ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
Open in Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
Show more638
Subscribers
-224 hours
-57 days
-1130 days
Posts Archive
✝ ✝ ✝
❤ #የቅዱስ_ኤጲፋንዮስ_ሥጋው_ወደ_ቆጵሮስ መመለስ፦ ይህም እንዲህ ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ወደ መንበረ ሢመቱ እንደማይደርስ ትንቢት እንደተናገረለት ወደ ቆጵሮስ ሳይደርስ በመርከብ ውስጥ ሳለ ግንቦት ዐሥራ ሰባት ቀን ዐረፈ። በዐረፈም ጊዜም በመርከብ ጭነው ወደ ቆጽሮስ ከተማ አደረሱት። ካህናቱና ሕዝቡ ሁሉ መጡ ከሳቸውም ጋር ወንጌሎች መስቀሎች መብራቶችና ማዕጠንቶችም የሐዋርያት ጉባኤ ከታላቂቱ ቤተ ክርስቲያን እስኪያደርሱት በዝማሬ በማኅሌት በሚገቡት ጸሎቶች ሁሉ እያመሰገኑ ሥጋውን ተሸክመው ካህናቱም መቃብሩን በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ሊያዘጋጁ ወደዱ። ቀድሞ ስለ ክፉ ሥራቸው ቅዱስ ኤጲፋንዮስ አውግዞአቸው የነበሩ ሁለት ዲያቆናት ተቃወሟቸው። ስለዚህም አርባ ቀን ተቀመጠ ነገር ግን ሽታው እንደ ሙታኖች ሽታ አልተለወጠም እንደ አንቀላፋ ሰው እንጂ።
❤ ከዚህም በኋላ አንድ ደግ ዲያቆን ወደ ቅዱስ ሥጋ ቀርቦ "አባቴ ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ አንተ ባለሟልነት እንዳለህ እኔ አውቃለሁ። ብትፈቅድስ ክፉዎች ተቃዋሚዎችን ልታሸንፋቸው ትችላለህ" አለ። የቅዱስ ኤጲፋንዮስንም እጅ ይዞ ምድርን መታባት በዚያንም ጊዜ ሁለቱ ዲያቆናት በግምባራቸው ተደፉ። ለመሞትም ደረሱ ወደ ቤታቸውም ወስደዋቸው ሞቱ።
❤ ቅዱስ ኤጲፋንዮስም ካህናቱ በሚጣፍጡ ሽቱዎች ገንዙት። በከበሩ ልብሶችም ጠቅልለው ከከበረ ደንጊያ በተሠራ ሣጥን ውስጥ ጨምረው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ቀበሩት። ቀድሞ በሕይወቱ ሳለ እንደሚሠራው ከሥጋው ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ኤጲፋንዮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ #የግንቦት_28_ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰአሉ_ለነ_አብርሃም_ይስሐቅ_ወያዕቆብ_አበወ ሕዝብ ወአሕዛብ ወዘመሐይምናን መክብብ ሰአሉ ለነ አስተምሕሩ ለነ"። ትርጉም፦ የምዕመናን ሹሞች የአሕዛብና የሕዝብ አባቶች #ቅዱሳን_አብርሃም_ይስሐቅ_ያዕቆብ ፈጽማችሁ ለምኑልን አማልዱ፡፡ #ሊቁ_አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ_በሰዓታት_ላይ፡፡
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለአመተ_ክርስቶስ_መንበርተ_ዓለም መኒና። እንተ ረሰየት ይእቲ ንቅዓተ ኰኵሕ መካና። ሠላሳ ወስምነ ዓመታት እስከ ኮና። ይቤሉ ነጋድያን ሶበ ምውተ ረከብና። ውሳጤ በዓት በህየ ቀበርና"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_28።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ71፥15 ወይም መዝ 4፥4። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ2፥1-21 ወይም ሉቃ 9፥18-23።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "አሌ ሎን ለከናፍረ ጒሕሉት። እለ ይነባ ዓመፃ ላዕለ ጻድቅ። በትዕቢት ወበመንኖ"። መዝ 30፥18 ወይም መዝ 50፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 7፥29-ፍ.ም፣ ያዕ 2፥19-ፍ.ም እና የሐዋ.ሥራ 5፥1-12። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 12፥22-39 ወይም ማቴ 9፥9-18። የሚቀደሰው የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ዐማኑኤል በዐል፣ የበዐለ ጰራቅሊጦስ ሰሞንና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት_፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን ተጋዳይ ለሆነች ዓለምን ንቃ ለተወች፤ አባ ዳንኤል ስርሷ እንደተናገረ የዓለምን ፍላጎት ሁሉ ድል ለነሣች፤ ለሠላሳ ስምንት ዓመታት አንዴ ወደ ገዳም ይዛ በሔደች ሽንብራና የጽዋ ውኃ ሳያልቅባት በተሰነጠቀ ዐለት ውስጥ ስትጋደል ለነበለች #ለቅድስት_አመተ_ክርስቶስ_ለዕረፍት_በዓል፣ #ለአባ_ጳኵሚስ_ገዳም ለሆነ በዕረፍቱ ጊዜ ሥጋው አጋዘን ተሸክመው ወደ ሚቀበርበት ቦታ ላመጡቱ #ለአባ_መርቆሬዎስ_ለዕረፍት_በዓልና ለታላቁ #ለቆጵሮስ_አገር_ሊቀ_ጳጳስ_ለቅዱስ_ኤጲፋንዮስ #ሥጋው_ወደ_ቆጵሮስ_ለደረሰበት_በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ከሚታሰቡ፦ በሰማዕትነት ከዐረፉ #ከአባ_ጌርሎስና #ከአርባ_አምስት_ልጆቹ፣ #ከአባ_ስንጣና_ከሰማዕት_አጋቦስ_ከመታሰቢያቸው ረድኤና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_አመተ_ክርስቶስ፦ አባ ዳንኤል እንዲህም አለ "በረሀም ሳለሁ በሌሊት ተነሥቼ በጨረቃ ብርሃን ተጓዝኹ በተራራ ላይ የተቀመጠ ሰውንም አየሁ ጠጉሩም ሁለመናውን ሸፍኖታል በልቤም ወደርሱ ሔድሁ። በአየችኝም ጊዜ ወደ ተሠነጠቀው አለት ውስጥ ገባች "ሰው ሆይ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ በረከትህን እንድቀበል እማልድሃለሁ" አልሁ እጅግም አብዝቼ ለመንሁ። ከዚህም በኋላ "አባት ሆይ አልወጣምና ይቅርታ አድርግልኝ" አለችኝ። እኔም "ስለምን አልኋት" እርሳም "እኔ ሴት ነኝ ራቁቴን ስለሆንኩ" አለችኝ። ይህንንም ሰምቼ የለበስኩትን ዐጽፍ ጣልሁላት ለብሳም ወጣች በአንድነትም ጸለይን።
❤ ከዚህ በኋላ "እናቴ ሆይ ከዓለም ወደዚህ ስለመውጣትሽ ይኸንን የተሠነጠቀ ዐለት እንዴት እንዳገኘሽ ንገሪኝ አልኋት"። እርሷም እንዲህ ብላ መለሰችልኝ በወላጆቼ ቤት ድንግል ሁኜ በኢየሩሳሌም የምኖር ነኝ ሁል ጊዜ የሚጎበኘኝ ከእኔ ጋራ የሚነጋገር አንድ መነኰስ ነበር። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ ወደርሱ ሔድኹ በእግዚአብሔር ፊትም ኃጢአቴን እየታመነ ሲአለቅስ አገኘሁት። ደጅንም በአንኳኳሁ ጊዜ አልከፈተልኝም እየተጸጸተ ልቅሶን አበዛ እንጂ። በዚያን ጊዜ በልቤ እንዲህ አልኩ እኔስ ስለ ጒስቍልናዬና ስለ ኃፍረቴ የማላለቅስና የማልጸጸት ለምድነው ወደ ማደሪያዬም ፈጥኜ ሔድኹ ማቅ ለበስኩ በዘንቢልም ሽምብራ በጽዋ ውኃን ያዝሁ። በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር ዘንድ እንዲህ ብዬ ጸለይኩ "አቤቱ ጽኑዕ ኃያል ለዘላለሙ ድንቅ የሆንክ የጠፋትን የምታድን የወደቁትንም የምታነሣቸው ወደ አንተ የሚጮኹትንም የምትሰማቸው የታመነችብህ ባሪያህን ታድናት ዘንድ ይቅርታህንና ምሕረትህን ላክ። ከምግባር ድኃ የሆንኩ ባሪያህን ጐብኘኝ ንስሐዬንም ተቀበል። ለረጅም ዘመን ስንቅ ይሆነኝ ዘንድ ይህን ሽምብራና ይህን የጽዋ ውኃ ባርከው ስለ ነፍሴ ድኅነት የአሰብኩትን እንዳላቃልል ለሆዴ ምግብ ስለሚአሻኝ"።
❤ ከዚህ በኋላ ነፍሴን በእግዚአብሔር ላይ በመጣል ወጥቼ ወደ በረሀ ሔድኹ እስከ ኤርትራ ባሕርም ደረስኩ። ከዚያም ወደዚህ በረሀ መጥቼ ይህን የተሠነጠቀ ዐለት አገኘሁ ይህ እግዚአብሔር ያዘጋጀልኝ መኖሪያዬ ነው አልሁ። "እንሆ በዚህ በረሀ ውስጥ ሠላሳ ስምንት ዓመት ሆነኝ ያለ አንተ ሰው አላየሁም። ይህም የዘንቢል ሽምብራና የጽዋ ውኃ ሠላሳ ስምንት ዓመት ከእርሳቸው ስመገብ አልጎደሉም ልብሴ ግን አለቀ ነገር ግን ይህ ቦታ ስለ ልብስ መከለያ ሆነኝ። የበጋ ፀሐይ ትኵሳትም አላስቸገረኝም ቊር ቢሆንም በዕድሜዬ ዘመን ሁሉ አላስጨነቀኝም"። ከዚህ በኋላም ከዘንቢል ካለው ሽምብራ እንድመገብ ማለደችኝ ከሽምብራውም በላሁ ከውኃውም ጠጣሁ። ግን አልጐደለም እግዚአብሔርንም አመሰገንሁት ልብሴንም ልተውላት ወደዱሁ እርሷም "ከዚህ የተሻለ አምጣልኝ" ብላ ይህን እምቢ አለችኝ።
❤ ከዚህ በኋላም ከእርሷ ዘንድ ሔድኩ ወደ ገዳም ደርሼ ስርሷ ለአበ ምኔቱ ነገርኩት። "እርሱም ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው አንዱን ይስጥ ብሎ ጮኸ ፈቃደኞች የሆኑም አመጡለት ያን ጊዜም ይዤ ሔድኩ ለአመተ ክርስቶስ ልሰጣት ብዙ ደከምኩ እርሷን በመፈለግ ዞርኩ አላገኘኋትም። ከጥቂት ቀኖች በኋላም አረጋውያን ወደ እኔ መጡ እንህም አሉኝ "ወደ ኤርትራ ባሕር የሚያደርሰውን መንገድ ይዘን በጣኔዎስ በረሀ ስንጓዝ ከዋሻ ዘንድ ሴት ተቀምጣ አይተን ከእርሷ በረከት ለመቀበል ሮጥን ሽሽታ ከዋሻው ገባች ወደ ዋሻውም አፍ ቀረብን ግን አላየናትም። ሽምብራ በዘንቢል ውኃም በጽዋ አግኝተን በላን ጠጣን ያን ጊዜም አለቀ እስከ ንጋትም አደርን።
❤ በነጋም ጊዜ በረከቷን ለመቀበል ቅድስቲቱን ፈለግናት ሙታም አገኘናት ጠጒሯም ሥጋዋን ሁሉ ሸፍኖአል። በዚያም ሰገድን በበዓቷም ውስጥ ቀበርናት የዋሻውንም አፍ በደንጊያ ዘጋን የቅድስቲቱን በረከት እንድንቀበል አድሎናልና እግዚአብሔርን እያመሰገን ወደ በዓታችን ገባን"። በሰማሁም ጊዜ አስቀድሜ ያገኘኋት እንደሆነች አወቅሁ የነገራችኝንም ሁሉ ነገርኳቸው። ጠላት ዲያብሎስን ድል ያደረገው ዘንድ ክፉዎች አጋንንትንም ደካማውን ድኃ የሚረዳ የተመሰገነ እግዚአብሔርን ፈጽመን አመሰገን ነው። ለእግዚአብሔር ይስጋና ይሁን እኛንም በዘመች ቅድስት አመተ ክርስቶስ ጸሎት ይማረን በረከተበም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_መርቆሬዎስ፦ አባ እንጦንዮስ እንዲህ አለ "ለእኔ ገዳም አለኝ ይኸውም የወንድማችን የመርቆሬዎስ ዕረፍቱ ቀረበ" እያሉ ወደእኔ መነኰሳት የመጡበት ነው እኔም በረከቱን ለመቀበል ወደርሱ በሒድኩ ጊዜ ነፍሱ ከሥጋው ሳትለይ በተመሥጦ ላይ አገኘሁት። ከመነኰሳቱ ጋራ በእርሱ ዘንድ ሦስት ሌሊቶች ኖርን በሦስተኛዪቱም ዕለት ነፍሱ ተመልሳ ዐይኖቹን ገለጠ በአየንም ጊዜ "ከእኔ ዘንድ ምን ሰበሰባችሁ" አለን እኛም የሆነውን ሁሉ ነገር ነውና ከዚህም በኋላ ያየውን እንዲነግረን ለመነው እርሱም የሚያስፈራ ሰው ወደርሱ መጥቶ ነፍሱን እንደወሰደ የኃጥአንን ሥቃይ እንዳሳየው የጻድቃንንም ዋጋቸውንና ተድላቸውን እንዳየው ነገራቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ወዮ ብሎ በማልቀስ በግምባሩ ከምድር ላይ ተደፋ እንዲህም አለን "ወንድሞቼ ሆይ ወደ ሐራጺት ገዳም ወደ አባ ጊዮርጊስ ማደሪያ ሒዱ። ከእኔ ጋራ የነበረውን መለአክ መርቆሬዎስን መልሳችሁ በትንሽ በዓት ውስጥ ሲጋደል የኖረ ጊዮርጊስን አምጡት ሲል ሰምቼዋለሁና ይቺም ሥጋው አስቲቋጠር የተጋደለባት የጨው በረሀ ናት"። ወንድሞች መነኰሳትም በሔዱ ጊዜ ሙቶ አገኙት ወደዚህ ገዳምም አምጥተው ቀበሩት። ይህም ወንድም መርቆሬዎስ እንደ ደረቀ እንጨት እስቲሆን ሥጋውን እጅግ አሠቃየ።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ ገዳም ይሔድ ዘንድ ተሰናበተኝ። ደግሞ "ግንቦት ሃያ ስምንት ቀን ወደኔ ና ታገኘኛለህና" አለኝ። በቀጠረኝም ቀን ወደርሱ ሒጄ አገኘሁደትና "እኔ ወደ አባቶቼ እሔዳለሁ" ወደ አንተም ሦስት አጋዘኖች ይመጣሉ ሥጋዬም በጀርባቸው ላይ ጫን እነርሱም ወደ ቦታዬ በእግዚአብሔር ፈቃድ ይመሩሃል። በዚያም በማደሪያዬ ውስጥ ድፈኑኝ" አለኝ። እንደ ቃሉም ሆነለት ከመቃብሩም ቍጥር የሌላቸው ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቁ አባ መርቆሬዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላሙ አሜን።
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት_፳፰ (28) ቀን።
❤ እንኳን #ለደብረ_ገሊላ_ለቅዱስ_ዐማኑኤል የቅዳሴ ቤት ዓመታዊ የንግሥ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ደብረ_ገሊላ_ቅዱስ_አማኑኤል ካቴድራል ታሪክ፦
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከሚገኙትና ከ100 ዓመታት በላይ የምሥረታ ታሪክ ካላቸው ገዳማትና አድባራት መካከል አንዱ የመሳለሚያ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ነው።
❤ ካቴድራሉ የተተከለው በ1905 ዓ.ም በልጅ ኢያሱ ዘመነ መንግሥት ሲሆን ከመቃኞ ጀምሮ በተለያየ ቅርጽ ቤተ ክርስቲያኑ ተገንብቶ አገለግሎት እንደተሰጠበት ታሪኩ ያስረዳል።
❤ ከፊታ አውታሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ እስከ ንግሥት ዘውዲቱ ፤ ከንቡረ ዕድ አባ ተፈራ መልሴ እስከ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ፓትርያርክ ድረስ ያካተተ በካቴድራሉ የታሪክ መቃን ላይ የተጻፉ ባለታሪኮችን የሚያስታውስ ካቴድራል ነው።
❤ የደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያንን የመጀመሪያውን መቃኞ ያሠሩት ፊት አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ሲሆኑ ጽላቱም በጎንደር ክፍለ ሀገር የነበረና ከዚያ መጥቶም በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የተቀመጠ ነበር።ታድያ ፊት አውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ያሰሩት የመጀመርያው መቃኞ ለአገልግሎት ምቹ ስላልነበር ሁለተኛ መቃኞ ድጋሚ ተሠርቶ ታቦቱ እንዲገባ ተደረገ።
❤ ንግሥት ዘውዲቱ በግንቦት 28 በ 1914 ዓ.ም የቅዱስ አማኑኤልን በዓል ተገኝተው ሲያስቀድሱ ምርጊቱ ተደርምሶ ሲወድቅ በማየታቸው ሦስተኛ መቃኞ እንዲሰራ አዘዙ። የደብሩ አስተዳዳሪም በጊዜው የተክለ ሃይማኖትን ቤተ ክርስትያንም አንድ ላይ ያስተዳድሩ ስለነበር ንግስቲቷ የቤተ መንግስታቸውን አጣኝ የመጀመርያው አስተዳዳሪ ሆነው ደብሩን እንዲጠብቁ አደረጉ። አለቃውም ሦስተኛ መቃኞ አሠርተው ታቦቱ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ገባ።
❤ ሕዝቡ እየበዛ መጣ። አገልግሎቱ መስፋት ኖረበት። ስለዚህም በንግሥት ዘውዲቱ አማካኝነት በ1920 አዲስ ሕንጻ ቤተ መቅደስ ግንባታ ተጀመረ። በ1931 ታህሳስ 28 ቀንም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ታቦቱ ወደ መንበሩ ገብቷል። ንግስት ዘውዲቱ ፍጻሜውን ሳያዩ ያረፉ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ደግሞ ክብ ቅርጽ ነበረው።
❤ አሁን ያለው ቤተ ክርስቲያን በጥር 28 ቀን 1969 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው የተጀመረ ሲሆን የወቅቱ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳዳሪ በነበሩት በሊቀ ሊቃውንት ንቡረ ዕድ አባ ተፈራ መልሴ አስተባባሪነት በምእመናን ርብርብና በቅዱስ አማኑኤል ሁሉን አከናዋኝነት ግንቦት 28 ቀን 1978 ዓ.ም ተጠናቆ ታቦተ ሕጉ ወደ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብቷል። ምንጭ፦ የካቴድራሉ እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት።
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን ጌታችን ይወደው ለነበረ ከሞቱ በኋላ በአራተኛው ቀን ላስነሳው #ለማርያምና_ለማርታ ወንድም #ለጻድቁ_ቅዱስ_አልዓዛር_ለዕረፍት_በዓል መታሰቢያና ለእስክንድርያ ሠላሳኛ ሊቀ ጳጳስ #ለአባ_ዮሐንስ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_አልዓዛር፦ ይህንንም ጻድቅ ሰው በአራተኛ ቀን ከመቃብር ከአስነሣው በኋላ በዚሁ ሳምንት ውስጥ መድኀኒታችን መከራ ተቀብሎ ተሰቅሎ ሞተ። ከትንሣኤውም በኋላ አልዓዛር ከሐዋርያት ጋራ አንድ ሆነ። አጽናኝ መንፈስ ቅዱስም በወረደ ጊዜ ከሐዋርያት ጋራ ጸጋውን ተቀበለ።
❤ ሐዋርያትም በቆጵሮስ አገር ላይ በአንብሮተ እድ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት። መንጋውንም በመልካም አጠባበቅ ጠበቀ። በሹመቱም አርባ ዓመት ኑሮ ግንቦት27 ቀን በሰላም በፍቅር ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጻድቅ አባት በቅዱስ አልዓዛር ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዮሐንስ፦ ይህም አባት በእስክድርያ ለተሾሙ ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳኛ ነው። ደግ የተማረም ነበር። ከልጅነቱም ጀምሮ በገድል ተጠምዶ የሚኖር ነበር። ከዚህም በኋላ በዋሻ ውስጥ ራሱን እሥረኛ አደረገ። የትሩፋቱና የዕውቀቱም ዜና በተሰማ ጊዜ በእስክንድርያ አገር ላይ ይዘው ሊቀ ጵጵስና ሹሙት። ብዙ ድርሳናትንም ደረሰ እግዚአብሔርም በዘመኑ የቤተ ክርስቲያንን ሥልጣን አጸና።
❤ ይህ አባት በተሾመበት ወራት ደግ ምዕመን አንስጣዮስ የሚባል ንጉሥ ነበር። በአንጾኪያም የከበረ አባት አባ ሳዊሮስ ነበር እርሱም ወደ አባ ዮሐንስ ስለ ቀናች ሃይማኖት እንዲህ ብሎ በመልእክቱ ውስጥ ጻፈ "ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተዋህዶው በኋላ እንደ አባቶቻችን እንደ አባ ድሜጥሮስና እንደ አባ ዲዮስቆሮስ እምነት ያለ መቀላቀል፣ ያለ መለዋወጥ፣ ያለ መለያየትና ያለ መጨመር አንዲት ባሕርይ አለችው"። አባ ዮሐንስም መልእክቱን ተቀበለው ኤጲስቆጶሳቱም ሁሉ ተለያይተው የነበሩ። ሕዋሳትም ተመልሰው አንድ ስለ ሆኑ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመሰገኑት።
❤ ከዚህም በኋላ ለመልእክቱ መልስ አባ ዮሐንስ ለአባ ሳዊሮስ እንዲህ ብሎ ጻፈለት "ይኸውም ስለ መለኮትና ትስብእት የአንድ ባሕርይ ህልውና ስለ ወልደ እግዚአብሔር ያለ መለያየት፣ ያለ መቀላቀልና ያለ መለወጥ ሁለት ያይደለ የሰውን ባሕርይ ከመለኮቱ ባሕርይ ጋራ አንድ አድርጎ በመዋሐድ ሰው ስለመሆኑ። ጌታችንንም የሚከፋፍሉትን ወይም ተጨመረበት የሚሉትን ወይም ስለእኛ መከራ ተቀብሎ ተሰቀሎ የሞተው ዕሩቅ ብእሲ ነው የሚሉትን በመለኮት ባሕርይ መከራ ተቀብለ የሚሉትን አወገዘ። "የቀናች ሃይማኖትስ ይቺ ናት እግዚአብሔር ከእኛ በነሣው ሥጋ ስለ እኛ መከራ እንደ ተቀበለ እናውቃለን እኮን። ይቺም የሚጓዝባት የማይሳሳትባትና የማይደናቀፍባት የሕይወት መንገድ ናት" አለ።
❤ አባ ሳዊሮስም ይቺን የአባ ዮሐንስን መልእክት በአነበባት ጊዜ በመልካም አቀባበል ተቀበላት። በአንጾኪያ አገርም ሰበከባት ስለ ቀናች ሃይማኖትም በመካከላቸው ሰላም ፍቅርና ስምምነት ሆነ። ይህም አባት ሕዝቡን እያስተማረ ዐሥራ አንድ ዓመት ኑሮ ከዚህ በኋላ ግንቦት 27 ቀን በሰላም አረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት27 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለአልዓዛር_ኤጲስቆጶስ_ዘተሠይመ። ረቡዐ መዋዕለ ድኅረ በመቃብር ተሐትመ። #ኢየሱስ_ክርስቶሰ ድኅረ አንሥኦቶ ቀደመ። ምስለ ምውታን እስከ ያነሥኦ ዳግመ። በዛቲ ዕለት አዕረፈ ወኖመ"። #ሊቁ_አርከ ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_27።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት። ወመኑ ዘያድኅና ለነፍሱ እምእደ ሲኦል። አይቴ ውእቱ ዘትካት ሣህልከ እግዚኦ"። መዝ 88፥48-49። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 23፥1-27።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኃይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 6፥1-12፣ 1ኛ ጴጥ 2፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አልዓዛር የዕረፍት በዓልና የበዓለ ጰራቅሊጦስ ሰሞንና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት ፳፯ (27) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ በምዕራብ ሐረርጌ በሜኤሶ ወረዳ የሚገኘውን #ታላቁ_ገዳም_ደብረ_ወገግ_ለመሰረቱ_ለአቡነ_ሳሙኤል_ለፍልሰተ_አፅማቸው ዓመታዊ ክብረ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ሳሙኤል_ዘወገግ፡- ጻድቁ አቡነ ሳሙኤል እንድርያስና አርሶንያ ከሚባሉ የበቁ ደጋግ አባትና እናታቸው የተወለዱት በሸዋ ሀገረ ስብከት ቀድሞ ጽላልሽ ዛሬ ቡልጋ በሚባለው አውራጃ ነው፡፡ የወላጆቻቸው በጎ ምግባርና ሃይማኖት ቅዱስ ተክለሃይማኖትን ከደብረ ሊባኖስ አነሣስቶ በቤታቸው ሄደው እንዲስተናገዱ አድርጓል፡፡ ልጅ ስላልነበራቸው ያዝኑ ነበርና አቡነ ተክለሃይማኖትም በጸጋ እግዚአብሔር ተገልጾላቸው "እግዚአብሔር ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ትወልዳላችሁ" ብለው ትንቢት ነግረዋቸዋል፡፡ በትንቢቱም መሠረት አቡነ ሳሙኤል ሐምሌ 10 ቀን 1248 ዓ.ም ሲወለዱ መልካቸው በአራት ልዩ ልዩ ሕብረ መልክ እየተለዋወጠ አንድ ጊዜ እንደ በረዶ፣ አንድ ጊዜ እንደ እሳት፣ አንድ ጊዜ እንደ ልምላሜና ቢጫ ሆነው ታይተዋል፡፡
❤ አቡነ ተክለሃይማኖትም በአባቱ እንድርያስ በኩል የሥጋ ዘመዱ ሲሆኑ የመንፈስ ቅዱስም አባት ሆኑትና በ40 ቀን ክርስትና አንስተው ስመ ክርስትናውን "ሳሙኤል" አሉት፡፡ ትርጓሜውም "እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰማኝ" ማለት ነው፡፡ ከሕፃንነትም ጀምረው በምግባር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳድገው ለዲቁና አብቅተው በኋላም አመንኲሰውታል፡፡
❤ "ደብረ ወገግ" የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ አስቦ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ አስቦን የብርሃን ውጋጋን ሲያጥለቀልቀው መላእክትም "ቦታውን ደብረ ወገግ" (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም "ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት" ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት እንዳረገ ድርሳነ ዑራኤል ላይ በሰፊው ተጽፏል፡፡ በቦታው ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡ በቦታው ላይ ስለተሰወሩት ቅዱሳን በኋላ በዝርዝር እናያለን፡፡
❤ ንጉሥ ዓምደ ጽዮን በክፉዎች ምክር የአባቱን ሚስት እንጀራ እናቱን በማግባቱ ምክንያት አቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው ያወገዙትን የቅዱስ ተክለሃይማኖትን ወገኖች በየአውራጃው በተናቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስንም ደሙ በምድር ላይ እስከሚንጣለል ድረስ ገርፈው ወደነበረበት ቤቱ ወሰዱት፤ ፊሊጶስም በሚሄድበት ቦታ ላይ ሳይደርስ በመንገድ ሞተ፡፡ እንድርያስ፣ አኖሬዎስና ተክለ ጽዮን ሁላቸው ከተከታዮቻቸው ጋር በሰማዕትነት አርፈው እነስድስተይ በምትባል ምድር ተቀበሩ፡፡ ጳጳሱን አቡነ ያዕቆብንም ደሙ በምድር ላይ እንደውኃ እስኪወርድ ድረስ ገርፈው ወደ ሀገሩ እንዲሰደደ አደረጉት፡፡
ከዚያም በኋላ ሃይማኖቱ የቀና ደግ ጻድቅ ንጉሥ ዳዊት በነገሠ ጊዜ አባታችን ሳሙኤል ዘወገግን አገኘውና "መማጸኛ እንዲሆነኝ በእንድርያስ መቃብር ላይ ቤተክርስቲያን ሥራልኝ" ብሎ ለመነውና የሩፋኤልን ቤተ ክርስቲያን ሠራለት፡፡ የእንድርያስንም አጽም ከመቅደሱ ስር አኖረው፡፡ ንጉሡም በዚያ በእንደግብጦን አውራጃ ሁሉ ላይ ፓትርያርክ አድርጎ ሾመው፡፡ በእነስድስታይ አገር ላሉ ሰዎችም ሁሉ አባት ሆናቸውና የመንፈስ ቅዱስ ልጁንም ታዲዮስን መምህርና አባት አድርጎ ሾመላቸውና ጽላልሽ ሄዶ እናቱን ይዞ ጽጋጋ ምድረ ወገግ ወስዶ አመነኰሳት፡፡
❤ አቡነ ሳሙኤል ወደ ምድረ ርስቱ ደብረ ወገግ እየሄደ በዚያ ያሉ ልጆቹን እያጽናና ወደ እንደግብጦን አውራጃም እየተመለሰ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን እያደረገ፣ ወንጌልን እያስተማረ፣ ጣዖት አምላኪዎችን ወደ ክርስትና እየቀየረ፣ አጋንንትንና መመለኪያ ቦታዎቻቸውን እያጠፋ፣ አብያተ ክርስቲያናትን እያነጸ በብዙ ተጋድሎ ኖረ፡፡ በቅዱስ ገድሉ ውስጥ በጣም አስገራሚ በሆነ መልኩ እጅግ ብዙ ታሪኮች ተጠቅሰዋል፡፡ እነዚህም ታሪኮች ውስጥ አቡነ ሳሙኤል በሀገራችን በጣም ብዙ ጣዖታትንና መመለኪያ ቤቶቻቸውን እያጠፉ፣ በሰዎች (በጠንቋዮች) ላይ፣ በዛፍና በባሕር ውስጥ አድሮ ይመለኩ የነበሩ ሰይጣናት አጋንንትን በሚያመልኳቸው ሰዎች ፊት እያጋለጡና እያዋረዱ ሰዎቹን አስተምረው አጥምቀው ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር እየመለሷቸው ቤተክርስቲያንም በመሥራት ሐዋርያትን መሰሉ፡፡ ሰይጣን አድሮባቸው የነበሩ ጠንቋዮች ይጠቀሙባቸው የነበሩ ዕቃዎችን ጻድቁ እየባረኩና እየቀደሱ ለቤተክርስቲያን መሥሪያና መጠቀሚያነት ያውሉት ነበር፡፡ ይህም ገና ሳይወለዱ በአቡነ ተክለሃይማኖት ትንቢት ተነግሮላቸው ነበር፡፡
❤ አቡነ ተክለሃይማኖት "ጣዖታትን የሚሰብር፣ አጋንንትን በጸሎቱ የሚያርቅ፣ ሕዝብን ከኃጢአት በሽታ የሚያድን፣ ፈጣሪውን የሚያስደስት ደግ ልጅ ይሆናል" ብሎው ትንቢት እንደተናገሩላቸው አቡነ ሳሙኤል በሰዎች፣ በባሕርና በዛፍ ላይ እያደሩ ይመለኩ የነበሩ በጣም ብዙ አጋንንትን አጠፏቸው፡፡ ጠንቋዮችንም በውስጣቸው ካደረባቸው ሰይጣን እያላቀቁ የእግዚአብሔር አገልጋይ ያደርጓቸውና ያመነኩሷቸው ነበር፡፡
❤ ጻድቁ አባታችን አባ ሳሙኤል ወንጌልን ዞረው በማስተማር ሐዋርያትን መሰሉ፣ ከዓላውያን ጋር ለመዋጋት ሰውነታቸውን ለሞት በመስጠት ሰማዕታትን መሰሉ፣ በጾም በጸሎት በስግደት በተጋድሎ ቅዱሳን ጻድቃንን መሰሉ፣ ይህን ኃላፊና ጠፊ ዓለም ንቀው በመተው ባሕታውያንን መሰሉ፣ በደልንና ኃጢአትን በማስተሠረይ ካህናትን መሰሉ፣ በጽሕናና በቅድስና መላእክትን መሰሉ እንደዚሁም ሌሎች ብዙ አስደናቂ ተአምራትንም በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ በትእምርተ መስቀል አድርገው እንደሙሴ ባሕርን ለሁለት ከፍለዋል፣ እንደ ኢያሱ በጸሎታቸው ፀሐይን አቁመዋል፡፡ አቡነ ሳሙኤል ተጋድሎአቸውን ፈጽመው ከጌታችን ታላቅ ቃኪዳን ተቀብለው ጥቅምት 29 ቀን በሰላም ዐርፈዋል፡፡ ዛሬ ግንቦት 27 ቀን ከዐረፉበት ዘርዘር ከተባለች ስፍራ የከበረ አጽማቸው ፈልሶ ወደ አሰቦት ደብረ ወገግ ገዳማቸው የፈለሰበት (የመጣበት) ነው።
❤ በገዳማቸው በአሰቦት ደብረ ወገግ የተሰወሩ እጅግ በጣም ብዙ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ አቡነ ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ በቦታው ላይ ከ1934 ጀምሮ እስከ 1972 ዓ.ም ድረስ የተሠወሩት ቅዱሳን በዝርዝር የታወቁም አሉ፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት እነዚያ በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያንኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ከአባታችን አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈ በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
❤ ክብር ይግባውና እግዚአብሔርም ባሕሩን በዚያ ዐውሎ ነፋስ እንደ ቀድሞው መለሰው በየዓመቱም እንዲህ ይሆናል ሁልጊዜ እስከ ዛሬ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ይደርብን ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "#ሰላም_ለቶማስ_እንተ_ደለዎ_ይግሥሦ። ለርጉዝ በግዕ ድኅረ ተንሥአ ደቂሶ። ለአንቅሖ ሙታን ሰብእ ወነፍሰ ድውያን ለፈውሶ። አንሶሰወ ውስተ ኵለሄ ወነገደ መርሶ። አምሳለ ፅፍነት እንዘ ይጸውር ማዕሶ"። #አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_26።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ18፥3-4። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 20፥24-ፍ.ም።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ብፁዕ ብእሲ ዘእምኀቤከ ረድኤቱ እግዚኦ። ወዘይሔሊ በልቡ ዘበላዕሉ። ውስተ ቈላተ ብካይ ብሔር ኀበ ሠራዕኮሙ"። መዝ 83፥5-6። የሚነበቡቱ መልዕክታት ሮሜ 8፥22-31፣ ይሁ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 14፥1-13። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ቅዳሴ ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ቶማስ የዕረፍት በዓል፣ የአቡነ አሞጽ የዕረፍት በዓል፣ የአቡነ ሀብተ ማርያም፣ የአቡነ ኢየሱስ ሞዐ የልደት በዓል፣ የጰራቅሊጦስ በዓል ሰሞንና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን ከዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ለሆነው #ዲዲሞስ ለሚባለው ለከበረ #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ቶማስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት #ለዕረፍቱ_በዓል_መታሰቢያ_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ ከቅዱሳን #አልፋውስና_ከዘካርያስ_ከሉክዮስና_ከቅድስት_አርሶንያም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤና በረከትን ያሳትፈን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ቶማስ፦ እርሱም በሕንደኬ አገር ሉክዮስ ለሚባል ለአንድ መኰንን ራሱን ባሪያ አደረገ መኰንኑም የንጉሥ ወዳጅ ነው ቅዱስ ቶማስንም "የምታውቀው ሙያህ ምንድነው?" አለው። ቅዱስ ቶማስም "እኔ ግንበኛ ነኝ ምኵራቦችን፣ አዳራሾችን እሠራለሁ ደግሞ ጠራቢ ነኝ ሞፈሮችን፣ ወንበሮችንም ሌሎች ዕቃዎችንም እሠራለሁ። ደግሞ ጥበበኛ፣ ባለ መድኃኃነኝ በሽተኛውን ሁሉ አድናለሁ" አለ። መኰንኑም ነገሩን በሰማ ጊዜ ነገሩ እጅግ ደስ አሰኘው "ለንጉሥ ጠቃሚ የሆነ ባሪያ አገኘሁ" አለ።
❤ በዚያን ጊዜ ለቅዱስ ቶማስ ገንዘብ ሰጥቶ ቤተ መንግሥትም እንዲሠራ አዝዞ መኰንኑ ወደ ንጉሥ ሔደ። እርሱ ቅዱስ ቶማስም የመኰንኑን ሚስት የእግዚአብሔርን ሕግ ያስተምራት ጀመር በፊቷም ተአምራት አደረገ። እርሷም በክብር ባለቤት ጌታችን አመነች ከርሷ ጋራም ብዙዎች አመኑ ንጹሕናዋን በመጠበቅ እንትጸና አዘዛት የሃይማኖትም ምሥጢር እንድታስተውል አደረጋት። መኰንኑም ከንጉሥ ዘንድ ሲመለስ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ያደረገውን አየ። ጠራውና "አንተ ክፉ ባሪያ እሠራቸዋለሁ ያልካቸው በጎ ሥራዎች ወዴት ናቸው" አለው። ቅዱስ ቶማስም "አልዋሽሁም ምኵራቦችና አዳራሾች የሠራኋቸው ለሰማያዊ ንጉሥ ማደሪያ የሆኑ እሊህ የሰዎች ነፍሳት ናቸው። የጠረብኳቸው ሞፈሮችም የኃጢአትን እሾህና አሜከላ ከሰዎች ልብ የሚነቅሉና አርሰው የሚያለሰልሱ እነርሱ የወንጌል ትምህርቶች ናቸው፤ ጥበብ ያልሁትም አንድ ነው የሚገድል የኃጢአትን መርዝ አጥፍቶ የሚፈውስ የክብር ባለቤት የሆነ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋና ደም ነው" ብሎ መለሰለት። መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ቅዱስ ቶማስንም በምድር ላይ እንዲአስተኙት በአራት ማዕዘንም ችካል ተክለው እጆቹንና እግሮቹን በገመድ ወጥረው አሥረው ቆዳውን እንዲገፉ ጨውና ኮምጣጤ በተገፈፈው ሥጋው ላይ እንዲደፉበት አዘዘ። መኰንኑም እንዳዘዘ ይሁን ሁሉ አደረጉበት እርሱም ከእግዚአብሔር በተሰጠው ትዕግሥት ይህን ሥቃይ ተቀበለ።
❤ የመኰንኑም ሚስት ቆዳውን ሲገፉት በቤቷ ሰገነት መስኮት በአየችው ጊዜ በድንጋጤ ወድቃ ሞተች መኰንኑም እጅግ አዘነ። የክብር ባለቤት ጌታችንም ቅዱስ ቶማስን አጸናው ወዲያውኑ ተነሣ ከላዩ የገፈፉትንም ቆዳ ወስዶ ከመኰንኑ ሚስት በድን ላይ ጥሎ "አርሶንያ ሆይ የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሺ" አለ። ወዲያውኑ ዐይኗን ተለጠች ፈጥና ተነሥታም ለሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ሰገደችለት ሉክዮስም አይቶ ደነገጠ። ለሐዋርያውም ሰገደለት ይቅርታም ያደርግለት ዘንድ በመለማመጥ ለመነው። ቅዱስ ቶማስም "በጌታችንን ካመንክ ትድናለህ" አለው እርሱም በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። እንዲሁም የአገር ሰዎች ሁሉም አመኑ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው። ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመላቸው። እያስተማራቸውና በቀናች ሃይማኖትም እያጸናቸው ከእርሳቸው ዘንድ ኖረ። ደዌ ያለበትንም በላዩ ቆዳውን ሲያኖርበት ወዲያው ይድናል።
❤ ከዚህ በኋላም ከእነርሱ ዘንድ ወጥቶ ቀንጦርያ ከሚባል አገር ገባ ሲገባም አንድ ሽማግሌ ሰው መራራ ልቅሶ እያለቀሰ አገኘ። ቅዱስ ቶማስም "እንዲህ ለምን ታለቅሳለህ" አለው። ሽማግሌውም "ሰባት ልጆች ነበሩኝ በሐሰት ነገር ንጉሥ ገደለብኝ። ደግሞም ዕዳ አለብኝ ከነእርሱ አንዱ እንኳ ቀርቶ ቢሆን ለኑሮዬ በተራዳኝ ነበር" ብሎ መለሰለት። ቅዱስ ቶማስም ሰምቶ ቆዳውን ሰጠውና "ይህን ወስደህ በልጆችህ መቃብር ላይ አኑር" አለው። እንዳዘዘውም በአደረገ ጊዜ ሰባቱ ሁሉ ልጆቹ ሌሎቹም ስምንት ወንዶች በዚያ አስቀድሞ ተቀብረው የነበሩ በአንድነት ተነሡ። ይቺም ተአምር በአገሮች ሁሉ ተሰማች የጣዖታት ካህናትም ተቆጥተው በደንጊያ ሊወግሩት ጀመሩ። ያን ጊዜ እጆቻቸው ደረቁ "የቸር አምላክ ሐዋርያ ሆይ ከፈጣሪህ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ሌላ አምላክ እንደሌለ አመን። ማረን ይቅርም በለን" እያሉ ጮኹ ያን ጊዜም አዳናቸው የቀናች ሃይማኖትንም አስተምሮአቸው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው። ኤጲስቆጶሳትን፣ ቀሳውስትንና ዲያቆናትንም ሾመላቸው።
❤ ከዚህ በኋላም ወደ አቴና ወደ መቄዶንያ ሔዶ በውስጥዋ በክብር ባለቤት ጌታችን ስም ሰበከ ስለእርሱም ነገሥታቱና መኳንንቱ ሰሙ። ይዘውም አሠሩት የንጉሡም ሚስት ከልጅዋ ጋራ ወደ ወህኒ ቤት እየመጣች የቅዱስ ቶማስን ትምህርቱን ትሰማ ነበር። ብዙዎችም በሥውር እየመጡ ያስተምራቸው ነበር በክብር ባለቤት ጌታችንም አመኑ። ንሡም ስለ ሚስቱ ተቆጣ ነገር ግን በሕዝብ መካከል መግደልን ፈራ። ከከተማውም ውጭ ቅዱስ ሐዋርያ ቶማስን አውጥቶ እስከሚሞትም በጦር እንዲወጉት አራት ወታደሮችን አዘዘ። የንጉሥ ልጅም ቁሞ ይመለከት ነበር። የአገር ሰዎችም በአወቁ ጊዜ ከወታደሮች እጅ ሊያስጥሉት ወጡ ግን ሙቶ አገኙት አንሥተው ገንዘው ከነገሥታት መቃብር በአንዱ አኖሩት።
❤ በንጉሡ ልጅም ሰይጣን ተጭኖበት የሚያንከባልለው ሆነ ከልብሱም ጥቂት ወስደው በንጉሡ ልጅ አንገት ላይ ሊአንጠለጥሉለት ወደ ቅዱስ ቶማስ ሥጋ መጡ መቃብሩንም በከፈቱ ጊዜ አላገኙትም። ጌታችን ከዚያ አፍልሶታልና ከመቃብሩ አፈርም በእምነት ወስደው በንጉሡ ልጅ አንገት ላይ አንጠለጠሉ ያን ጊዜ ዳነ። ንጉሡም የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ።
❤ ከዚህም በኋላ ቅዱስ ሐዋርያ ቶማስም ለብዙዎች ተገለጸላቸው እርሱ ሕያው እንደ ሆነ ጌታችንም በመንግሥቱ ውስጥ እንደተቀበለው ነገራቸው። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የቀናች ሃይማኖት እንዲጸኑ አዘዛቸው። የሐዋርያ ቅዱስ ቶማስም በረከቱ ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
❤ ዳግመኛም ከተአምራቶቹ አንዱን እንጽፋለን። አንድ ጻድቅ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራ በግብጽ አገር ይነግድም ዘንድ ወደ ሕንደኬ ሔደ። ግንቦት ሃያ ስድስትም ሲሆን በሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ በዓል ብዙ ሕዝቦችን የቅዱስ ቶማስ እጅ በውስጡ በምትኖርበት ባሕር ዳር ተሰብስበው አያቸው። በዚያንም ጊዜም የባሕሩን ውኃ ጨርሶ እስከ ሚአስወግደው ድረስ ጥልቅ ነፋስ ተነሣ ሰዎችም ሁሉ በደሴት ወደአለች ቤተ ክርስቲያን ገብተው ሲጸልዩ አደሩ። በማግሥቱም በቅዱስ ቶማስ በዓል ቅዱስ ቊርባንን ለማቀበል ቀደሱ። የሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ እጅ ያለ ጥፋት ሕይወት ያላት ስለሆነች የጌታችንን ሥጋ በላይዋ አደረጉ።
❤ በቅዱስ ሐዋርያ ቶማስ እጅም ቅዱስ ቊርባንን ሊቀበሉ አንዱም አንዱ ከሕዝቡ መጡ። አንድ ሕዝባዊ ሰውም ሊቀበል መጥቶ የቅዱስ ቶማስ መሐል እጁን ጨበጠ። ያን ጊዜ ተሠወረች ሁሉም "ኪርያላይሶን" እያሉ በጠጮህ ብዙ ጊዜ ረጅም ጸሎት ጸለዩ። ከዚህ በኋላም የቅዱስ ቶማስ መሐል እጁ ተገለጠችና ያሰው ቅዱስ ቊርባንን ተቀበለ። ሕዝቡም ሁሉ ተቀበሉ ከዚህም በኋላ ከቤተ ክርስቲያን ወጥተው ወደ ቤታቸው በሰላም ገቡ።
❤ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ መጥተው በሐይቁ ዳር ቆመው ሳለ ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ በእግሩ በውኃው ላይ እየሄደ እያሳያቸው ተከትለውት እንዲሄዱ ነገራቸው። አባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ሐይቁን በእግራቸው ጠቅጥቀው ተራምደው ተሻግረው አቡነ ኢየሱስ ሞዐን አገኟቸው፡፡ እርሳቸውም አቡነ ተክለ ሃይማኖት ወደ እርሳቸው እየመጡ እንደሆነ በመንፈስ ዐውቀው ነበርና ሲያገኟቸው በጣም ተደስተው ከተቀበሏቸው በኋላ አመነኵሰዋቸዋል፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅግ በጣም ብዙ መነኰሳትን አፍርተዋል፡፡ የመጀመሪያው መነኩሴ አባ እንጦንስ ነው፡፡ እንጦንስ መቃርስን፣ መቃርስ ጳኵሚስን፣ ጳኵሚስ ቴዎድሮስን፣ አቡነ አረጋዊንና 8ቱን ቅዱሳን አመነኰሱ፡፡ አቡነ አረጋዊም ወደ ኢትዮጵያ በ460 ዓ.ም መጥተው ክርስቶስ ቤዛን፣ አባ ክርስቶስ ቤዛም መስቀለ ሞዐን፣ መስቀለ ሞዐም አባ ዮሐኒን፣ አባ ዮሐኒም አባ ኢየሱስ ሞዐን፣ አባ ኢየሱም ሞዐም አቡነ ተክለ ሃይማኖትን አመነኰሱ፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ምን ያህል ቀደምትና ባለ ታሪክ አባት እንደሆኑ ከዚህ መረዳት ይቻላል፡፡
❤ በዮዲት ጉዲት እጅጉን ተጐድታ የነበረችው አገራችን ዳግም የወንጌሉ ብርሃን እንዲበራባት ሊቃውንት፣ እንዳይታጡባት፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እንዳይቆነጻጸሉ፣ መነኰሳት አባቶች ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ወርደው ገዳማትን እንዲያስፋፉ ያደረጉት አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለአገራችን ትልቅ ባለውለታ ናቸው፡፡ በተለይም በሐይቅ እስጢፋኖስ ያፈሯቸውን 800 ሊቃውንት መነኰሳት በመላዋ ኢትዮጵያ በመሰማራታቸው ዛሬ የምናያቸውን አብዛኛዎቹን ገዳማትና ቅዱሳት መጻሕፍት አቆይተውልናል፡፡ አባታችን ለ45 ዓመታት ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳምን በአበ ምኔትነት እያስተዳደሩ ከቆዩ በኋላ ኅዳር 26 ቀን 1292 ዓ.ም በዕለተ እሑድ ዐርፈዋል፡፡ ከአባታች ከኢየሱስ ሞዐ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።
❤ መጀመሪያ ስትገባ የጋኔን ምትሐት መስላው ነበርና፤ ሰው መሆኗን ባወቀና በተረዳ ጊዜ ተቆጣት። "አንቺ ዘማዊት ሴት ምንኵስናየን ታፈርሽ ዘንድ ከየት መጣሽ" አላት። "ወይም ደግሞ ሰይጣን በልብሽ ገብቷልን"። "ጌታዬ እኔስ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጅ ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ነኝ እንጅ አንተ እንደምትለኝ ዘማዊት አይደለሁም" አለችው። "ነገር ግን ቤቴን ንብረቴን ያለኝን ትቼ መጥቻለሁ፣ በዓለም ውስጥ ያለውን ሁሉ ንቄ እመንን ዘንድ እወዳለሁና ስለዚህም ወደዚህ ምድር በዳ መጣሁ። በዚህም ገዳም ወይም በረሃ ሰው እንዳለ አላውቅሁም ነበር፤ ሰውን የሚባሉ አራዊት ብቻ የሚኖሩበት ይመስለኝ ነበር" አለችው።
❤ ይህም ባሕታዊ በትሕትና በፈሪሃ እግዚአብሔር ይህን የሚያስደንቅ መልካም መልስ በመለሰችለት ጊዜ። አንድ ሰዓት ያኽል ካሰበ በኋላ "በፍቅር አንድነት ወደ ቤትሽ ተመለሽ" ብሎ በሰላም ተናገራት። እርሷም "ወደዚህ ቦታ ዳግመኛ አልመጣም እንጅ ካንተ ዘንድ ተለይቼ እሄዳለሁ። ነገር ግን ወደ ቤቴ ተመልሼ አልሄድም። ከገዳማት በአንድ ቦታ መንኵሼ መኖር እወዳለሁ እንጅ" አለችው። ጌታ "በወንጌል እርፍን በእጁ ይዞ ወደ ኋላ የሚያርስ የለም" እንዳለ ወደ ዓለም አልመለስም" አለችው።
❤ ያም ባሕታዊ "ምንኵስናስ የለሽም አልታዘዘልሽም፤ ነገር ግን በሰላም ወደ ቤትሽ ወደ ሕጋዊ ባልሽ ተመለሽ። የተፈቀደልሽንስ እነግርሻለሁ ከሕጋዊ ባለቤትሽ ወንድ ልጅን ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ይሆናል። የገድሉና የትሩፋቱ ዜና እስከ ዓለም ዳርቻ ይደርሳል፤ በሕይወተ ሥጋ ሳለ በፈጣሪው በእግዚአብሔር ፈቃድ የብዙዎቹን ሰዎች ነፍሳት ከሲኦል ያወጣል። እንደ መላእክትም ክንፈ ጸጋ ተሰጥቶታል። በሰው አካል በሥጋ ሁኖ ሳለ በተመሥጦ ወደ ሰማይ ወጥቶ የሥላሴን የአንድነትን የሦስትነት ምሥጢር ያያል"።
❤ ቅድስት ዮስቴናም ከአረጋዊ ባሕታዊ ይህን ነገር ሰምታ አደነቀች፤ "የፈጣሪየ ፈቃድ ከሆነ ወደ ቤቴ እመለሳለሁ" አለች፤ ይህን ብላ ተመልሳ ወደ አገሯ ወደ ቤቷ ገባች፤ ቤተሰቦቿም መውጣቷንም መግባቷንም ምንም አላወቁባትም፤ ጥቂት ወራትም ከቆየች በኋላ፤ መልኩ እንደ በረዶ ነጭ እንደ ጽጌ ረዳም ብሩህ ቀይ የሆነ መልከ መልካም ልጅ ወለደች ሁለተናውም ጨረቃ የጉለቱ ምልዓት 15 ሌሊት ሁኖ በብሩህ ብርሃን በምልዓት በሚያድርበት ጊዜ እንደሚያበራው መልካም ብርሃን ገጹ ብሩህ የሆነ ልጅ ወለደች፤ ይህ ሕፃን በግንቦት ወር በ 26 በተወለደ ጊዜ በአባቱ (ፍሬ ብሩክ)ና በእናቱ ቤት ታላቅ ደስታን ሆነ፤ ሜሉን ገቹን አርደው ዘመዶቻቸውን ጎረቤቶቻቸውን አማቾቻቸውን ምርዓቶቻቸውን ጠርተው ለበዓሉ እንደሚገባ መብሉንና መጠጡን ሰጥተው በሚገባ አጠገቡዋቸው፤ ...ካህኑም ተቀብሎ አጠመቀው ከአጠመቀውም በኋላ ለነፍሱ ዋስ (ለክርስትና አባቱ) አሳልፎ ሰጠው ስሙንም ሀብተ ማርያም ብሎ ሰየመው፤..." ከአባታችን ከአቡነ ሀብተ ማርያም ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን። ምንጭ፦ ገድለ አቡነ ሀብተ ማርያም።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ፦ አገራቸው ጎንደር ክፍለ ሀገር ስማዳ ወረዳ ሲና ዳኅና በሚባል ቦታ ነሐሴ 26 ቀን ተፀንሰው ግንቦት 26 ቀን 1210 ዓ.ም ከአባታቸው ከቅዱስ ዘክርስቶስና ከእናታቸው ከቅድስት እግዚእ ክብራ ተወለዱ፡፡ የተወለዱትም በቅዱስ ነአኲቶ ለአብ ዘመነ መንግሥት ነው፡፡
❤ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት የቆብ አባት ሲሆኑ ታላቁን ሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስን ገዳም የቆረቆሩ ደገኛ አባት ናቸው፡፡ ዕድሜያቸው 30 ዓመት እስከሚደርስ ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ትምህርተ ሃይማኖትንና ግብረ ገብን ሲማሩ ከቆዩ በኋላ በ1240 ዓ.ም ይህንን ዓለም በመተው ወደ ደብረ ዳሞ ገዳም ገቡ፡፡ በደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳቱን እየረዱ፣ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያጠኑ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን እየገለበጡ ለሰባት ዓመታት ከቆዩ በኋላ የደብረ ዳሞ 3ኛ አበ ምኔት ከሆኑት ከአባ ዮሐኒ እጅ ምንኲስናን በ1247 ዓ.ም ተቀበሉ፡፡
❤ አንድ ቀን ሌሊት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ወደርሳቸው መጥቶ "የስምህ መክበርያ ወደሆነው ሐይቅ ወደ ተባለው ሥፍራ ሂድ" አላቸው፡፡ አባታችንም "ቦታውን እንዴት ዐውቀዋለሁ?" በማለት መልአኩን ቢጠይቁት "ተነሥ! ጉዞህን ጀምር ቦታውን እኔ አሳይሃለሁ" አላቸው፡፡ አባ ኢየሱስ ሞዐ በመልአኩ እንደታዘዙት ከበዓታቸው ተነሥተው ተከተሉት፡፡ የብዙ ወራት መንገድ የሆነውን ጐዳናም በስድስት ሰዓት አደረሳቸው፡፡ በዚያን ወቅት ከሐይቅ ገዳም በስተ ሰሜን ወደነበረው የቅዱሳን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ደረሱ፡፡ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ከመግባታቸው በፊት ለ 6 ወራት ያህል በቅዱሳን በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን አገልግለዋል፡፡ ያገለግሉበት በነበረው ቤተ ክርስቲያን ቀን ቀን ሕዝቡን ሲያስተምሩ በመዋል ሲመሽ ወደ ሐይቁ በመግባት ሲጸልዩ ያድሩ ነበር፡፡ በሐይቅ እስጢፋኖስና በዙርያው ለነበሩ አበው ማታ ማታ አንድ ብርሃን ወደ ሐይቁ ሲገባ ጠዋት ጠዋትም ሲወጣ ይታያቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ አባታችን በገዳሙ አባቶች ልመናና በልዑል እግዚአብሔር ትዕዛዝ ወደ ሐይቅ ገዳም ገብተው አበምኔት ሆኑ፡፡
❤ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ከደሴ 30 ኪሎ ሜትር ርቆ የሚገኝ ሲሆን የመሠረቱት ካልዕ ሰላማ የተባሉ ግብፃዊ ጻድቅ ናቸው፡፡ ሐይቅን አባ ሰላማ ካልዕና ዐፄ ድል ነአድ በ862 ዓ.ም ነው የቆረቆሩት። ገዳሙን ካቀኑት በኋላ "የማንን ታቦት እናስገባ?" ብለው ሲያስቡ ቶራ የምትባል እንስሳ ጭነት ተጭና ከመካከላቸው ተገኘች፤ ጭነቱን አውርደው ቢያዩት በሐር ጨርቅ የተጠቀለለ የቅዱስ እስጢፋኖስንና የቅዱስ ጊዮርጊስን ሁለት ታቦት አገኙ፡፡ በላዩም ላይ "ይህንን ታቦት በኢየሩሳሌም የሚኖሩ የተሰወሩ ቅዱሳን ከእግዚአብሔር ታዘው የላኩት ነው" የሚል ጽሑፍ አገኙ፡፡ ይህ ከሆነ ከ 400 ዘመን በኋላ ነው አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ወደዚህ ቦታ የመጡት፡፡ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ለ52 ዓመት ቀን ቀን መንፈሳዊ ሥራቸውን እየሠሩ ሌሊት ሌሊት ሐይቁ ውስጥ ቆመው ሲጸልዩ ያድራሉ፡፡
❤ አባ ኢየሱስ ሞዐ በሐይቅ እስጢፋኖስ በአበ ምኔትነት በቆዩባቸው 45 ዓመታት ከየገዳማቱ ቅዱሳን መጻሕፍትን በመገልበጥና በማሰባሰብ የመጀመርያው ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን ቤተ መጻሕፍት በሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም እንዲቋቋም አድርገዋል፡፡ በዚሁ ገዳም ውስጥ የመጀመርያውን የቤተ ክርስቲያን ቋሚ ትምህርት ቤት በማቋቋም 800 መነኰሳትን በትምህርተ ሃይማኖት አሠልጥነው በንቡረ ዕድነት ማዕረግ ሾመው በመላ ሀገራችን እንዲሠማሩ አድርገዋቸዋል፡፡ ከእነዚህም ተማሪዎቻቸው መካከል አቡነ ተክለ ሃይማኖት (ደብረ ሊባኖስ)፣ አቡነ ኂሩተ አምላክ (ጣና ሐይቅ ዳጋ እስጢፋኖስ)፣ አቡነ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቦረና)፣ አባ በጸሎተ ሚካኤል (ቦረና)፣ አቡነ ገብረ እንድርያስ (ቦረና)፣ አቡነ ሕዝቅያስ (ቦረና)፣ አቡነ እስትንፋሰ ክርስቶስ (ዳውንት)፣ አቡነ አሮን (መቄት)፣ አቡነ ተክለ ኢየሱስ ሞዐ (ሐይቅ)፣ አቡነ አላኒቆስ (ትግራይ)፣ አቡነ በግዑ (ሐይቅ)፣ አቡነ ሠረቀ ብርሃን (ሐይቅ)፣ አቡነ ብስጣውሮስ (ሐይቅ)፣ አቡነ ዮሴፍ (ላስታ) ዋና ዋናዎቹና በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ጻደቁን ንጉሥ ዐፄ ይኩኖ አምላክንም በትምህርተ ሃይማኖት አንጸውና ኮትኩተው ያሳደጉት ጻድቁ አባታችን ናቸው፡፡
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት ፳፮ (26) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያውያኑ_ጻድቃን መልአከ ሞትን የማያሳይ ታላቅ ቃልኪዳን ላላቸውና #ታላቁን_ቀብጽያ ገዳምን ለመሠረቱት ለታላቁ #ለአባት_አቡነ_አሞጽ ለዕረፍታቸው፣ ለአባታችን #ለአቡነ_ሀብተ_ማርያምና ታላቁ ገዳም #ሐይቅ_እስጢፋኖስ ላቀኑ #ለአቡነ_ኢየሱስ_ሞዐ #ለልደታቸው_ዓመታዊ_መታሰቢያ_በዓል በሰላም አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_አሞፅ፦ ትውልዳቸው ሸዋ ሲሆን የመነኰሱት ደብረ ሊባኖስ በአቡነ ዮሐንስ ከማ እጅ ነው፡፡ አቡነ ዮሐንስ ከማ በመልአክ ታዘው 10 መነኰሳት 500 ሕዝብ ተከትሏቸው ወደ ትግራይ ሲሄዱ ሳምረ ወረዳ ላይ ሲደርሱ ሕዝቡ ቢራብ ዋርካ ዕለቱን አብቅለው ባርከው መግበውታል፣ ውኃም አፍልቀው አጠጥተውታል፡፡ ከዚኽም በኋላ የበቁትንና ቅዱሳን የሆኑትን ዓሥሩን መነኰሳት ገዳም እንዲገድሙ ወደተለያዩ ቦታዎች ላኳቸው፡፡ ከእነዚኽም ዓሥር ቅዱሳን መነኰሳት መካከል አቡነ አሞፅ አንዱ ናቸው፡፡
❤ አባታችን አባ አሞጽም ቀብፅያ የተባለችውን ቦታ ለመገደም እና በቦታው ለመቀመጥ ዘወትር የማትለያቸውን ጽላት ማርያምን ይዘው ወደ ደላ ከተማ መጡ ነገር ግን ይህ ስፍራ አስቀድሞ ዓለም ሳይፈጠር ጀምሮ የተባረከች እና የስውራን ባሕታውያን ቦታ ስለነበር ስለ ክብሯ ተሰወረቻቸው እርሳቸውም ቦታይቱ እስክትገለጥላቸው ድረስ በደላ ከተማ የምትገኘው በቅድስት ማርያም ደብር ለሦስት ዓመት ሱባኤ ያዙ ነገር ግን ስላልተገለጠላቸው በትግርኛ ቋንቋ "ቀቢጼያ" በማለት ተናግረው ወደ መንፈስ አባታቸው ወደ አቡነ ዮሐንስ ከማ ተመልሰው ሄዱ ቀቢጼያ ማለት አጣኋት ማለት ነው።
❤ ከዚህ በኋላ አቡነ አሞጽ ከመንፈስ አባታቸው ከአቡነ ዮሐንስ ከማ ጋር ተመልሰው ወደ ደላ ከተማ በመምጣት በአንድነት ሱባኤ ገቡ ሱባኤያቸውን በፈጸሙ ሰዓት ከእግዚአብሔር የታዘዘ አንበሳ እየመራቸው ወደ ገዳሙ አደረሳቸው በደረሱም ጊዜ የገዳሙን ስም መጀመሪያ ቦታዋን አጥተው ስላገኝዋት "ቀቢጼያ" ከምትል ቃል ተነስተው "ቀብፅያ" በማለት ሰየሟት የመንፈስ አባታቸውም ቦታውን ባርከው ከሰጧቸው በኋላ ወደ በዓታቸው ተመለሱ ከዚህም በኋላ ፃድቁ አባታችን አባ አሞጽም በቦታው ላይ አንዲት የተፈጥሮ ዋሻ አግኝተው ለአንድ መቶ ዓመታት ተጋድሏቸውን ፈጸሙ።
❤ አቡነ አሞፅ ሰቆቃወ ድንግል የሚባለውን የእመቤታችን መከራ የሚተርከውን ድንቅ ድርሰት ሙሉውን ክፍል በብራና ላይ በሥዕል ገልጸው በክብር አስቀምጠውታል፡፡ ከሰማይ የወረደላቸው የወርቅ መስቀላቸውም በገዳሙ ይገኛል፡፡
❤ በዘንዶዎች የሚጠበቀው ይህ አስደናቂ ገዳም በብዙ መልኩ ከሌሎች ገዳማት የተለየ ነው፡፡ የገዳሙን አፈር ቅዱሳን መላእክት ናቸው ከገነት ያመጡት፡፡ ጌታችን 12 እልፍ መላእክቱ ልኮ ከገነት አፈር አምጥተው በዝናብ አምሳል በቀብጽያ ገዳም ላይ እንዲነሰንሱት አዟቸዋል፡፡
❤ ገዳሙን የተሳለመ ሰው ኢየሩሳሌም ጎልጎታን እንደተሳለመ የሚቆጠርለት ሲሆን በገዳሙ ውስጥ የተቀበረ ሰው ወቀሳ የለበትም፡፡ ከአካሉም ላይ ፀጉሩን ወይም ጥፍሩን ቆርጦ በገዳሙ ክልል ውስጥ የቀበረ ሰው ቢኖር መልአከ ሞትን ፈጽሞ እንደማያይና ገዳሙ የሚገኝበት አካባቢ በእግር ለመጓዝ አስቸጋሪ ቢሆንም ቦታውን የረገጠ እስከ 15 ትውልድ ምሕረትን እንደሚያገኝ ጌታችን በቃልኪዳን አጽንቶታል፡፡ ሌላው ቀብጽያ ገዳምን ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር ፈዋሹ ጠበል ከጻድቁ አቡነ አሞፅ መቃነ መቃብር ሥር የሚፈልቅ መሆኑ ነው፡፡ ከዋሻው ሥር የተንጠባጠበው ጠበል ወደ ጠንካራ ዓለትነት የሚቀየር ሲሆን እርሱን ለእምነት የተጠቀሙበት ሰዎች ከተለያዩ በሽታዎች ተፈውሰዋል፡፡ በቅርቡም ከ6 ዓመት በፊት በዚህ እምነት የተሻሸች አንዲት ሴት ከዘመኑና መድኃኒት ካልተገኘለት ከHIV በሽታና ከመካንነቷ ተፈውሳ ልጅ ወልዳለች፡፡ ይህ አስደናቂ ቀብጽያ ገዳም ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ ቢሆንም ከጊዜና ብዛት ጉዳት ስለደረሰበትና የሚያድሰው አካል ስላላገኘ በአሁኑ ወቅት ሌላ አዲስ ቤተ መቅደስ እየታነጸ ይገኛል፡፡ በቀብጽያ ገዳም ውስጥ 336 ዓመት የሆነው የወይራ ዛፍ የሚገኝ ሲሆን በቅርቡ ስውራን የሆኑ ቅዱሳን ሦስት ጊዜ ደወል ሲደውሉበት ተሰምቷል፡፡
❤ አቡነ አሞፅ በ1592 ግንቦት 26 አርብ ቀን ሲያርፉ ጌታችን ከድንግል እናቱ ጋር ተገልጾላቸው ከላይ ያየናቸውን አስደናቂ ቃልኪዳኖች ከሰጣቸው በኋላ ነፍሳቸውን እመቤታችን አቅፋ አሳረገቻቸው፡፡ ዐፅማቸው ያረፈበትን መካነ መቃብር ታላላቅ ዘንዶዎች ይጠብቁታል፡፡ ጠበላቸውም የፈለቀው ከመቃብራቸው ሥር ነው፡፡ ቦታው በስውራን ስለሚገለገል የከበሮ ድምፅ የሚሰማ ሲሆን የእጣንም ሽታ ይሸታል፡፡ ከአባታች ከአቡነ አሞፅ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከገዳሙ ካሳተመው ስዕል ጀርባ የተገኘ ታሪክ እና ከገድላት አንደበት።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ሀብተ_ማርያም_ልደት፦" የኢትዮጵያ ንጉሥ እስክንድር በነገሠ በሺህ አራት መቶ ሰማንያ ስድስት ዓመተ ምሕረት ቅዱስ ፍሬ ብሩክ የሚባል አንድ ሰው በዚያች ሀገር ውስጥ ነበር፤ ይኸውም ከከበሩም ሰዎች ተለይቶ ብዙ ገንዘብ ያለው ባለ ጸጋ ነበር። በሕጋዊው ጋብቻ ስሟ ቅድስት ዮስቴና የምትባል ሴት አገባ፤ ይኽችውም ሴት በደግ ሥራ ሁሉ የተሸለመች ያጌጠች ነበረች።
❤ ብዙ ደግቷንና ትሩፋቷን ኋላ እንነግራችኋለን፤ ነገር ግን አስቀድመን በዚህ ዓለም ከሕጋዊ ባሏ ጋር በንጽሕ ጋብቻ እግዚአብሔር በመፍራት ምጽዋትን በመስጠት የውሃትንና ትሕትናን ገንዘብ አድርጋ በትግሥት በበጎ ሥነ ምግባር ሁሉ ጸንታ እንደኖረች እነግራችኋለን።
❤ እንዲህ ባለ ሥራ ሳለች መንፈሳዊ ሐሳብ እንዲህ ሲል ተነሳባት፤ "ለአንቺ በዚህ ዓለም መኖር ምን ይረባሻል የሚል መጣባት፤ ዛሬ የሚያልፍ የሚጠፋ ነውና፤ ጌትነቱ የሚመሰገንበት ለዘለዓለም የሚኖር የማያልፍ ሌላ ዓለም ይገለጣልና"፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል "ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ቢነዳ በነፍሱ ከተጎዳ ምን ይጠቅመዋል ምን ይረባዋል" እንዳለ።
❤ "ለአንቺ ግን በሰማይ ጸንቶ መኖርና ሁለተኛዋን ሀገር መያዝ ይሻላል" የሚል ሐሳብ መጣባት፤ ይህን ካሰበች በኋላ ፈጥና ተነሥታ በሌሊት ከቤቷ ወጥታ፤ በሀገሯ አንጻር ትይዩ ወደ ሆነው በረሃ ሄደች፣ በውስጡ ከሰው ወገን የማይኖርበት ቦታ መካከሉ ምድረ በዳ ወደ ሆነው በረሃ ደረሰች። ከጅቦች፣ ከነብሮች፣ ከዓሣሞች፣ ከጦጦችና ከዝንጆሮች በስተቀር ምንም ምን የማይኖርበት በረሃ ነበር።
❤ በዚያችም ቦታ ደጃፏ ያልተዘጋች ትንሽ ዋሻ አገኘች ምንም ምንም ሳትናገር ከዋሻው ውስጥ ገባች። በዋሻው ውስጥ ቁሞ በትጋት መዝሙረ ዳዊትን በአንክሮ በተደሞ የሚደግም ክቡር ባሕታዊን አየች፤ ባየችውም ጊዜ ደነገጠች። እርሱም ሴቲቱን ባያት ጊዜ ፍርሃት መንቀጥቀጥ በላዩ ላይ ወረደበት፣ በመስቀል ምልክትን አማተበ። ይህም ቅዱስ ባሕታዊ ፊቱን በአማተበና ስመ እግዚአብሔርንም በጠራ ጊዜ እንዳልሸሸች ስለአየ ይህች ሴት ክርስቲያን መሆኗን አወቀ።
❤ ሉክያኖስ መኰንንም "ብዙ ገንዘብ ሰጥቼህ ከጭፍሮቹ ሁሉ በላይ እጅግ ከፍ ከፍ አድረግህ ዘንድ ለአማልክት ለአጵሎንና ለአርዳሚስ ለመሠዋት ተዘጋጅ" አለው። ቅዱስም እንዲህ ብሎ መለሰለት "ልብ የሌለህ ደንቆሮ ሆይ እምነቱን በሰው ላይ ላደረገ ሰው ወዮለት ግን እምነቱ በእግዚአብሔር ላይ የሆነ የተመሰገነ ነው የሚል በቅዱሳት መጻሕፍት ተጽፏል። እኔም ለረከሱ አማልክት አልሠዋም አለኝታዬ እግዚአብሔር ስለሆነ ለእርሱ ብቻ እሠዋለሁ"። ያን ጊዜም መኰንኑ ተቆጥቶ እንዲገርፉትና እሾህ ባላቸው በብረት ዘንጎችም እንዲደበድቡት ደሙ እንደ ውኃ እስቲፈስ ድረስ እንዲአሠቃዩት አዘዘ። ጌታችንም በመልአኩ እጅ አጽንቶ አዳነው ጤነኛም ሆነ። ሕዝቡም ይህን ድንቅ ተአምር በአዩ ጊዜ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ዐረፉ። ቊጥራቸውም ሠላሳ ሺህ አምስት መቶ ነው። መኰንኑም መሠቃየቱ በሰለቸው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ።
❤ እንሆ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጸለትና እንዲህ አለው "ብፁዕ ኄሮዳ ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን አትፍራ እኔ ፈጣሪህ ክርስቶስ ነኝ እንሆ መቀመጫህን ከቅዱሳን ጋራ በሰማያት አዘጋጅቼልሃለሁ። በእውነት እነግርሃለሁ በመታሰቢያህ ቀን መከራ ድካምህን አስቦ መሥዋዕት፣ ለሚያቀርብ ለድኃ ምጽዋትን ለሚሰጥ በእንስሶቹ ውስጥ ርባታ ይሆናል። በቤቱም የተባረከ ልጅ አይታጣም። ሰይጣንም በእርሱ ላይ በሥራውም ሁሉ ሊበረታበት አይችልም። የገድልህን መጽሐፍና ስምህን የሚጽፈውንም እኔ በሕይወት መጽሐፍ ስሙን እጽፋለሁ የዕዳ ደብዳቤውን እደመስሳለሁ። ደግሞ በችግር በመከራ ውስጥ ስምህን ጠርቶ የሚለምነኝን ከመከራው ሁሉ እኔ አድነዋለሁ። መታሰቢያህንም ለሚያደርግ ሁሉ በደሉን ሁሉ እተውለታለሁ ሰላሜም ከአንተ ጋራ ይሁን" ይህንንም ብሎ መድኃኒታችን ከእርሱ ዘንድ ዐረገ።
❤ የከበረ አባ ኄሮዳም ፍጹም ደስታን ተደሰተ። ተጋድሎውንም በሚፈጽምበት ጊዜ በዚያ ወደ አሉት ሕዝቡ ተመልሶ "ከውስጣችሁ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ያለ ከሆነ ሥጋዬ በጎ በረከትን እስከሚያደርግለት ድረስ ሥጋዬን ወስዶ በእርሱ ዘንድ ያኑረው" አላቸው። ያን ጊዜም አንገቱን ዘረጋላቸው በሰይፍም ቆረጡት የምስክርነቱ አክሊልንም በግንቦት ወር በሃያ አምስት ቀን ተቀበለ።
❤ ከሦስት ወር በኋላም ዘመዶቹ መጡ ሥጋውንም ወሰዱ ተሸክመውም ወደ አገሩ ስብስጣ አድርሰው በአነፁለት ቦታ አኖሩት ከሥጋውም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ ለድውያን ፈውስ ተገኘ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ኄሮዳ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ #የግንቦት_25_ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለኄሮዳ_እግዚአብሔር_ዘሐወጾ። ከመ የሀቦ ኪዳነ በኢሐስዎ ወዐምፆ። ለዝ መዋዒ ትግርምት መኰንን ኢያደንገፆ። በብልሐ ቅትራት አመ ገቦሁ ደጐፆ። በአእዳወ ኀፂን ካዕበ እንዘ ይጸፍዕ ገጾ። #ሊቀ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የግንቦት_25።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አድኅነኒ እምደም እግዚአብሔር አምላክ መድኃኒትየ። ይትፌሣሕ ልሳንየ በጽድቀ ዚአከ እግዚኦ። ትከሥት ከናፍርየ ወአፉየ ያየድዓ ስብሓቲከ። መዝ 50፥14-15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 9፥20-ፍ.ም።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ዘአቀመ ስምዐ ለዮሴፍ። አመ የሐውር ብሔረ ግብጽ። ወሰምዐ ልሳነ ዘኢየአምር"። መዝ 80፥5። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ጢሞ 2፥8-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 4፥12-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 16፥8-15። የሚነበበው ወንጌል ማር 15፥40-42። የሚቀደሰው ቅዳሴ የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓል፣ የቅድስት ሰሎሞ የዕረፍት በዓልና የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ግንቦት ፳፭ (25) ቀን።
❤ እንኳን #የክብር_ባለቤት_ጌታችን_አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስ_የዮሴፍን_በትሮች በአረንጓዴ ቦታ ላይ ተክሎ ወዲያውኑ #ዛፎች_ላደረገበት ዓመታዊ በዓል (ይህ በዐል #ከእመቤታችን_ከ33_በዐላት አንዱ ነው)፣ #ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም #ለአክስት_ልጅ #ለብፅዕት_ቅድስት_ሰሎሜ ለዕረፍት በዓል መታሰቢያ፣ ስብስጣ ከሚባል ለሆነ በዕረፍቱ ጊዜ ጌታችን ተገልጦ ብዙ ቃል ኪዳንን ለሰጠው #ለአባ_ኄሮዳና #ከእንዴናው_አገር አገር ለሆነ ለከበረ በቀን መቶ እንዲሁ በሌሊትም መቶ ጸሎታትን ይጸልይ ለነበረ #ለቅዱስ_ኮጦሎስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት #ለዕረፍቱ_በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህ ቀን ከሚታሰቡት፦ #ከአባ_ኄሮዳ_ማኅበረ_ሰማዕታት #ከሠላሳ_ሺህ_አምስት_መቶ ሰዎች፣ #ከከበሩ_ቅዱሳን_በላኖስ_ከእሎንትራን_ከራምኔሳ፣ከ#መቶ_ኃምሳ_ሰማዕታት፣ #ከቈስጠንጢኖስና ከእናቱና #ከሔላም ከመታሰብያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #የእመቤታች_የአክስት_ልጅ_ቅድስት_ሰሎሜ፦ እርሷም የማጣት ልጅ የሌዊ ልጅ የሚልኪ ልጅ የካህኑ አሮን ልጅ ናት። ለማጣት ሦስት ሴቶች ልጆች አሉት የታላቂቱ ስማ ቅድስት ማርያም ነው የሁለተኛዪቱ ስም ቅድስት ሶፍያ የሦስተኛዪቱ ስም ቅድስት ሐና ነው ይቺም ቅድስት ማርያም ቅድስት ሰሎሜን ወለደቻት ቅድስት ሶፍያም ቅድስት ኤልሳቤጥን ወለደቻት ቅድስት ሐናም ቅድስት ድንግል ማርያምን ወለጀቻት።
❤ እመቤታችንም ድንግል ስትሆን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወለደችው ጊዜ ይቺ ቅድስት ሰሎሜ የእመቤታችንን አወላለድ እንደ ሴቶች ሁሉ አወላለድ መስሏት ተጠራጠረች ከዚህም በኋላ የድንግል እመቤታችንን ገላዋን ዳሠሠቻት ያን ጊዜ እጇ ተቃጠለ ሕፃኑን በዳሠሠችው ጊዜ ደግሞ ዳነች። በዚህም በኅቱም ድንግልና አምላክን እንደወለደችው አወቀች።
❤ ከተረገመ ኄሮድስ ፊት እመቤታችን በሸሸች ጊዜ ከቅዱስ ዮሴፍ ጋራ በመሆን አብራ በመሰደድ የእመቤታችንን ድካሟን ተካፍላ አገለገለቻት ከስደት እስከ ተመለሱ ድረስ ሕፃኑን ታዝለዋለች የምታጥብበት ጊዜ አለ። መድኃኒታችን ሰው በሆነበት ወራት ሁሉ አልተለየችም በመከራውም ቀን ከእመቤታችን ጋራ ከከበሩ ሁሉ ሴቶች በትምህርቱ ወራት ከተከተሉት ጋራ እያለቀሰች ነበር። በተነሣባት ዕለት ወደ መቃብር ገሥግሣ ከሐዋርያት ቀድማ ያየች ናት።
❤ በኃምሳኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ ከባልንጆሮቿ የከበሩ ሴቶች ጋራ ሰማያዊ ሀብትን ተቀብላ በክብር ባለቤት መድኃኒታችን ስም ሰበከች ብዙዎችንም አሳመነች። ከአይሁድም ብዙ ስድብና ሽሙጥ አገኛት ከዚያም ግንቦት25 ቀን ዐረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ሰሎሜ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከሁላችን ጋራ ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ኮጦሎስ፦ የዚህም ቅዱስ እናትና አባቱ እግዚአብሔር የሚፈሩ ናቸው አባቱም የእንዴናው ገዥ መኰንን ነው ልጅ አልነበረውም ይህን ቅዱስ ልጅ እስከ ሰጠው ድረስ ጌታችንን አዘውትሮ ይለምነው ነበር የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት አስተማረው። ከታናሽነቱ ጀምሮ ንጹሕ ሆነ ለራሱም ሥርዓት በመሥራት በቀን መቶ እንዲሁ በሌሊትም መቶ ጸሎታትን ይጸልያል። ጥቂት በአደገ ጊዜም ወላጆቹ ሊአጋቡት ፈለጉ እርሱ ግን አልፈቀደም። ነገር ግን ከእርሱ በኋላ የተወለደች ሴት ልጅ ነበረቻቸውና እርሷን ከአርያኖስ ጋራ አጋቧት። አባቱም ከሞተ በኋላ ለስደተኞች የእንግዳ መቀበልን ጀመረ።
❤ ከዚህም በኋላ የጥበብ መጽሐፍን ተምሮ ሐኪም ሆነ። በሽተኞቹ ሁሉ ወደ ርሱ ይመጣሉ እርሱም ያለዋጋ ይፈውሳቸዋል። ዲዮቅልጥያኖስም በካደ ጊዜ አርያኖስ ስለ ሹመቱ ከንጉሡ ጋራ ተስማምቶ ሰማዕታትን የሚያሠቃያቸው ሆነ። ይህም ቅዱስ ሰማዕት ለመሆን ይተጋ ነበር ወደ ፍርድ አደባባይም ሒዶ አርያኖስን ንጉሡንም አለቆቹን ሁሉ ረገማቸው ጣዖታቱንም ሰደበ። አርያኖስ ስለ እኅቱ በእርሱ ክፋ ሊአደርግበት አልቻለውም ወደ እኅቱ ላከው እንጂ። እርሷም ከመታሠር አዳነችው።
❤ ከአርያኖስም በኋላ ሌላ መኰንን ተሾመ የዚህ የቅዱስ ኮጦሎስን ዜና ነገሩት። ጭፍራ ልኮ ወደርሱ አስመጣውና በርሱ ላይ በመቆጣት "ለአማልክት ካላጠንክ ይህ ካልሆነ ጽኑ ሥቃይ አሠቃይሃለሁ" አለው። ቅዱሱም "እኔ ለረከሱ አማልክት ዕጣን አላቀርብም ለክብር ባለቤት ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ንጹሕ መሥዋትን አቀርባለሁ እንጂ" ብሎ መለሰለት። በዚያን ጊዜም መኰንኑ ተቆጥቶ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ እንዲአሠቃዩት አዘዘ። የእግዚአብሔር መልአክም ወደ ርሱ መጥቶ ይፈውሰው ያጽናናውና ያረጋጋው ነበር።
❤ ጌታችንም በእጆቹ ታላቅ የሆነ ድንቆች ተአምራትን አደረገ። ማሠቃየቱ በሰለቸው ጊዜ በሰይፍ ራሱን ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። የሰማዕትነትንም አክሊል ግንቦት25 ቀን ተቀበለ ቤተሰቦቹም ገንዘው በመልካም ቦታ አኖሩት። ከሥጋውም እጅግ ብዙ ድንቆች ተአምራት የሚታዩ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ኮጦሎስ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ኄሮዳ፦ ይህም አባት ስብስጣ ከሚባል አገር የሆነ ነው። ከከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በክርስቲያን ወገኖች ላይ የስደት ወራት በሆነ ጊዜ ይህ ቅዱስ አባ ኄሮዳ ከሕፃንነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን ይፈራ ነበር።
❤ በአንዲት ሌሊትም በአልጋው ተኝቶ ሳለ እርሱም ስለ እግዚአብሔር ፈቃድ በማሰብ "በኃላፊው ዓለም ውስጥ መኖር ምን ይጠቅማኛል። በከበረ ወንጌል የተናገረውን የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ቃል ይህን ዓለም ያልካደ ሊያገለግለኝ አይችልም ያለውን ሰምቻለሁና አሁንም ተነሥቼ ሒጄ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ደሜን አፈሳለሁ" አለ። ይህንንም በልቡ ሲያስብ እንሆ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ወደርሱ መጥቶ "የከበርክና የተመሰገንህ ኄሮዳ ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን አትፍራ እግዚአብሔር የክብር ዙፋን አዘጋጅቶልሃልና እኔም የመላእክት አለቃ ሚካኤል ነኝ። እኔም ወደ ፍርድ አደባባይ ከአንተ ጋራ እሔዳለሁ በከበረ ሥጋህም ላይ ምንም የሚበረታብህ የለም" ብሎት ሰላምታም ሰጥቶት ወደ ሰማይ ዐረገ።
❤ ከዚህም በኋላ ብፁዕ አባ ኄሮዳ ወደ ምዕራባዊ አገር ወጣ። ፊቱንም ወደ ምሥራቅ መልሶ እንዲህ ብሎ ጸለየ "ልዩ ሦስት አንድ አምላክ ሆይ ጌትነት በረከት ክብር ገንዘብህ የሆነ ለአንተም ለብቻህ ስግደትና አምልኮት የሚገባህ የተሳልኩትን እስከምፈጽም ታጽናኝ ዘንድ እለምንሃለሁ"። ይህንንም ብሎ ወደ ፍርድ ሸንጎ ሔዶ "እኔ ክርስቲያን ነኝ" ብሎ በግልጥ ጮኸ። መኰንኑም "ክርስቲያንስ ሁነሃል አገርህ ወዴት ነው? አንተ ማነህ? ስምህስ ማነው? ወገንህስ ምንድነው? አለው። የከበረ ኄሮዳም "በብህንሳ አውራጃ ስብስጣ ከሚባል አገር ነኝ። ከልጅነቴ ጀምሮ ለምድራዊ ሟች ለሆነ ንጉሥ ሳገለግል ኖርኩ እንግዲህስ ሕያው ለሆነ ሰማያዊ ንጉሥ አገለግላለሁ" ብሎ መለሰለት።
