𝖊-𝖘𝖆𝖋𝖊
Open in Telegram
This channel is mainly focused on - Programming tutorial - Technology news - Technology tips & - job opportunities our market channel @esafemarket contact @esafeSupport
Show more1 115
Subscribers
No data24 hours
-97 days
-1830 days
Posts Archive
1 115
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለሰው ልጆች አደጋ ደቅኗል - መስክ
የአለማችን ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች በአሜሪካ ምክክር አድርገዋል
የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ወይንም ሰው ሰራሽ አስተውሎት በአለማችን ላይ የደቀነውን አደጋ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ጭምር መግለጽ ጀምረዋል።
የኤክስ ወይንም የቀድሞው ትዊተር ባለቤት ኤለን መስክ ቴክኖሎጂው በገለልተኛ አካል ቁጥጥር እስካልተደረገበት ድረስ የሚደቅነው አደጋ ከባድ መሆኑን መጠራጠር የለብንም ብለዋል።
“ሰው ሰራሽ አስተውሎት ሁሉንም የሰው ልጆች የማጥፋት እድሉ ከዜሮ ከፍ ያለ ነው” በማለትም ከዚህ ቀደም በባለሙያዎች ሲነሱ የቆዩ ስጋቶችን ተጋርተዋል።
የአለማችን ቀዳሚው ቢሊየነር ኤለን መስክ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ላይ ጥብቅ እና ቅድመ ክትትል የሚያደርግ ገለልተኛ ተቋም ሊኖር ይገባል የሚለውን አስተያየታቸውን ለአሜሪካ ሴናተሮች መግለጻቸውንም ኤንቢሲ ዘግቧል።
ኤለን መስክን ጨምሮ የማይክሮሶፍቱ ቢል ጌትስ እንዲሁም የሜታው ማርክ ዙከርበርግ ትናንት በካፒቶል ሂል በተካሄደ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ጉባኤ ተሳትፈዋል።
ለሶስት ሰአታት የተደረገው ምክክር የአለማችን ፈተናም እድልም ሆኗል የተባለው የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ላይ በቀጣይ ምን ይደረግ የሚል ይዘት ያለው ነበር።
ከስብሰባው በኋላ ከጋዜጠኞች ጋር ቆይታ ያደረጉት ኤለን መስክ “ሁሉም የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እንዲያድግ ይፈልጋሉ፤ በቴክኖሎጂው ወደ ኋላ መቅረት የሚያደርሰውን ጉዳትም ያውቁታል፤ ችግሩ ስጋት የሚሆኑ ጉዳዮችን መቀነሱ ላይ ነው” ሲሉ አብራርተዋል።
ቴክኖሎጂው በየትኛውም አለም የሚገኝ የሰው ልጅን አደጋ ላይ ሊጥል መቻሉንም መዘንጋት የለብንም ነው ያሉት።
የአሜሪካ መንግስት የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለመቆጣጠር ያግዛል ያለውን ፖሊሲ ከቴክኖሎጂ ኩባንያዎቹ ጋር መክሮበታል።
ስብሰባውን የመሩት የዴሞክራት ሴናተሩ ቹክ ስቹመር ጉባኤውን “ታሪካዊ” ነው ቢሉትም የቴክኖሎጂ ኩባንያዎቹ ስራ አስፈጻሚዎች የሰው ሰራሽ አስተውሎትን ለመቆጣጠር ምን አይነት እርምጃ ይወሰድ በሚለው ዙሪያ ስምምነት ላይ አለመድረሳቸውን አብራርተዋል።
የኦፕንኤአይ ኩባንያ ባለፈው አመት ያስተዋወቀው ቻትጂፒቲ ለየትኛውም ጥያቄ ምላሽ የመስጠትና የተለያዩ ጽሁፎችንም የማዘጋጀት አገልግሎት ጀምሯል።
ይሁ እንጂ ቴክኖሎጂው የሚሰጣቸው መልሶች ስህተት አላቸው፤ የሌሎችን የፈጠራ ውጤቶች በመቀማት የባለቤቶችን ዋጋ ያሳጣል የሚሉና ሌሎች ትችቶች ሲነሱ ቆይተዋል።
ቴክኖሎጂው በተለይ የቢሮ ስራዎችን እንደሚቀማ የሚያመላክቱ በርካታ ጥናቶች መውጣታቸውም ይታወሳል።
https://t.me/esafeSoftwareSolution
1 115
የዋትስአፕና ፌስቡክ መልዕክቶችን የሚሰርቀው መተግበሪያ
መተግበሪያው የድምጽና ጽሁፍ መልዕክቶችን፣ የስልክ ቁጥርና ሌሎች ሚስጢራዊ መረጃዎችን ይመነትፋል
የአንድሮይድ ስልክ ተጠቃሚዎች የዋትስአፕ እና ፌስቡክ መልዕክቶችን ከሚሰርቀው መተግብሪያ ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተመክሯል።
የሳይበር ጥናት ተቋምይ ሳይፊርማ እንዳስታወቀው አዲሱ የአንድሮይድ ስልኮችን በተለየ እያጠቃ ያለው መተግበሪያ “ሴፍቻት” ይሰኛል።
“ሴፍቻት” እንደ ሌሎች መተግበሪያዎች ሁሉ የተለያዩ መረጃዎችን ለመውሰድ ፈቃዳችን ይጠይቅና ምንተፋውን ይጀምራል።
ይህ መተግበሪያ በአሁኑ ወቅት ከፕሌይ ስቶር ቢወገድም በጫኑት ሰዎች ላይ የጥፋት ተልዕኮውን ቀጥሏል ይላል ሳይፍሪማ።
የዋትስአፕ እና ፌስቡክ መልዕልክት ልውውጣችን፣ የስልክ ቁጥሮች፣ የስልክ ንግግር ቅጂ እና የጽሁፍ መልዕክቶችን እየመነተፈም መተግበሪያውን ለስለላ አላማ ለገዙት ኩባንያዎች ያቀብላል።
“ሴፍቻት” የስልክ እና ኮምፒውተር መለያ ቁጥር (አይፒ አድራሻዎች)፣ የተጫኑ መተግበሪያዎች ዝርዝር፣ የስማርት ስልኩን ሙሉ መረጃ እና ሌሎች ሚስጢራዊ መረጃዎችንም ይሰርቃል ነው የተባለው።
የሳይፍሪማ ተመራማሪዎች ሰዎች መተግበሪያውን እንዲጭኑ የሚያስተዋውቀው እንዴት ነው የሚለውን አልጠቆሙም።
ይሁን እንጂ ምናልባትም ከተለያዩ ሀገራት መንግስታት ጋር በቅርበት ሊሰራ እንደሚችል ግምታቸውን አስቀምጠዋል።
የህንዱ “ባሃሙት” የተባለ የመረጃ መንታፊ ቡድን ኩባንያ ይህን መተግበሪያ መረጃን ከሚመነትፍ ቫይረስ ጋር ለተጠቃሚዎች እንዳቀረበው የሳይፍሪማ መረጃ ያሳያል።
መተግበሪያው ከ2017 ጀምሮም የበርካታ የአንድሮይድ ስልኮች ተጠቃሚዎችን መረጃ ሲመነትፍ መቆየቱን ነው የሚገልጸው።
ባለፈው አመትም የአንድሮይድ ስልኮችን የሚሰልሉ ሀሰተኛ የቪፒኤን መተግበሪያዎችን ይሄው “ባሃሙት” የተባለው የመረጃ መንታፊ ቡድን ማሰራጨቱን ዴይሊ ሜል አስታውሷል።
https://t.me/esafeSoftwareSolution
1 115
አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እንዴት ለሰው ልጆች መጥፋት ምክንያት ሊሆን ይችላል?
June 11, 2023
የተወሰኑ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ቢያንስ ለስድስት ወር ያህል ተጨማሪ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ማሻሻያዎች እንዳይኖሩ ጠይቀዋል
የዓለማችን ቴክኖሎጂ በየጊዜው እየዘመነ መጥቶ የሰው ልጆችን ህይወት በማቅለል ላይ ይገኛል።
ይሁንና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ብዙ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ባንድ ላይ በመያዝ ፍጹም አቅም መፍጠር የቻሉ የአርቲፊሻል ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ይፋ ሆነዋል።
እነዚህ ፈጠራዎች ግን በተለይም የኮምፒውተር ጠበብቶችን ብእጉ እንዳሳሰባቸው ፈጠራው ለራሱ ለሰው ልጆችም አደጋ መሆኑን በመናገር ላይ ናቸው።
ዩሮ ኒውስ የአርቲፊሻል ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች እንዴት ለሰው ልጆች ስጋት ይሆናል ሲል ባለሙያዎችን አነጋግሮ የትንታኔ ይዘቱን አጋርቷል።
የቀድሞው የጎግል ቴክኖሎጂ ባለሙያ የሆኑት ሞ ጋውዳት እንዳሉት ቴክኖሎጀሂው የሰው ልጆችን ህይወት ቀላል በማድረጉ ሰዎች ልጅ እንዳይወልዱ ሊያደርግ ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
እንደ ባለሙያው ገለጻ ከሆነ ወላጆች ለልጆቻቸው ስለ አርቲፊሻል ቴክኖሎጂ ማስተማር የለባቸውም፣ ቴክኖሎጂውን ማስተማር የለባቸውም።
የብዙ ቴክኖሎጂዎች ድምር ውጤት የሆነው አርቲፊሻል ቴክኖሎጂ ሁሉም ነገሮችን በቀላሉ በማቅረብ ሰዎች የበለጠ ነገሮችን ለማወቅ ያላቸውን ፍላጎት የሚቀንስ ነውም ብሏል ባለሙያው፡፡
ቴክኖሎጂው የሰው ልጆችን ያለመፈለግ ስሜት በመጨመር ሰዎች ከመተዛዘን ይልቅ ወደ አሉታዊ አመለካከት እና ድርጊቶች እንዲያመሩ የማድረግ እድል አለውም ተብሏል።
ይህን ተከትሎም ቴክኖሎጂውን በመጠቀም ጅምላ ጨራሽ ወረርሽኞች እና የጦር መሳሪያ እንዲፈበረኩ እንደሚያደርግም ባለሙያው አስጠንቅቀዋል።
የዓለማችን ቀዳሚ ባለጸጋ የሆኑት ኢለን መስክ እና የአፕል መስራቹ ስቲቭ ዋዝኒያክ በይፋ አዲስ የአርቲፊሻል ቴክኖሎጂ ፈጠራዎች ቢያንስ ለስድስት ወራት እንዲታገዱ በፊርማ መጠያቃቸው ይታወሳል።
በአጠቃላይ አርቲፊሻል ቴክኖሎጂ የሰው ልጆችን ስራ በመረከብ፣ አላስፈላጊ ፉክክሮችን በመፍጠር እና የሰው ልጆችን ፈጠራ በመግታት ለሰው ልጆች ስጋት መሆኑን በመናገር ላይ ናቸው።
የቡድን ሰባት ሀገራት ከሁለት ሳምንት በፊት በጃፓኗ ሂሮሽማ ባደረገው ጉባኤ አርቲፊሻል ቴክኖሎጂ የቁጥጥር ስርዓት ሊዘረጋለት እንደሚገባ ከስምምነት ላይ መድረሱ ይታወሳል።
በርካታ የዓለማችን ሀገራትም ቻት ጅፒቲን ጨምሮ በርካታ የአርቲፊሻል ቴክኖሎጂ ሰጠራዎችን በሀገራቸው ጥቅም ላይ እንዳይውል ክልከላ በመጣል ላይ ይገኛሉ።
የተወሰኑ ሀገራት ደግሞ ከራሳቸው ህዝብ ሰነ ልቦና እና ፍላጎት ጋር ተስማሚ የሆኑ የአርቲፊሻል ቴክኖሎጂዎችን በማልማት ላይ ናቸው።
https://t.me/esafeSoftwareSolution
1 115
አገር አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡባቸው እና የምረቃ ቀናት እንዲሁም የሬሜዲያ ፈተና ወጤት አያያዝ ላይ ቅያሪ ተደርጓል።
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ/ም ያስተላለፈውን ሴርኩላር በተመለከተ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከክልል ት/ቢሮ አመራሮች ጋር በድጋሚ ግንቦት 22 ቀን 2015 በበይነ-መረብ ውይይት አድርጓል።
በውይይቱ መሰረትም ፦
- ፈተናዎች የሚሰጡባቸው ቀናት፣
- የተማሪዎች ምረቃ በዓል፣
- የሪሜዲያል ፈተና ውጤት አያያዝ በተመለከተ ቅያሪ መደረጉን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች በፃፈው ደብዳቤ ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ የተላከውን ደብዳቤ #ትክክለኝነት ከሚመለከታቸው አካላት አረጋግጧል።
በዚህም ፦
- በ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ፕሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 30 ከመቶ፣ #በማዕከል የተዘጋጀው ፈተና 70 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደት እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።
- በ2015 ዓ/ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 እስከ 8 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ ውጤት ሐምሌ 10 ቀን የሚገልጽ ይሆናል ተብሏል።
- የተማሪዎችን ምረቃ በተመለከተ ከሐምሌ 11 እስከ ሐምሌ 16 ቀን ባሉት ቀናት ውስጥ ማካሄድ የሚቻል መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር የገለፀ ሲሆን በመርሃ-ግብሩ ላይ የሚሳተፉት የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች #ብቻ ናቸው ብሏል።
- የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 16 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።
https://t.me/esafeSoftwareSolution
1 115
ትምህርት ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ ፈተናዎችን መቼ ለመስጠት እቅድ ይዟል ?
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰውና በትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ፣ ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለሁሉም የክልል ትምህርት ቢሮዎች የተሰራጨ አንድ ደብዳቤ የዚህ ዓመት የሀገር አቀፍ ፈተናዎች ሊሰጡ #የታቀደበትን ጊዜ ያመለክታል።
የደብዳቤውን ትክክለኝነት ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከታቸው የትምህርት ሚኒስቴር አካላት #ማረጋገጥ ችሏል።
በዚህ መሰረት ፦
1ኛ. በ2014 የ12ኛ ክፍል አጠናቀው ፈተና በመውሰድ በልዩ ሁኔታ የሬሜዲያል ኘሮግራም ተጠቃሚ ለሆኑ ተማሪዎች ለአንድ ሴሚስተር የተሰጠው ትምህርት #በማዕከል የጋራ ፈተና ተዘጋጅቶ ለተቋማት እንዲላክ፤ ተቋማት ፊተናውን የማስተዳደር ውጤት የመግለፅና በ2016 ፍሬሽማን ኘሮግራም ለመከታተል ብቁ ሆነው የተገኙት (ማለትም በተቋማት የውስጥ ፈተና 50 ከመቶ፣ በማዕከል የተዘጋጀውን ፈተና 50 ከመቶ) ተደምሮ በድምሩ 50 ከመቶና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡቱን እንዲያሳወቁ፣ ይህ አጠቃላይ ሂደትም እስከ ሰኔ 30 ቀን ድረስ እንዲጠናቀቅ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስመቅጧል።
2ኛ. በ2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡ በግልና በመንግስት ተቋማት የሚገኙ እጩ ምሩቃንና ባለፉት ዓመታት የህግ መውጫ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያላስመዘገቡት ተማሪዎች የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የመፈተኛ ማእከላት ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 3 /2015 እስከ ሐምሌ 13 /2015 ባሉት ቀናት ተሰጥቶ እንዲጠናቀቅ አቅጣጫ ተቀምጧል።
3ኛ. የ2015 የ12ኛ ከፍል ማጠቃለያ ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 30 የሚሰጥ ሆኖ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ከሐምሌ 15 ቀን ጀምሮ ለዚሁ ሥራ ብቻ ዝግጁ እንዲሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አቅጣጫ አስቀምጧል።
በተጨማሪም እንደ አገር ዓመታዊ የትምህርት ካላንደር ከ2016 ጀምሮ ለማስተካከል ሁሉም ተቋማት ፕሮግራሞቻቸውን በዚሁ ማዕቀፍ አንዲያስተካክሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አሳስበዋል።
ከሀገር አቀፍ ፈተናዎች ጋር በተያያዘ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች የሚሰራጩ የተለያዩ #ያልተረጋገጡ መረጃዎችን እየሰሙ አለመረጋጋት ውስጥ መግባታቸውን ሲገልፁልን ነበር ፤ በቀጣይም ትምህርት ሚኒስቴር / የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የሚሰጡትን ትክክለኛ መረጃ #ብቻ እንድትከታተሉ ፤ በቀረው አጭር ጊዜም ዝግጅታችሁን ታጠናክሩ ዘንድ መልዕክት እናስተላልፋለን።
https://t.me/esafeSoftwareSolution
1 115
https://www.ethiorobot.com/
check this site(Chat GPT API) you can get Ethiopian EUEE exams with full explanation
join @esafeSoftwareSolution channel for more
1 115
Repost from N/a
WALRAM M2 SSD
#512GB Hard Drive SSD #M.2 NVMe PCIe 3.0 2280 Internal Hard Disk HDD For Laptop Desktop MSI
price: 4500 birr
contact: @Esafebot or call 0711665699
https://t.me/esafemarket
1 115
Repost from N/a
WALRAM M2 SSD
#512GB Hard Drive SSD #M.2 NVMe PCIe 3.0 2280 Internal Hard Disk HDD For Laptop Desktop MSI
price: 4500 birr
contact: @esafeSupport
https://t.me/esafemarket
1 115
Before buying a new phone or laptop, there are several things you should consider, such as:
1. Purpose: Consider what you will be using the device for. Is it for personal use, work or gaming?
2. Budget: Set a budget and look for devices that fit within it.
3. Operating System: Decide if you prefer Windows, MacOS, iOS or Android.
4. Processor: Look for a device with a fast processor that suits your needs.
5. RAM: Check the device's RAM capacity and make sure it's sufficient for your usage.
6. Storage: Look for a device with sufficient storage capacity for your needs.
7. Display: Consider the display size, resolution and brightness as per your requirements.
8. Battery Life: Check the battery life and estimated usage time to make sure it meets your needs.
9. Connectivity: Consider the connectivity options such as WiFi, Bluetooth, and cellular data.
10. Brand and Support: Look for a reputable brand with good customer support and warranty options.
Taking the time to consider these factors will help you choose the device that best fits your needs and budget.
https://t.me/esafeSoftwareSolution
