en
Feedback
ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ

Open in Telegram

ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።

Show more
636
Subscribers
No data24 hours
-47 days
-1130 days
Posts Archive
                          ✝ ✝ ✝   ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ቡሩክ ዘይመጽእ በስመ እግዚአብሔር። ባረክናክሙ እምቤተ እግዚአብሔር። እግዚአብሔር እግዚእነ አስተርአየ ለነ"። መዝ 117፥25-26። የሚነበቡት መልዕታት ገላ 4፥12- 21፣ 1ኛ ዮሐ 5፥1-9 እና የሐዋ ሥራ 22፥16-20 የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥1-14። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ።  መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ❤ ❤ "#የተባረከ_የሚያዝያ_ወር_ቀኑ_ዐሥራ_ሦስት ሰዓት ሲሆን ከዚያም ይጨምራል" ።             ❤ #ሚያዝያ ፩ (1) ቀን። ❤ እንኳን #ለካህኑ_ለቅዱስ_አሮን (ለሊቀ ነቢያት #ለቅዱስ_ሙሴ_ወንድሙ) ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ለከበረ አባት የሲዖል ሥቃይ አይቶ "ወደዘላለም ጨለማ ሊወስዱኝ ዛሬ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ብርሃን ማየት አልሻም" እያለ ፊቱን በቆብ ሽፍኖ ዕድሜው ሙሉ ሲያለቅስ ለነበረ #ለአባ_ስልዋኖስ ለዕረፍት በዓልና #ለቅድስት_መጥሮንያ_ለዕረፍቱ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱስ_አበከረዙንም ጋር በሰማዕትነት ከዐረፉ #ከቅዱስ_ዮስጦስና_ከሚስቱ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን በእስክንድርያ ከተማ በሚገኝ በግብጻውያን መጽሐፍ እንደ ተጻፈ በላዕላይ ግብጽ ያለ ግብጻዊውም እንደተጻፈ ለእንበረም ልጅ #ለቅዱስ_ሙሴ_ወንድሙ_ለሆነ_የካህኑ_ቅዱስ_አሮን የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ ይላሉ። ❤ በኦሪቱ መጽሐፍ የተጻፈው ግን እስራኤል ከግብጽ ከወጡ በሁለተኛው ወር በሦስተኛው ቀን ዐረፈ ይላል። ይኸውም ግንቦት ስምንት ነበር የእስራኤል ወሮች በጨረቃ እየተቈጠሩ ዓመቱን ስለሚዞሩ በዚያች ዓመት ሚያዝያ አንድ ቀን ሁኖ ስለተገኘ። ❤ በእኛ(በኢ.ኦ.ተ) ዘንድ ግን የኦሪት ዘኊልቊ መጽሐፍ በአምስተኛው ወር መባቻ ስለሚል መታሰቢያውን ነሐሴ አንድ ቀን እናደርጋለን።                                 + + + ❤ ካህኑ ቅዱስ አሮን፦ ይህም ሰው የነቢያት አለቃ ለኦሪት ሕግ መምህር ለሆነ ለሙሴ ለነቢዪት ማርያምም ወንድም ነው እርሱም ከሌዊ ነገድ ነው። ❤ እግዚአብሔርም በግብጽ ምድር ብዙ አስደናቂ ተአምራትን በእጆቹ አደረገ። እግዚአብሔርም እርሱንና ልጆቹን መርጦ ካህናቶቹ አድርጎ ከእስራኤል ልጆች ከገንዘባቸውና ከመሥዋዕታቸውም ዓሥራትን ሰጣቸው። የቆሬም ልጆች በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ እግዚአብሔር ፈርዶ አጠፋቸው ምድርንም አዘዛት አፍዋንም ከፍታ ዋጠቻቸው። ❤ በበጎ ተጋድሎውና የኦሪትንም ሕግ በመጠበቅ እግዚአብሔርን ከአገለገለ በኋላ የክብር ባለቤት ወደሆነ እግዚአብሔር ሔደ። የካህኑ የቅዱስ አሮን ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለም ትኑር አሜን።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_ስልዋኖስ፦ ይህም አባት በአስቄጥስ ገዳም ከከበረ አባ መቃርስ ዘንድ በታናሽነቱ መነኰሰ በጠባብ መንገድ ሁሉ ተጋደለ በብዙ ጾምና ጸሎት በመትጋት በትሕትና በፍቅር ተወስኖ ኖረ ታላቅ አባትም ሆነ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችንም አምላካዊ ራእይን ይገልጽልት ነበር ድንቅ የሆኑ ነገሮችንም ይነግረዋል። ይህም እንዲህ ነው በአንዲት ዕለት ልቡ ተመስጦ በምድር ላይ በግምባሩ ተደፍቶ ብዙ ጊዜ ቆየ በዚያም በኋላ ነቅቶ ራሱን ቀና አደረገ። ከእርሱ ዘንድ ያሉ ወንድሞች መነኰሳትም በእርሱ ላይ የደረሰበትን ይነግራቸው ዘንድ ለመኑት ዝም ብሎ መሪር ልቅሶ ያለቅሳል እንጂ ሊነግራቸው አልወደደም። ከእርሱ የሆነውን ያስረዳቸው ዘንድ ግድ ባሉት ጊዜ እንዲህ አላቸው "ተድላ ወዳለበት ገነት አውጥተውኝ በዚያ የጻድቃንን መኖሪያ አየሁ ደግሞ የሥቃይ ቦታዎችንም። ሁለተኛም ብዙዎች መነኰሳትን ወደ ገሀነም ብዙዎች ምዕመናን ወደ መንግሥተ ሰማያት ሲወስዷቸው አየሁ እንግዲህ እኔ ለነፍሴ የማላለቅስ ለምድንድነው" አላቸው። ከዚያች ቀንም ጀምሮ "በኋላ ወደዘላለም ጨለማ ሊወስዱኝ ዛሬ የዚህን የኃላፊውን ዓለም ብርሃን ማየት አልሻም" እያለ ፊቱን በቆብ ሽፍኖ የሚያለቅስ ሆነ። ❤ ይህም አባት በመንፈሳዊ ሥራ የተጠመደ ሆነ ደቀ መዛሙርቱንም ለምግባቸው የሚሆን ሥራን ከመሥራት እንዳያቋርጡ ከዕለት ምግባቸው የሚተርፈውንም እንዲመጸውቱ ያዛቸዋል። ❤ በአንዲት ቀንም አንድ ታካች የሆነ መነኰስ ወደርሱ መጣ ሽማግሌውን አባትና ደቀ መዛሙርቱን ሲሠሩ አይቷቸው "ለኃላፊ ምግብ ትሠራላችሁ ትደክማላችሁ የዘላለም ሕይወት ለሚሆን ምግብ ሥሩ ድከሙ እንጂ ይህ በከበረ ወንጌል የተጻፈ አይደለምን "ማርያምም የማይቀሟትን በጎ ዕድል ትምህርትን አንደመረጠች" ብሎ ጠቀሰ። ሽማግሎው አባ ስልዋኖስም እንዲህ ሲናገር በሰማው ጊዜ ደቀ መዝሙሩን እንዲህ ሲል አዘዘው "ይህን መነኰስ ከእንግዳ ማሳረፊያ ቤት አስገብተህ የሚያነበው መጽሐፍ ስጠው በሩንም በላዩ ዝጋ በእርሱ ዘንድም ለመብል የሚሆን ምንም ምን አትተው "። ረድኡም ሽማግሌው መምህሩ እንዳዘዘው አደረገ። ዘጠኝ ሰዓትም ሲሆን መነኰሳቱ ተሰበሰቡ ከሽማግሌው አባትም ጋር ጸሎት አድርገው ምግባቸውን ተመገቡ። ያን እንግዳ መነኰስ ግን አልጠሩትም እርሱም ቢጠሩኝ ብሎ ወደ ደጃፍ እየተመለከተ ይጠብቅ ነበር። በረኃብም በተቃጠለ ጊዜ ከበዓቱ ወጥቶ ወደ አባ ስልዋኖስ ሒዶ "አባቴ ሆይ መነኰሳቱ ራታቸውን በሉን" አለው ሽግሌውም "አዎን በሉ" ብሎ መለሰለት። ሁለተኛ ደግሞ "እኔ እንግዳ ስሆን ለምን አልጠራችሁኝም" አለ የከበረ አባት ስልዋኖስም "አንተማ ሥጋዊ መብል የማትሻ መንፈሳዊ ሰው ነህ በጎ ዕድልን ስለመረጥክ እኛ ግን ሥጋዊያን ሰዎች ለሥጋዊ መብል የምንሠራ የምንደክም ነን ስለዚህም ለምግባች የሚሆነውን በእጃችን እንሠራለን" ብሎ መለሰለት። ያ መነኰስም በንግግሩ እንደበደለ አወቀ። አባ ስልዋኖስንም "አባቴ ሆይ እኔ በድያለሁና ይቅር በለኝ" ብሎ ሰገደለት። ❤ አባ ስልዋኖስም " ማርታ በመሥራት እንደ ደከመች እንድከም እንሥራ ከማርያም ይልቅ ማርታ የተዘጋጀች ሁናለችና" ብሎ መለሰለት። ያ ታካች የነበረ መነኰስም በዚህ አባት ትምህርት ተመክሮና ተገሥጾ ሁልጊዜ የሚሠራና ከእርሱ የሚተርፈውንም ለድኆች የሚመጸውት ሆነ። ❤ ይህም አባት ስለ መንፈሳዊ ተጋድሎ ጥቅም ያላቸው ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ። ❤ ዕድሜውም በመልካም ሽምግልና በተፈጸመ ጊዜ የሚያርፍባትን ሰዓት እግዚአብሔር ነገሮት በእርሱ አቅራቢያ ያሉ መነኰሳትን ጠርቶ ከእርሳቸው በረከትን ተቀበለ። በጸሎታቸውም እንዲያስቡት ለመናቸው እርሱም በእግዚአብሔር ዘንድ እንዲያስባቸው ለመኑት እርስበርሳቸውም ተሰነባበተው በፍቅር በሰላም ሚያዝያ1 ዐረፈ። የአባ ስልዋኖስ ጸሎቱ በረከቱ ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን ደግሞ በላይኛው ግብጽ ያሉ ዐረቦች ተሰብሰበው በአስቄጥስ ያሉ አድባራትናንና ገዳማትን የአባ መቃርስንም ቤተ ክርስቲያን ከበቡ በአድባራቱና በገዳማቱ ያለውንም ዕቃ ሁሉ ማረኩ። መነኰሳትም ተሰበሰቡ በከበረ አባቶችም ስም ወደ እግዚአብሔር በጸሎት ማለዱ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እነዚያን ዓረቦች አስደግጦ አሳደዳቸው ያንጊዜም ማንም የተከተላቸው ሳይኖር ድል ሁነው ሸሹ። ከክብር ባለቤት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በቀር ማንም የተከተላቸው ሳይኖር ነው። ይቅር ብሏቸዋልና ጌታችንን አመሰገኑት ለእርሱም ክብር ምስጋና ገንዘቡ ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ1 ስንክሳር።                           ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለስልዋኖስ_ቢጸ_መላእክት_ዘኮነ። ፍትወተ ዓለም እምልቡ እስመ ተመነነ። እምአመ ርዕየ ጽልመተ ኃጥአን ደይነ። በቆብዐ ርእሱ ገጾ ከደነ። ህየንተ በዘምድር ይርአይ በሰማይ ብርሃን"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የሚያዝያ_1።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤             ❤ #መጋቢት ፴ (30) ቀን። ❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ ድርሳነ ቅዱስ ሚካኤልንና ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤልን ለደረሱት ለታላቁ አባት #ለአባ_ዮሐንስ_አፈቅራዊ_ዘአክሱም ለዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #አቡነ_ዮሐንስ_አፈቅራዊ_ዘአክሱም፦ የተባሉት ኢትዮጵያዊው ጻድቅ የአክሱም ሊቀ ጳጳስ የነበሩ ሲሆን በድርሰታቸው የታወቁ ስለሆኑ ዳግማዊ ዮሐንስ አፈወርቅ የሚል ስያሜ የተሰጣቸውና ግብፃዊያንም በጣም የሚያከብሯቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ድርሳነ ቅዱስ ሚካኤልንና ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤልን የደረሱ አባት ናቸው፡፡ ድርሳኑንም ሲጽፉ ቅዱስ ሚካኤል ይመራቸው ነበር፡፡ በደብረ ዳሞ ተቀምጠው ዘጠኙ ቅዱሳን ያመጧቸውን ከ300 በላይ የሚሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሰብስበው እንደገና በልዩ አምስት ዓምድ አድርገው አዘጋጅተው ያስቀመጡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ አባታችን ተደግፈው ይጸልዩባት የነበረችው ዛፍ እርሳቸው ከማረፋቸው በፊት ለመነኮሳቱ "አባታችን ዛሬ ያርፋልና ተጠንቀቁ" ብላ አስቀድማ የተናገረችላቸው ጻድቅ ናቸው፡፡ ገድላቸው በደብረ ዳሞ፣ በደብረ ጽሞና፣ በገዳመ ሞጊና፣ በአክሱም፣ በጣና፣ በደብረ በንኮል ይገኛል፡፡ ከአባታች አቡነ ዮሐንስ አፈቅራዊ ዘአክሱም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።

❤ ምሕረትንና ርኅራኄን የተመላች እመቤቴ የብርሃን እናት ድንግል ማርያም ይህን ስትናገረኝ እንሆ በእጃቸው የጦር መሣሪያ የያዙ ኃይለኖች ሰዎችን የተመሉ መርከቦችን በቅርብ አየኋቸው እጅግም ፈራሁ እመቤቴ ማርያምም ተሠወረችኝ። ነገር ግን ከደመና ውስጥ "ማጥመቅንም አታቋርጥ" የሚለኝን ቃል እሰማ ነበር። እኔም በታላቅ ቃል "ፈጣሪዬ ሆይ ይህን የባሕር ውኃ ለእሊህ ለተጣሉ በጎች ሰይጣንም ለማረካቸው ጥምቀትን አድርገው ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በዚህ ባሕር ጥምቀት እሊህን ሰዎች በሦስትነትህ ስሞች የልጅነትን ክብር የሚቀበሉ አድርጋቸው" በማለት አሰምቼ ተናገርኩ። እንዲህም ይህን እያልኩ ከባሕሩ ውኃ ዘግኜ ሰዎች በአሉባቸው መርኮቦች በላያቸው ረጨሁት የሰዎቹም ቁጥራቸው አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ነው። ❤ እኔ ወደአለሁበት የባሕር ዳር በደረሱ ጊዜ ከመርከባቸው ወጥተው ፈለጉኝ እኔም እመቤቴ የብርሃን እናት እንዳዘችኝ በፊታቸው ቆምኩ በረድኤቷ ተማምኛለሁና አልፈራሁም። በአዩኝም ጊዜ ሁሉም በፊቴ ሰገዱ በአንድ ቃልም "ቅዱስ ጳውሎስ ሆይ ፍቅር አንድነት ለአንተ ይሁን ወደአንተ ከመድረሳችን በፊት በመርከቦች ውስጥ እያለን እኛ ያየነውን አየህን?" አሉኝ። እኔም "አዲስ የተወለዳችሁ ልጆች ሆይ ምን አያችሁ?" አልኋቸው "የሰማይ ደጆች ተከፍተው የቀኝ እጅ እንደ እሳት ነበልባል ተዘርግታ አየን ደግሞ የፊቷ ብርሃን ከፀሐይ ሰባት እጅ የሚበራ ሴት አየን። እርሷም ከደመና በታች የምትረጨውን ውኃ ተቀብላ በላያችን ትረጨዋለች ትስመናለች ታቅፈናለችም። በራሶቻችንም ላይ የብርሃን አክሊሎችን ታደርጋለች" አሉኝ። ይህንንም በሰማሁ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለኝ በስሙ በምንሠራው ሥራ ሁሉ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር እንዳለ ተረዳሁ። ❤ ከዚህም በኋላ ሌሎች መርከቦች መጡ ኃይለኞች ሰዎችን ከጦር መሣሪያ ጋር የተመሉ ናቸው እንዲህም እያሉ ዛቱብኝ "አንተ ሥራየኛ ጥበበኞች ሕርምስና በለንዮስ ታምራት የሚያደርጉባቸው የጠልሰም መጻሕፍቶች ከእኛ ጋራ እንዳሉ ዕወቅ" በማለት እኔም "ቸር ፈጣሪዬ ሆይ የቀደሙትን በጎች ይቅር እንዳልካቸውና በውስጣቸው ኃይልህን እንደገለጥክ ለእነዚህም እንዲሁ ኃይልህን ግለጥ ይቅር በላቸው" አልኩ። ከዚያም በኋላ ከባሕሩ ውኃ ዘግኜ በላያቸው ረጨሁ "ይህ ውኃ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥምቀትን ይሁናችሁ" አልኩ ወዲያውኑ መርኮቦች ከባሕሩ ዳር ደረሱ። ሁሉም ሰዎች ከመርከብ ወጥተው በፊቴ ሰገዱ "የቸር አምላክ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሆይ እናመሰግንሃለን" አሉኝ። ይህንንም ድንቅ ተአምር ከቀደሙት ባልንጀሮቻቸው ጋራ ተነጋገሩ ዜናዬም በዚያች አገር ንጉሥ ዘንድ ተሰማ እርሱም ከሠራዊቱ ጋራ ተነሣ በመርከቦችም ተጭነው ወደእኔ መጡ። እኔም ዓይኖቼን ወደ ሰማይ አቅንቼ የፈጣሪዬን ስም ጠራሁ ባሕርዋንም በመስቀል ምልክት አማተቡኩባት። እንዲህም አልኳት "አንቺ ባሕር በእግዚአብሔር ልጅ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ትከፈዪ ዘንድ አዝሻለሁ ምድሩም ይገለጥ መርከቦችም በየብስ ውስጥ ይቁሙ"። ነገሬም ሳልጨርስ ባሕርዋ ተከፈለች በውስጥዋም ዐሥራ ሦስት ጎዳናዎች ተገለጡ መርከቦችም ውኃ በሌለው ምድር ላይ ቆሙ ይህንንም አይተው ሰይፎቻቸውን መዘዙ ዕንጨቶችም ሁነው አገኟቸው እኔም ከባሕሩ ውኃ ዘግኜ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያልኩ በላያቸው ረጨው። በዚያን ጊዜ እሊያ መርከቦች ነፋስ ተሸክሟቸው ያለ ውኃ ከምድር ከፍ ከፍ ብለው ተጓዙ ሰዎችም ከውስጣቸው ወጥተው ወደእኔ መጥተው ሰገዱ። ከእርሳቸው የቀደሙ ሰዎች ሰላምታ እንዳቀረቡልኝ ንጉሡም ከአገር ሰዎች ሁሉ ጋር በፊቴ ሰገደ። ❤ ከዚያም በኋላ ከእርሳቸው ጋር ወሰዱኝ ወደ ከተማውም በደረቅ ያለ መርከብ ገባን በምኵራባቸውም ተከልለው የሥንዴ እሸትም እንደ መሥዋዕት ሁኖ ተጥሎ አየሁ ይህንንም አይቼ እጅግ አዘንኩ። የአገር ሰዎችም "ክቡር መምህር ሆይ በዚች ዕለት ለአማልክት በዓል የምናደርግባት እንደ ነበረ ዕወቅ አሁን አንተ ለማን ታዘናለህ ለአብ እናድርገውን ወይም በወልድ ስም ወይም በመንፈስ ቅዱስ ስም በስማቸው ያጠመቅከን ስለሆነ" አሉኝ። ❤ እኔም "እግዚአብሔርን ያመልኩት ዘንድ የሚገባቸውን ሃይማኖትን አስተማርኳቸው መጻሕፍትንም በእጄ ጻፍኩላቸው። በአማላጅነቷ ከርኵስ ሰይጣን ተገዥነት ስለዳኑ ያንን በዓል የብርሃን እናት በሆች በእመቤታችን በድንግል ማርያም ስም እንዲያደርጉት አዘዝኋቸው ዕለቱም የእግዚአብሔርን ልጅ እንደምትፀንሰውና በሥጋ እንደምትወልደው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ያበሠረበት ስለሆነ። ❤ እኔም አምላካዊ ትምህርት አስተማርኳቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አደረግኋቸው ውኃው በተከፈለበትም ላይ በእመቤታችን ድንግል ማርያም ስም ታላቅ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ አዘዝኳቸው። በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራቶችንም አደረኩላቸው። ከዚያ በኋላ ከእርሱ ዘንድ ወጥቼ መጣሁ"። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የአባታችን የሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ በረከቱም በላያችን ይደር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት29 ስንክሳር።                                                                  ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለፅንሰትከ_በከርሠ_ማርያም_ፅሌ። መጽሐፈ ሐሤት ክርስቶስ ዘኢኮንከ መጽሐፈ ወይሌ። ሶበ ርእዩከ በታሕቱ እንዘ ኢተዓርቀ እምሉዔሌ። አእኰቱከ ቃለ አኰቴት በሃሌ። ሰላም በምድር ወበሰማይ ሃሌ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_27።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አንሰ ተሠየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ። በጽዮን በደብረ መቅደሱ። ከመ እንግር ትእዛዞ ለእግዚአብሔር"። መዝ 2፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥26-39።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አንተ እግዚኦ አቅደምከ ሣርሮታ ለምድር። ወግብረ እደዊከ እማንቱ ሰማያት። እማንቱሰ ይትኃጎላ ወአንተሰ ትሄሉ"። መዝ 101፥25 ወይም 109፥3። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 1፥1-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 1፥13-22 እና የሐዋ ሥራ 17፥13-30። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥1-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ  ነው። መልካም የጌታችን የጽንሰት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #መጋቢት ፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ለበኵረ በዓላት ለሆነ #ለጽንሰት በዓልና፣ #ለጥንት_ትንሣኤ_በዓል፣ ዓለም ለተፈጠረበት ቀንና #ለሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ እልዋሪቆን በምትባል አገር ገብቶ #በእመቤታችን_በቅድስት_ድንግል_ማርያም ረዳትነት (አማላጅነት) ላስተማረበትና ብዙ ሺህ ሰዎች በጌታችን ስም ላጠመቀበት በሰላም አደረሰን።                                                    ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ቀን #ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም_የከበረ_መልአክ_ቅዱስ_ገብርኤል_የምሥራች የነገረበት ድኅነትን የተመላች ታላቅ በዓል ናት። ❤ በዚህም የከበረ ወንጌል ምስክር ሁኗል እንዲህ ሲል፦ "ቅድስት ኤልሳቤጥ ከፀነሰች በኋላ በስድስተኛው ወር ቅዱስ ገብርኤል የገሊላ ክፍል የሆነች ናዝሬት ወደምትባል አገር ከዳዊት ወገን ለሆነ ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ። የድንግሊቱም ስም ማርያም ነው። መልአኩም ወደርሷ ገብቶ "ደስተኛ የሆንሽ ደስ ይበልሽ ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ" አላት። ❤ እርስዋም አይታ ከንግግሩ የተነሣ ደንግጣ "እንዲህ ያለ ሰላምታ ይቀበሏል" ብላ አሰበች። መልአኩም እንዲህ አላት "ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻልና አትፍሪ። እንሆ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ እርሱ ታላቅ ነው የልዑል እግዚአብሔር ልጅም ይባላል። እግዚአብሔር አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል ለያዕቆብ ወገንም ለዘላለም ነግሦ ይኖራል ለመግሥቱም ፍጻሜ የለውም" አላት።ማርያምም መልአኩን "ወንድ ሳላውቅ ይህ እንደምን ይሆናል" አለችው። መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት "መንፈስ ቅዱስ መጥቶ ያድርብሻል የልዑል ኃይልም ያጸናሻል ከአንቺ የሚወለደው ከሦስቱ አካል አንዱ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ይባላል። እንሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥም እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ፀንሳለች ወንድ ልጅም አገኘች ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና። ማርምም "እንሆኝ የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ" አለችው። ❤ ያን ጊዜም ድንግል ስትሆን ረቂቅ ፅንስን ተቀበለች የእግዚአብሔር አካላዊ ቃል ወልድ ዋህድ ለኩነተ ሥጋ ወርዶአልና ይህም አንድ ባሕርይ አንድ ህልውና ሲሆን ከሦስቱ አካል አንዱ ነው ከዓለም መፈጠር አስቀድሞ የነበረ በማይመረመር ድንቅ በሆነ ተዋሕዶ እንዴትም እንደሆነ በማይታወቅ በቅድስት ድንግል ማርያም ማሕፀን አደረ ፅንስ ሁኖ ኖረ። በዚያን ጊዜም የኋላ ኋላ መለየት ከቶ የሌለው ፍጹም ሰውነት ነሥቶ ተዋሐደ መለኮቱ ከትስብእቱ ጋራ ያለ መለያየት አንድ ሁኖአልና። ❤ ይቺም ዕለት የበዓላት ሁሉ በኵር ናት በእርሷም የዓለም ድኅነት ተጀምሮዋልና። ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቸር አባቱና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስ ጋር ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ዕለት ደግሞ በመድኃኒታችን በከበረች ልዩ በሆነች ትንሣኤው የዓለም ድኅነት ሆነ በረቀቀ ጥበቡ ሠላሳ ሦስት ዓመት ያህል በምድር ላይ ሥራውን ሠርቶ በፈጸመ ጊዜ በፈቃዱ ሕማማተ መስቀል ተቀብሎ ሙቶ ከተቀበረ በኋላ በሦስተኛው በዚች ቀን በሃያ ዘጠኝ ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷልና። ❤ በዚች ቀን አስቀድሞ ደጅ ለሚጠኑት በዓለም ላሉ ሰዎች ሰው በመሆኑ ድኅነታቸውን አበሠራቸው እንዲሁም ደግሞ በዚች ዕለት ከሲኦል በመዳን ሙታንና ሕያውን ደስ አላቸው በዚች በጌታችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መነሣት መነሣታቸውን አረጋገጡ የከበረ ቅዱስ ጳውሎስ በመነሣቱ ክርስቶስ የሙታን በኵር ሆነ እንዳለ እርሱ ለሙታን በኵራቸው ነውና። ለእርሱም ክብር ምስጋና ለዘላለሙ ይሁን አሜን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የከበረ_ሐዋርያ_ቅዱስ_ጳውሎስ እልዋሪቆን ከምትባል አገር ደርሶ አስተማረ ይቺም ምድር ዳርቻ ናት። ራሱ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ አለ "ከዚያም በእግዚአብሔር መልአክ ትዕዛዝ ወደዚያች አገር ሔድኩ አገሪቱም እንደ ሮሜ አምሳል ታላቅ የሆነች እጅግ ውብ ናት ፍሬዋም የበዛ ነው። በውስጡ የሚታለፍበት ስሙ ገርጋ የሚባል ባሕር ግን አግድመቱ ሦስት መቶ ምዕራፍ ነው። ❤ መጋቢት ሃያ ሰባት ቀንም በመጀመሪያ ከዚያ ከባሕሩ ዳርቻ ደረስኩ ለአገሩም ሰዎች በዓላቸው ነበር የጽጌ ረዳ አክሊልም እየታቱ በጣዖቶቻቸው ራስ ላይ ያኖራሉ ከስንዴአቸውም አዲስ እሸትን ለጣዖቶቻቸው ያቀርባሉ። የአገር ጠባቂ የሚሉትም በጠልሰም የተቀረጸ ሥዕል በአገሩ ቅጽር ላይ ተደርጓል ወደዚያች አገር የሚመጣ እንግዳ ሰው ሲያይ በላዩ ያደረ ርኵስ መንፈስ በታላቅ ድምጽ ይጮኻል። የአገር ሰዎችም የዚያን ጠልሰም ጩኸቱን በሚሰሙ ጊዜ ወደ አገራቸው የመጣውን እንግዳ ወጥተው ይገድሉታል ሕጋቸው እንዲሁ ነውና ወደ አገራቸው ይገባ ዘንድ ማንንም አይተዉም አያሰናብቱም። ❤ እኔም ወደዚያች አገር ደርሼ ወደ ባሕሩ በቀረብኩ ጊዜ ያ ጠለሰም እንሆ እንግዳ ወደ እናንተ ደረሰ ብሎ በአገራቸው ቋንቋ ጮኸ። የአገር ሰዎችም ድምፁን ሰምተው ከንጉሣቸው ጋራ ብዙ ሠራዊት መጡ በዚያን ጊዜ ስለ በዓላቸው ተሰብስበው ነበርና ፈለጉኝ እኔ ግን የአሽኮኮዎች መሸሻ ወደ ሆነ ዋሻ ገባሁ። ከዚያም ገብቼ በረሀብና በጥም ስለተሠቃየሁ አለቀስኩ። በዚያን ቀን የፀሐይ ትኩሳት ከመጽናቱ የተነሣ ሐሩር ሆኖ ነበርና በዚያም እስከ ሌሊት ቆይቼ ከዚያ ወጥቼ ከባሕሩ ውኃ ጠጣሁ ቁሜም ወደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለይኩ። ❤ ንጋትም በሆነ ጊዜ ከዚያ ዋሻ ወጥቼ ወደ አገር ለመግባት ፈለግሁ። ያ ጠለሰም አሁንም መምጣቴን እየገለጠ ሁለተኛ እንደ ታላቅ ነጐድጓድ ጮኸ ለባሕሩም ልማድ አለው ጠለሰሙ በሚጮኸ ጊዜ ይታወካል ማዕበሉም ይነሣል ያን ጊዜም ያገር ሰዎች ሊገድሉኝ መጡ። ከሩቅ በአየኋቸውም ጊዜ ፈራሁ እንደቀድሞውም በዚያ ዋሻ ደግሜ ተሸሸግሁ ጌታ ክርስቶስንም እለምነው ዘንድ ጀመርኩ በአባት በቅዱስ ጴጥሮስ ጸሎት ተማፀንኩ በወንድሞቼ በሐዋርያትም ጸሎት። ይልቁንም ንጽሕት ድንግል በሆነች በብርሃን እናት በእመቤታችን ማርያም በአማላጅነቷ ተማፀንኩ በሌሊቱ ርዝመት ሁሉ ስጸልይ አደርኩ። ❤ በነጋም ጊዜ ወደ ባሕሩ ዳር ወጣሁ ያም ጠልሰም እንደ ልማዱ ጮኸ ተራራዎችም እስቲናወጹ ጨኸቱን አበዛ የባሕሩም ማዕበል ታወከ። ውኃውም እንደ ደም ሆነ የአገሩም ሰዎች ከሠራዊቶቻቸው ጋራ እንደ ቀድሞው ወጡ ባሕሩም መርከቦችን ተመላ እኔም ልሠወር ሮጥኩ። በዚያን ጊዜም የብርሃን እናት እመቤታችን ድንግል ማርያም ቁማ አየኋት "ጳውሎስ ሆይ ወዴት ትሸሻለህ አምላክህ ክርስቶስ እንዲህ እንድትሸሽ አዘዘህን? እርሱ ራሱ ሥጋችሁን የሚገድሉትን አትፍሯቸው ነፍሳችሁን ግን መግደል አይችሉምና ያለ አይደለምን። አንተም በቦታህ ጸንተህ ቁም እኔም ከአንተ ጋራ አለሁ እጄንም ከአንተ አላርቅም በርታ ጠንክርም የዚችን አገር ሰዎች ሁሉንም በዚህ የባሕር ውኃ እንደምታጠምቃቸው ዕወቅ በእጅህም አምነው ሙታን በሚነሱባት ዕለት ዕድላቸው ከአንተ ጋር ይሆናል ባሕሩም ቃልህን ሰምቶ ይታዘዝልሃል" አለችኝ።

🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን። 🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔 በዛሬው ዕለት በረጲ ጎለጎታ መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የደብራችን ሰንበት ትት ቤ
+2
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴 በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን። 🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔 በዛሬው ዕለት በረጲ ጎለጎታ  መድኃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን  የደብራችን ሰንበት ትት ቤት ህፃናት ከሌሎች አድባራት ጋር ባደረጉት የጥያቄና መልስ ውድድር ላይ አንደኛ በመውጣት አጠናቀዋል። በዚህም ሰንበት ት/ት ቤታችን በማስጠራታቸው። እንኳን ደስ አለን  ለማለት እንወዳለን። እንዲሁም ህፃናቱን ቃለ ህይወት ያሰማልን በዕድሜ በፀጋ ይጠብቅልን ለማለት እንወዳለን። በዚህም ለሰንበት ትት ቤታችን ህፃናት ክፍልን ከዚህ ይበልጥ በእውቀት በልፅገው በህይወታቸውም ፍሬያማ እንዲሆኑ አበክረን መስራት እንዳለብን አረጋግጠናል። ። ። የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ት ቤት ፅ/ቤት ከህፃናት አደራጅ ክፍል ጋር በመተባበር

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ እንኳን #ለዐቢይ_ጾም_ሰባተኛ_ሳምንት_ለኒቆዲሞስ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ።                            ✝ ✝ ✝ ❤ #የዚህ_ሳምንት_የኒቆዲሞስ_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "ሖረ ኀቤሁ #ዘስሙ_ኒቆዲሞስ ወይቤሎ #ለኢየሱስ_ረቢ_ንህነ_ነአምን ብከ ከመ እምኀበ #አብ_መጻእከ መራሔ ሕይወትነ ወሠራየ ኀጢአትነ ከመ #እምኀበ_አብ_መጻእከ ከመ ትኩን መምህረ ዕጓለ አንበሳ ሰከብከ ወኖምከ አንሥአኒ በትንሣኤከ። ትርጉም፦ አስቀድሞ ሌሊት ወደ እርሱ ይሄድ የነበረ #ስሙ_ኒቆዲሞስ የሚባል መምህር ሆይ #ከአብ_አካል_ዘእምአካል ባሕርይ ዘእምባሕርይ ተወልደህ ወደዚህ ዓለም እንደ መጣህ ፈጽሞ እናምንብሃለን፤ የሕይወታችን መሪ ኀጢአታችንን ይቅር የምትል ነህ አለው"። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓው_ላይ።                                ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅዱስ_ኒቆዲሞስ፦ ከፈሪሳውያን ወገን የአይሁድ አለቃ የነበረው ሰው ነው፡፡ የአይሁድ አለቆች አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን "ምልክት አሳየን" እያሉ ይፈታተኑት ነበር፡፡ ጌታችን ስለ ሞቱና ትንሣኤው በምሳሌ እያስረዳ ቢያስተምራቸውም እነርሱ ግን አልገባቸውም ነበር፡፡ ከዚህም አልፎ ጌታችን በተአምራቱ የታመሙትን ሲፈውስ "ሕጋችን ተሻረ" ይሉ ነበር፡፡ በዚህ ዅሉ ተአምራትና ትምህርት የአይሁድ አለቆች ክርስቶስን ለመክሰስ በሚፈልጉበት ወቅት ከአይሁድ አለቆች አንዱ ኒቆዲሞስ በቀን እንዳያደርገው አይሁድን ቢፈራ፣ አንድም ጊዜ ባያደርሰው እንደ ባልንጀሮቹ ክርስቶስን ሳይቃወም በሌሊት ወደ ጌታችን ዘንድ እየሔደ ወንጌልን ይማር ነበር፡፡ ❤ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በነፍስ የታመሙትን በቃሉ፣ በሥጋ የታመሙትን በተአምራቱ ሲፈውስ ኒቆዲሞስ ሰምቶ፣ ተመልክቶ በመምህርነቱ ሳይኮራ አለቅነቱን መመኪያ ሳያደርግ በልቦናው የተሳለውን እውነትን የመፈለግ ስሜት አንግቦ ከጌታው፣ ከመምህሩ ከክርስቶስ ዘንድ በሌሊት ይገሰግስ ነበር (ዮሐ. ፫፥፩)፡፡ ምስክርነቱንም እንዲህ ሲል መስጠት ጀመረ፤ "መምህር ልታስተምር ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን፡፡ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ከኾነ በቀር አንተ የምታደርገውን ተአምራት ሊያደርግ የሚችል የለምና" (ዮሐ. ፱፥፳፬፤ ሐዋ. ፲፥፴፰)፡፡ ❤ ይህን ምስክርነቱን በሚሰጥበት ጊዜም ጎዶሎን የሚሞላ፤ አላዋቂነት በአዋቂነት የሚለውጥ፤ ከምድራዊ ዕውቀት ወደ ሰማያዊው ምሥጢር የሚያሸጋግር አምላክ "ዳግመኛ ያልተወለደ የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማየት አይችልም"። በማለት የአይሁድ መምህር ለኾነው ኒቆዲሞስ ቢያስተምረው ምሥጢሩ አልተገለጠለትም ነበርና "ሰው ከሸመገለ በኋላ ዳግመኛ መወለድ እንደምን ይቻላል? ዳግመኛ ይወለድ ዘንድወደ እናቱ ማኅፀን ተመልሶ መግባት ይችላልን?" በማለት ጥያቄ አቅርቧል (ዮሐ. ፫፥፮፤ ፩ኛጴጥ. ፩፥፳፫)፡፡ "እውነትእውነት እልሃለሁ፤ ዳግመኛ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ ያልተወለደ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፡፡ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስነውና"። (ኤፌ. ፭፥፳፮) በማለት አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኒቆዲሞስ ቢያስረዳውም ምሥጢሩ ከአቅሙ በላይ ስለ ኾነበት እንደምን ይቻላል? በማለት ጠይቋል፡፡ ❤ አበ ብዙኃን አብርሃም ከአምላኩ ሞገስን አግኝቶ የሰዶምና ገሞራ ጥፋት እንዳይደርስ ለመማለድ ከእግዚአብሔር ጋር ሲነጋገር እንደ ነበረ፤ ኒቆዲሞስም አላዋቂነቱን አምኖ ያልገባውን ምሥጢር ከአምላኩ በጠየቀ ጊዜ ኢየሱስ ክርስቶስም፡- "አንተ የእስራኤል መምህራቸው ኾነህ ሳለ ይህን ነገር አታውቅምን? በምድር ያለውን ስንነግራችሁ ካላመናችሁ በሰማይ ያለውን ብንነግራችሁ እንደምንታምናላችሁ? ከሰማይ ከወረደው ከሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይየወጣ የለም … ሙሴ በምድረ በዳ እባቡን እንደ ሰቀለ የሰውልጅ እንዲሁ ይሰቀላል፡፡ ያመነበት ዅሉ ለዘለዓለም ሕያው ኾኖ እንዲኖር እንጂ እንዲጠፋ አይደለም ..." እያለ ሰው በመብል ምክንያት የአምላኩን ትእዛዝ አፍርሶ ከእግዚአብሔር ቢለይም የሰው ልጅ ያጣውን ልጅነት ለመመለስ፣ ስመ ክርስትናን፣ ሀብተ ወልድን ለመስጠት ጌታችን መምጣቱን አስረዳው (ዮሐ. ፫፥፲፬)፡፡ ይህን የክርስቶስን የማዳን ሥራና በሥጋ መገለጥም "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ አመከርከኒ ወኢተረክበ ዐመፃ በላዕሌየ ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፤ ልቤን ፈተንኸው፡፡ በሌሊትም ጐበኘኸኝ፤ ፈተንከኝም፡፡ ምንም አላገኘህብኝም፡፡ የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው" (መዝ. ፲፮፥፫) በማለት ቅዱስ ዳዊት ከኒቆዲሞስ ሕይወት ጋር በማዛመድ አመሥጥሮታል፡፡ ❤ በሌሊት ከአምላኩ ተምሮ ምሥጢሩ የተገለጸለት ኒቆዲሞስ ቀድሞ በአደባባይ ሔዶ መማርን ይፈራ እንዳልነበረ ምሥጢሩ ሲገለጽለት ግን አይሁድ ጌታችንን በሰቀሉት ዕለት ፍርኃት ርቆለት ከአርማትያሱ ዮሴፍ ጋር ቅዱስ ሥጋውን ገንዞ ለመቅበር በቃ፡፡ "ወአልቦ ፍርኃት ውስተ ተፋቅሮትነ፤ ፍጹም ፍቅር ፍርኃትን አውጥቶ ይጥላል" ተብሎ እንደ ተጻፈ (ማቴ. ፳፯፥፶፰፤ ፩ኛዮሐ. ፬፥፲፰)፡፡                                                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ። አመከርከኒ ወኢትረክበ ዐመፃ በላዕሌየ። ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው። መዝ16፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 7፥1-14፣ 1ኛ ዮሐ 4፥18-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥34-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 3፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም ዕለተ ሰንበት (ኒቆዲሞስ)ና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ #መጋቢት ፳፰ (28) ቀን። ❤ እንኳን #ለጻድቁ_ለታላቁ_ንጉሥ የክርስቶስ መስቀል ላገኘችው ለንግሥት ለቅድስት ዕሌኒ ልጅ #ለቅዱስ_ቈስጠንጢኖስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓልና #ለአርእስተ_አበው_ለቅዱሳን_ለአብርሃም፣ #ለይስሐቅና_ለያዕቆብ ለበዓላቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰ።                                                          ✝ ✝ ✝ ❤ #ታላቁ_ንጉሥ_ቅዱስ_ቈስጠንጢኖስ፦ የዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም ቊንስጣ የእናቱም ስም ቅድስት ዕሌኒ ነው። ቊንስጣም በራንጥያ ለሚባል አገር ንጉሥ ነው። መክስምያኖስም በሮሜ በአንጾኪያ በግብጽ ላይ ነግሦ ነበር። ❤ ይህም ቊንስጣ አረማዊ ነበር፤ ግን በጎ ሥራ ያለው እውነትን የሚወድ በልቡናውም ይቅርታና ርኅራኄን የተመላ ክፉት የሌለበት ነበር። ወደ ሮሐ ከተማ በሔደ ጊዜ ቅድስት ዕሌኒን አይቶ ሚስት ልትሆነው አገባት እርሷም ክርስቲያናዊት ናት። ንጉሥ ቈስጠንጢኖስንም ፀንሳ ወለደችው ስሙንም ቈስጠንጢኖስ ብላ ጠራችው ይህም ዝንጉርጒር ማለት ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ንጉሥ ቊንስጣ ዕሌኒን በዚያም ትቷት ወደ በራጥያ ከተማ ተመለሰ። እርሷም ልጇን እያሳደገች በዚያው ኖረች የክርስትናን ትምህርት አስተማረችው ይቅርታንና ርኅራኄን በክርስቲያን ወገኖች ላይ እንዲያደርግ በልቡናው ትዘራበት ነበር። እርሷ ክርስቲያን ስትሆን የክርስትና ጥምቀትን ታጠምቀው ዘንድ አልደፈረችም መንፈሳዊ ዕውቀትን ሁሉ ለማስተማር አሳደገችው ዳግመኛም ለመንግሥት ልጆች የሚገባውንም ሁሉ። ❤ ከዚያም በኋላ ወደ አባቱ ሰደደችው አባቱም በአየው ጊዜ ደስ ተሰኘበት ዕውቀትን የተመላ ሁኖ አግኝቶታልና በበታቹም መስፍን አድርጎ ሹሞ በመንግሥቱ ሥራ ላይ ሁሉ ሥልጣን ሰጠው። ❤ ከሁለት ዓመትም በኋላ አባቱ ዐረፈ ቈስጠንጢኖስም መንግሥቱን ሁሉ ተረከበ የቀና ፍርድንም የሚፈርድ ሆነ ከእርሱ በፊት የነበሩ ነገሥታት የጫኑባቸውን ጽኑ አገዛዝ ከሰዎች ላይ አስወገደ። አሕዛብም ሁሉ ታዘዙለት ወደዱትም የአገዛዙ ቅንነትና የፍርዱ ትክክለኛነት በአገሮች ሁሉ እስቲሰማ ተገዙለት። ❤ የሮሜ ሰዎች ታላላቆች መልክትን ወደርሱ ላኩ ከከሀዲ መክስምያኖስ ጽኑ አገዛዝ እንዲያድናቸው እየለመኑ እርሱ አሠቃይቷቸው ነበርና። መልእክታቸውንም በአነበበ ጊዜ ስለ ደረሰባቸው መከራ እጅግ አዘነ ያድናቸውም ዘንድ ምን እንደሚያደርግ በዐደባባይ ተቀምጦ እያሰበ ሲያዝን እንሆ ከቀኑ በስድስት ሰዓት በቀትር ጊዜ ኅብሩ እንደ ከዋክብት የሆነ መስቀል ታየው በላዩም በዮናኒ ቋንቋ "ኒኮስጣጣን" የሚል ጽሑፍ አለ ትርጓሜውም በዚህ ጠላትህን ድል ታደርጋለህ ማለት ነው። የመስቀሉም ብሔር የፀሐይን ብርሃን ሲሸፍነው በአየ ጊዜ አደነቀ። በላዩ ስለተጻፈውም አስቦ ለጭፍሮቹ አለቆችና ለመንግሥቱ ታላላቅ ባለሥልጣኖች አሳያቸው። እርሱም ቢሆኑ ይህ መስቀል ስለምን እንደተገለጠ አላወቁም። ❤ በዚያችም ሌሊት የእግዚአብሔር መልአክ ለቈስጠንጢኖስ በራእይ ተገልጦ እንዲህ አለው "በቀኑ እኩሌታ በቀትር በአየኸው በዚያ መስቀል አምሳል ላንተ ምልክት አድርግ በርሱም ጠላትህን ድል ታደርጋለህ" አለው። ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ልቡ ጸና የወርቅ መስቀልም አሠርቶ በነገሠበት ዘውድ ላይ አደረገው መኳንንቱንና ወታደሮቹን ጭፍሮቹን ሁሉ መስቀል ሠርተው በጦር መሣሪያቸው ላይ ያደርጉ ዘንድ አዘዛቸው እርሱም እንዳዘዛቸው አደረጉ። ❤ ይህም የሆነው በበራንጥያ በነገሠ በሰባተኛ ዓመት ነው። የሮሜን ሰዎች ከሥቃያቸው ሊያድናቸው ሥራዊቱን ሰብስቦ ተነሥቶ ወጣ። መክስምያኖስም ሰምቶ በታላቅ ወንዝ ላይም ታላቅ ድልድይ ሠርቶ ወደ ቈስጠንጢኖስም ተሻግሮ ከእርሱ ጋር ተዋጋ። የመስቀሉም ምልክት ቀድሞ በታየ ጊዜ የመክስምያኖስ ሠራዊት ድል ይሆኑ ነበር የቈስጠንጢኖስ ሠራዊት ከመክስምያኖስ ሠራዊት ብዙ ሰው ገደሉ። የቀሩትም ሸሽተው ሲሔዱ ከመክስምያኖስ ጋር ሊሻገሩትና ወደ ወሜ ሊገቡ ድልድይ ላይ ወጡ ድልድዩም ፈርሶ ፈርዖን ከሠራዊቱ ጋራ እንደ ሠጠመ እንዲሁ መክስምያኖስ ከሠራዊቱ  ጋራ ሠጠመ። ❤ ቈስጠንጢኖስም ወደ ሮሜ ከተማ ሲገባ የሮሜ ሰዎች ከካህናት ጋራ መብራቶች ይዘው በዕንቊ የተሸለሙ አክሊሎችን ደፍተው እምቢልታ እየነፋ ተቀበሉት የተማሩ ሊቃውንትም የከበረ መስቀልን ሲያመሰግኑት የአገራችን መዳኛ ይሉት ነበር ለከበረ መስቀልም ሰባት ቀን በዓል አደረጉ። ❤ ቈስጠንጢኖስም ዳግመኛ በሮሜ ነገሠ ከሀዲዎች የሆኑ መክስምያኖስና ዲዮቅልጥያኖስ ስለ ክብር ባለቤት ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት ያሠሩሯቸውን እሥረኞች ሁሉንም ፈታቸው ደግሞ የጣዖታት ቤቶች ይዘጉ አብያተ ክርስቲያናት ይከፈቱ ብሎ ዓዋጅ አስነገረ። ዳግመኛም ክርስቲያኖችን እንዲያከብሯቸው እንዲ እንዳያዋርዷቸው የጣዖታቱንም ገንዘብና ምድራቸውን በአረማውያን ላይ እንዲሾሙ አደረገ። ዳግመኛም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዘዙ ማንም ሰው በሰሙነ ሕማማት ሥራ እንዳይሠራ አዘዘ። ❤ በነገሠ በዐሥራ አንድ ዓመት በሮሜ ሊቀ ጳጳሳት በሶል ጴጥሮስ እጅ የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቀ። ሠራዊቱም ሁሉ ይህም የከበረ መስቀል ከተገለጠለት በኋላ በአራት ዓመት ነው። ❤ ከዚህ በኋላም በእርሱ ርዳታና ድል ያገኘበትን የሚያድን ስለ ሆነ ስለ ጌታችን መስቀል ትመረም ዘንድ እናቱ ቅድስት ዕሌኒን ወደ ኢየሩሳሌም ላካት። እርሷም ዓመፀኞች አይሁድ ቀብረው ከደፈኑት ቦታ አወጣችው። ❤ በዘመኑ ሃይማኖታቸው የቀና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት ጳጳሳት የአንድነት ስብሰባ በኒቅያ ስለ አርዮስ ተደረገ። ለክርስቲያኖች መመሪያ በበጎ አሠራር ክርስቲያናዊት ሥርዓት ተሠራች። ❤ ከዚህም በኋላ በበራንጥያ ታላቅ ከተማ ሊሠራ አሰበ እንደ አሰበውም ታላቅ ከተማ ሠርቶ በስሙ ቊስጥንጥንያ ብሎ ጠራት። በውስጧም አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በአግያና በሶፍያም ታላቅ ቤተ ክርስቲያን ሠራ መንፈሳዊ በሆነ በመልካም ጌጥ ሁሉ አስጌጣት በውስጥዋ ከሐዋርያት የብዙዎቹን ዓፅም ከሰማዕታትና ከቅዱሳን ጻድቃን ሥጋቸውን ስለሚሰበስብ። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችንን ደስ አሰኝቶ መልካም ተጋድሎውን ከፈጸመ በኋላ በኒቆምድያ ከተማ ጥቂት ታሞ መጋቢት28 ዐረፈ።ገንዘውም በወርቅ ሣጥን አድርገው ተሸክመው ወደ ከቊስጥንጥንያ አደረሱት የጳጳሳት አለቆችና ካህናቱ ከሁሉ ሕዝብ ጋር ወጥተው ተቀበሉት በብዙ ጸሎት በመዘመርና በማኅሌት በምስጋና ወደ ከበሩ ሐዋርያት ቤተ መቅደስ አስገብተው በክብር አኖሩት። የቅዱስ ቈስጠንጢኖስም በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት28 ስንክሳር።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #መጋቢት ፳፯ (27) ቀን። ❤ እንኳን #ለጌታችን_ለአምላካችንና_ለመድኀኒታችን፤ #ለፈጣሪያችንና_ለአዳኛችን_መድኃኔዓለም ለጥንተ ስቅለት መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል፣ ከአዳም ቀድሞ ገነት ለገባው #ለቅዱስ_ጥጦስ (ፈያታይ ዘየማን) ገነት ለገባበት፣ ጌታችን ለገነዙት ቅዱሳን ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ለመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                                                    ✝ ✝ ✝ ❤ በዚችም ቀን የክቡር ባለቤት #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ። ❤ ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳይለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር። እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደሲኦል ወረደች። ❤ እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑል ባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና ክብር ዘላለሙ የሆነ ራሱን ሠውቶ ያዳነን የመንግሥቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ የከፈተልን ለእርሱ ስግደት አምልኮት ይገባዋል ለዘላለሙ የመስቀሉም በረከት በላያችን ይደር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 27 ስንክሳር።                              ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዮሴፍ_ወለኒቆዲሞስ እለ አምጽኡ አፈወ ከርቤ ወዐልወ ወበልብሰ ገርዜን ሐዲስ፤ #እለ_ገነዝዎ_ለክርስቶስ፤ እለ ገሰሱ ሥጋሁ ወእለ ሰዓሙ አፉሁ"። ትርጉም፦ ከርቤ፣ ሽቱ፣ የሽቱ ወገን የሚኾን ዋግራ አምጥተው ዐዲስ በኾነ በፍታ ክርስቶስን የገነዙት፤ ሥጋውን ዳስሰው አፋን የሳሙት ለኾኑ #ለዮሴፍና_ኒቆዲሞስ_ሰላምታ_ይገባል።                                ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለዮሳፍጥ_ዘውእቱ_ፈያታይ_ዘየማን ዘአርኀዋ ለአንቀጸ ገነት ሶበ ቀጸበቶ #ዕለተ_መድኃኒት"። ትርጉም፦ ያውም የድኅነት ዕለት በተጠቀሰችው ጊዜ የገነት ደጃፍን የከፋታት #ፈያታይ_ዘየማን_ነው፤ ለርሱ #ለዮሳፍጥ_በረኸኛ_ለጥጦስ_ሰላምታ_ይገባል። #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በተአምኆ_ቅዱሳን_ላይ።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ተንሥኡ ላዕሌየ ሰማዕተ ዐመፃ። ወዘኢየአምር ነበቡ ላዕሌየ። ፈደዩኒ እኪተ ህየንተ ሠናይት"። መዝ34፥11-12። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ23፥1-17።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም። ወገብረ መድኃኒተ በማእከለ ምድር። አንተ አጽናዕካ ለባሕር በኃይልከ"። መዝ 73፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥1-16፣ 1ኛ ጴጥ 3፥15-20 እና የሐዋ ሥራ 10፥30-40። የሚነበበው ወንጌል ማቴ27፥1-55። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው። መልካም የመድኃኔ ዓለም የጥንት ስቅለቱ በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤        ❤ #መጋቢት ፳፮ (26) ቀን። ❤ እንኳን #ለክብር_ባለቤት_ለጌታችን_ለአምላካችን #ለመድኃኒታችን_ለኢየሱስ_ክርስቶስ ደቀ የመዛሙርቱን እግር ላጠበበትና፣ #የሐዲስ_ኪዳንን_የቊርባን_ሥርዓት_ለመሰረተበት (ለጥንት ጸሎተ ሐሙስ)ና ለከበረችና ለተመሰገነች ለድንግሊቱ ከዘጠኛ ዓመቷ ጀምሮ ስትጋደል ለኖረች፤ ዐቢይ ጾም ምን ሳትባለ ትጾም ለነበረች #ለቅድስት_ኢዮጰራቅስያ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከቅድስት_ኢዮጰራቅስያ_ጓደኛ (ከመጋቢዋ)ና #ከእመ_ምኔቷ ከዕረፍታቸው መታሰቢያና #ከቅዱስ_ፍርፍርዮስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።                            ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ዕለት #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_የደቀ_መዛሙርቱን_እግር_አጠበ እንዲህም አላቸው "እናንተም ለባልንጀሮቻችሁ እንዲሁ አድርጉ"።                            ✝ ✝ ✝ ❤ ደግሞ #የሐዲስ_ኪዳንን_የቊርባን_ሥርዓት አሳያቸው። አሁንም በዚች ዕለት የክብር ባለቤት ጌታችንን ለአይሁድ ይሁዳ አሳልፎ ሰጠው። ነቢያት ትንቢት እንደተናገሩ የሽያጩን ዋጋ ሠላሳ ብር ተቀበለ። ይቅርታው ቸርነቱ ከሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ጋር ለዘላለሙ ይኑር አሜን።                                                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ቅድስት_ኢዮጰራቅስያ፦ ይችም የተቀደሰች ብላቴና የንጉሥ አኖሬዎስ ዘመዱ ለሆነ በሮሜ ከተማ ከቤተ መንግሥት የአንድ ታላቅ መኰንን ልጅ ናት። የሚሞትበትም ቀን በደረሰ ጊዜ እርሷን ልጁን ለንጉሥ አኖሬዎስ ይጠብቃት ዘንድ አደራ ሰጠው። አባቷም ካረፈ በኋላ ለአንድ ታላቅ መኰንን ልጅ ንጉሥ አኖሬዎስ አጫት። ❤ በዚያም ወራት እናቷ የመሬቷን ግብር ልትቀበል ባሏ የተወላትን የአትክልት ቦታዎቿም ያፈሩትን ይችንም ቅድስት ብላቴናዋን ከእርሷ ጋር ወሰደቻት። ዕድሜዋ ዘጠኝ ዓመት ሁኖ ሳለ አስከትላት ወደ ግብጽ ሔደች። ❤ ወደ ግብጽ አገርም በደረሱ ጊዜ ሥራቸውን እስከሚፈጽሙ በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ ኖሩ። በዚያ ገዳም ውስጥ የሚኖሩ ደናግል ለገድል የተጸመዱ ናቸው። የሥጋ መብልን፣ ቅባትም ቢሆን ጣፋጭ ፍሬዎችንም ምንም ምን አይበሉም፣ ወይንም ቢሆን ከቶ አይቀምሱም ያለ ምንጣፍም በምድር ላይ ይተኛሉ። ኢዮጰራቅስያም በዚያ ገዳም ውስጥ መኖርን ወደደች ገዳሙን ከምታገለግል መጋቢዋ ጋር ተፋቅራለችና። መጋቢዋም "አንቺ ከዚህ ገዳም ወጥተሽ ተመልሰሽ እጮኛሽን ላትፈልጊ ቃል ግቢልኝ" አለቻት ኢዮጰራቅስያም በዚህ ነገር ቃል ገባችላት። ❤ እናቷ ሥራዋን በፈጸመች ጊዜ ወደ አገርዋ ልትመለስ ወደደች ልጅዋ ግን "እኔ የዚህን ኃላፊውን ዓለም ሙሽርነት ስለማልሻ ራሴን ለክብር ባለቤት ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰማያዊ ሙሽራ ሰጥቻለሁ" ብላ ከእርሷ ጋር መመለስን አይሆንም አለች። ብላቴናዋ ከእርሷ ጋር እንደማትመለስ በተረዳች ጊዜ ገንዘቧን ለድኆችና ለጦም አዳሪዎች መጽውታ ከልጅዋ ጋር በዚያ ገዳም ብዙ ዘመን ኑራ ከዚያ በኋላ ዐረፈችና በዚያው ቀበሯት። ❤ ንጉሥ አኖሬዎስም የኢዮጰራቅስያ እናቷ እንደሞተች ሰምቶ ለአጫት ያጋባት ዘንድ ኢዮጰራቅስያን እንዲያመጧት መልእክተኞችን ላከ። ቅድስቲቱም "ንጉሥ ሆይ ዕወቅ የክብር ባለቤት ለሆነ ለሰማያዊ ሙሽራ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ ራሴን ሰጥቻለሁና" ብላ ወደ ንጉሥ ላከች። ንጉሥ አኖሬዎስም መልእክቷን በሰማ ጊዜ አደነቀ ስለርሷም አለቀሰ እርሷ በዕድሜዋ ታናሽ ብላቴና ናትና። ❤ ይህቺ የከበረች ኢዮጰራቅስያ ግን ታላቅ ተጋድሎን ታጋደለች ለመንፈሳዊ ሥራ እጅግ የተጠመደች ሆነች በየሁለት ቀን ሁለት ሁለት ቀን እያከፈለች መጾም ከዚያም በሦስት ቀን ሦስት ሦስት ቀን ትጾም ጀመር ከዚያም በየሰባት ቀን ሰባት ሰባት ቀን የምትጾም ሆነች። በተለየች በከበረች አርባ ጾም ምንም ምን የምትበላ አልሆነችም። ❤ ሰይጣንም በእርሷ ላይ ቀንቶ አስጨናቂ በሆነ አመታት እግርዋን መታት ብዙ ቀኖችም በሕማም ኖረች ከዚያም እግዚአብሔር ራርቶላት ከደዌዋ አዳናት በሽተኞችንም ታድናቸው ዘንድ በሽተኞችን የምትፈስበትን ሀብት ሰጣት። ❤ ለእመ ምኔቷና ለእኅቶቿ ደናግል በመታዘዝ ታገለግላቸው ነበር በእኅቶች ደናግል ሁሉ ዘንድ የተወደደች ናት። ❤ በአንዲት ዕለትም እመ ምኔቷ አክሊላትንና አዳራሾችን እንደ አዘጋጁ ራእይን አየች እርሷም እያደነቀች "ከልጆቼ ለማን ይሆን ይህ የሚገባት" ስትል "እሊህ አክሊላትና አዳራሾች የተዘጋጁላት ለልጅሽ ለኢዮጰራቅስያ ነው እርሷም ወዲህ ትመጣለች" አሏት። ይህንንም ራእይ ለደናግሎች ነገራቻቸው እግዚአብሔርም በዚህ ዓለም መከራ ሊያሳርፋት እስከ ወደደበት ቀን ለኢዮጰራቅስያ እንዳይነግሯት አዘዘቻቸው። ❤ ከዚህ በኋላ በሆድ ዝማ ሕማም ጥቂት ታመመች ሁሉም ደናግል ከእመ ምኔቷ ጋር ወደ እርሷ ተሰበሰቡ ያቺ ቃል ኪዳን ያስገባቻት የምትወዳት መጋቢዋም መጣች። በእግዚአብሔርም ዘንድእንድታስባቸው ለመኑዋት እርሷም በጸሎታቸው እንዲያስቧት ለመነቻቸው ከዚያም መጋቢት 26 ቀን ዐረፈች። የተቀደሰችና የተባረከች እርሷን እኅታቸውን አጥተዋታልና ደናግሉ እጅግ አዝነው አለቀሱ። ❤ ከዚህም በኋላ የምትወዳት የገዳሙ መጋቢ የነበረችው ዐረፈች። ከእርስዋም በኋላ እመ ምኔቷ ጥቂት ቀን ታመመች ደናግሎቹንም ሰብስባ "በላያችሁ የምትሾሙትን እመ ምኔት ምረጡ ስለ እኔ ኢዮጰራቅስያ ለምናለችና እኔ ወደ ጌታዬ ኢየሱስ እሔዳለሁ አሁን ግን ደጁን በላዬ ዘግታችሁ ሒዱ" አለቻቸው እነርሱም እንዘዘቻቸው አደረጉ። በማግሥቱም ማለድ ብለው ሲደርሱ ዐርፋ አገኟት። የእሊህም የከበሩ እናቶች በረከታቸው ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 26 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ተሐፅበኒ እምበረድ እጸዓዱ (ወእጻዓዱ)። ታሰምዐኒ ትፍሥሕተ ወኃሤት። ወይትፌሥሑ አዕፅምተ ጻድቃን"። መዝ 50፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ 11፥20-30፣ 1ኛ ዮሐ 3፥18-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 4፥24-31። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥14-31። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ወይም የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤           ❤ #መጋቢት ፳፭ (25) ቀን። ❤ እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት ለአንዱ ጌታችንም በአገረ ናይን የመበለቲቱን ልጅ በአስነሣው ጊዜ አይቶ ከአይሁድነት #በኢየሱስ_ክርስቶስ_አምኖ ለተከተለው ለከበረና ለተመሰገነ #ለሐዋርያ_ለቅዱስ_አንሲፎሮስ ለዕረፍት በዓልና #ለዘመነ_ሐጋይ(በጋ) መውጫ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #ሐዋርያ_ቅዱስ_አንሲፎሮስ፦ ይህም ከእስራኤል ልጆች ከብንያም ነገድ ነው። ወላጆቹም የኦሪትን ሕግ የሚጠብቁ ናቸው። እርሱም ሥራዎቹን በአየ ጊዜ ትምህርቶቹንም በሰማ ጊዜ ጌታችንን ተከተለው። ❤ ድንቅ የሆኑ ተአምራቶችን እየተመለከተ ጥቂት ቀን ተቀመጠ ጌታችንም በአገረ ናይን የመበለቲቱን ልጅ በአስነሣው ጊዜ ከዚያ ነበር። ይህን አይቶ ወዲያውኑ አመነ ሌላ ምልክት አልሻም ብልጭ ብልጭ ሲል የነበረ የአይሁድ የሕግ ፋናን ትቶ ወደ እውነተኛ ፀሐይ ወደ ጌታ ኢየሱስ ቀርቦ ደመ መዝሙሩ ሆነው እንጂ። ❤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከዐረገ በኋላ በጽዮን አዳራሽ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ የመንፈስ ቅዱሳን ጸጋ ተቀብሎ የሐዋርያትንም በመከተል በብዙ አገሮች አስተማረ። ❤ ሐዋርያትም በአገረ አቴና ኤጲስቆጶስ አድርገው ሾሙት በውስጥዋም ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን አሳመነ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው በትምህርቱና በምክሩ ዕውቀት እንዲያድርባቸው አደረጋቸው በትምህርቱም ከደዌ ሥጋ ከደዌ ነፍስ ፈወሳቸው። ❤ ተጋድሎውንም በፈጸመ ጊዜ መጋቢት25 በሰላም ዐረፈ። በድል አድራጊነትም የክብር አክሊል ተቀበለ። መላ ዘመኑ ሰባ ዓመት ነው። በአይሁድ ሕግ ሃያ ዘጠኝ ዓመት በክርስትና ሕግ አርባ አንድ ዓመት ኖረ። ❤ እንሆ የከበረ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም በመልእክቶቹ አስታውሶታል ሰላምታም አቅርቦለታል። ከሐዋርያ ቅዱስ አንሲፎሮስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት25 ስንክሳር።                            ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ለአንሲፎሮስ_እግዚአብሔር_ዘጸውዖ። ምስለ ሐዋርያት በጽዮን መንፈስ ቅዱስ ይቅብዖ። ለወልደ መበለት ምውት በሀገረ ናይን ጊዜ አንሥኦ። መንክሮ ነጺሮ ወትምህርተ ቃሉ ሰሚዖ። #ለወልደ_ማርያም አብደረ ከመ ይኩን ረድኦ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_25።                           ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 2፥1፥10-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 2፥1-6 እና የሐዋ ሥራ 20፥22-28። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 7፥11-18። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አንሲፎሮስ የዕረፍት በዐልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤            ❤ መጋቢት ፳፬ (24) ቀን። ❤ እንኳን #ለእስክንድርያ_ሃምሳ_ዘጠነኛ_ሊቀ ጳጳሳት በእናቱ ምክር ተመርቶ የምዕመናኑንም ነፍሳቸውን ለማዳን መጻሕፍትን በማስነበብ፣ በመምከርና በመገሠጽ እያነቃ ሲታገል ለኖረ #ለአባ_መቃርስ ለዕረፍት በዓልና ለእናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ለወራዊ መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።                             ✝ ✝ ✝ ❤ በዚች ዕለት ዕለት ደግሞ አይሁድ በጌታችን ላይ አጽንተው መከሩ። ለእርሱም ክብር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።                              ✝ ✝ ✝ ❤ #አባ_መቃርስ፦ ይህም የከበረ አባት ሳብራ ከምትባል አገር ነው። ከታናሽነቱ ጀምሮ ይህን ዓለም ንቆ ትቶ የምንኵስናን ልብስ ሊለብስ ወደደ። ወደ አስቄጥስ ገዳምም በመግባት በታላቁ አባ መቃርስ ቤተ ክርስቲን ውስጥ መነኰሰ። በተጋድሎም ተጠምደ ከእርሱም በጎ ሥራዎችና ትሩፋቶች ተገልጸው ታዩ። ❤ ከእርሱ አስቀድሞ የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቆዝሞስ በዐረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶሳቱ ይሾሙት ዘንድ በአንድ ምክር ተስማምተው ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ያለ ፈቃዱ ሳይወድ በግድ ሾሙት። ❤ ወደ እስክንድርያም ይዘውት ሲሔዱ እግረ መንገዱ ከተወለደበት አገር ደረሰ እናቱም በዚያ በሕይወት አለች እርሷም የዚህን የኃላፊውን ዓለም ክብር የምትጠላ እግዚአብሔርን የምትፈራ እውነተኛ ሰው ናት። ወደርሷም እንደመጣ ስለርሱ በሰማች ጊዜ ልትቀበለው አልወጣችም። ነገር ግን እርሱ ራሱ እርሷ ወዳለችበት ቤት ገባ ተቀምጣም ትፈትል ነበር በሰላምታ ልትገናኘው ያልተነሣችው ያላወቀችው መስሎት "እኔ እገሌ ልጅሽ አይደለሁምን ለምን ሰላምታ አትሰጪኝም ወይስ አላወቅሺኝምን" አላት። እርሷም "እኔስ አውቄሃለሁ ራስህን ያላወቅህ አንተ ነህ በዚህ በሊቀ ጵጵስና ክቡር ሁነህ ከማይህ ሙተህ ተገንዘህ ባይህ በወደድኩ ነበር አሁን በፊት የምትጠየቀው በራስህ ኃጢአት ብቻ ነበር ከዛሬ ጀምሮ ግን በምዕመናን ሁሉ ኃጢአት ነው" ብላ መለሰችለት። ❤ ከዚህ በኋላ ሁለቱም በአንድነት አለቀሱ ይህም እናቱ የተናገረችው ነገር በልቡ አደረ ስለ ራሱ ድኅነትና የምዕመናኑንም ነፍሳቸውን ለማዳን መጻሕፍትን፣ በማስነበብ በመምከርና በመገሠጽ እያነቃ ሲታገል ኖረ። ❤ ደግሞ በእውነተኞች ካህናት ምስክርነት በቀር ካህናትንና ኤጲስቆጶሳትን ከመሾም የሚጠነቀቅና የሚጠበቅ ሆነ። ከቤተ ክርስቲያንም ገንዘብ የማይገባውን ምንም ምን አይወስድም ነበር። ኤጲስቆጶሳትንና ቀሳውስትን ወገኖቿቸውን ጥቅም በአላቸው በቅዱሳት መጻሕፍት ቃል በመምከር ይጠብቋቸው ዘንድ ያዛቸው ነበር። ❤ በሰላምና በጸጥታ ሁኖ በማርቆስ ወንበር ሃያ ዓመት ኖረ በሹመቱም ወራት አብያተ ክርስቲያናት ተቃንተው ተስተካክለው ያለ መቋረጥም በጸሎትና በቅዳሴ ተሠርተው አገልግሎት ሲሰጡ ኖሩ። በዚህም በኋላ መጋቢት24 በሰላም ዐረፈ። ከአባ መቃርስ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 24 ስንክሳር።                             ✝ ✝ ✝ ❤ "#ሰላም_ዕብል_ለሊቀ_ጳጳሳት_መቃሪ። እምሀገረ ሳብራ። ዐቂበ መርዔቱ እንበለ መከራ። እንተ መሀረቶ በሠናይ ምግባራ። ሶበ ተዘከረ ለእሙ ነገራ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የመጋቢት_24።                             ✝ ✝ ✝ ❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ቆመ ማኅበረ አማልክት። ወይኴንን በማእከለ አማልክት። እስከ ማዕዜኑ ትኴንኑ ዐመፃ"። መዝ 81፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥12-21፣ 1ኛ ጴጥ 1፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 28፥28-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 26፥1-6። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የጾም ወራትና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።