✞ ይታመናል TUBE 🇪🇹✞
Open in Telegram
የዚህ ቻናል ዓላማ:- 👉 የሚታመኑበትን ጌታ በዝማሬ ያመልኩታል። 👉ሌላው አስተማሪ የሆኑ መልክቶች ና ጽሑፎች እንለቃለን። ✦ መዝሙር ለመላክ እና ሀሳብ አስተያየት ለመስጠት በ @yetamenaltube_bot ላይ አድርሱን። 👉አጋር ቻናል የህይወት ዜማ Tube 👉አጋር ቻናል worship God @yetamenaltube
Show more1 643
Subscribers
+124 hours
+67 days
-230 days
Posts Archive
1 642
👉 ዛሬም ሆነ ነገ የማይቀየር ርዕሳችን "ኢ-የ-ሱ-ስ" ነው። የምሥራቹን ቃል ማብሠር ግዴታችን ስለሆነ የምንመካበት ነገር አይደለም፤ እንዲያውም የምሥራቹን ቃል ሳናበስር ብንቀር ወዮልን። (1ቆሮ.9፥16)
👉 ለዚህ የምሥራች ቃል እናገለግል ዘንድ የመረጠን ጌታ ስሙ ይባረክ!!! # # # እስከ አሁን ድረስ እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር ረድቶናል (አ-ቤ-ን-ኤ-ዘ-ር)
1 642
# # # "ዓይኖቼ ወደ ተራሮች አነሣሁ፤ ረዳቴ ከወዴት ይምጣ? ረዳቴ ሰማይና ምድርን ከሠራ
ከ-እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር ዘንድ ነው።" (መዝ 121፥1-2)
👉 ዓይኖቼን ወደ አንተ አነሳለሁ። አንተ ብቻ የልቤን ጓዳ ታውቃለህ፥ ቸል አትበለኝ መልስህን ላክልኝ። ዝም አትበለኝ በረከትህን ስደድልኝ፣ እንዳትረሳኝ ዘንበል በልልኝ። የኔ ከፍታ ተራራ አይደለም፤ የኔ ትልቁ ነገር አንተ ነህ። አንተ የነገሩህን የማትረሳ የለመኑህን የማትነሳ ረድዔቴ ሆይ ክበርልኝ።
👉 ረዳት ፍለጋ የሰው ደጅ አልጠናም፤ አንተ ለምኑኝ ብለሃል በፍፁም ትህትና ራሴን አዋርጄ እለምንሃለው። አትዘግይብኝ በቀንህ ድረስልኝ። ባቃተኝ ነገር ላይ ሙሉ አቅም ያለህ አንተ ነህና ድረስልኝ።
👉 በምትወደው ልጅህ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ለመንኩህ አንተም ስለሰማኸኝ ተመስገን!!! አሜን።
1 642
👉 ወዳጆቼ፥ ያለንበት ሁኔታ ለእኛ አልተመቸን፣ አልወደድነው ይሆናል፤ የምንፈልገው ስፍራ ላይ አልሆን ይሆናል፤ ነገር ግን ያስቀመጠን ህ-ል-ው-ና-ው ባለበት፣ ያኖረን መ-ገ-ኘ-ቱ ባለበት፣ ያሰፈረን እርሱ በ-ሚ-ገ-ዛ-በ-ት ክልል ውስጥ ነው።
👉 ስለዚህ ያለንበት ሁኔታ ባይመቸንም እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር ራሱን አምኖ ባለንበት አኑሮናልና የእርሱ አብሮነት እየታወሰን ልንደሰት ይገባል።
👉 የምንዘነጋው ነገር ቢኖር እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር እየጠቀመን የከለከለን ነገር የለም፣ የሚጎዳንንም ፈቅዶ አልሠጠንም።
👉 ያለንበት ሁኔታ ባያስደስተን እንኳን እግዚአብሔር የወደደውና የፈቀደው ነውና ደስ ይበለን። ከእኛ በላይ ስለ እኛ ግድ የሚለው እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር የእኛ አባት ነው።
1 642
👉 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናው አይመካ፤
👉 ነገር ግን የሚመካው፦ ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔን በማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር። (ኤርምያስ 9፥23-24)
1 642
👉 በስራ ላይ ያለ፣ አገልግሎት እየሰጠ ያለ ነገር ይደክማል፣ ጉልበቱ ይዝላል፣ ያረጃል። ስለዚህ ቆም አድርገን እድሳት ስናደርግለት ጉልበቱ ወጣት ይሆናል።
👉 ሕይወትም እንዲህ ናት ሁልጊዜ መኖር፣ መስራት፣ መሯሯጥ ብቻ ሳይሆን አንዳንዴም ቆም ብለን የትላንትና ጉዟችንን የምንፈትሽበት፣ ችግራችንን የምንለይበት፣ የቱ ጋር ወደቅን ምን ብናደርግ ነጋችንን እናሳምራለን ብለን ራሳችንን የምንፈትሽበት የጥሞና ጊዜ ያስፈልጋል።
1 642
👉 ያረጀ የወይን ጠጅ ጣፋጭ ይሆናል፥ ግን ጊዜ ይፈጃል ዋጋም ያስከፍላል። እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር-ም በህይወታችን የሚዘገየው የበሰለ ጣፋጩን ስጦታ ሊሰጠን ነው።
👉 እነ አብርሃም የተረሱ በመሰላቸው ሰዓት በረከታቸውን እንደታቀፉ እኛም የተረሳን በመሰለን ሰዓት የልመናችንን ጣፋጭ መልስ እንታቀፋለን፤ የተዘነጋን በመሰለን ሰዓት የጩኸታችንን፣ የፀሎታችንን፣ ዓመታት ያስቆጠረ የፀሎታችን መልስ እናገኛለን።
👉 ሁልጊዜ በማንኛውም ሁኔታዎች ውስጥ ስንሆን የጸናውን ማሰብ ይሁንልን!!!
1 642
# # # 2ኛ ቆሮ 1
👉 ³ የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።
👉 ⁴ እርሱ በመከራችን ሁሉ ያጽናናናል፥ ስለዚህም እኛ ራሳችን በእግዚአብሔር በምንጽናናበት መጽናናት በመከራ ሁሉ ያሉትን ማጽናናት እንችላለን።
1 642
👉 ለመጫወቻ ቦታ፣ ለመነጋገር ስፍራ፣ ለመመገብ ቤት እንደሚያስፈልግ ሁሉ፥ ለማልቀስም ዕንባን ተቀባይ፣ ዕንባን አንባቢ ያስፈልገናል።
👉 ሁሉ ነገር ለሰው አይነገርም፤ ሁሉም ነገር አይተነፈስም። ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ፥ አንተ ጋር ግን ያለ ምንም ፕሮቶኮል ያለ ምንም ይሉኝታ ነፍሳችንን እናፈሳለን።
አንተን ላለ አንተ አለህለት።
1 642
👉 ወንድሞቼ ሆይ፤ ልዩ ልዩ መከራ ሲደርስባችሁ እንደ ሙሉ ደስታ ቍጠሩት፤
👉 ምክንያቱም የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንደሚያስገኝ ታውቃላችሁ።
👉 ምንም የማይጐድላችሁ ፍጹማንና ምሉኣን እንድትሆኑ ትዕግሥት ሥራውን ይፈጽም። (ያዕቆብ 1፥2-4) (አዲሱ መ.ት)
1 642
👉 ፊቱ ብናለቅስ የማይታዘበን፣ ማጣታችንን ብንነግረው የማይጠየፈን፣ ኃጢአታችንን እያወቀ የሚያቅፈን፣ ሸክማችንን የሚያራግፍልን ብቸኛና እውነተኛ ወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
👉 ሰው ንቋችኋል እርሱ ግን ከእናንተ ጋር ማዕድ ይቆርሳል። ሳንፈልገው ፈልጎን በራችንን ያንኳኳል፣ ራሳችንን እየዳበሰ ያጽናናናል። ስሙ ብሩክ ይሁን!!!
1 642
# # # ሮሜ 10
👉 ⁹ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤
👉 ¹⁰ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና።
👉 ¹¹ መጽሐፍ፦ በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና።
1 642
👉 ወጥነት ሕይወት ለመኖር ብቸኛውና ተመራጩ ነገር ከ-እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር ጋር በ-ሕ-ል-ው-ና-ው መቆየት ወይም መሰንበት ነው።
1 642
👉 ሰው እ-ኔ-ነ-ት-ን ብቻ ገንዘቡ ሲያደርግ ከሰውም ከ-እ-ግ-ዚ-አ-ብ-ሔ-ር-ም ይነጠላል። ክርስትና ከ-እ-ኔ-ነ-ት ወደ እ-ኛ-ነ-ት መለወጥ ነው። እውነተኛ መንፈሳዊ ሕይወትም የሚጀምረው ከ-እ-ኔ-ነ-ት ወደ "እ-ኛ-ነ-ት" ስንሻገር ነው።
👉 ወዳጆቼ፥ በእኔነት የምናሳካው ስኬት የምንደርስበት ከፍታ የለምና፥ ጌታ እንዲህ ካለው ከሚጸየፈው በሽታ ያርቀን ዘንድ የልቦናችንን ዓይኖች ይክፈትልን። አሜን!!!
1 642
👉 ወዳጆቼ፥ መንገዳችሁ ከእሾህና ከእንቅፋት የጠራ፣ ህይወታችሁ ደግሞ እንደ ማለዳ ፀሐይ ብሩህና ተስፋ የሞላበት ይሁን። በብዙ ተባረኩ!!!
1 642
👉 ወዳጆቼ፥ ክ-ር-ስ-ቶ-ስ-ን መምሰል መከራንም ይጠይቃል። ጌታችን እንዲህ አለ፦ "ማንም ሊከተለኝ ቢወድ፥ ራሱን ይካድ፥ መስቀሉንም በየቀኑ ተሸክሞ ይከተለኝ።" (ማቴዎስ 16፥24)
👉 እርሱን መከተል ምቾትን ከመፈለግ ይልቅ ለእውነት መቆምን ይጠይቃል። ክ-ር-ስ-ት-ና-ች-ን መምሰልን እየተወ ማስመሰልን መልመድ የለበትም። ክ-ር-ስ-ቶ-ስ-ን መምሰል የራስን ዝቅ ማድረግ ጌታን ማጉላት ነው።
👉 ሰዎች እኛን ሲመለከቱ ክ-ር-ስ-ቶ-ስ-ን ማየት ይሁንላቸው። የእርሱን ፈለግ መከተል፣ የእግሩን ዱካ እየረገጥን መሄድ ይሁንልን። ትህትናህን ያልብሰን፣ ፍቅሩን በልባችን ይሙላ። መንፈስ ቅዱስ በነገር ሁሉ ይርዳን። የምንሠራው ሁሉ ለክብሩ ይሁን። አሜን!!!
