Don't get caught by a cheater! Telemetrio finds and tags such channels 👉 If you want to see the tag, subscribe 👈
ዥ ን ጉ ር ጉ ር . . .
Open in Telegram
2 469
Subscribers
+224 hours
+37 days
+2930 days
1 184
Post views
~ 41424 hours
~ 48748 hours
47.95%
Engagement rate
No data
Posts per day
Posts Archive
2 470
እንደ ያኔ ቤትህ መጣሁ ስትይ የጎጆዬን አዋራ ፧ የደጄን ዳዋ እንዳልጠረኩ ፤ ገፍቼሽ ስትቀሪ ጊዜ ሳሎኔን አልፎ ልቤን ድር ወረሰዉ::
ዛሬስ? ሁሉ ይቅር መጣሁ አትይም? ምክንያት ሆኖ ቤቴን ; በሰበብ ሆኖ ልቤን እንዳጸዳዉ…
.
.
@samuel_dereje
2 470
እኔ የማልጨክን ፥ እሷም የማትረጋ ናት። ያን አዉቃለሁ።
"ሁለት ልጅ ቤት አይሰራም" ይላሉ። ቤት ምን አባቱ … ከእሷ ጋር ደጅም አድራለሁ — እላለሁ።
ሙሉ ሌሊት እሷ ኮኮብ ፥ እኔ ስንቴ እንደሳቀች እቆጥራለሁ . . .
.
.
@samuel_dereje
2 470
ልጅ ሆኜ በበጋ ምሽት በረንዳ ላይ ጋቢ ለብሳ ሃሳብ ከያዛት እናቴ ጎን ተሸሽጌ ኮኮብ እቆጥር ነበር። ጣቴን ጠቁሜ … አንድ … ሁለት … ሶስት እያልኩ። መሃል ላይ የቆጠርኩት ፥ ካልቆጠርኩት ሲማታብኝ ዳግም ከአዲስ ‘ጀምራለሁ። ጥቂት ቆጥሬ … ደሞ እንደ አዲስ …
ኮኮቡ አልሰለች … መቁጠርም።
ዛሬ .. ጋቢ አልብሶ ባላቀፈኝ ዉርጫም ክረምት አንቺን ወድጄ .. ራሴን ናፍቆት ስቆጥር አገኘሁት። አይንሽን ነበር … ጉንጭሽን ነበር… ልብሽን ነበር … ፀጉርሽን ነበር .. ከንፈሮችሽን … እረሳና ዳግም አይንሽን …
ነግሬሽ አይደል ኮኮብ አልሰለች — አትሰለቺ።
ብርሃን ፀዳል … የናፈቀኝን ብቆጥር አታልቂ።
.
.
@samuel_dereje
2 470
ባልወቅስህ … ስላልተዉከኝ አይደለም። ዉርጫም ብርድ ብቻዬን ስላልገፋሁ ፥ ቃልህ እንደእርጅና ጥርስ ስላልረገፈ ፥ ከእምባዬ እልህ ስላልገባሁ ወይ ማስመሰሉን ስለቻልኩት ።
ባልወቅስህ … መርሳት ስለቀለለኝ አይደለም። ትዝታህ በስለት ስለተወኝ ፥ በስምህ ስለማልደነግጥ ፥ ልቤ ለናፍቆት ስለደደረ ፥ ባረፍኩበት ስለለመድኩ።።
ባልወቅስህ ስላልጠላሁህ አይደለም ስለማይገባህ እንጂ።
ሳዉቀዉ ነዉ … ሰበብ የለኝም።
ድሮም … ልቤ እንጂ አንተ አልጣልከኝም።
.
.
@samuel_dereje
2 470
ቀኑም ፥ ሰማዩም ጨክኖ ሃምሌ አለ! በበጋ ጸሃይን ፥ በሰኔ ተስፋሽን ሞኩ። አንቺም ቀረሽ ፥ ጸሃይዋን ዳመና በላት ፥ ተስፋሽም ነዶ አለቀ። ናፍቆትሽ ግን አልጎደለም!
ልጠብቅ? . . . ንገሪኝ!
ጉጉቴ ጋቢ ፥ ምኞቴ ቡሉኮ ቢሆነኝ . . .
.
.
@samuel_dereje
2 470
ማወቅና ማድረግ ለየቅል ነዉ!
ብዙ የማዉቀዉ ግን የማላደርገዉ አለ። መወሰን እየከበደኝ። መጨከን እየደከመኝ። መፀፀት እየፈራሁ
. . . እልፍ ጊዜ ደግሞ እየሰነፍኩ!
እንደማትመጪ አዉቃለሁ . . .
ግን አልተዉኩሽም።
እንደማልረሳሽ ታዉቂያለሽ. . .
ግድ አላለሽም።
አዎ . . . ማወቅና ማድረግ ለየቅል ነዉ!
የማዉቀዉን እንደማላደርገዉ ፣
እያረኩት ፥ የማላዉቀዉ ደሞ እልፍ ነዉ።
አንቺን መዉደድ እንደዛ ነዉ…
.
.
@samuel_dereje
2 470
ሳዉቅ መዉደድ ቀላል ነበር – ወይ ነዉ ፣ ወይ አይደለም።
ዛሬ ደርሶ ዉስብስብ ሆነ።
አንዷ ኩሸት ከቧታል።
ከበባት እንጂ ወና ነዉ።
ቆማ ብታስብ ይገባታል - ግን ቆማ ለማሰብም አይገዳትም። ብልህ ናት። ከፍርሃቱጋ ማ ይላተማል።
አንዱ ይቸኩላል …
መዉደድ ፥ መወደድ ይፈራል ከመባል -
ችኩል ነዉ ቁብ የለዉም ፥ አይረጋም መባል ይቀላልና።
ሞኝ ነዉ። በራሱ ጥድፊያ ፥ ራሱን ይጥላል።
አብዛኛዉ … የማይጨበጥ ያሳዳል።
ያልወደደዉን ፥ የሸሸ የሮጠዉን።
የወደደዉ ያንስበታል። ያፈቀራት ይቀልባታል።
በማታቅፈዉ ትከለላለች። በማያገኘዉ ይደበቃል።
ፍሪ ነዉ የሞላዉ ፥
ኩሸቷን ገልፆ ሚወዳት ትመኛለች … ግን የለም።
ችኮላዉን አልፋ የምትታገስ ይመኛል … ግን አያገኝም።
ዛሬ ቀላል አይደለም።
መሃል ቤት ሆኗል
"ነዉ" የለም "አይደለምም”!
.
.
@samuel_dereje
2 470
ስለጥረትህ አለም ግድ የለዉም።
እልፍ ወዳቂ በሞላዉ ሃገር ለሞከረ የሚዜም እሹሩሩ የለም። ተሸናፊ ዜማ አልባ ነዉ። ለወዳቂ ሙሾ እንኳን ዉድ ነዉ።
ያሬድ ቢታወስ በሰባት ዉድቀቱ አይምሰልህ ፤ በተነሳበት ስምንተኛ ነዉ። ሺ ጊዜ ጥሮ ቀና ያላለ እልፍ ያሬድ አለ።
ሞክር …
ካልተነሳህ - ትረሳለህ።
.
.
@samuel_dereje
2 470
ሰባት አመቴ ላይ የሸሸኝ ንጋት ነበር። አለም የነጠቀችኝ ብርሃን። እሷ ግን ግድ አይላትም። ከህፃን ነጥቃ ማንም ቀማኛ አይላትም። እንዳሻት ናት . . . ተቆጪ ፥ ፈራጅ የለባትም።
ስምንት አልኩ ህይወትም እንደማትከሰስ ገባኝ!
-
አስራ አራት የሞላኝ አመት ስለብዙ ነገሮች እጓጓ ነበር። ብዙ ቃል ነበረኝ - ከህይወት። ታደርግልኝ የምጠብቀዉ። "እመነኝ ነገ ይሆናል" ያለችኝ። እኔ አመንኩ "ነገ" ግን አልታመነም። ተስፋዬ ወና ዳከረ ፥ ጉጉቴም አልቆረጠ…
አስር አምስት አልኩ ነገን ማመን ጥላ እንደሆነ አወኩ - የማይጨበጥ!
-
ሃያ ሳልሆን እንደሆንኩት ተዉኝ ባይ ነበርኩ። አለም ግን ከርካሚ ናት። ለሚታየዉ አበጃጀችኝ። ሙሉ ያልኩትን ጎዶሎ ፥ የቆረቆረኝን ልመድ አሉኝ። የመጣ ሁሉ ገማጋሚ ፥ ያየኝ ሁሉ ታዛቢ ሆነ። እንዳምፅ ግዜ አልሰጡኝም - ከትወናዉ አላመዱኝ።
ሃያ አልኩ መድረክ የሆነችን አለም በጭንብሌ ተዋወኩ!
-
እስከ መች ለት … ልወድ አላመነታም ነበር። እስኪገባኝ። ምን ገባኝ… ብዙዉ ሰዉ አጥር ስር የወሸቀዉ ልብ እንዳለ። ማንም ቀዳሚ ተዘራሪ መሆን አንደማይፈልግ። እንቁ ያለዉን የራሱን ልብ እየሸሸገ ፥ አለት ባረገዉ የሌላ ልብ እንደሚሳለቅ።
ገባኝ አልኩ … በጨለመ ዲስኩር ርህራሄዬን ከረከምኩ ፥ ኮረት ልብ አበጀሁ። ደነደንኩ።
… ግን አላመለጥኩም። እድሜ ተዕምረኛ … ተማርኩ ። ልቤ ላይ እንደማላዝ … ህይወቴ ላይም።
በምንቆጥረዉ ስንዝር ሁሉ የቻልን ይመስላል ፥ የገባን። ይመስላል ግን አይደልም…
.
.
@samuel_dereje
2 470
እንጓጓለሁ!
ይሄኛዉ ቢሰምር ፥ ቢቀና ብዬ።
እንፈራለሁ!
ሰምሮ ቢያሳሳኝ ብዬ።
ገር እንዳልሆን ፥ ወና እንዳይተወኝ።
ችኩል ነኝ…
በኩሸት ጥድፊያ ራሴን ጥዬ… "ይኀዉ" ለማለት።
አትከልይኝም?? ከራሴ እንቅፋት?
.
.
@samuel_dereje
2 470
ነግሬሽ ነበር?
ደመና ቀን እንደማልወድ? ካፊያ እንደሚጨንቀኝ ፥ ዝናብ ድብርቴ እንደነበር? ደሞም ተራ ሁነት – ተጠልዬ ፣ ኮት ደርቤ የማሳልፈዉ።
ተደነቅ ሲል
ጥላ ጨብጠሽ ፥ ዝናብ ላይ አጊጠሽ አይቼ
ይኀዉ … ክረምት ናፋቂ ሆኛለሁ።
ቀልብ አይሰንፍ . . .
ሃምሌ መሃል ወለም ላለኝ ልብ
የካቲት ላይ እታሻለሁ!
.
.
@samuel_dereje
2 470
አንዳንድ አሁን አሁን የሚበሉኝ ሃሳቦች
፩
We need to talk about nothing!
Not in a poetic way. Literally nothing.
ስላየሩ ፥ ጠዋት ስለገጠመን ነገር ፥ ማታ ስላየነዉ ህልም ፥ ስላስታወስነዉ የልጅነት ትዝታ ፥ ስለሰለቸን ወይ ሥላሳቀን ጥቃቅን እዉነት …
ከነዚህ በላይ ዉብ ምን አለ? ስለተራ ነገሮች ከማዉራት በላይ የሚሻል ሃሴትስ? ሠዉን ከሃልዮቱ ፥ ከምክንያቱ በላይ በስሜቱ ያዉቁት የለ?
ደሞም ያሰለቻል።
ስለትላልቅ ሸክም ሃሳቦች ወሬ ሊፈጥሩ መታተር። እንደሚያራቅቁት ባዉቅም… ጥልቅ ፥ ዉብ ወዘተ እንደሚያስመስሉት። ሳልጀምረዉ ይታክተኛል። ስለጥበብ ፥ ህመም ፥ ትርጉም ፥ ሃልዮት ወዘተ … ሲያብራሩ። እዉነት ያለዉ እስከማይመስለኝ።
እንዲ ያሉት ሸክም ወጎች አልፎ አልፎ ብቻ ብዙ ካወቁት ሰዉ ጋ ሲያጣቅሱት የሚያምር … የክት ጌጥ ነዉ። የዘወትር ሸማዉ ተራ ፥ ገለባ ይሉት ወግ ነዉ። ቢያንስ ለኔ!
፪
የዉሸት ዉብ ሰዉነት እየገነባን ነዉ - ሁላችን። performative authenticity ይሉት ሰዉ መሆን… መዋሸትን ፥ ማስመሰልን ፥ እንዲወደዱ መሞከርን…. እንደሚጨምር ልንረሳ እየታገልን ይመስላል።
ሌላን ሊመስሉ ከመሞከር በላይ ሰዉ የሚመስል ባህሪ ምን አለ? ሰዉ ሊወደድ የሚጥር ፍጥረት ነው። መልኩን ለተመልካች ፥ ራሱን ለወዳጅ ያስተካክላል። ታዲያ ሰዉ መልኩን እንዲቀበል ሲሰብኩ ( Self Love ወዘተ ብለዉ) ለዚህ ሰዋዊ ባህሪዉ ግን ስለምን አይራሩም?
“ራስን መሆን” ብሎ ተረት የለም። ማንነት ከአራስነት ጀምሮ በተዋስናቸዉ ፥ በወረስናቸዉ ጥቃቅን ልቅምቃሚዎች የተሞላ ነዉ። ሁሉም ዉስጡን ቢያይ የተዉሶ ነዉ።
የኮልኮሌዎች ድምር ነን። ልዩ ነን። በብዙ ነገሮች ደግሞ አንድ አይነት። የምንጠላ የምንወደዉ ፥ የሚያስቅ የሚያሳዝነን ፥ የሚያሳሳ የሚያስናፍቀን ፥ የሚያስቀና የሚያሸሸን ሁሉ ብዙ ሩቅ አይደለም።
በእልፍ ልምምድ ለእኛ የቀረበዉን "እኛነት" መጨበጥ ከቻልን እድለኛ ነን። ብዙዉ ግን ለዛም አልታደለም።
ራስን መሆን ወይ መዉደድ …… ይሉት ነገር ካለ ... ያልሰለከከ አፍንጫችንን ወይ ዞማ ያልሆነ ፀጉራችንን መቀበል አይመስለኝም። ይልቅ ለመወደድ መሻታችንን ፥ ማስመሰ ፥ ዉሸታችንንወዘተ … የጤነኛ እኛነታችን አካል መሆኑን መቀበል ነዉ።
To be human is to be performative!
.
.
.
@samuel_dereje
2 470
Love is a strange phenomenon, maybe the strangest of all. It bends logic, rearranges time, and makes fools out of a steady men.
Midnight, but thinking of doing it again. Hearing a lier called a brain saying ...
She’s one in a million. Not because of what she sees in the mirror (she always gets that part wrong) but because of the impossible feeling she stirs inside me.
unruly, without a name. Something I can’t control, even if I try.
Maybe that’s why I want it again.
Not for the promise of forever. I knew it wouldn’t last. And yet, there’s something in me that keeps reaching for the phone, wanting to hear her voice, again.
Even if it ends the same way it did before.
Even if it breaks me the same way.
Some things are worth losing for!
even for the second time.
@samuel_dereje
Content available for users 18+
By signing in to the service, you confirm that you are 18 years of age or older.
