ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Open in Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Show more636
Subscribers
-124 hours
-37 days
-1330 days
Posts Archive
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፰ (28) ቀን።
🌹 እንኳን #ለቅዱስ_አማኑኤል_ዓመታዊ_በዓል፣ #አባቱ_ኖኅ_እግዚአብሔር_የያፌትን_አገር_ያስፋለት ብሎ ለመረቀው #ለቅዱስ_ያፌት_ለመታሰቢያ_በዓሉ፣ #ለቅዱሳን_ሰማዕታት_ለመርትያኖስና_ለመርቆሬዎስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከአባ_መቅብዩ፣ #ከአባቶቻችንም_ከቅዱሳን_ከአብርሃም_ከይስሐቅና_ከያዕቆብ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ቅዱሳን_ሰማዕታት_መርትያኖስና_መርቆሬዎስ፦ እሊህም ለቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ለአባ ጳውሎስ ደመ መዛሙርቱ ናቸው ይህም እንዲህ ነው አርዮሳዊ የሆነው ሁለተኛው ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ አባ ጳውሎስን በተጣላው ጊዜ ወደ አርማንያ አጋዘውና በዚያም በሥውር አሥር ቤት ውስጥ አንቀው እንዲገድሉት አደረገ እሊህ ቅዱሳን መርትያኖስና መርቆሬዎስ ግን የዕረፍቱን ቀን ገድሉንም ጻፉ አርዮሳዊውያን ንጉሥ ረገሙት።
🌹 አንድ ክፉ ሰውም ወደ ንጉሡ ሒዶ እነርሱ እንደረገሙት ወነጀላቸው ንጉሡም ያን ጊዜ ከአታክልት ቦታዎች በአንዲቱ ቦታ ተቀምጦ ሳለ ወታደሮች ልኮ ወደርሱ አስቀረባቸው በሰይፍም እንዲገድሏቸው አዝዞ ገደሏቸው በዚያም በገደሏቸው ቦታ ቀበሩአቸው እስከ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዘመንም በዚያ ቦታ ኖሩ እርሱም ዜናቸውን በሰማ ጊዜ መልእክተኞችን ልኮ ሥጋቸውን ወደ ቊስጥንጥንያ በክብር አስመጣ ያመረች ቤተ ክርስቲያንንም ሠርቶላቸው ሥጋቸውን በውስጧ አኖረ በዚችም ቀን ጥቅምት 28 በዓልን አደረገላቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ቅዱሳን ሰማዕታት መርትያኖስና መርቆሬዎስ በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 28 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ትውልደ ጻድቃን ይትባረኩ። ክቡር ወብዕል ውስተ ቤቱ። ወጽድቁኒ ይነብር ለዓለም"። መዝ 111፥12-13 ወይም መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 6፥9-15፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 3፥12-17። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 20፥36-41። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አማኑኤል በዓል፣ የአቡነ ይምአታ የዕረፍት በዓልና የጽጌ ጾም ለሁላችንም ይሁንልን።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፯ (27) ቀን።
🌹 እንኳን #ለታላቁ_ለግብጻዊ_አባት በንስር አሞራ የተመሰለ መልአክ ትኩስ የሆነ የቅዱሳንን አስክሬን እያመጣ የሚያስቀምጥበትን #አርብ_ሐራ_መስካበ_ቅዱሳን_መድኃኔዓለም_ገዳምን_ለመሠረቱት_ለአቡነ_ሐራ_ድንግልም_ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ግብፃዊው_አቡነ_ሐራ_ድንግል፦ ብዙ ተአምራት የሚደረግበትንና በንስር አሞራ የተመሰለ መልአክ ትኩስ የሆነ የቅዱሳንን አስክሬን እያመጣ የሚያስቀምጥበትን አርብ ሐራ መስካበ ቅዱሳን መድኃኔዓለም ገዳምን የመሠረቱት ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በ9ኛ መ/ክ/ዘመን ዮዲት ጉዲት ነግሣ አብያተ ክርስቲያናትን ለ40 ዓመታት ያህል ስታጠፋ ግብፃዊው አቡነ ሐራ ድንግል በአክሱምና በታላላቅ ገዳማት የነበሩትን ቅርሶችና ቅዱሳት መጻሕፍት ሰብስበው በአርብ ሐራ መድኃኔዓለም ገዳም ዋሻ ውስጥ አስቀምጠው ነበር፡፡ በተከታታይም ከግብፅ ሀገር ከገዳመ አስቄጥስ አርባ ቅዱሳን በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ ሀገራችን መጥተው ከአቡነ ሐራ ድንግል ጋር ተቀምጠው በጾም ጸሎት ተወስነው ብዙ ትሩፋትን ፈጽመዋል፡፡
🌹 አቡነ ሐራ ድንግል አንድ ቀን "ወንድሞቼ ሆይ! ይህን ዋሻ ውስጥ ለውስጥ የምንፈለፍልበት መሣሪያ ፈልጉና አምጡ" አሏቸው፡፡ አርባው ቅዱሳንም ወደ ሀገራቸው ግብፅ ተመልሰው ሄደው የዋሻ መፈልፈያ መሣሪያ አምጥተው ለጻድቁ ሰጧቸው፡፡ እርሳቸውም ቅዱሳኑ እየተራዷቸው ውስጥ ለውስጥ 4 ሰዓት የሚያስኬድ አስደናቂ ዋሻ ፈልፍለው በውስጡ ልዩ ልዩ ክፍሎች ሠሩ፡፡ ከዚያም አቡነ ሐራ ድንግል ቅዱሳኑን ወንጌልን እየተዘዋወሩ ይሰብኩ ዘንድ አሰማሯቸውና እርሳቸው በዋሻው አጠገብ በታላቅ ተጋድሎ በጾም ጸሎት ኖሩ፡፡ ብዙ መናንያንም ወደ እርሳቸው እየመጡ ቡራኬአቸውን ይቀበሉ ነበር፡፡ አቡነ ሐራ ድንግል በእንዲህ ያለ የተጋድሎ ኑሮ ሲኖሩ አንድ ቀን ሠርገኞች ሙሽሮችን አጅበው ሲሄዱ ጻድቁ በሚጸልዩበት አርብ ሐራ በተባለው ገዳም ሲደርሱ ሁለቱ ሙሽሮች ከበቅሎ ላይ ተንከባለው ከዋሻው በር ላይ ወድቀው ሞቱ፡፡ የሙሽሮቹ አጃቢዎችም ከፍተኛ ሀዘን ደረሰባቸው፡፡ አቡነ ሐራ ድንግልም ይህን ሁኔታ አይተው በጸሎታቸው ኃይል የሞቱትን ሙሽሮች አስነሥተው ለሠርገኞቹ አስረከቧቸው፡፡ ሠርገኞቹም ደስታቸው ዕጥፍ ድርብ ሆነ፡፡ ከጻድቁ እግር ሥር ወድቀው መንገዳቸውን ቀጠሉ፡፡
🌹 ከዚህም በኋላ የጻድቁ ዜና ይበልጥ በሁሉ ዘንድ ተሰማ፡፡ በላስታ የመራ ተክለ ሃይማኖት መንግሥት እንደተጀመረ ዋካ የሚባል ኃይለኛ ሽፍታ አቡነ ሐራ ድንግል ወዳሉበት ዋሻ መጥቶ "ይህን ዋሻ እፈልገዋለሁና ይልቀቁልኝ" ብሎ ገና ቃሉ ከአፉ ሲወጣ መብረቅ በድንገት ከሰማይ ወርዶ ከነተከታዮቹ ገድሎ ፈጽሞ አጠፋቸው፡፡ ጻድቁም የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ አይተው አደነቁ፡፡ አስከሬኑንም በወቅቱ የጣለው ጎርፍ ወሰደው፡፡ ሽፍታውም በመንዝ አውራጃ የታወቀና ኃይለኛ ስለነበር በመቅሰፍት መሞቱን ሰዎች ሲሰሙ ተደሰቱ፡፡
🌹 በአንድ ወቅትም የመንዙ ገዥ ልጁ ሞቶበት በታላቅ ሀዘን ውስጥ ሳለ ምእመናን ለገዥው "በግዛትህ ውስጥ የሚገኙት ጻድቁ አቡነ ሐራ ድንግል የልጅህን አስክሬን ብትወስድላቸው ከሙታን ለይተው ያስነሡልሃል" ብለው መከሩት፡፡ እርሱም የልጁን አስክሬን አሸክሞ አምጥቶ ከአቡነ ሐራ ድንግል ፊት ጣለውና "ክቡር አባቴ ሆይ! በተሰጠዎት ሀብተ ጸጋ ልጄን ያድኑልኝ" ብሎ በግንባሩ ወድቆ ለመናቸው፡፡ ጻድቁም ወደ እግዚአብሔር ጸልየው የሞተውን የገዥውን ልጅ አስነሡለት፡፡ ገዥውና ሕዝቡም ሁሉ በቅዱሳኑ ላይ ድንቅ ነገርን የሚያደርግ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ጻድቁንም እጅግ አከበሯቸው፡፡ የሀገሩ ገዥና ምእመናንም ልብስና ገንዘብ እያመጡ ጻድቁ ለሚያስተምሯቸው ተማሪዎች እንዲሆን ሰጧቸው፡፡ ጻድቁም ለተማሪዎቻቸውና ለጦም አዳሪዎች አከፋፍለውታል፡፡ አቡነ ሐራ ድንግል ለመንዝ ሕዝብ የቅዱሳት መጻሕፍትን ቃል በሚገባ አስተምረዋል፡፡ በተአምራታቸውም ብዙ ድውያንን ፈውሰዋል፡፡ ሙታንን አስነሥተዋል፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በ220 ዓመታቸው ጥቅምት 27 ቀን በክብር ዐርፈዋል፡፡
🌹 አቡነ ሐራ ድንግል ከማረፋቸው በፊት በጸሎት ላይ ሳሉ ጌታችን ተገልጦ ብዙ ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ዐፅማቸውንም አንድ ቅዱስ መነኵሴ በክብር ገንዞ በዋሻው ውስጥ አስቀምጦታል፡፡ ከግብፅ መጥተው እሳቸውን ሲያገለግሉ የነበሩት አርባው ቅዱሳንም ብዙ ካስተማሩና የትሩፋት ሥራ ሲሠሩ ከኖሩ በኋለ ዐርፈው በዚያው የጻድቁ ዐፅም ባረፈበት ዋሻ በክብር ተቀምጠዋል፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለአቡነ ሐራ ድንግል ከሰጣቸው አስደናቂ ቃል ኪዳኖች አንዱ "…እስከ ዕለተ ምጽዓት ድረስ እኔን አምነው የሚነሡ ቅዱሳን የማረፊያቸው ቦታ ክቡር ዐፅምህ ባለቤት ቦታ ይሁንልህ" የሚለው ነው፡፡
🌹 በዚህም ቃልኪዳን መሠረት እነሆ ከልዩ ልዩ ሥፍራ ነገር ግን ከየት እንደመጣ የማይታወቅ በንስር አሞራ የተመሰለ መልአክ ትኩስ የሆነ የቅዱሳንን አስክሬን እያመጣ ከአርብ ሐራ መድኃኔዓለም ገዳም ዋሻ ውስጥ ያስቀምጣል፡፡ ነጩ ንስር የቅዱሳንን ዐፅም ሲያመጣ በመጀመሪያ ከዋሻው ውስጥ የሚወጣው ጢስ መዓዛው ከከበረ ሽቱ ይበልጣል፡፡ የዕጣኑም ጢስ ከዋሻው ሲወጣ ይታያል፡፡ ቀጥሎም አስፈሪ የሆነ የነጎድጓድ ድምጽ ይሰማል፡፡ ወዲያው ነጭ ንስር ከዋሻው በር ላይ ባለው ዛፍ ላይ ሲያርፍ ይታያል፡፡ ወዲያው ዝናብ በሌለበት በፀሐይ ወቅትም ቢሆን የዋሻው በር በቀስተ ደመና ተከቦ ይታያል፡፡ ይህ በሚደረግበት ጊዜ እረኞችና ምሥጢሩ የሚገለጥላቸው ሰዎች ከዋሻው ራቅ ብለው ተአምራቱን ያያሉ፡፡ በማግሥቱ በዋሻው ሥር ያሉ እረኞችና ምዕመናን ወደ ዋሻው ውስጥ ገብተው ሲመለከቱ ከወትሮው የተለየ ትኩስ የቅዱሳን ዐፅም በሰሌን ተጠቅሎ መቁጠሪያና መቋሚያ ይዞ ይገኛል፡፡ በዚህ ዋሻ ውስጥ የሚታዩትን እጅግ አስገራሚ የሆኑትን ተአምራት በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡ በቦታው ላይ አዲስ የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን እየተሠራ ይገኛል፡፡
🌹 በአካባቢው ያለው የገጠሩ ምእመን በስዕለት ለዚህ ቅዱስ ቦታ የሚያስገባው መብዓ እና ከከተማ ለሚሄደው ተሳላሚ የሚሰጠው እምነት ለየት ያለ ነው፡፡
ከአባታችን አቡነ ሐራ ድንግል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከት ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ አቡነ ሐራ መድኃኔዓለም ገዳም ያዘጋጀው መጽሐፍ።
ነው፡፡ የመድኃኔዓለምን የሞቱን መታሰቢያ ያደረገ ግን የተኮነኑ ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፣ በሞቱም ጊዜ ሥቃይን አያያትም"፡፡
🌹 የአቡነ መብዓ ጽዮን በዓለ ዕረፍታቸውም እጅግ አብዝተው በሚዘክሩበትና ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ታስቦ በሚውለው በመድኃኔዓለም ቀን ጥቅምት ሃያ ሰባት ነው፡፡ ከአባታችን አቡነ መብዓ ጽዮን እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #አቡነ_ጽጌ_ድንግል፡- ደራሲና ማኅሌታዊ ሲሆኑ የላመ የጣፈጠ ከመብላት ተቆጥበው ጥሬ ቆርጥመው 9 ዓመት ከቆዩ በኋላ የእመቤታችንን ስደት በጣም በጥልቀት የሚተርከውን "ማኅሌተ ጽጌን" የደረሱ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ውኃም በሦስት ቀን አንድ ጊዜ ብቻ ነበር የሚጠጡት፡፡
🌹 አቡነ ጽጌ ድንግል ከደብረ ሐንታው ከአቡነ ገብረ ማርያም ጋር እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነው እመቤታችንንና ፈጣሪ ልጇን በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየመሰለ የሚያመሰግነውን ድርሰቱን በመዝሙረ ዳዊት መጠን 150 አድገው ደርሰዋል፡፡ አቡነ ገብረ ማርያምና አቡነ ጽጌ ድንግል ማኅሌተ ጽጌን በጥምረት ሊደርሱት የቻሉት አቡነ ገብረ ማርያም በወሎ ክፍለ ሀገር በወረኢሉ አውራጃ ልዩ ስሙ ደብረ ሐንታ በሚባለው ገዳም የሕግ መምሕር ሆነው በተሾሙበት ወቅት ነው፡፡ እነዚህም ሁለት ቅዱሳን የዘመነ ጽጌ የማኅሌት አገልግሎትን ሳይለያዩ በሰላምና በፍቅር በአንድነት አግልግለዋል፡፡ ይኸውም የሆነው እንዲህ ነው፦ አንድ ዓመት አቡነ ገብረ ማርያም የክረምት መውጫና የዘመነ ጽጌ ዋዜማ በሆነው መስከረም 25 ቀን ከደብረ ሐንታ መጥተው ደብረ ብሥራት አቡነ ጽጌ ድንግል ገዳም ገብተው ከመስከረም 25 ቀን እስከ ኅዳር 5 ቀን ያለውን የዘመነ ጽጌ የ40 ቀን አገልግሎት ከአቡነ ጽጌ ድንግል ጋር ፈጽመው ኅዳር 8 ቀን ወደ ደብራቸው ደብረ ሐንታ ይመለሳሉ፡፡ በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ አቡነ ጽጌ ድንግል ከገዳማቸው ከደብረ ብሥራት ተነሥተው ወደ ደብረ ሐንታ ሄደው እንዲሁ እንደ አቡነ ገብረ ማርያም 40ውን ቀን አግልግለው ይመለሳሉ፡፡ እነዚህ ሁለት ቅዱሳን እንደዚህ እያደረጉ በየተራ አንደኛው ወደ ሌላኛው ገዳም እየሄዱ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው ድረስ በፍጹም ፍቅርና በትሕትና አብረው እመቤታችንን ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡ ይኸውም በራሳቸው በአቡነ ገብረ ማርያም ገድል ላይ እና በአቡነ ዜና ማርቆስ ገድል ገጽ 72-73 ላይ በሰፊው ተጠቅሶ ይገኛል፡፡ የሁለቱ ድርሰታቸው የሆነው "ማኅሌተ ጽጌ" ድርሰት የእመቤታችንንና የልጇን የጌታችንን ሥጋዊ ስደት የሚገልጽ ሲሆን በጨማሪም ስደት የማይገባው አምላካችን ወደ አህጉራችን አፍሪካ ተሰዶ የሠራቸውን ድንቅ ድንቅ ተአምራትና የእመቤታችንን ንጽሕናዋን ቅድስናዋን አማላጅነቷን የሚያስረዳ ድንቅ መጽሐፍ ነው፡፡
🌹 አባ ጽጌ ድንግል ከማኅሌተ ጽጌ በተጨማሪ ሌሎች በርካታ አስደናቂ ድርሰቶችን ደርሰዋል፡፡ የጻድቁ ቅዱስ ዐፅማቸው፣ ታቦታቸውና የደረሷቸው በርካታ ድርሰቶች በገዳማቸው ደብረ ጽጌ ውስጥ በክብር ተጠብቀው ይገኛሉ፡፡ አምሃራ ሳይንት ቦረና ከአቡነ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገዳም የ5 ሰዓት የእግር መንገድ ከተሄደ በኋላ የሚገኘው ገዳማቸው "ደብረ ጽጌ" ከአንድ ወጥ ዓለት ተፈልፍሎ የተሠራው ሲሆን አሠራሩም እጅግ ድንቅ ነው፡፡
🌹 የአቡነ ጽጌ ድንግል ገዳም ከአቡነ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገዳም ጋር የሚያገናኘው "የእግዜር ድልድይ" የተባለ አስገራሚ ታሪክ ያለው ድልድይ አለው፡፡ ሁለቱ ቅዱሳን በመንፈስ ተጠራርተው ለመገናኘት ቢያስቡም የወለቃ ወንዝ ሞልቶ በአካል ሳይገናኙ ቀሩ፡፡ በዚህም በጣም አዝነው ከወንዙ ወዲያና ወዲህ ሆነው ተላቅሰው አፈር ተራጭተው ወደየገዳማቸው ቢመለሱም ያ ተላቅሰው የተራጩት አፈር በተአምር ትልቅ ድልድይ ሆነ፡፡ ድልድዩን ሁለቱም በበዓታቸው ሆነው በመንፈስ አዩት፡፡ የበጎ ነገር ጠላት ሰይጣንም ይህንን ሲመለከት ድልድዩን በትልቅ ሹል ድንጋይ በስቶ ሊያፈርሰው ሲል አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በመንፈስ አዩትና ከጋስጫ ተነሥተው በደመና ተጭነው በመሄድ ሰይጣኑን በግዘፈ ሥጋ ገዝተው ያንን ድልድዩን አፈርስበታለሁ ያለውን ትልቅ ሹል ድንጋይ አሸክመውት በዓታቸው ጋስጫ ድረስ ወስደውታል፡፡ ያ ድንጋይ ዛሬ በጋስጫ አቡነ ጊዮርጊስ ገዳም ለመነኮሳቱ ደወል ሆኖ እያገለገለ ይኛል፡፡ ድልድዩም እስከ አሁን ድረስ ለአካባቢው ኢስላም ማኅበረሰብ ብቸኛው የወለቃ ወንዝ መሻገሪያቸው ሆኖ እያገለገላቸው ነው፡፡ ከአባታች አቡነ ጽጌ ድንግል እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ይሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን! ምንጭ፦ገድለ አቡነ መባዓ ጽዮን፣ መዝገበ ቅዱሳን።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፯ (27) ቀን።
🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን ማኅሌተ ጽጌን #ከአባ_ገብረ_ማርያም ጋር በመሆን ለደረሱት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ጽጌ_ድንግል፣ ጌታችን በዕለተ አርብ የጠጣው መራራ ሐሞት እያሰብ ሁል ጊዜ አርብ አርብ ኮሶ ይጠጡና #የመድኃኔዓለም_ዝክር_ይዘክሩ ለነበሩት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_መብዓ_ጽዮንና በዋሻ ውስጥ አርባ ዓመት ለኖሩ መና ሲመገቡ ለነበሩት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጣና ለዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ ከእግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #አቡነ_ጊዮርጊስ_ዘጣና፦ አገራቸው ጣና ዘጌ ነው። በዋሻ ውስጥ አርባ ዘመን ሙሉ ዘግተው ሲኖሩ መና ከሰማይ እየወረደላቸው ውሃም በዋሻ ውስጥ ፈልቆላቸው ይኖሩ ነበር። አንድ ቀን መልአክ መጥቶ ምን ቢጋደሉ የጌታችንሠን ስጋውን በልተው ደሙን ካልጠጡ እንደ ማይድኑ ነገራቸው። በመልአኩም ትዕዛዝ መሰረት ከዋሻው ወጥተው ሊቆርቡ ቤተ ክርስቲያን ገቡ በቅዳሴም ላይ ሳሉ አንድ ድንቅ ምስጢር ተመለከቱ ይህም በጸሎተ ሐሙስ ዕለት ካህኑ "ሀበነ" ሲል ጌታችን በዕለተ አርብ እንተ ተሰቀለ ሆኖ ደሙ ሲፈስ የካህኑ እጅ በደም ተነክሮ በመንበሩ ቆሞ ቢያዩት በድንጋጤ ሳይቀሳቀሱ አርባ ዓመት ተኝተዋል ይህም በሰው አቆጣጠር በጌታችን ዘንድ ግን ምን ያይህል ጊዜ እንደ ሆነ እራሱ ባለቤቱ ያውቀዋል። በመጨረሻም ጻድቁ በዐረፉ ጊዜ መቃብራቸውን አራዊት ቆፍረውላቸው መነኰሳቱ ገንዘው ቀብረዋቸዋል። ታቦታቸው በጣና ይገኝል። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳንና ቅዱሳን በዓላት።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #አቡነ_መብዓ+ጽዮን፡- አባታቸው ንቡረ ዕድ እናታቸው ደግሞ ሀብተ ጽዮን ይባላሉ፡፡ በሌላኛው ስማቸው ተክለ ማርያም ይባላሉ፡፡ ይህንንም ስም ያወጣችላቸው እመቤታችን ናት፡፡ እመቤታችንን ከሕፃንነታቸው ጀምረው እጅግ ይወዷት ነበር፡፡ ትንሽ ልጅ ሳሉ አንድ ካህን ወደ ሀገራቸው በእግድነት መጣና አባታቸው ሀብተ ጽዮን አሳደሩት፡፡
🌹 እንግዳውም ካህን የእመቤታችንን ሥዕል ምስለ ፍቁር ወልዳን ይዞ ነበር፡፡ ሲተኛም በራስጌው ያኖራት ስለነበር በሀብተ ጽዮንም ቤት አድሮ ጠዋት ተነሥቶ ሲሄድ የእመቤታችንን ሥዕል በራስጌው እንዳኖራት እረስቶ ሄደ፡፡ ያንጊዜ ሕፃን የነበሩት አባ መብዓ ጽዮንም ሥዕሏን ወስደው ሳሟት፣ በእርሷም ደስ ተሰኙባት፡፡ ለሌላም ሰው አልሰጥም ብለው በአንገታቸው አሰሯት፡፡ ሀብተ ጽዮንም "ይህችን የእግዳው ካህን ንብረት የሆነች የእመቤታችንን ሥዕል ከቤት እንዳላስቀምጣት ኃጢአት ይሆንብኛል እንዳልሰጠውም ከየት አገኘዋለሁ" እያለ ሲቀጨነቅ ከዕለታት በአንደኛው ቀን ያንን እንግዳ አገኘው፡፡ ባገኘውም ጊዜ ከቤት የተዋትን የእመቤታችንን ሥዕል እንዲወስድ ነገረው፡፡ መጀመሪያ ሕፃን መብዓ ጽዮን እንዳገኛትና በጣም እንደወደዳት ለሌላ ሰውም አልሰጥም ብሎ በግድ ቀምቶ እንዳስቀመጣት ነገረው፡፡ እንግዳውም ይህን ሲሰማ "የሥዕሊቱ ባለቤት እርሷ የሕፃኑ እንድትሆን ፈቅዳለታለች፤ ከእኔ ዘንድ መሆኗን ፈቅዳ ቢሆንማ ኖሮ ባልተረሳችኝ ነበር ለዚያ ላገኛት ልጅህ የተገባች ናት" ካለው በኋላ እርስ በእርሳቸው ሰላምታ ተሰጣጥተው ተለያዩ፡፡
🌹 አቡነ መብዓ ጽዮን ዕድሜያቸው ከፍ ሲል ወላጆቻቸው ሚስት ሊድሩላቸው ሲሉ እርሳቸው ግን አላገባም ብለው የዚህን ዓለም ጣዕም ንቀው ነው የመነኑት፡፡ የምንኩስና ልብስ ከለበሱበት ጊዜ ጀምረው በበቅሎና በፈረስ ላይ ተቀምጠው አያውቁም፤ በአልጋም ሆነ በምንጣፍ ላይ አልተኙም ይልቁንም የአንድ ሰው ሸክም የሚያህል ትልቅ ድንጋይ በደረታቸው ተሸክመው ከአመድ ላይ ይተኙ ነበር እንጂ፡፡ ከሰንበት ቀናት ውጭ ሲቀመጡም ድንጋዩን በራሳቸው ላይ ይሸከሙታል፣ ሲሰግዱም በጀርባቸው ያዝሉት ነበር፡፡
🌹 አባታችን ለቅዱስ ሥጋ ወደሙ እጅግ ትልቅ ክብር ስለነበራቸው የቆረበ ሰው ከቤተክርስቲያን ወጥቶ ሲሄድ እንቅፋት እንኳን ሲመታው ስለሥጋ ወደሙ ክብር ብለው እግሩ የደማበትን ሰው ደሙን ይጠጡት ነበር፣ ደሙ የፈሰሰበትንም አፈር ይልሱታል፡፡ ይህም የመድኃኔዓለምን ሥጋና ደም ከማክበራቸው የተነሣ ነው፡፡ ጻድቁ ጌታችን በዕለተ ዓርብ መራራ ሐሞት መጠጣቱን አስታውሰው ሁልጊዜ ዐርብ ዐርብ ኮሶ ይጠጡ ነበር፡፡ መድኃኔዓለምም በየጊዜው በሕፃን አምሳል ይገለጥላቸዋል፡፡ በዕለተ ዓርብም እንደተሰቀለ ሆኖ ይገለጥላቸው ነበር፡፡ ዳግመኛም ጌታችን ለአቡነ መባዓ ጽዮን በመሠዊያው ላይ በነጭ በግ አምሳል ይገለጥላቸው ነበር፡፡
🌹 መከራ ሞቱን እያስታወሱ ሰውነታቸውን ይጎዱ እንደነበር በቅዱስ ገድላቸው ላይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏል፡- "በተቀደሰች በዓርባ ጾምም የመድኃኔዓለምን ግርፋት እያሰበ ሰውነቱን በእጅጉ ገረፈ፡፡ ደሙ ከመሬት እስኪወርድ ድረስ ልቡንም አጥቶ ከምድር ላይ ወደቀ፡፡ የመድኃኔዓለምን መከራውን አስቦ እንደሞተም ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም ወደ እርሱ መጣና "ተነሥ እኔ ቁስልህን እፈውስሃለሁ" ብሎ የጀርባውን ቁስል ዳሰሰው፡፡ ምንም ሕማም እንዳላገኘውም ሆነ፡፡ መድኃኔዓለምም አባታችንን "በአንተው እጅ ትገደልን? እኔ እንኳ የተገደልኩት በአመፀኞች በአይሁድ እጅ ነው" አለው፡፡ በዚያችም ሰዓት ጌታ የመባዓ ጽዮንን ከንፈሮቹን ይዞ ሦስት ጊዜ እፍ አለበትና "የከበረ ትንፋሼም ከትንፋስህ ጋራ ይጨመር፣ ሥጋህም ከነፍስህ ጋራ የከበረ ይሁን› አለው፡፡ "አንተ በላዩ እፍ ያልህበትም የተቀደሰና የከበረ ይሁን" አለው"፡፡
🌹 ጌታችን ለአቡነ መብዓ ጽዮን የወርቅ በትር ሰጥቷቸው በእርሷ ነፍሳትን ከሲኦል ያወጡባት ነበር፡፡ መቋሚያዋም እሳቸው ካረፉ በኋላ የሚሞተውን ሰው እየለየች ትናገር ነበር፡፡ አባታችን እንደ አቡነ ተክለሃይማኖት ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም በመልአክ ተጥቀው ተወስደው የሥላሴን መንበር ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር አጥነዋል፡፡ ጌታችን ከተረገመችና ከተወገዘች ዕፅ ጋር በተገናኘ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክና ለአቡነ መብዓ ጽዮን ልዩ ምሥጢር እንደነገራቸው በሁለቱም ቅዱሳን ገድላት ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡
🌹 አቡነ መብዓ ጽዮን በይበልጥ የሚታወቁት ሁልጊዜ ወር በገባ በሃያ ሰባት መድኃኔዓለምን አብልጠው በመዘከራቸው ነው፡፡ በዚህም ምክንያት "እንደ አንተም በየወሩ በሃያ ሰባት የሞቴ መታሰቢያ ለሚያደርግ ነፍሳትን ከሲኦል አወጣለታለሁ" የሚል ድንቅ ቃልኪዳን ከጌታችን ተቀብለውበታል፡፡ ይኸውም የመድኃኔዓለምን የሞቱን መታሰቢያ የሚያድርግ ቢኖር ነፍሳትን ከሲኦል እንደሚያወጣ ሲነግራቸው ነው፡፡ ቅዱስ አባታችን "ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ! በዓልህን አደርግ ዘንድ አንተ የምትወደውን ግለጥልኝ" ብለው ጌታችንን ሲጠይቁት እርሱም "የሞቴን መታሰቢያ ያደረገ እንደ እኔ ነፍሳትን ከደይን ያወጣል፣ "በእኔ የሚያምን እኔ የምሠራውን ይሠራል፣ ከዚያም የበለጠ ይሠራል" ብዬ በወንጌሌ እንደተናገርሁ" አላቸው"፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን ለልጆቻቸው እንዲህ ብለው መከሯቸው፡- "ክርስቲያኖች ሁሉ የፈጣሪያችንን የመድኃኔዓለም ክርስቶስን የመታሰቢያ በዓሉን እናድርግ፡፡ የአባቶቻችን የሐዋርያት፣ የጻድቃን፣ የሰማዕታት፣ የመላእክት መታሰቢያቸው ባረፉበት በተሾሙበት ቀን ይከበራል፡፡ እነርሱን የፈጠራቸው እርሱ መድኃኔዓለም ነው፣ ያከበራቸው፣ ከፍ ከፍ ያደረጋቸው፣ ስማቸውን ለጠራ መታሰቢያቸውን ያደረገ እንደሚድን ቃልኪዳን የሰጣቸው እርሱ
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፯ (27) ቀን።
🌹 እንኳን #ለመድኃኔዓለም_ለስቅለቱ_ዓመታዊ መታሰቢያ በዓልና #ለሀገረ_ቃው_ኤጲስ_ቆጶስ #ለአባ_መቃርስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ በዋሻ ከሚኖር #ከጳውሎስና_ከዮልያኖስ ከእነርሱም ጋር ላሉ ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 በዚችም ቀን የክቡር ባለቤት #ጌታችን_መድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ስለ ዓለም ድኅነት በሥጋ ተሰቀለ።
🌹 ፈጣሪዋ በዕንጨት መስቀል ላይ ተዘርግቶ ተሰቅሎ በአየችው ጊዜ ፀሐይ ጨለመች እርሱም ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣትን ለባዊት ነባቢት የሆነች ነፍሱን ከሥጋው ለያት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በሥጋ ምውት ሲሆን በመለኮት ሕያው ነው እንዳለ ነፍሱ ከመለኮት ሳትለይ ከሥጋ ተለየች በዚያ ጊዜ ሥጋ ከመለኮት ሳይለይ በዕንጨት መስቀል ላይ ተሰቅሎ ነበር። እንዲሁም ነፍስ ከመለኮት ጋራ አንድ ሁና እሥረኞች ነፍሳትን ትፈታቸው ዘንድ ወደሲኦል ወረደች።
🌹 እርሱ ከሰማያት በላይ ከፍ ከፍ ያለ ልዑል ባሕርይ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋራ በጌትነቱ ዙፋን ተቀምጦ ያለ ለእርሱም ምስጋና ክብር ዘላለሙ የሆነ ራሱን ሠውቶ ያዳነን የመንግሥቱን ደጆች በፈሳሽ ደሙ የከፈተልን ለእርሱ ስግደት አምልኮት ይገባዋል ለዘላለሙ የመስቀሉም በረከት በላያችን ይደር አሜን። ምንጭ፦ የመጋቢት 27 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 #አባ_መቃርስ_ዘሀገረ_ቃው፡- ለዚህም ቅዱስ የዝንጉዎችን ምክር ተከትሎ ያልሔደ በኃጢአተኞችም ጎዳና ያልተጓዘ በዘባቾችም መቀመጫ ያልተቀመጠ የእግዚአብሔርን ሕግ መጠበቅ ፈቃዱ የሆነ እንጂ ሕጉንም በቀንና በሌሊት የሚያነብ የሚያስተምር ብፁዕ ነው የሚለው የነቢይ ዳዊት ቃል ተፈጽሞለታል።
🌹 ይህም አባ መቃርስ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በመጠበቅ በመክሊት ነግዶ ዕጥፍ አድርጎ አትርፎአልና እግዚአብሔርም በእጆቹ ያደረጋቸውን ታላላቆች ድንቆች ተአምራት ስንቱን እናገራለን። ስለርሱም እንዲህ ተባለ እርሱ በአገረ ቃው ተሾሞ በወንበር ተቀምጦ ሕዝቡን በሚያስተምራቸው ጊዜ ዘወትር ያለቅሳል ከደቀ መዛሙርቶቻቸውም አንዱ በእግዚአብሔር ስም ካማላቸው በኋላ ለምን ሁልጊዜ እንደሚያለቅሱ በመሐላው አምሎ ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም ስለመሐላቸው ፈርተው ነገሩት "ዘይት በብርሌ ውስጥ ጎልቶ እንደሚታይ የወገኖቼም ኃጢአት እንዲሁ በታየኝ ጊዜ አለቅሳለሁ" አሉት፡፡ በሌላም ጊዜ ጌታችን በመሠዊያው ላይ ሆኖ ተገልጦላቸው የእያንዳንዱን ሰው ኃጢአት መላእክት ሲያቀርቡለት አሳያቸው፡፡ ቀጥሎም "ሕዝቡን አስተምረህ ከክፋታቸው መልሳቸው" አላቸው፡፡ እሳቸውም "አይሰሙኝም" ቢሉት ጌታችንም "አስተምረሃቸው ከክፋታቸው ባይመለሱ ደማቸው በራሳቸው ላይ ይሆናል" አላቸው፡፡
🌹 መናፍቁ ንጉሥ መርቅያኖስና ተከታዮቹ ክብር ይግባውና ጌታችንን "ሁለት ባሕርይ" በማለታቸው ጉባዔ ሠርተው አባቶች ሲሰበሰቡ ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ አባ መቃርስን አስከትሎ በጉባዔው ተገኘ፡፡ አባ ዲዮስቆሮስና አባ መቃርስም ሁለት ባሕርይ ባዮችን አስተምረዋቸው እምቢ ቢሏቸው አውግዘውና እረግመው ከቤተ ክርስቲያን ለዩአቸው፡፡ ለመከራም የተዘጋጁ ሆነው ራሳቸውን አሳልፈው ሰጧቸው፡፡ ከሃዲው ንጉሥም ወደ ጋግራ ደሴት አጋዛቸው፡፡ አባ ዲዮስቆሮስም ለአባ መቃርስ "አንተ በእስክንድርያ ሀገር ሰማዕትነት ትቀበላለህ" በማለት ትንቢት ነግረዋቸው ከአንድ ነጋዴ ጋር ወደ እስክንድርያ ላኳቸው፡፡ እዚያም ሲደርሱ መናፍቁ ንጉሥ መርቅያኖስ አባ መቃርስን ይዞ ብዙ ካሠቃያቸው በኋላ ኩላሊታቸውን ብሎ ገደላቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ጥቅምት 27 ቀን ሆነ፡፡ ክርስቲያኖችም ሥጋቸውን ወስደው ከነቢዩ ኤልሳዕና ከመጥምቁ ዮሐንስ ሥጋ ጋር በአንድነት አኖሩት፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛን በአባ መቃርስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 27 ስንክሳርና መዝገበ ቅዱሳን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እግዚአብሔርሰ ንጉሥ ውእቱ እምቅድመ ዓለም። ወገብረ መድኃኒት በማእከለ ምድር። አንተ አጽናዕካ ለባሕር በኃይልከ"። መዝ 73፥12-13። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 27፥20-57።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦"ተሣሃለኒ እግዚኦ እስመ ኬደኒ ሰብእ። ወኵሎ አሚረ አሥርሐኒ ቀትል። ወኬዱኒ ፀርየ ኵሎ አሚረ በኑኀ ዕለት። መዝ 55፥1-2 ወይም 110፥9። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 12፥20-28፣ 1ኛ ጴጥ 2፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 5፥12-17። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 3፥11-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ ነው። መልካም የመድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ በዓል፣ የአባ ጽጌ ድንግል፣ የአቡነ መብዓ ጽዮን፣ የአቡነ ጊዮርጊስ ዘጣና የዕረፍታቸው በዓልና የጽጌ ጾም ለሁላችንም ይሁንልን።
🌹 #ጥቅምት ፳፮ (26) ቀን።
🌹 #1993 ዓ/ም በግፍ የተገደሉት የፈጻሜ መንግሥት #ግርማዊ_ቀዳማዊ_አፄ_ኃይለ_ሥላሴ ፍልሰተ አጽም የተደረገበት ታሪካዊ ቀን ነው::
በምስሉ ስር የታዕካ ነገሥቱ የኔታ ተስፋ
"ጊዜ ሠለስቱ ሰአት ጸለየ ኃይለ ሥላሴ ወአርኃወ ቤቱ ታዕካ ነገሥት ዘይኔጽር መንገለ ገጸ መንበረ ጸባኦት ወሰምዐ ጸሎቶ ለኃይለ ሥላሴ ንጉሰ ነገስት"
የሚለውን ግስ ሲቃኙ ነው።
🌹 በዚህ ዕለት የንጉሡ አጽም በአደራ ከቆየበት ከታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ተነስቶ በሠረገላ ሆኖ በመስቀል አደባባይ አድርጎ በቸርችል ጎዳና አልፎ ፒያሳ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሲደርስ የታየው ነገር ቃል አይገልጸውም ልዩ ነበር
ንጉሠ ነገሥት ተብለው ቅብዓ መንግሥት ተቀብተው ቅዱስ ስጋውን ክቡር ደሙን ተቀብለው በቅዱስ ወንጌል ምለው ጸሎተ እግዝዕትነ ማርያም ተጸልዮ ሉቃስ 1 ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን እና ኢትዮጵያን ሊጠብቁ ቃል ገብተው ዘውድ የደፉበት ታላቅ ቤተመቅደስ ነው። "አብርህ ገጸከ ላዕለ ገብርከ" ሊቃውንተ ገነተ ጽጌ የጥንቶቹ እያነቡ አዲሶቹ እየተደመሙ የነበረው ዝማሬ ልብ ይነካ ነበር።
🌹 ከዚያም በቀኃሥ መንገድ በራስ መኮንን ድልድይ አድርጎ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ሲደረስ የነበረው የህዝብ ብዛት የቅልብ ወታደሮቹ ግልምጫና እርግጫ የሕዝቡ ትዕግስት ያስደንቅ ነበር። የንጉሠ ነገሥቱ አጽም ገና ከቤተክርስቲያኑ ሳይደርስ ሕዝቡ ሞልቶ ከፓርላማው ጀምሮ በጣሳ እንደተሰፈረ እህል ሕዝቡ ግጥም ብሎ ነበር።
🌹 ያ ገናና ቤተክርስቲያን የንጉሡ አጽም ሲደርስ የቤተ ክርስቲያኑ ደውል ሳያባራ ሲደወል ከአይነ ሞት የተረፈው ከስደት የተመለሰው ትውልድ እንባና ለቅሶ የወጣቱ ጩሁት የግቢው አጸድ ወፎች ዝማሬ ድብልቅልቅ ያለና እጅግ ስሜትን የሚነካ ነበር።
ዛፎቹ ሁሉ ወጣቶች ወጥተው ሰፈረውበታል ወተት በማጥቆር ማር በማምረር የተካኑ የታሪክ አተላዎች ብዙ አፈር ቢዘሩም ጃንሆይን የማያቅ ትውልድ ታሪክ አንብቦ አክብሮ በቀብራቸው የተገኘው በቁጥር የማይገለጥ ወጣት ነው።
🌹 በወቅቱ መንግስት ተገቢውን ክብር ቢነሳም አልፎ ተርፎም ስድብ አዘል መግለጫ ወስዳችሁ ጣሉ አይነት ቢልም። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ከሌሎች አበው ጋር ከሚመለከታቸው አካላትም ጋር ተባብረው ወደር የሌለው አኩሪ ታሪክ ሰርተዋል።
አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ "የንጉሠ ነገሥቱን ታላቅነት ባልናገር ስራቸው ከፊቴ ቆሞ ይናገራል እኔንና መሰል መነኰሳትን ለዛሬይቱ ቤተክርስቲያን ያስፈልጋሉ ብለው ውጭ ሀገር ድረስ ልከው ያስተማሩን ጃንሆይ ናቸው።"
ብለው የንጉሡን ታላቅነት በመግለጽ ያደረጉት ታሪካዊ ንግግርም አንዱ ነው።
🌹 ክቡር መጋቢ ምስጢር ወልደ ሩፋኤል
ካቀረቡት ቅኔ፦
🌹 "እስከ ማዕዜኑ ውእቱ ዘይትቤቀለነ። ኃይለ ሥላሴ ደምከ ዘተክዕዎ በአመፃ። እመ ለቃሕከነ ወርቀ እስመ ፈደይናከ ሆፃ። ወዕፃነ ኢያእመርነ ለኢትዮጵያ እንዘ አንተ ዕፃ። ወክፍለ ዘመንከ አመ ሞፃ እንዘ በበመትልው ይመልእ ለቤተመቅደስ ሕፀፃ።
🌹 የንጉሣችን የኃይለ ሥላሴን እግዚአብሔር አምላክ ነፍስ ይማርልን አሜን። ምንጭ፦ ከአንተነህ ኃይሌ የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፮ (26) ቀን።
🌹 እንኳን #ጌታችን_ከመረጣቸውናና በሽተኞችን ሁሉ ይፈውሱ ዘንድ አጋንንትንም ያወጡ ዘንድ ሥልጣን ከሰጣቸው #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእትና_ከሰባቱ_ዲያቆናት አንዱ ለሆነው #ለቅዱስ_ለሐዋርያው_ቅዱስ_ጢሞና ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓልና #ለጌታችን_ወንድም ለተባለው #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ያዕቆብ ለመታሰቢያ በዓሉ በሰላም አደረሰን፡፡ በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከፊልጶስና ከሰማዕት አግናጥዮስ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #ሐዋርያው_ቅዱስ_ያዕቆብ፦ ይህም የጠራቢው የዮሴፍ ልጅ ነው። እርሱም ከልጆቹ ሁሉ የሚያንስ ነበር። እርሱም ንጹሕ ድንግል ነበር ከጌታችን ጋራ አደገ ስለዚህም ክብር ይግባውና የጌታችን ወንድም ተባለ። ከጌታችን ዕርገትም በኋላ ሐዋርያት በኢየሩሳሌም አገር ላይ ኤጲስቆጶስ አድርገው ሾሙት። ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አስተምሮ ብዙዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው። እግዚአብሔርም በእጆቹ ታላላቅ ድንቆችንና ተአምራቶችን አደረገ።
🌹 በአንዲት ዕለትም በጎዳና ሲጓዝ አንድ ሽማግለሸ አገኘ። ቅዱስ ያዕቆብም "ሽማግሌ ሆይ በቤትህ ታሳድረኛለህን?" አለው። አረጋዊውም "እሺ እንዳልክ ይሁን" አለ በአንድነትም ሲጓዙ ጋኔን ያደረበት ሰው አገኘው በአየውም ጊዜ "የክርስቶስ ሐዋርያ ሆይ እኔ ካንተ ጋር ምን አለኝ ልታጠፋኝ መጣህን" ብሎ ጮኸ። ሐዋርያውም "በናዝሬቱ ኢየሱስ ስም ተዘጋ ከሰውዬውም ውጣ" አለው። ወዲያውም ያ ጋኔን ከሰውዬው ላይ ወጣ።
🌹 ያ ሽማግሌም ይህን ድንቅ ተአምር አይቶ ደነገጠ ከሐዋርያው እግር በታችም ወድቆ እንዲህ አለው "ወደ ቤቴ ልትገባ አይገባኝም ነገር ግን እድን ዘንድ ቤተ ሰቦቼም ሁሉ ይድኑ ዘንድ ምን ላድርግ" አለ ያን ጊዜም ሐዋርያው "አቤቱ ጌታዬ ሆይ መንገዴን አሳምረህልኛልና አመሰግንሃለሁ" ብሎ ጌታችንን አመሰገነው። ወደ ሽማግሌዎች ተመልሶ የድኅነትን ነገር ነገረው ከብር ይግባውና ስለጌታችን ሰው መሆን ስለ መከራው ስለ ሞቱና ስለ መነሣቱ አስተማረው።
🌹 ከዚህም በኋላ ያ ሽማግሌ ሐዋርያውን ወደ ቤቱ አስገባው ቤተ ሰቦቹም ሁሉ ወደርሱ ተሰበሰቡ ቅዱስ ያዕቆብም አስተምሮ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው። ሥጋውንና ደሙንም አቀበላቸው።
🌹 የከተማው ሰዎችም በሰሙ ጊዜ በሽተኞችን ሁሉ ወደርሱ አመጡ ሁሉንም አዳናቸው ለእነርሱም ሃይማኖትን አስተምሮ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው። ቀሳውስትንና ዲያቆናትንም ሾመላቸው ያንን ሽማግሌም ኤጲስቆጶስ አድርጎ ሾመው ክብር ይግባውና የጌታችንንም ወንጌል ሰጣቸው።
🌹 ከዚህም በኋላ ያስተምር ዘንድ ወደ ሌሎች አገሮች ወጥቶ ሔደ። አንዲትም መካን ሴት ነበረች እግዚአብሔር ልጅን ይሰጣት ዘንድ ስርሷ እንዲጸልይላት ቅዱስ ያዕቆብን ለመነችው። እርሱም ጸለየላትና ወንድ ልጅን ወለደች ስሙንም ያዕቆብ ብላ ጠራችው ልጅዋንም ተሸክማ ወደ ሐዋርያው መጥታ ሰላምታ አቀረበችለት ከልጅዋም ጋር ከእርሱ ተባረከች።
🌹 ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን ብዙዎች አይሁድ ወደርሱ ተሰበሰቡ ስለ ጌታ ስለ ኢየሱስም የማን ልጅ እንደሆነ ይነግራቸው ዘንድ ጠየቁት እነርሱ እርሱ ጌታች የዮሴፍ ልጅ እንደሆነ እርሱም ወንድሙ እንደሆነ እንዲነግራቸው አስበው ነበርና። ቅዱስ ያዕቆብም በሦስተኛ ደርብ ላይ ወጥቶ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነም ከአብ ጋራም ትክክል እንደሆነ ይገልጽላቸው ጀመረ።
🌹 ይህንንም በሰሙ ጊዜ እጅግ ተቈጡ ከደርቡ ላይ አውርደው የጸና ግርፍትን ገረፉት ከእነርሱም ውሰጥ የልብስ ማጠብያ የእንጨት ገበታ የያዘ አንድ ሰው መጣ በዚያ እንጨትም ቅዱስ ያዕቆብን ራሱ ላይ መታው ያን ጊዜም ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ።
🌹 ስለርሱ ወይን እንዳልጠጣ ደም ከለው ወገን እንዳልበላ በራሱም ላይ ምላጭ እንዳልወጣ በውሽባ ቤት እንዳልታጠበ ሁለት ልብስን እንዳለበሰ ሁል ጊዜም እንደሚቆምና እንደሚሰግድ ተጽፏል። ከመቆም ብዙ የነሳ እግሮቹ አብጠው ነበር። ከዚህም በኋላ ዐረፈና በቤተ መቅደሱ ጎን ቀበሩት። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የሐምሌ 18 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 #ቅዱስ_ጢሞና፦ ይህም ቅዱስ ቁጥሩ ከሰባ ሁለቱ አርድእት ውስጥ ነው። ቅዱስ ጢሞና ሰማያዊ ሀብትን መለኮታዊ ኃይልን ገንዘብ አድርጎ በሽተኞችን ፈወሳቸው አጋንንትም ተገዙለት ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ በምድር ሳለ አገለገለው። ወደ ሰማይም ከዐረገ በኋላ ሐዋርያትን አገለገላቸው በሃምሳኛው ቀንም ጰራቅሊጦስ በወረደ ጊዜ የአጽናኛ መንፈስ ቅዱስን ጸጋ ከእርሳቸው ጋር ተቀበለ።
🌹 ከዚህም በኋላ ሰባት ሁነው ከተቆጠሩት ዲያቆናት ጋር ሐዋርያት ሾሙት እነርሱ መንፈስ ቅዱስን ዕውቀትንም የተመሉ እንደሆኑ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ምስክር ሁኖአል። በዲቁና አገልግሎትም ጥቂት ከአገለገለ በኋላ ብልቃ ከሚባ አገር በስተምዕራብ በሆነ ስብራ በሚባል አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት በውስጧም ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት አስተማረ ከዮናውያንና ከአይሁድም ብዙዎችን አጠመቃቸው።
🌹 የዚያች አገር ገዢም ይህን በሰማ ጊዜ ቅዱስ ጢሞናን ይዞ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃይቶ በእሳት አቃጠለው በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ጥምቀት 26 ቀን ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያ በቅዱስ ጢሞ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 26 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለጢሞና_እምኍልቈ_ሰብዓ_ወክልኤቱ አርድእት። #ወእምሰብዓቱ_ዲያቆናት። ዘፈጸመ ስምዐ በዋዕየ እሳት። ወካዕበ ዓዲ በዛቲ ዕለት። ሰላም እብል ለኄራስ ሰማዕት"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥቅምት_26።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ወአንሰ እጼሊ። ፈደዩኒ እኪት ህየንተ ሠናይት። ወጸልዑኒ ህየንተ ዘአፍቀርክዎሙ"። መዝ 108፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 13፥14-ፍ.ም።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ይዌስክ እግዚአብሔር ላዕሌክሙ። ላዕሌክሙ ወላዕለ ውሉድክሙ። ቡሩካኑ አንትሙ ለእግዚአብሔር"። መዝ 113፥22-23። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 1፥15-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 2፥18-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 6፥1-8። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-12። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ጢሞ የዕረፍት በዓል፣ የሐዋርያው የቅዱስ ያዕቆብ የመታሰቢያ በዓልና የጽጌ ጾም ለሁላችንም ይሁንልን።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፭ (25) ቀን።
🌹 እንኳን #ለኢትዮጵያ_ጻድቅ_ለአቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ለአጎት_ልጅ ለታላቁ አባት ከበሬ ጋር ተጠምደው ሰማዕትነትን ለተቀበሉት #ለአቡነ_ሕፃን_ሞዐ_ቃል_ኪዳን_ለተቀበሉባት ለመታሰቢያ በዓላቸው እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #አቡነ_ሕፃን_ሞዐ፡- በአባታቸው አርከሌድስ እናታቸው ትቤ ጽዮን ይባላሉ፡፡ የተወለዱት ጥር 25 ነው፡፡ አቡነ ሕፃን ሞዐ እና ከእነ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ጋር የሥጋ ዝምድና አላቸው፡፡ ይኸውም አባታቸው አርከሌድስና ጸጋ ዘአብ ወንድማማቾቸ ናቸው፡፡ አርከሌድስና ጸጋ ዘአብ ሌሎች ሌሎች አራት ወንድሞች አሏቸው፡፡
🌹 እነርሱም እንድርያስ፣ ዘርዐ አብርሃም፣ ቀሲስ ዮናስ እና ቀሲስ ዮሐንስ ናቸው፡፡ አርከሌድስ ሕፃን ሞዐን ይወልዳል፣ ጸጋ ዘአብ ተክለ ሃይማኖትን ይወልዳል፣ እንድርያስ ሳሙኤል ዘወገግን፣ዘርዐ አብርሃም ታላቁ አኖሬዎዮስን፣ ቀሲስ ዮናስ ገላውዲዮስንና የፈጠጋሩን ማትያስን፣ እና ቀሲስ ዮሐንስ ዜና ማርቆስን ይወልዳሉ፡፡ እነዚህ የከበሩ ቅዱሳን አባቶቻችን በእናታቸውም ወገን ቢሆን እንዲሁ በዝምድና የተቆራኙ ናቸው፡፡ አቡነ ሕፃን ሞዐ በሌላኛው ስማቸው ሕፃን ዘደብረ በግዕ ተብለውም ይጠራሉ፡፡ ይኸውም የደብረ በግዕን ገዳም የመሠረቱት እርሳቸው ስለሆኑ ነው፡፡
🌹 ከአራባ ሰባቱ የአገራችን ቀደምት ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ በመንዝና በተጉለት የሚገኙ ታላላቅ ገዳማትን አብዛኞቹን የመሠረቷቸው አቡነ ሕፃን ሞዐ ናቸው፡፡ ጻድቁ በክፉዎች ወሬና ሴራ ምክንያት ከበሬ ጋር ተጠምደው ሰማዕትነት የተቀበሉ አባት ናቸው፡፡ ከበሬ ጋር ሲታረሱ ውለው በእጅጉ ከደከማቸ በኋላ በኃይል የተነፈሱባት ምድሪቱ ዛሬም ድረስ ልክ እንደሰው የሚሞቅ ትንፋሽ ታወጣለች፡፡ ያም በጻድቁ እስትንፋስ አምሳል ከመሬት ውስጥ የሚወጣው እስትንፋስ ለአስም በሽታ መድኃኒት ሆኖ ብዙዎችን እየፈወ ነው፡፡ ገዳማቸው ከደብረ ብርሃን ከተማ በእግር የሁለት ሰዓት መንገድ ርቀት ይገኛል፡፡ ይኸውም ከወንይዬ ተክለ ሃይማኖት ገዳም አጠገብ ነው፡፡ ጻድቁ ጥር 25 ቀን ልደታቸው፣ ጥቅምት 25 ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ዕለት ሲሆን ሐምሌ 25 ደግሞ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፬ (24) ቀን።
🌹 እንኳን #አገሩ ጋዛ_ለሆነ_አባ_ኤጲፋንዮስንም ላመነኰሰውና ለደሴተ ቆጵሮስም ኤጲስ ቆጶስ እንደሚሆን ትንቢት ለተናገረው #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅና_ቅዱስ_ባስልዮስ ላመሰገኑት ለታላቁ ለመስተጋድል መነኰስ #ለአባ_አብላርዮስ_ለዕረፍት_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦#ከሰማዕት_ለጊኖስ ባልንጀራው ከሊቀ ጳጳሳት#አባ_ጳውሎስ_ከዘይና_ከአውስያና_ከቈስጠንጢኖስም ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #መስተጋድል_መነኰስ_አባ_አብላርዮስ፦ ይህም ቅዱስ ጋዛ ከሚባል አገር ነው ወላጆቹም አረማውያን ናቸው የዮናናውያንንም ትምህርታቸውንና ፍልስፍናቸውን አስተማሩት ሰውነቱ ለጥበብ ማደሪያዋ እስከሆነ ድረስ በዕውቀቱ ከጓደኞቹ በላይ ሆነ።
🌹 ከዚህም በኋላ ከአገሩ የሌለ መልካም የሆነ ጥበብን ከውጭ አገር መማርን ወዶ ተነሥቶ ወደ እስክንድርያ አገር ሔደ መምህራንም ሁሉ ከሚኖሩበት ቦታ ገብቶ ከእርሳቸው ዘንድ ብዙ ትምህርትን ተማረ በዚያንም ጊዜ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ለመማር ተነሣሥቶ ቸኰለ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ብዙዎቹን አነበበ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ እለእስክንድሮስም ይተረጒምለትና ያስረዳው ነበር።
🌹 ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የክርስትናን ጥምቀት ተጠመቀ ከዚያም መንኲሶ በምንኲስና ሕግ ጸንቶ ገድልን ተጋደለ ወደ አባ እንጦንዮስም ሔዶ መንፈሳዊ የሆነ የትሩፋትን ሥራ እየተማረ በእርሱ ዘንድ ብዙ ወራት ኖረ። ወላጆቹም እንደሞቱ በሰማ ጊዜ ሒዶ የተዉለትን ገንዘባቸውን ሁሉንም ወስዶ ለድኆችና ለችግረኞች መጸወተ ከዚህም በኋላ ከሶርያ ገዳማት ወደ አንዱ ገዳም ገባ በዚያም በጾም በጸሎት በስግደት በመትጋት ፍጹም ገድልን ተጋደለ በየሰባት ቀን እስቲመገብ ድረስ ምግቡም የዱር ሣር ነበር።
🌹 እግዚአብሔርም ሀብተ ትንቢትን ሰጥቶት ልቡናው ብሩህ ሆነ ድንቆች ተአምራትንም የሚያደርግ ሆነ ኤጲፋንዮስንም ያመነኰሰውና ለደሴተ ቆጵሮስም ኤጲስ ቆጶስ እንደሚሆን ትንቢት የተናገረለት እርሱ ነው።
🌹 የዚህም አባት መላ ዕድሜው ሰማንያ ዓመት ነው ከክርስትውና ከምንኲስናው በፊት ዐሥራ ሰባት ዓመት በምንኲስናም ስልሳ ሦስት ዓመት ነው ክብር ይግባውና እግዚአብሔርንም ካገለገለ በኋላ ጥቅምት 24 ቀን በሰላም ዐረፈ። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም አመስግኖታል ሁለተኛም ቅዱስ ባስልዮስ በመጻሕፍቱ አመስግኖታል። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አብላርዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 24 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_ለአብላርዮስ_ለከርሡ ዘሠርዐ። ማየ ባሕር ስቴ ወሣዕረ ገዳም መብልዐ። በዕለተ አዕረፈ ዮም እንዘ ይብል አኅዓድ። ኢትፍርሂ ነፍስየ እምነ ሥጋ ወጺአ። እስመ ተቀነይኩ ለክርስቶስ ዓመታት ሰብዓ"። #ሊቀ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የጥቅምት_24።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #የዕለቱ_ምስባክ፦ "ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊት ገዳም። ወከዐዉ ደሞሙ ከመ ማይ ዐውዳ ለኢየሩሳሌም። ወኀጥኡ ዘይቀብሮሙ"። መዝ 78፥2-3። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 14፥26-34፣ 1ኛ ጴጥ 3፥5-10 እና የሐዋ ሥራ 16፥13-16። የሚነበበው ወንጌል ማር13፥11-24። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ወይም የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የፀበለ ማርያምና የአባ ዘግሩም የመታሰቢያ በዓልና የጽጌ ጾም ለሁላችንም ይሁንልን።
@Teamihokidusan
አጣሁት ስለርሱም በጠየቅሁ ጊዜ በቀድሞ ዘመን ዮሐንስ አፈ ወርቅን ንግሥት አውዶክስያ እንዳሳደደችው በክፉዎች ሰዎች ምክር ንግሥቲቱ ሚስቴ ማሳደዷን የቀኖናውንም ትእዛዝ በመተላለፍ በፈቃዳቸው ሌላ ጳጳስ እንደሾሙ ነገሩኝ"።
🌹 እርሱ አባ ዮሐንስም ከኢትዮጵያ በአሳደዱት ጊዜ ወደ አስቄጥስ በመሔድ አስቀድሞ በመነኰሰባት በአባ ሙሴ ጸሊም ገዳም በዚያ ተቀመጠ። የኢትዮጵያ ንጉሥ መልእክትም ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ በደረሰች ጊዜ አነበባት ስለ ኢትዮጵያ ንጉሥ የሃይማኖት ጽናት እጅግ ደስ አለው ፈጥኖም ወደ አስቄጥስ ገዳም መልእክተኞችን ልኮ አባ ዮሐንስን ወደርሱ አስመጥቶ አረጋጋው አጽናናው ከዚያም በኋላ ከደጋጎች ሰዎች ጋር ወደ ኢትዮጵያ አገር ላከው።
🌹 አባ ዮሐንስም ወደ ኢትዮጵያ አገር በደረሰ ጊዜ ቸነፈር ተወገደ ዝናብም ዘነበ ንጉሡና መላው የኢትዮጵያ ሰዎች ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑት። ይህም ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ መናፍቃንን የሚገሥጻቸው ሆነ ሕዝቡንም ከአባቶቻቸው በተቀበሏት በቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አስተማራቸው ከቅዱሳት መጻሕፍትም ለእነርሱም ሥውር የሆነውን ተርጉሞ ያስረዳቸዋል ያስገነዝባቸዋልም በትምህርቱና በጸሎቱም እንዲህ ጠበቃቸው ጌታችንም በእጆቹ ብዙዎች ተአምራትን አደረገ ያማረች ገድሉንም ፈጽሞ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ጥቅምት 23 ቀን በሰላም በፍቅር ዐረፈ። መላ የሕይወቱም ዘመን ሰባ ስምንት ነው ከምንኲስና በፊት ሃያ አመት በምንኲስና ተጋድሎ ሠላሳ ዘጠኝ ዓመት በሊቀ ጵጵስና ሹመት ዓሥራ ዘጠኝ ዓመት ኖረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሴፍ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
🌹 #የከሀዲ_ዱድያኖስ_ንጉሥ_ሚስት_ሰማዕቷ #ቅድስት_እለእስክንድርያ፦ ይኸውም ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ መስሎ ቅዱስ ጊዮርጊስ በዘበተበት ጊዜ ዝንጉዕ ዱድያኖስም ዕውነት መስሎት ራሱን ሊስም ተነሣ። ቅዱሱ ግን ለአማልክት ከመሠዋት አስቀድሞ አይሆንም ብሎ እንዳይስመው ከለከለው።
🌹 ከዚህ በኋላም ዱድያኖስ ወደ ቤተ መንግሥቱ አዳራሽ ቅዱስ ጊዮርጊስን አስገባው በዚያም በንግሥት እለእስክንድርያ ፊት የዳዊትን መዝሙር በማንበብ ጸለየ። በሰማችም ጊዜ ይተረጒምላት ዘንድ ለመነችው ያን ጊዜም ተረጐመላት የክብር ባለቤት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ጌትነቱን ገለጠላት ትምህርቱም በልቡዋ አድሮ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነች።
🌹 ከዚህም በኋላ ሲነጋ ለአማልክት ወደሚሠዋበት ቅዱስ ጊዮርጊስን ወሰዱት እርሱም የረከሱ አማልክትን ትውጣቸው ዘንድ ምድርን አዘዛት ምድርም ዋጠቻቸው። ንጉሥ ዱድያኖስም አፈረ እየአዘነና እየተከዘ ወደ ሚስቱ ወደ እለእስክንድርያ ዘንድ ገባ። እርሷም "ክርስቲያኖችን አትጣላቸው አምላካቸው ጽኑዕና ኃያል ነው አላልኩህምን" አለችው። ይህንንም ሰምቶ በእርሷ ላይ ተቆጣ ያሠቃዩዋት ዘንድ ጡቶቿንም ሠንጥቀው ይሰቅሏት ዘንድ አዘዘ። የሰማዕትነትንም አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት እለእስክንድርያ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። የሚያዝያ 15 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_ዲዮናስዮስ፦ በዐላውያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ሰማዕትነት ተቀበለ። ይህንንም ቅዱስ በያዙት ጊዜ ብዙ ሥቃይን አሠቃዩት ማሠቃየቱንም በሰልቹ ጊዜ ራሱን በሰይፍ አስቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ። የቅዱስ ዲዮናስዮስ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥቅምት 23 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
🌹 "#ሰላም_እብል_ለሊቀ_ጳጳሳት_ዮሴፍ። ዘእምሀገረ መኑፍ። ዘተውህበ ሎቱ አእምሮ መጽሐፍ። ወሰላም ካዕበ ለተልእኮቱ ዕስቁፍ። እንተ ክሣዶ መቲረ ዘኢይክል ሰይፍ"። #ሊቀ_አርከ_ሥሉስ_አርኬ #የጥቅምት_23።
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 #ጥቅምት ፳፫ (23) ቀን።
🌹 እንኳን #ለእስክንድርያ_አገር_ኀምሳ_ሁለተኛ #ሊቀ_ጳጳሳት_ለአባ_ዮሴፍ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ፣ በዐላውያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን በሰማዕትነት ለተቀበለ #ለቆሮንቶስ_አገር_ኤጺስቆጶስ_ለቅዱስ_ዲዮናስዮስ ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓልና ለከሀዲ ንጉሥ ለዱድያኖስ ለሚስት #ለቅድስት_እለእስክንድርያ መታሰቢያዋ በዓልና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱሳን_ኢላርዮስ_ከጣንቅያቅ፣ #ከቴዎደስዮስ_ከቴዎላስ_ከዮሳብና_ከገድላ ከሰማዕት እስክድርያም ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የእስክንድርያ_አገር_ኀምሳ_ሁለተኛ_የሆነ #ሊቀ_ጳጳሳት_አባ_ዮሴፍ፦ ይህም አባት ከመኑፍ አገር ከታላላቆች ተወላጆች ወገን ነው ወላጆቹም ብዙ ገንዘብ ያላቸው ነበሩ ታናሽም ሁኖ ሳለ አባትና እናቱ ትተውት ሲሞቱ ድኃ አደግ ሆነ አንድ እግዚአብሔርንም የሚወድ ሰው አሳደገው።
🌹 አድጎ በጎለመሰም ጊዜ የወላጆቹን ገንዘብ ሁሉንም ወስዶ ለድኆችና ለምስኪኖች መጸወተ ከዚህም በኋላ ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጥቶ ከአንድ ፃድቅ ሽማግሌ ሰው አባት ዘንድ መነኰሰ በበጎ ገድል ሁሉ እየተጋደለ ኖረ።
🌹 ዳግማዊ አባ ማርቆስም ሊቀ ጵጵስና በተሾመ ጊዜ የዚህን አባ ዮሴፍን በጎ ጠባዩንና የትሩፋቱን ዜና ሰምቶ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው በቤቱም አኖረው። ከብዙ ወራትም በኋላ አባ ዮሴፍ ሊቀ ጳጳሳቱን አባ ማርቆስን "ወደ አስቄጥስ ገዳም እሔድ ዘንድ ተወኝ" ብሎ ለመነው ያን ጊዜም ቅስና ሹሞ አሰናበተው ሊቀ ጳጳሳት አባ ስምዖንም እስከ ዐረፈ ድረስ በዚያ በእስቄጥስ ገዳም ኖረ ከዚህም በኋላ የግብጽ አገር ያለ ሊቀ ጳጳሳት ብዙ ወራት ኖረች ።
🌹 ከዚህም በኋላ ኤጲስቆጶሳቱ መማለጃ ስለተቀበሉ ከአንድ ሚስቱ ከሞተችበትና መዓስብ ከሆነ ጸሐፊ ጋር ሊቀ ጵጵስና ይሾሙት ዘንድ ተስማሙ እኩሌቶቹ ግን ተቃወሟቸው እንዲህም አሏቸው "የአባቶቻችን ቀኖና መማለጃ የሚቀበለውን ሁሉ ወይም ስለ ክህነት ሹመት መማለጃ የሚሰጠውን ያወግዛል። ይልቁንም ይህ ሰው ሚስት አግብቷል እንዴት ሊሾም ይችላል በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ የሚሾም ንጹሕ ድንግልም ነውና"። ይህንንም በአሏቸው ጊዜ ፈሩ ተመልሰውም ተስማሙ ለዚች ለከበረች ሹመት የሚሻለውን ይገልጽላቸው ዘንድ ክብር ይግባውና ወደ ጌታችን በአንድ ምክር ሁነው ጸለዩ እግዚአብሔርም ሰምቷቸው ለዚች የከበረች ሹመት የሚሻል አባ ዮሴፍ እንደሆነ አሳሰባቸው።
🌹 ከዚህም በኋላ አባ ዮሴፍን ያመጡት ዘንድ ወደ አስቄጥስ ገዳም መልእክተኞችን ላኩ መልክተኞችም "ይህን አባት ዮሴፍን የመረጥከው ከሆነ ምልክትን ትገልጥልን ዘንድ አቤቱ እንለምንሃለን የቤቱም ደጃፍ ክፍት ሁኖ ካገኘን ምልክት ይሁንልን" ብለው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ።
🌹 በደረሱም ጊዜ አንዱን መነኰስ እየሸኘ የበዓቱም ደጃፍ ክፍት ሁኖ አባ ዮሴፍን አገኙት በአያቸውም ጊዜ መንፈሳዊ ሰላምታ በመስጠት እጅ ነሣቸውና በደስታ ተቀብሎ ወደ በዓቱ አስገባቸው በዚያንም ጊዜ "ለአባ ዮሴፍ ሊቀ ጵጵስና ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል" እያሉ ይዘው አሠሩት። እርሱ ግን "እኔ ብዙ ኃጢአትን ሠርቻለሁና ይህ የከበረ ሹመት አይገባኝም" እያለ ይጮህ ነበር እነርሱም ወደ እስክንድርያ ከተማ ወስደው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እንጂ ምንም ምክንያት አልተቀበሉትም።
🌹 በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበርም በተቀመጠ ጊዜ ለአብያተ ክርስቲያን እጅግ የሚያስብ ሆነ ለርሱ የሆነውን የግብሩን ገቢ ወስዶ ምድሮችን በመግዛት ለአብያተ ክርስተያን መተዳደሪያ ሊሆኑ ጉልቶች ያደርጋቸው ነበርና። አዘውትሮም ሕዝቡን የሚያስተምራቸው ሆነ በምንም በምን ለየአንዳንዱ ቸለል አይልም ነገር ግን ሰይጣን ስለቀናበት ያለ ኀዘን አልተወውም። ይህም እንዲህ ነው በምስር አገር የተሾሙ ሁለት ኤጲስቆጶሳት በሕዝቡ ላይ ክፉ ነገር በማድረግ በማይገባ ሥራ አስጨነቋቸው እርሱም በርኅራኄና በፍቅር መንጎቻቸውን እንዲጠብቁ አዘዛቸው ለመናቸውም እነርሱ ግን ሰምተው ከክፋታቸው አልተመለሱም።
🌹 በሕዝቡም ላይ ችግርን በአበዙ ጊዜ ሕዝቡ ሁሉም በጠቅላላ ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ መጡ በፊቱም እንዲህ ብለው ጮኹ "እሊህን ኤጲስቆጶሳት ከላያችን ካላነሣሃቸው እኛ ወደሌላ ሃይማኖት እንገባለን አባ ዮሴፍም በመካከላቸው ሰላምን ለማድረግ ብዙ ትግልን ታገለ ግን አልተቻለውም።
🌹 ከዚህም በኋላ በግብጽ አገር ያሉትን ኤጲስቆጶሳት ለጉባኤ ሰበሰባቸውና ስለ እሊህ ሁለት ኤጲስቆጶሳት ነገራቸው አሁንም ከመንጋዎቻቸው ጋር ሊአስታርቅ ሽቶ እሊህን ኤጲስቆጶሳት ወደ ጉባኤው አስቀረባቸው እነርሱ ግን የጉባኤውንም የእርሱንም ቃል አልተቀበሉም ስለዚህም ያ ጉባኤ ከሹመታቸው ሻራቸው። እነርሱም ወደ ግብጽ ንጉሥ ሒደው በሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ ላይ በሐሰት ነገር ሠሩበት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍንም ያመጡት ዘንድ ንጉሡ ወንድሙን ከጭፍራ ጋር ላከው።
🌹 የንጉሡም ወንድም ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ በደረሰ ጊዜ ተበሳጨ ሊገለውም ወዶ ሰይፉን መዞ ሊቀ ጳጳሳቱን ሊመታው ሰነዘረበት ግን እጁ ወደ ሌላ አዘንብሎ ምሰሶ መትቶ ሰይፉ ተሰበረ እጅግም ተቆጥቶ ሌላ ሰይፍን መዝዞ በመላ ኃይሉ መታው ያን ጊዜም ሰይፉ ከአንገቱ ወደ ወገቡ ተመልሶ ልብሱንና ቅናቱን ብቻ ቆረጠ የንጉሡም ወንድም ከክፋት ንጹሕ እንደሆነ ስለዚህም አምላካዊት ኃይል እንደምትጠብቀው አሰበ አስተዋለም። ወደ ንጉሡም በክብር አደረሰው ወንድሙ ለሆነ ንጉሥም በእርሱ በሊቀ ጳጳሳቱ ላይ የሆነውን ሁሉ ነገረው ንጉሡም ፈራው አከበረውም።
🌹 ከዚህም በኋላ ስለከሰሱት ስለ ሁለቱ ኤጲስቆጶሳት ጠየቀው እርሱም ስለ ክፉ ሥራቸው በጉባኤ እንደተሻሩ እውነቱን ለንጉሡ አስረዳው ያን ጊዜም ሐሰተኞች እንደሆኑ ንጉሥ አወቀ ይገድሏቸውም ዘንድ አዘዘ። ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍም ንጉሡን እንዲህ ብሎ ማለደው "ጌታችን በክፉ ፈንታ በጎ እንድናደርግ እኛን አዞናልና ስለ እግዚአብሔር ብለህ እሊህን ማራቸው እንጂ አትግደላቸው" ንጉሡም ስለ የዋህነቱ አደነቀ ልመናውንም ተቀብሎ ማረለት።
🌹 ከዚህም በኋላ በሹማምንቱና በኤጲስቆጶሳቱ ሁሉ ላይ የፈለገውን ያደረግ ዘንድ ቢፈልግ እንዲሾም ወይም እንዲሽር የሚቃወመው እንዳይኖር ደብዳቤ በመጻፍ ሥልጣንን ሰጠው።
🌹 በዚህም አባት ዘመን የኢትዮጵያ ንጉሥ ወደዚህ አባት ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሴፍ እንዲህ ብሎ መልእክትን ላከ "ለወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ መንበርና በላዩ ለመቀመጥ ለተገባው ቅድስናህ እጅ እነሣለሁ በእኔና በመንግሥቴ ላይ በመላው ወገኖቼ በኢትዮጵያ ሰዎች ላይ ይቅርታ እንድታደርግና አባታችንን አባ ዮሐንስን እንድትልክልን እለምንሃለሁ ከሀገራችን ሰዎች ከእውነት መንገድ የወጡና የሳቱ ጳጳሳችንን አባ ዮሐንስን እኔ ሳልኖርና ሳላውቅ አባረውታልና ስለዚህም በሀገራችን ቸነፈርና ድርቅ ሁኖ ከሰዎችም ከእንስሶችም ብዙዎች አለቁ። አሁንም አባቴ ሆይ ስንፍናችንን ይቅር በል መሐሪና ይቅር ባይ ወደ ሆነ እግዚአብሔር ፈጽሞ ይማልድልን ዘንድ በከበረች ጸሎቱም ከዚህ መከራ እንድን ዘንድ አባታችንን አባ ዮሐንስን ላክልን። አባቴ ሆይ የተባረረበትን ምክንያት እኔ አስረዳሃለሁ እኔ ልጅህ ከአባቴ ከጳጳስ አባ ዮሐንስ ቡራኬ ተቀብዬ እርሱ ከሠራዊቴ ጋር በፍቅር አሰናብቶኝ ወደ ጦር ሜዳ ሔድሁ ከጦር ሜዳም በተመለስኩ ጊዜ አባቴን አባ ዮሐንስ ጳጳሱን
🌹 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። 🌹
🌹 እንኳን #ለዘመነ_ጽጌ_ለማኅሌተ_ጽጌ_አራተኛ #ሳምንት_ዕለት_እሑድ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "#ጸገየ_ወይን_ወፈርየ_ሮማን ወፈርዩ ኵሉ ዕፀወ ገዳም ቀንሞስ ዕቁረ ማየ ልብን #ሠርዐ_ለነ_ሰንበተ_ለዕረፍተ_ዚአነ ጸገዩ ጽጌያት ጸገዩ ደንጐላት፤ አዝ፣ ኃለፈ ክረምት ቆመ በረከት #ተሠርገወት_ምድር_በስነ_ጽጌያት፤ አዝ፣ #እግዚኣ_ለሰንበት_ወአቡሃ ለምሕረት ሠርዐ ለነ ሰንበተ ለእረፍተ ዚአነ #ሠርዐ_ለነ_ሰንበተ_ለዕረፍት_ወለመድኃኒት። ትርጉም፦ #አበቦች_አበቡ_የሱፍ_አበቦችም_አበቡ፣ ክረምት አለፈ፣ በረከት ተተከለ፣ #ምድር_በአበቦች ውበት ተጌጠች፣ #አቤቱ_የሰንበት_ጌታ_የምሕረት_አባቷ #ለዕረፍትና_ለመድኃኒት_ሰንበት_ሠራ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
✝ ✝ ✝
🌹 #የዚህ_ሳምንት_ዕለቱ_ምስባክ፦ "ዓጸደ ወይን አፍለስከ እምግብፅ። ሰደድከ አሕዛበ ወተከልከ ኪያሃ። ወፄሕከ ፍኖተ ቅድሜሃ"። መዝ 79፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 11፥13-25፣ ራዕ ዮሐ 12፥13-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 11፥1-12። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 21፥33-ፍ.ም። የሚቀደሰው የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ኤልሳዕና የአቡነ ዮሴፍ የዕረፍት በዓልና ዕለተ ሰንበትና የጽጌ ጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
