨፉኑ ትንሽ
ቆይቶ ግለፁ አላቸው። አይናቸውን ማመን ተሳናቸው። አይናቸው
ነው? ህልማቸው ነው? ይህንን አያውቁም
ይቀጥላል...
@eiduka 🦋🦋
ዲና ሞተች እያላቹ ነው"አለች። ሌላኛው ዶክተረ"አዎ እናዝናለን
ገብታቹ ማየት ትችላቹ"አለና የክፍሉን በረ ከፈተላቸው።ዶክተር
ሉሊት ምንም ማለት አልቻለችም ደረቃ ቀረታለች።አዳምና ሄዋን
ገቡ። አዳም ልክ ሲያያት ሳቁን ለቀቀው"ዲናዬ ቀልድ ነው አደል?"
አለ።ሄዋን ወደ ዲና ሄዳ እየጉተጎተች ይበቃሻል በቃ ቀልድ ነው
አዎ እናውቃለን ንቂ ዲና ንቂ"አለች። ዲና ግን አልነቃችም እጆቿ
ቀዝቅዘዋል ዲና ዲና ዲናናናናናና ሞታለች። አዎ ሰው ከመባል
ወደ በድን ፣ሟች ፣እሬሳ፣ አስክሬን ተቀይራለች። ከእዚህ በኋላ
ማንም የእሷን ድምፅ መስማት አይችልም ዲና ሟታለች አዎ እሷ ለዘላለም ላትመለስ ምድርን ተሰናብታለች። አዳምም ወደ ዲና ተጠግቶ "ቆይ ቆይ አታስጨንቂያት
ሄዋኔ ትነቃለች ሞት የሚባል ነገር የለም አዎ የለም" አለ።
ዶክተሮች ሄዋን እና አዳምን ይዘዋቸው ወጡ። አለቀሱ፤
ተንሰቀሰቁ ኡኡኡ አሉ፤ አበዱ ጮኩ ብዙ ነገር አወሩ ግን ዲና
ልትነሳላቸው አልቻለችም። ቀኑን በሙሉ ሲያለቅሱ ዋሉ። ዶክተረ
ለአዳም ሰራተኖች ዜናውን ነገራቸው አለቀሱ። እንባቸው ተገድቦ
ቢሰፈረ በህይወት ዘመናቸው ካለቀሱት እና በሳቅ ስበብ እንባቸው
የረገፈው ቢስፈር ለዲና ያለቀሱላት ይብሳል።ዲናን ለምደዋት ነበረ
ከእዚህ በኋላ እሷ አለመኖሯን ማናቸውም ማሰብ አልቻሉም።
ደቂቃው ሄደ ሰአቱም ቀጠለ። ለቦስ የዲናን መሞት ከሞተች ከ4
ሰአት በኋላ ዶክተረ ነገሩት። ቦስ ቀልድ መሰለው የምረም
መሰለው ስምቷል ግን ምንም እንዳልተፈጠረ ሆነ። ጭንቅላቱ
ማመን ተሳነው። ዶክተረ የቦስ ዝምታ አስፈራቸው ቦስ የተኛበት
ክፍል በዝምታ ተዋጠ። በድንገት ቦስ ጮከ በጣም ጮከ በጣም
ከዛም ዶክተረ ሉሊት ማደንዘዣ ወግታ አስተኛችው።
፨ ዛሬ የዲና የቀብር ስነስርአት የሚፈፀምበት ጊዜ ነው። ቦስም
ከሀኪም ቤት ወጣ።ቤታቸው በዲና ወዳጆች የቅረብ ስዎች
ማለትም ጓደኞች እና የስራ ባልደረቦች፤ ዶክተረ እና ዶክተረ
ሉሊት ፤ሄዋን እና አዳም፤ ስራተኞች እና ዘበኛው ከእና አዳም
መኖሪያ ቤት ወጥተው ዲናን ለመቅበረ እየሄዱ ነው።
፨አዳም "የሚወዱትን ስው ጉድጎድ አስገብቶ ምንም
እንዳልተፈጠረ መሆን አይከበድም? ዲናዬ ፤አንቺ አፈር ስትገቢ
በዝምታ አልቅሼ ልሽኝሽ?" እያለ አነባ። ሄዋን አዝና ከውሰጧ
ከማልቀስ ውጪ ምንም ቃል አላወጣችም። ቦስም እንደዛው
ሌሎች ግንእያለቀሱ ነው። ቀባሪዎች የዲናን እሬሳ የተቆፈረው
ጉድጓድ ውስጥ አስገብተው አፈረ አለበሱት ።
፨"የዲና የምድረ ቆይታዋ ከአፈሩ ጋራ ተዳፈነ። ዲና ከእዚህ በኋላ
ምድረ ላይ የምትኖረ ሰው አደለችም። ዲና ካሁን በኋላ ታሪክ ናት
ለምትወዳቸው ስዎች የተሰዋች መሰዋት ናት።" አለ አዳም ዲና
ከሞተች በኋላ ሰልስቷ አልፎ ለአመታቷ ባዘጋጁት ዲናን
የማስታወሻ ስረአት ላይ ነው። የተናገረው ንግግሩን
እንደጨረሰ።ለዲና የገጠምኩት አንድ ግጥም አለ። ብሎ ማንበብ
ጀመረ።
"እንዴት ነሽ ዲናዬ? እኔ እንዳለው አለው
በአለም ዙሪያ ላይ ብዙ ታዝቢያለው
ካንቺ ተለይቼ እየኖረኩኝ ሳለው
አለም መንታ መንገድ ስታስኬድም አየው
መንታ ይመስላል እንጂ ተቃራኔ እኮ ነው
ለገነት ወረፋ ጥድፊያው ቢበዛም
ሲኣል ላለመግባት ግብግብ አልበዛም
ለነገሩ ተይው ዲናዬ እህቴ
ሀጢያታችን በዝቶ ገነት ገቢ ጭራሸ እንኳን የለም
ዲና.. አንቺስ የት ለመግባት ተስልፈሽ ይሆን
አንቺ ግን .. አይዞሽ ምስጡ ቢበላሽም
ካፈሩ ደባልቆ አፈር ቢያረግሽም
እኛም በተራችን ለፍረድ እንቀረባለን
ዳግመኛ ሞት ካለ አደራ ጠብቂን"
የሚል ግጥም ነበረ። ሁሉም አለቀሱ አነቡ ተንሰቀሰቁ
ይቀጥላል...
@eiduka 🦋
@eiduka 🦋
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 39
""""
""""
""""
፨ጌዲዮን ያስተላለፈውን መልክት ማክስ ለባሹ በመቀበል ዲና
ላይ ተኮሰባት። አዳም አይይይይሆሆሆ ንንንንምምምም ብሎ ጮከ
ዲና አቃስታ ተዘረረች። ሄዋን ደርቃ ቀረች ስራተኞችም
እንደዛው። ጌዲዮን ሳቁን ለቀቀው በእነ አዳም
የፊት ሁሌታ ውስጣዊ ርካታ ተሰማወሸ። ቦስን ማንም ልብ አላለውም። ጌዲዮን በድጋሜ
"ተኩስ ተኩስባት" አለው። ባለ ማክሱ ተንጋላ የወደቀችዋ እና
የምታቃስተዋ ዲና ላይ በድጋሜ ተኮሰ። ከዛም አሁንም በድጋሜ
ስቆ "ስማ አዳም እንዲ በቀላሉ አልተውህም መቼም አልተውህም
ኢቺ አሽቃባጭክን አሁን ሄዋን የነበረችበት ሀኪም ቤት በር ላይ
ወስደን እንጥላታላን ከቻልክ መጥተክ ቆሻሻክን አንሳ።ሀሀሀሀሀሀሀ
እንደማትጠፋ ተስፋ አረጋለሁ ይህንን የማረገው አይንክ እያየ
እንድትሞት ነው። ሀሀሀሀ አስበከዋል እሳቱ ጠበቃ አዳም በዲና
ሞት ጓደኛክም ያዝናል እንዴት እንደሚወጣው አላውቅም፤ ስለዚህ
እስቲ እሱንም ምን እንደማረገው ገምት" አለና የማያቆረጥ
ሳቁን ከጣራው በላይ እየለቀቀ..... ስልኩ ዘጋው ።
፨ አሁን ሁሉም ቦስ መውደቁን አስተዋሉ በእከክ ላይ እከክ
፤በቁስል ላይ ቁስል፤ በችግረ ላይ ችግር። በስአታት አስተናገዱ።
አዳም እና ሄዋን ቦስን ተሽክመው ወደ አዳም መኪና አስገቧት።
ሄዋን ከቦስ ጋራ ከኋላ ገባች። ሄዋን ቦስን ደገፉ ከኋላ
ተቀመጠች።ዘበኛው የመኪና ማስገቢያ እና ማስወጫ በር
ከፈተላቸው አዳም መኪናውን አስነስቶ መኪናው አየር ላይ እስክትበር ድረስ መንገዱን እየሰነጠቀ በረረ... ሁለት
ሀሳብ ውጥ ገብቷል። አንደኛው ጊዜው ሳይደርስ ዲና ጋራ ለመድረስ ሌላው
ቦስን ሀኪም ቤት ለማድረስ አዳም መኪናውን በጣም በፈጥነት
እየነዳ ሀኪም ቤት በረ ላይ ደረሰ። ከዛም ወረዶ እረዱኝኝኝኝ ብሎ
ጮከ።ሄዋን ቦስ እንዲበረታ እና ዲና እንድትተረፋ እየፀለየች ነው።
፨አዳም ሲጮክ የስሙት ነረሶች በረንዳ ላይ ያለውን ቃሬዛ እየገፉ
ቦስን ከመኪና አውረድው እየገፉ አስገብት። አዳም እና ሄዋን
ደንዝዘው ቆሙ። ወዲያው የሆነ ድምፅ ተሰማ "ኧረ እዛ ጋረ ሰው
ወድቋል ኑ እናንሷት ሴት ናት" አሉ አዳምና ሄዋን ከድንዛዜያቸው
ነቅተው ወደተባለው ቦታ እየሮጡ ሄዱ። ሊሎች ነረሶች ሌላ ቃሬዛ
እየገፉ ሰው ወደቀ ወደተባሉት ቦታ በጥድፊያ ሄዱ። ያቺ ሴት ዲና
ነበረች። ልብሷ በደም ተነክሯል ፤ አዳም አለቀሰ ፤ሄዋን
አለቀሰች፤ ያቺ ሳቂታዋ ፣ተጫዋቾ፣ ቀልደኛዋ ፣ ጠንካራዋ
፣የችግር አማካሪዋ ፣ቀልጣፋዋ ዲና በሞት እና በህይወት
መካከል ሆና እያጣጣረች ማየት በጣም ያማል ይህንን ስሜት
ማስተናገድ ከባድ ነው።
፨ዲናን በቃሪዛ ይዘው ወደ መታከሚያ ክፍል እያከነፉ አስገቧት።
ሄዋንና አዳም ተከትለውዋቸው ገብ። የምትታከምበት ክፍል
ገባች። አለቀሱ ተጨነቁ። ዶክተረን ከሩቅ አዩዋቸው። ሲያይዋቸው
ሆድ ባሳቸው አለቀሱ። ዶክተር ወደ እነሱ በጥድፊያ ተጠጉ።
ዶክተረ በፋራቻ እና በተንቀጠቀጠ ድምፅ "ምን ነው? ምን
ተፈጠረ ቦስና ዲናስ የት ሄደው ነው? እናንተስ ምን ሆናቹ ነው?"
አሉ።
፨ አዳም ለቅሶ በዘጋው ድምፁ "ያ ስይጣን ጌዲዮን ዲናን ዲናን
ዲናን በሽጉጥ መቷት እዚህ ጣላት፤ ቦስም ደንግጦ እራሱን ሳተ
ሁለቱም ሊታከሙ ገብተዋል፤ ዶክተረ ንገሩኝ የሚተረፉ
ይመስልካል?፤ ዲናዬስ በህይወት ከእዚህ ትወጣለች?" አላቸው።
አዳም ዶክተረ "አዎ ዲና ይሻላታል" ስላሉ የሚሻላት መሰለው
ጭንቀት ላይ ያለ ሰው እንዲህ ነው። ዶክተር ደንግጠው
ጆሯቸውን ማመን ተሳናቸው። "ምን? አሁን የት ናቸው?"
አሉዋቸው። ሄዋን "ዲናዬ እዚህ ናት ቦስን ግን እኔ አላውቅም"
አለች።"ዶክተረ ተረጋጉ" አሉና በፈጥነት ከአይናቸው ተሰወሩ እና
አለቀሱ።
፨ ከቆይታ በኋላ አንድ ዶክተረ ዲና ከገባችበት ክፍል ወጡ።
አዳም እና ሄዋን ምን እንደተፈጠረ ለማወቅ ወደ ዶክተሩ ተጠጉ
አዳምና ሄዋን በጋራ "እንዴት ናት" አሉ። ዶክተሩም "ያው
ቀልሀዎችን አውጥተንላታል ቢሆንም አስጊ ደረጃ ላይ ናት" አለና
ሄደ። አዳምም ሄዋንም ዲናን እያሰቡ በጭንቀት ስአታት
አስቆጠሩ።ስአቱ ግን ዘገየባቸው ሌሊቱን በጭንቀት አሳልፈው
እንዳፈጠጡ አሳለፉ።ጠዋት ቦስ ትዝ አላቸው። ሁለቱም ቦስ የት
እንደገባ ለመጠየቅ ወደ ዶክተረ ቢሮ ሄዱ።ዶክተር አዳሪ ስለነበሩ
ቢሮቸው ውስጥ ገብተው የታካሚ ሪፓርተርት በማየት ላይ ናቸው።
አዳምና ሄዋን የዶክተርን ቢሮ በር አንኳኩ ዶክተረ ይግቡ አሉ።
ሄዋን ቀደም ብላ ገባች። አዳም ተከተላት።ሄዋን ዶክተርን
ስታያቸው እንዳዘኑ ያስታውቃል ብስጭትም ይታይባቸዋል። ከዛም
ሄዋን "ምነው ዶክተር ችግረ አለ?"።አለቻቸው አዳምም ምን ሆነው
ነው?" አለ።ዶክተረ ረዥም ሴኮንዶች ኡፋፋፋፋፋ አሉና ምንም
የዲና ነገረ አሳስቦኝ ነው አሉ።ሄዋንም "እሺ እንደዛ ከሆነ ፆናቱን
ይስጦት እኛም አዝነናል ግን ዶክተሩ ቀልሀዎችን አውጠተንላታል
ብሏል ፈጣሪ ይረዳናል ደና ትሆናለች" አለች።
፨ሄዋን እንዲ ስትል እልሀዊ የሆነ ንዴት ይታይባታል። አዳም "እሺ
አሁን ቦስ የት ነው ያለው?" አለ። ዶክተር "ኑ ላሳያቹ እሱ በጣም
ደና ነው ግን ድንዛዜው አለቀቀውም" አሉና። ከመቀመጫቸው
ተነስተው መውጫ በሩን በቀኝ እጃቸው ጠቆሟቸው።
፨ቦስ ወደተኛበት ክፍል አምርተው ደረሱ። በሩን ዶክተር በቀስታ
ከፈተው ገቡ አዳምና ሄዋንም ተከትሏቸው ገቡ።ቦስ ጣራ
ጣራውን እያየ ፈዞል።ዶክተረን ቀና ብለው አያቸው። የቦስ እንባ
ፈሰሰ።ቦስ ካለበት ቀና አለ።አዳምና ሄዋንን አያቸው "ተኮሰባት
አደል?፤ ገደላት አደል?፤ እ ንገሩኝ" አላቸው። ሁለቱም በዝምታ
እያዩት እንባቸውን አፈሰሱት ቦስ ተንሰቀስቀ "በቃ አትንገሩኝ
አውቄዋለው" አለ።ሄዋን "አታስብ አሁን ደና ናት" አለችው። ቦስ
"እና የታለች?" አለ። አዳም "ህክምና ላይ ናት" አለው። ቦስ ከእዛ
በኋላ ምንም አላወራም በዝምታ ውስጥ ሆኖ ቀረ። አዳም ሄዋን
እና ዶክተረ ከክፈሉ ወጡ። ከቦስ ከተለዩ በኋላ ዲና ክፍል ሄዱ።
ዲናን በመስታወቱ በኩል አዩዋት። ዶክተር "በቃ አሁን ደና
ስለሆነች ቁርሳችውን ሂዱና ብሉ ዲና እና ቦስም እንድታዝኑ
በጭራሽ አይፈልጉም ስለ እዚህ ሂዱ" አላቸው። ሊቃወሞቸው
አልፈለጉም እና "እሺ" ብለው ሄዱ። ካፌ ምግብ አዘው መጣ ፉል
እና ሻይ ነበረ ያዘዙት ግን ሊበላላቸው አልቻለም። ሻይዩን ትንሽ
እንደጠጡ። "በቃ ወደ ዲና ክፍል እንሂድ" ተባብለው
እየሄዱ።ከዛም እየሄዱ ዶክተረ ሉሊት ስራ እየገባች አገኞት።
ዶክተር ሉሊት ደንግጣ "ምን ተፈጠረ? ምን ሆናቹ? ቆይ ቦስና
ዲናስ" አለች። ሄዋን የተፈጠረውን ነገረ ነገረቻት። ዶክተር ሉሊት
ደንግጣ "ምን እያልሽኝ ነው?" አለችና እንባዋን አረገፈችው
እያለቀስች "በቃ ኑ እንሂድ እና ሁለቱንም
እንያቸው"አለች።መጀመሪያ ቦስ ጋረ ሄዱ እና አሳዩዋት ቦስ ፈዟል
ማውራት አልቻለም ወጡ ወደዲና ክፍል ሄዱ።በሩ ጋራ ሲደረሱ
ዶክተር እና ነርሶች በሀዘን ፊት ተዉጠዋል።አዳም ወደ ዶክተር
አፈጥጦ"ምንድነው ዶክተረ ንገሩኝ ምን ተፈጠረ"አለ።ዶክተረ
በደነዘዘ ድምፅ"በጣም አዝናለው ዲና ዲና አርፋለች"
አሉ።አዳም ቃሉን እንዲደግሙለት ወደ ዶክተረ እያፈጠጠ "ምን"
አለ።ሄዋን"ምን እያላቹ ነው ቆይ የምትሉትን ታውቁታላቹ ለመሆኑ
እናት ናችሁ።በጣም ነው የምወዳቹ በጣም ትንከባከቡናላቹ
ቤታችንን ትጠብቁልናላቹ ብዙ ነገረ ነው ያረጋችውልን።
ሁላችሁንም እወዳችዋለው በጣምም ማናችሁም በጭራሽ
እንዳታዝኑ። ወደ እናንተ ከተመለስኩ ደስታው የእኔ ነው።
ካልሆነም አትዘኑ። ዛሬ ወይም ነገ ምንም ሳልሆን ምንአልባት
እመለስ ይሆናል እኮ እንዲሁ ስለፈራው ነው። ጊዲዮን ምንም
ቢላቹ ማናችሁም በጭራሽ ወደ እሱ እንዳመጡ ስቃዩ የአዳም
ነው ምክንያቱም አዳምን ለመጉዳት መጀመሪያ አዳም
የሚወዳቸውን ስዎች እንደሚጎዳ አውቃለሁ" አለችና ከዶክተር ጋራ
ስላጋጠማት ነገር አጠር አድረጋ ፃፈች ሁሉም እንባ አረገፉ አዳም
ማንበብን ቀጠለ።እና የምወዳቹ የምትወዱኝ ከሆነ ያልኳችውን
አድረጉ እወዳችዋለው ሁሌም በውስጤ አላቹከ ዲና ይላል
፨ አዳም አለቀስ "እኔ አልቻልኩም በቃ አልቻልኩም" አለ ቦስ
ደብዳቤውን አነሳው ከጀረባውም ፁሁፋ አገኘ። "የኔ ውዶች
ያልነገርኳቹ ነገረ አለ። ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ጠዋት ውሀ እረጭቼ
ከእንቅልፋቹ የቀሰሰቀስኳቹ እለትን አስታወሳቹ ከእዛን ቀን ጀምሮ
ያሳለፍነውን ነገረ በእየቀኑ እፅፈው ነበር ወደ መፅሀፍ የመቀየረ
ሀሳብም ነበረኝ። ግን እናንተ ጨርሱት የማውቀው ሂስ( የልቦለድ
ገምጋሚ) አሉት ሊቁ ጻውሎስ ይባላሉ አድራሻቸው ከስረ የፃፍኩት
ነው። ቪዲዮም አለ ሁሌም ጠዋት ስትነሱ ስቀስቅሳቹ እቀርፃቹ
ነበረ። የመጀመሪያ ቀን ለቦስዬ አሳይቼው ነበረ እዩት አንብቡት
ትወዱታላቹ አደራ መፅሀፉን አሳትሙት የእራስጌ ቁም ሳጥን ላይ
አላቹ " ይላል ይህንን ቦስ ጮክ ብሎ አነበበ።
፨ ሄዋን ድምፅ እያወጣች አለቀስች በጣም ሁሉም አለቀሱ ቤቱ
በለቅሶ ተሞላ። ሀዘን ሀዘን ሀዘን ሀዘን ጭንቀት ጭንቀት ጭንቀት
ጭንቀት ለቅሶ ለቅሶ ለቅሶ ለቅሶ ሁሉም በተመሳሳይ ሰአት
እያስተናገዱ ነው። ቦስ ስልኩን ከ ጠረጴዛው አንስቷ ዲና ስልክ
ላይ ደወለ።,'ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ነው' ይላል ቦስ
ስልኩን ወረውረው ከግድግዳው ጋራ አመሳሰለው። የቦስ ስልክ
ግድግዳው ላይ ተበታትኖ መሬት እረገፈ። ልክ እንደ ልቡ ስልኩም
ተበታተነ ፤ልክ እንደ ሀሳቡ ስልኩ በተለያየ አቅጣጫ ተበታተነ።
ቦስ ከዛ ደንዝዞ ዝም አለ። ከእዛን ስአት በኋላ ከዛን ደቂቃ በኋላ
ቤቱ በዝምታ ተዋጠ።
፨ጥጥ ቢወድቅ እንኳን ግዙፋ ነገረ እንደወደቀ የሚስማበት
ይመስላል። የአዳም ስልክ ጮከ ማንሳት አቅቶት እጁ ተንቀጠቀጠ
ሄዋን ስልኩን ከአዳም ተቀበለችው ምክንያቱም ማንሳት አቃተው
ሄዋን "ሄሎ አለች።" ኦኦኦኦኦኦ ዡሌታችን ሀሀሀሀሀሀሀ ምነው
ድምፅሽ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ አጫዋችሽን ወሰዱብሽ ኣኣኣ የሆነ
ዘፈን ትዝ አለኝ ልጅ እያለን የምንዘምረው"።
" አረ አምሳለ ኧረ አምሳለ
ኧረ ሆይ ኧረ ሆይ
ኧረ እንዴት ነሽ(2)
አለሁ በመከራ እባዬን ሳዘራ
ለምን ታዘሪያለሽ አንድ አጫዋችሽስ
አንድ አጫዋቼማ ጌዲዮን ቀማኝ
ሀሀሀሀሀሀ እ ሀሀሀሀሀሀ ትስሚያለሽ አሁን የስልኩን ዳታ ክፈች
እና የማሳያቹ ነገር አለ ትይንቱን ትወጅዋለሽ" አላት ሄዋን
በፍጥነት ዳታ አበራች ወዲያው በቪዲዮ ተደወለ። አነሳችው።
፨ ሁሉም ወደ ስልኩ ተሰብስበው አፈጠጡ። ጥቁር በጥቁረ
የለበስና በፊቱ ላይ ማክስ ያረገ ስው ዲናን እያዳፋ አመጣት ከዛ
እየጎተተ ጣላት። አዳም "አይሆንምምም" ብሎ ጮከ። ቦስ
"አትጎትታትት" አለ" ቁሚ" አላት በጩከት ስውየው ዲና በግድ
ቆመች። ቦታው መብራት አለው መጋዘን ይመስላል። አዳም እና
ሌሎቹ በጣም ተደናግጠው ማየት ጀመሩ።አንድ ሌላ ሰው መጥቶ
ለጎታቹ ሽጉጥ አቀበለው። ጎታቹ ሽጉጡን ወደ ዲና አቀባሎ እራቅ
ብሎ ቆሞ አነጣጠረው
ጊዲዬን ተኩሰው የሚል ድምፅ ከሳቅ ጋራ አወጣ። ቦስ እራሱን
ስቶ ወደቀ።
ይቀጥላል...
@Hayitiye 🦋
😘አለሜ ነሽ😘
✍️እድል
🔥ክፍል 38
"""
"""
"""
"""
ሄዋን፣አዳምና ቦስም ተኝተው ስለነበረ መልክቱን አላዩትም። ዲና በጠዋት
ውሀ እረጭታ ስታስነሳቸው እንጂ አስደንጋጭ መልክት
በስልካቸው ልካላቸው አንብበው አያውቁም....ሄዋን ከእንቅልፎ እንደነቃች የሌሊት ልብሷን ቀይራ
ወደ ሳሎን ሄደች።
ስልኳን ከእስማርት ቲቪው ጋራ አገናኝታ የዘወትር ልምዷን የሆነውን በጠዋት መዝሙር የመስማትና አብራ የመዘመር ፍቅሯን ልትወጣ መዝሙር ለመክፈት
ስልኳን ስትነካካ ቅድም ከቲቪው ጋር ለማገናኘት ስትሞክር ያላየችው አሁን ያስተዋለችው መልዕክት እንዳላት ምልክቱን አየች... ። የላኪው ማንነት ዲና ስለሆነች ግራ እየተገባች
"ምንድነው?" ብላ ከፍታ
ለማየት ወደ መልክት መፃፊያ እና መላኪያው ጋራ ሄደች። ሄዋን
አነበበችው አይኗን ማመን ተሳናት ህልም ቅዠት ቀልድ መሰላት
ሮጣ ወደ ዲና ክፍል ሄደች ዲና የለችም፤ ወደ በረንዳ ሄደች
አሁንም ዲና የለችም፤ መታጠቢያ ቤት ሄደች ዲ ና የለችም።
ሄዋን ዲናናናናናናናናናናናናናናናናናና ብላ ጮኸች። ቦስ ፣አዳም
ሰራተኖቹ እና ዘበኛው ተሯሩጠው ሄዋን ወዳለችበት መፀዳጃ ቤት
ሄዱ።
፨ አዳም "ምነው ምን ተፈጠረ?" አለ። ስልካችውን እዩት ዲና ዲና
ዲና መልክት ልካላችዋለች አለቻቸው። ቦስ እና አዳም
እየተሯሯጡ ወደ ክፍላቸው ሄዱ። ስራተኞቹ ሄዋንን ይዘው ሳሎን
ወስደው አስቀመጧት። አዳም እና ቦስ ስልካቸውን ካስቀመጡበት
አውጥተው መልክቱን አነበቡ። አዳም ከክፍሉ ወጥቶ ወደ ውጪ
ወጣ ቦስም ተከተለው። ሄዋን "የት ነው የምትሄዱት" አለችው....
"ዲና እንዲህ ሆና እንዴት አስችሎኝ እቀመጣለው ያን ምንም
እንዲያረገኝ አልፈቅድም በቃ" አለ።ቦስም "አዎ እኔም ዲናዬን
አጥቼ መኖር አልችልም" አለ። ሄዋን "አይ አትሂዱ የእናንተ መሄድ
ነገሩን ያብሰዋል እንጂ በጭራሽ አያቀለውም። ትንሽ እንታገስ እና
ከዛ መወሰን ያለብንን እንወስናለን" አለች። ሄዋን ንግግሯን
እንደጨረሰች የአዳም ስልክ ላይ መልዕክት ገባ። ወዲያው
አውጥቶ አየው። የማያውቀው ቁጥር ነበረ። መልክቱ እንዲህ
ይላል "ስላም ላንተ ይሁን አዳም ሰለ ዲና ሀሳብ አይግባክ" ።
ሄዋን ከተቀመጠችበት ሶፋ ብድግ ብላ ከአዳም እጅ ላይ ስልኩን
መንጭቃ ጮክ ብላ አነበበቸው።
፨ ቦስ "ማነው እንዲህ ያለው እየቀለዱብን ነው አውቀው ነው አ?"
አለ። ሄዋን "አይ እኔ ግን የተለየ ሀሳብ ነው ያለኝ።ምን አልባት
የጊዲዮን ጠላት ሊሆን ይችላል" አለች። አዳም "ሲጀመር እኮ እሱ
ወዳጅ ሳይሆን አሽርጋጅ ነው ያለው" አላት። ቦስም "እና ምን
እናድርግ ቆይ ምን ይሻላል ኧረ መላ ፍጠሩ ዝም ብለን እጃችንን
አጣምረን እንቀመጥ ወይ እሺ ካልሆነ አስቀመጥኩት ያለችውን
ነገር እናንብበው" አለ። ሄዋን "አይ አይሆንም መታገስን መልመድ
አለብን ከእዚህ በኋላ ትግስት ያስፈልገናል እሺ አሁን ልሄድ ብላቹ
የት ነው የምትሄዱት?" አለች።ቦስ "የትም በቃ ምን እንደሚፈጠር
እስቲ እንናያለን ዲና ካለችው ሰዓት ካለፍ ግን ወደ ፓሊስ ጦቢያ
ነው የምንሄደው እሺ" አለ።አዳም "አይ ወዳጄ ሞኝ የዋህ ገራገር
ነክ ልበል እስካሁን ይህ ነገር የጠፍኝ መስሎክ ነው ግን
ስለማይሆን ነው የትኛውም ፓሊስ ጣቢያ የጌዲዮን ስዎች ነው
ያሉት። ለመክሰስ እንደምትፈልግ ነገረካቸው ከተስማሙ በኋላ
የምትከሰው ሰው እሱ መሆኑን ሲያውቁ ይሸሹካል መቼም
የማይሆን ነገር ነው። እንደምታስበው ቀላል አደለም እንጂ ቢሆን
ኖሮ እኔ ድሮ ነበረ የማሳስረው እንኳን መረጃ ሳይኖርክ ቢኖርክም
መቼም አይሰሙክም" አለ። ቦስ "ቆይ ታዲያ ምን ተሻለ?" አለና
የለበስውን ቲሽርት እስከሆዱ በብስጭት ገለፀው። አዳምም
"ምንም ምንም ማረግ አንችልም በቃ ቁጭ ብለን መጠበቅ ብቻ"
አለ።
፨ ቦስ ዲና ስልክ ላይ ደወለ። "የደወሉላቸውን ደንበኛ አሁን
ማግኘት አይችሉም እባኮ ትስሽ ቆይተው ይደውሉ" ይላል።
ደጋግሞ ሞከረ ግን የዲናን ድምፅን መስማት አልቻለም።አዳምም
ሄዋንም በተደጋጋሚ ሞከሩት ግን ስልኳ አይስራም። በጣም ተጨነቁ ፣ተንጎራደዱ፣ተቁነጠነጡ ፣አለቀሱ የማይደረስ ቀን
፤የማይነጋ ለሊት ፤የማይሄድ ወንዝ የለምና ስአትም ሰአት እየተካ
የሚጠብቁት ስአት ደረሰ።
፨ምሽት 1:00 አዳም "አሁን በጭራሽ መታገስ አልችልም"
አለና።ዲና መኝታ ቤት ገባና ቁም ሳጥኑን ከፍቶ ወረቀቱን ይዞ
ሳሎን መጣ። ሄዋን ቦስ እና ሰራተኞቹ በጉጉት ምን እንደሚል
ለመስማት ወደ አዳም
አፈጠጡ አዳምም ተስገብግቦ እና ቸኩሎ ከፈተው ጮክ ብሎ
ማንበብ ጀመረ።
፨ "ዛሬ ከእናንተ መለየቴን ሳስበው በጣም ከፍኝ ፤እጅክ አድረጌ
እወዳችዋለሁ። ቦስዬ አንተን ደሞ አፈቅረካለው አንዳንዴ
ከምንወዳቸው ጋራ ለዘላለም የምንኖረ ይመስለኛል። ብዙ
የአብሮነት ጊዜ እንደምናሳልፍ እኔም አስቤው ነበረ። ቦስዬ
የማልዋሽክ ነገረ ቢኖረ ገና አዳምዬ ፎቶክን ሲያሳየኝ ካንተ ጋራ
ጥሩ ፍቅር ውስጥ እንደምገባ ልቤ ነግሮኝ ነበር።እና ሆነ ቀለበት
አሰርክልኝ ያኔ በጣም ደስ ብሎኝ ነበረ ከዛ ደሞ እንዳገባክ
ስትጠይቀኝ ደስ አለኝ። በጣም ተመኝቼ ያልሆነው ነገር ቢኖር
ለዘላለም ሚስትክ የልጆክ እናት አለመሆሄ እና አንተን የማይዘልቅ
ፍቅር ውስጥ መክተቴ ነው። አዳም 'ትክክለኛ ፍቅር አንዴ
ይይዛል' ብሎኛል።ዝረዝሩን አዳምን ጠይቀው"። የሚለውን አዳም
ሲያነበው ሁሉም ፈገግ አሉ። አዳም ማንበቡን ቀጠለ "የኔ ውዶች
ሁሌም ፈገግ በሉልኝ ይህንን ቦታ ስታነብት ፈገግ እንደምትሉ
አውቃለው ። ቦስዬ ልብክ እንደሚሰበር አውቃለው ግን ቦስዬ በቃ
ምን ላድረግ።
፨ አምዳዬ አንተ አንተ ደሞ ከፈጣሪ የተሰጠከኝ ወንድሜ ስጦታዬ
ነክ።የህይወት መምህሬ ነክ ፍቅሬን እንዳውቅ ፈጣሪ የሰጠኝ
አንተንም መጀመሪያ ቀን ሳይክ ብዙ ነገር እንደምታስተምረኝ አውቄ
ነበረ። እና አልተሳሳትኩም አስተምረከኛል።
፨ሄዋንዬ የኔ ጩኸታም የኔ ሳቂታ ሳቂታዬ ሁሌም ሳቂልኝ እሺ
እንዲህ ስልሽ ፈገግ እንደምትይ አውቃለው" ይላል ሄዋን
እውነትም ፈገግ ብላለች አዳም ማንበብን ቀጠለ "ሄዋንዬ አንቺ
ማለት ደሞ ስለፍቅረ እንድማረ ር ምክንያት የሆንሽኝ ነሽ። ማለቴ
ያው ለማለት የፈለኩት ያው እንኳን ታመምሽ እያልኩሽ አደለም።
ከአንቺ ጋራ በጣም የተቀራረብንበትን እና የሳቅንበትን ቀን
ታስታውሽዋለሽ በጋራ ሻውር የወሰድንበትን ቀን እኔ ደስተኛ
ነበርኩ። አንቺም እንደዛው ትውስታሽ በመመለሱ ያከበርንበትን ቀን
፤ ፀጉራችንን ስንሰራራ አዳምና በቦስ ሲያናድዱን ወይ አንቺ ወይ
አኔ መኝታ ቤት ቁጭ ብለን የምናማቸው ነገረ አይ የኔ ነገር
ሚስጥር አወጣው አደል እና ጥሩነትሽን መቼም ቢሆን አረሳውም
አንቺም ልክ እንደ አዳም ስጦታዬ ነሽ አሁን የምሄድበት ስአት
እየደረስ ሰለሆነ ለሰራተኞቻችን የምወዳቸው ስዎች በጋራ ልፅፍ
ተገድጃለሁ።" የሚለው ጋራ አዳም ሲደረስ ሁሉም ፈገግ አሉ።
አዳም ማንበብን ቀጠለ።
፨"እናንተ ማለት ደሞ በቃ ምን ብዬ እንደምገልፆቹ አላውቅም
እናንተን ሰራተኞች ስል በጣም ይከፍኛል በጣም እናንተ ማለት
በቃ የእኛ ተንከባካቢ ፤መጋቢ ፤ሲከፋን አባባይ፤ በቃ ልክ እንደ
Selam Selam endet nachu aleme nesh kefl 39 zare mata yileqeqal yixebqun.38 demo letwesta bedgame leqenal
____
ራስህን ስጋት አታድርግ፡፡ መልካም ሰው ማንንም አያማርርም ። ያለፍቅር ሕይወት ዋጋ የለውም ፡፡ ፍቅር የሕይወት ውሃ ነው ፣ ፍቅርን የሚያቅ ሰው የነፍስ መብራት ነው። ሁሉም ነገር እና ሁሉም ሰው ከማይታዩ ብዙ ህብረቶች ጋር የተሳሰረ ነው።
ምን ዓይነት ፍቅርን መፈለግ እንዳለብህ አትጠይቅ…የምስራቃዊ ወይም ምዕራባዊ እያልክ ክፍፍል አትፍጠር፣ ያንተ ክፍፍሎች ወደ ብዙ መከፋፈል ከማምራት በቀር አንተን አይቀይሩህም፡፡ ፍቅር ስያሜ የለውም ፣ ትርጓሜ የለውም፡፡ንፁህ እና ቀላል ነው።
የሰዎችን ልብ አትስበር ፡፡ከአንተ ይልቅ ደካማ እንደሆኑ አርገህ ቁልቁል አትመልከት፡፡በአንደኛው የዓለም ክፍል ውስጥ ያለ ሀዘን መላውን ዓለም ሊያሰቃይ ይችላል ፣በዛው ልክ ደግሞ የአንድ ሰው ደስታ እና ፈገግታ መላውን ዓለም ፈገግ ሊያደርገው ይችላል።
አብዛኛዎቹ ግጭቶች እና ውጥረቶች በቋንቋ ምክንያት የሚከሰቱ ናቸው።ለቃላቶች በጣም ትኩረት ስጥ ፣ በፍቅር ሀገር ውስጥ ቋንቋ የራሱ የሆነ ቦታ የለውም።
ፍቅር ውብ ዝምታ ነው ፡፡
ከፍቅር ሌላ ምንም ዕዳ አይኑርባችሁ!!
@eiduka
ውድ የቻናሌ ቤተሰቦች ሰላም እንዴት ናቹ 🙏
ከዚ በፊት ሲተላለፍ የነበረው "አለሜ ነሽ" የተሰኘው ድርሰት በመቋረጡ ይቅርታ እየጠኩ አሁን ግን ከተቋረጠበት ክፍል ጀምሮ በቅርቡ ይቀጥላል!!
ሰዎች የነዱት ሰው ጸጸት
“ሌሎች ሰዎች ከእኔ የሚጠብቁብኝን ሳይሆን እኔው ራሴ ያመንኩበትን ሕይወት የመኖር ድፍረት ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ!”
ብሮኒ በመጀመሪያ የምትተርከው ግሬስ ስለምትባል በታላቅ ጸጸት ውስጥ ስላለች ሴት ነው፡፡ ግሬስ ከሃምሳ አመታት በላይ በጋብቻ ሕይወት አሳልፋለች፡፡ ግሬስ ከልቧ ከምትወዳቸው ልጆቿ ከምታገኘው ደስታ ባሻገር “የአስራዎቹ” አመታት ወጣት የልጅ ልጆች ማግኘቷ የማይጠገብ የደስታ ምንጭ ሆኖላታል፡፡ ሆኖም፣ ይህ ደስታዋ ሙሉ እንዳይሆን ያደረገባት አንድ ጥቁር ነጥብ ግን በሕይወቷ ነበር፡፡ ይህም ሁኔታ የባለቤቷ ጉዳይ ነበር፡፡
አምባ ገነንና ጨካኝ የሆነው ባለቤቷ ባሳለፉት አመታት ውስጥ ጋብቻን አስቸጋሪ ያደረገባት ሰው ነበር፡፡ ወደጋብቻ ከመጡበት እለት ጀምሮ የቅስም ሰባሪ ቃላትና የተለያዩ የክፉ ተግባሮች ሰለባ አድርጓታል፡፡ ይህንንም ሁኔታውን ለማስተካከል መውሰድ የነበረባት እርምጃዎች እንዳሉ ብታውቅም፣ አንዱንም ምርጫ ለመውሰድ ድፍረቱ ሳይኖራት ለአመታት ተቀጥቅጣ ኖራለች፡፡ የባለቤቷ አስቸጋሪነት እጅግ ከመክፋቱ የተነሳ ከጥቂት አመታት በፊት ከእርጅና የተነሳ በአረጋውያን መጦሪያ ማእከል በመግባቱ እርሷ ብቻ ሳትሆን ሁኔታውን የሚያወቁ ሰዎች ሁሉ ደስተኛ ነበሩ፡፡
ግሬስ በትዳር አመታቶቿ በሙሉ አንድ ቀን ከባሏ ክፉ ተጽእኖና ጨካኝ ሁኔታ ውጪ ሆና ደስተኛ ሕይወትን ለብቻዋ የምታጣጥምበትን ቀን እንደናፈቀች ኖራለች፡፡ አሁን በሰማኒያዎች አመታት ውስጥ ብትሆንም፣ ለእድሜዋ የሚመጥን መጠነኛ ጤንነትና የአካል ብቃት ነበራት፡፡ ወደማእከሉ ስትመጣ ወዲህ ወዲያ ለማለት የሚያበቃት አቅም ነበራት፡፡
እድሜዋን በሙሉ “በድብደባ” ያሳለፈው አእምሮዋ አሁን ለዚህ ሁኔታ ከዳረጋት ባለቤቷ በመለየቷ ምክንያት የእረፍትን ጭላንጭል ያየ ይመስላል፡፡ ለብዙ ዘመናት የጠበቀችውን ይህንን ለብቻ የመሆንና ካለምንም የውጪ ሰው ተጽእኖ የማሰብ “ነጻነት” ባገኘች በአጭር ጊዜ ውስጥ በድንገት በጽኑ መታመም ጀመረች፡፡ ሕመሙ ከተሰማት ከጥቂት ቀናት በኋላ ብዙም እድሜ እንደማይኖራት የሚጠቁም ምልክት ተገኘባት፡፡ ሁኔታውን እጅግ ልብን የሚሰብር ያደረገባት፣ የህመሙ መንስኤ ለብዙ አመታት ባለቤቷ በቤት ውስጥ ሲያጨስ ከነበረው የሲጃራ ጭስ እንደሆነም ማወቋ ነው፡፡ የበሽታው ደረጃ እጅግ ከመክፋቱ የተነሳ በአንድ ወር ውስጥ አቅሟን ሁሉ አጥታ የአልጋ ቁራኛ ሆነች፡፡
“ለምን ያንን ዘመን ሁሉ እኔ ያመንኩበትንና የፈለግሁትን ነገር አላደረኩም? ለምን እንደፈለገ እንዲገዛኝና እንዲያንገላታኝ ፈቀድኩለት?” የሚሉት ጥያቄዎች ካለማቋረጥ ከግሬስ አንደበት ሲወጣ ይደመጥ ነበር፡፡ ያመነችበትን ትክክለኛ ሕይወት ለመኖር ድፍረት ሳይኖራት ዘመኗ በማለፉ ምክንያት በራሷ ላይ እጅግ በጣም ትበሳጭ ነበር፡፡ ልጆቿም ቢሆኑ እንደፈለገ ባደረጋትና ባደረገባት ባሏ ምክንያት ስላሳለፈችው ከባድ ሕይወት በግልጽ ይመሰክሩ ነበር፡፡
“አንቺ ማድረግ የምትፈልጊውን ትክክለኛ ነገር ከማድረግ ማንም ሰው እንዲከለክልሽ አትፍቀጂለት” በማለት ለተንከባካቢዋ ለብሮኒ ደጋግማ ትነግራት ነበር፡፡ “እባክሽን ይህንን እኔ የሰራሁትን ስህተት እንዳትሰሪ ቃል ግቢልኝ” በማለት ታሳስባት ነበር፡፡ አንድ ቀን ግሬስ ይህንኑ ምክር ደግማ ከነገረቻት በኋላ፣ ብሮኒ በእሺታ ምክሯን ተቀብላ እንደምትተገብረው ቃል በመግባት፣ “ራስን የመቻልና ያመኑበትን ትክክለኛ ነገር የማድረግን ትምህርት ያስተማረችኝ እናት ስለነበረችኝ እድለኛ ነኝ” በማለት ለግሬስ ነገረቻት፡፡
“አሁን ያለሁበትን ሁኔታ ተመልከችው” አለች፣ ግሬስ በመቀጠል፡፡ “በመሞት ላይ ነኝ፡፡ በሞት አፋፍ! እንዴት ቢሆን ነው እነዚያን አመታት ሁሉ ነጻና ራሴን የቻልኩ ሆኜ ለመሆን ስጠብቅ ኖሬ፣ አሁን እዚያ የተመኘሁበት የሕይወት ምእራፍ ላይ የደረስኩ ሲመስለኝ ጊዜው ያለፈብኝ?” እነዚህን መራራ ቃላት የሰማችው ብሮኒ የግሬስ ሁኔታና ጸጸት እንድታስብ ያነሳሳትን እውነታ ማሰላሰል ጀመረች፡፡
የደረሰችበትም ድምዳሜ፣ “ማንኛውም ሰው የራሱን አመለካከት ማወቅ፣ ትክክለኛውን መንገድ መለየትና ያንንም ያመነበትን ትክክለኛ ጎዳና መከተል አለበት” የሚል ነበር፡፡
ግሬስ በውስጧ የምታምንበትንና የሚሰማትን ስሜት ሳይሆን የዚያን ተቃራኒ ገጽታን በውጪ እያንጸባረቀች ዘመኗን አባከነች፡፡ እድሜዋን በሙሉ እርሷ ያመነችበትንና ከነበረባት የጭካኔ ሰለባ የሚያወጣትን ሕይወት ሳይሆን ሌሎች ሰዎች ከእርሷ የሚጠብቁባትን አይነት ሕይወት ስትኖር ካሳለፈች በኋላ፣ አሁን በመጨረሻዎቹ አመቶቿ ምርጫው የእርሷ እንደነበርና፣ ፍርሃት ከትክክለኛው ምርጫ እንደገታት ተገነዘበች፡፡ ራሷን ይቅር የማለት አስፈላጊነት ቢነገራትም እንኳን አሁን ሌላ ምርጫ ያለውን ሕይወት ለመኖር ጊዜው ያለፈባት መሆኑን ስታስብ ከአቅሟ በላይ የሆነ ስሜት ይወርሳታል፡፡
ብሮኒ በሞት አፋፍ ላይ ያሉ ሰዎች በሚኖሩበት ማእከል ውስጥ ስትሰራ ካጠናቻቸው የሰዎች ጸጸቶች ይህኛው፣ “ሌሎች ሰዎች ከእኔ የሚጠብቁብኝን ሳይሆን እኔው ራሴ ያመንኩበትን ሕይወት የመኖር ድፍረት ኖሮኝ ቢሆን ኖሮ!” የሚለው ጸጸት አብዛኛዎቹን ሰዎች የሚያጠቃውና ቀንደኛው ነው፡፡ ብዙ ሰዎች የሕልማቸውን ግማሽ እንኳን ሳያጣጥሙ ዘመናቸው የሚያልፈው ያመኑበትን ትክክለኛ የሕይወት አቅጣጫ ለመከተል ምርጫ እንዳላቸው ካለማወቅና ወይም ትክክለኛውን ምርጫ እያወቁ ያንን ምርጫ ለመከተል ጉልበት ከማጣት የተነሳ ነው፡፡
ዶ/ር እዮብ
@eiduka🦋
