🗞 የ አቡጁነይድ መልዕክቶች Abujunaid posts
Open in Telegram
ይህ በአቡ ጁነይድ ሳላህ አህመድ የቀረቡ የድምፅና የፅሁፍ መልዕክቶች የሚሰበሰቡበት ቻነል ነው። አላህ ጠቃሚ እውቀትን ከመልካም ስራ ጋር ያግራልን! You can contact me here @salehom100
Show more2 213
Subscribers
-224 hours
-67 days
-3430 days
Posts Archive
⛱ ተጋሾችን አበስራቸው
🎙አቡጁነይድ
ሳላህ አሕመድ
🔗 Telegram Link
https://t.me/abujunaidposts/416
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
Repost from ነሲሓ መጽሔት / Nesiha Magazine
የመውሊድ በዓል በሚዛን ላይ
""""""""""""""""""""""""
ነሲሓ መጽሔት ቅጽ Vol2 ቁጥር 1
ምስጋና ለአለማት ጌታ ለአላህ የተገባ ነው ፡፡ ሰላት እና ሰላም ለዐለማት እዝነት በተላኩት በነቢያችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በሰሃባዎቻቸው እና እነርሱን በመልካም በተከተሉት ሁሉ ላይ እስከ እለተ ቂያማ (ትንሳኤ) ድረስ ይውረድ፡፡
ቁርዓን እና ሐዲስን እንዲሁም ዝርዝር የሸሪዓ ህግጋትን በትክክል መረዳት ለሁሉም ሙስሊም በእጅጉ አስፈላጊ ቢሆንም ቀላል ግን አይደለም።
አላህ ለዚህ ኡማ ታላቅ ውለታ በመዋል ኡለማዎችን ሰጥቶን ያላቸውን ታላቅ ክብር ገልፆልናል፡፡ የሙስሊሞችን እምነት፣ የአምልኮ ‘ዒባዳ’ አተገባበር እና የስነምግባር እሴቶችን ማረም የዑለሞች ተቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ ከሰሀቦችና እነሱን ከተከተሉ ታቢዒዮች መካከል ታላለቅ ዑለማዎች እና የፊቅህ ጠበብቶች ቁርዓንን በተገቢው መልኩ በመረዳት እና ዕድሜያቸውን ሙሉ በማስተማር ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል። ሰሃባዎች ከማንም በበለጠ በዕውቀት የበለፀጉ ከመሆናቸው ባሻገር የመልእክተኛውን ﷺ ንግግር እና ሱና በመተግበር ፋና ወጊዎች እንደነበሩ አያጠያይቅም።
አብደላህ ኢብን መስዑድ አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና በአንድ ወቅት ስለሰሃባዎች እንዲህ ብለው ነበር፤ "ከዚህ ከነቢዩ ዑመት ከማንም በበለጠ፤ ቅን ልቦና፣ የጠለቀ እውቀት፣ የተቃና ፈለግ እና ያማረ ስብዕና ባለቤት ነበሩ። እነሱ ማለት አላህ ለነብዩ ጓደኝነት የመረጣቸው ህዝቦች ናቸው፡፡ ክብራቸውን እወቁላቸው። ፋናቸውንም ተከተሉ። እነሱ ቀጥተኛው መንገድ ላይ ነበሩ።" ኢብኑ ዐብደል በር / ጃሚዑል በያኒል ዒልም በሚባለው ኪታባቸው ቅጽ 2/946-947 ሰሃባዎች በሐቅ ላይ አንድነታቸውን ለመጠበቅ የተለያዩ ሸሪዓዊ አጀንዳዎች ላይ ይመካከሩና ይተራረሙ ነበር፡፡ ያልደረሳቸውን መረጃ ሲያገኙም ወደ ሐቅ ከመመለስ የሚያግዳቸው ነገር አልነበረም። ለሐቅ ተገዢ ስለነበሩ እርምት ለሰጣቸው አካል ምስጋና እና ክብራቸው ከመጨመሩ ባሻገር በመካከላቸው የነበረው ወዳጅነት አልጎዳም። ኢብኑ ተይሚያ እንዲህ ብለዋል "ሰሃባዎች፣ ታቢዒዮች እና ከእነርሱ በኋላ የመጡት ዑለማዎች በመካከላቸው አለመግባባት በተፈጠረ ጊዜ የአላህን ትዕዛዝ ይከተሉ ነበር፡፡ አላህ እንዲህ ብሏል «በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትሆኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው፡፡» ሱረቱ ኒሳዕ : 59 በተለያዩ የዲን አጀንዳዎች ላይ በምክክር መልክ ይወያያሉ፡፡ አልፎ አልፎ የዒልምና እና የተግባር ጉዳዮች ላይ የአቋም ልዩነት ሲኖር መዋደድን፣ መተሳሰርን እና ኢስላማዊ ወንድማማችነትን በጠበቀ ሁኔታ ይተራረማሉ።" መጅሙዑል ፈታዋ 24/172
በየዓመቱ የረቢዐል አወል ወር በገባ ቁጥር የነቢያችንን የልደት በዓል መውሊድን የማክበር ጉዳይ ሰዎችን ሲያወዛግብና መነጋገሪያ ሲሆን ይታያል። አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ሙእሚኖችን በመሰረታዊም ይሁን በቅርንጫፋዊ የዲን ጉዳዮች ላይ አለመግባባት ቢፈጠሩ ጉዳያቸውን ወደ ቁርዓንና ሐዲስ በመመለስ መፍትሄ እንዲፈልጉ በሚከተለው የቁርዓን አንቀጽ አዟል፡፡
فَإِن تَنَازَعْتُمْ فِي شَيْءٍ فَرُدُّوهُ إِلَى اللَّهِ وَالرَّسُولِ إِن كُنتُمْ تُؤْمِنُونَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ ذَٰلِكَ خَيْرٌ وَأَحْسَنُ تَأْوِيلًا ٤:٥٩
«በማንኛውም ነገር ብትከራከሩ በአላህና በመጨረሻው ቀን የምታምኑ ብትኾኑ የተከራከራችሁበትን ነገር ወደ አላህና ወደ መልክተኛው መልሱት፡፡ ይህ የተሻለ መጨረሻውም ያማረ ነው» ሱረቱ ኒሳዕ : 59
ከዚህ ቁርአናዊ መመሪያ በመነሳት ለአንባቢዎቻችን ነሲሓ ይሆን ዘንድ ትክክለኛውን አቋም እናመላክታለን። አላህ ሀቁን አይተው ከሚከተሉት ሰዎች ያድርገን። ይህ በዓል በሸሪዓ መሰረት የሌለውና ሰዎች በዲን ውስጥ የጨመሩት አዲስ ነገር ከመሆኑ ባሻገር አላህና መልእክተኛው ያልደነገጉትን ተግባር በቀን የተገደበ ወደ አላህ መቃረቢያ አምልኮ ማድረግ መሆኑ ዋነኞቹ የመውሊድ ችግሮች ሲሆኑ፤ በተጨማሪም ክርስቲያኖችን በመፎካከር የመጣ መሆኑ ከእነሱ ጋር መመሳሰል ነው። በተጨማሪ በዚህ በዓል ውስጥ በሸሪዓ የተወገዙ በርካታ ተግባራት ይፈፀማሉ። መውሊድ አንድን ስራ ቢድዓ የሚያሰኙ ምክንያቶች ሁሉ እንዳሉበት አያጠራጥርም። ይህም በሚከተሉት ሶስት ነጥቦች ይብራራል፤
1) አዲስ ነገር መፍጠር (ኢሕዳስ)
ካለ ሸሪዓዊ ማስረጃ፤ ማንኛውንም ቀን ወይም ወር ልዩ ሀይማኖታዊ ክንውን የሚፈፀምበት እንደሆነ በማሰብ በዋጂብነት ወይም ሱናነት ሰዎችን የምናበረታታበት ከሆነ በዲን ውስጥ አዲስ ነገር መፍጠር ነውና ሀራም ነው።
አሏህ እንዲህ ብሏል:-
أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ
«ከሀይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነሱ የደነገጉ ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?» ሱረቱ ሹራ ቁጥር 21
ቡኻሪ እና ሙስሊም በዘገቡት የተረጋገጠ ሰሂህ ሐዲስ ነቢያችን ﷺ ብለዋል፤
مَنْ أحْدَثَ في أمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ
«በዲናችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን ነገር የፈጠረ ስራው ተመላሽ ይደረግበታል» ብለዋል።
ይህ ማለት በሸሪዓ ያልተደነገገን ነገር ፈጥሮ ቢፈፅም ተቀባይነት አያገኝም ማለት ነው።
እንደሚታወቀው፤ መውሊድን ረሱል ﷺ የተከበሩት ኸሊፋዎች እና ሌሎችም ሰሀባዎች አላከበሩትም። እንደዚሁ በተከበረው ዘመን ውስጥ የኖሩት ሰሀባዎችን በመልካም ሲከተሉ የነበሩ ታቢዒዮች አልሰሩትም። እነሱ ደግሞ ከማንም በላይ የሱና አዋቂዎችና ለነቢያችን የነበራቸው ውዴታም ከማንም በላይ እንደነበር እሙን ነው። የነብዩን ፈለግ በሚገባ በመከተልም የማይታሙ እንደ ነበሩ ለማንም ግልፅ ነው። ለኛ አርአያ መሆናቸውም ተነግሮናል። ምንም ሳንጨምር መንገዳቸውን አጥብቀን እንድንይዝ የአላህ መልዕክተኛ አደራ ብለውናል፤
عَلَيْكُمْ بِسُنَّتِي وَسُنَّةِ الْخُلَفَاءِ الرَّاشِدِينَ الْمَهْدِيِّينَ، وَعَضُّوا عَلَيْهَا بِالنَّوَاجِذِ، وَإِيَّاكُمْ وَمُحْدَثَاتِ الْأُمُورِ، فَإِنَّ كُلَّ مُحْدَثَةٍ بِدْعَةٌ، وَكُلَّ بِدْعَةٍ ضَلَالَةٌ
«የእኔን እና የቅን ምትኮቼን ሱና አደራ! በጥርሶችችሁ አጥብቃችሁ ያዙ! አዳዲስ ፈጠራዎችን ተጠንቀቁ (ተከልከሉ)፣ በዲን ውስጥ የተጨመረ ፈጠራ ሁሉ ጥመት ነው» ኢማሙ አህመድ ዘግበውታል
መውሊድ በቀደምቶቹ ዘመን እንዳልነበረ እና ኃላ የተፈጠረ (ሙህደስ) ለመሆኑ መውሊድ አክባሪዎች ሁሉ የማይክዱት እውነታ ነው። መውሊድ ማክበርን ለመጀመሪያ ጊዜ የጀመሩት ከአራተኛው
ክ/ዘመን በኋላ እራሳቸውን ፋጢሚዮች ብለው ይጠሩ የነበሩት ኡበይዲዩች ግብፅን በ362 ዓመተ ሂጅራ የወራሩ ጊዜ ነበር።
ቀጣዩን ያንብቡ👇 https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=1336321059824881&id=1003047829818874
የመዲና ጃሚዓ ስኮላርሺፕ ማመልከቻ የምዝገባ ፕላትፎርም ለ45 ቀናት ክፍት ነው። ለየሀገሩ የሚሰጠው ኮታ ውስን ስለሆነ፤ ለመማር ውሳኔ ያላችሁ ብቻ አስፈላጊ መረጃዎችን በማሟላትና በተከታዩ ሊንክ ቋንቋውን ወደ እንግሊዝኛ በመቀየር አመልክቱ።
ባረከላሁ ፊኩም
https://minhatee2.iu.edu.sa
#إعلان عزيزي طالب (المنحة الخارجية):-
يمكنك - وعلى مدى (45) يوما - تقديم طلب قبول للدراسة بـ #الجامعة_الاسلامية من خلال الرابط التالي 🌐
https://minhatee2.iu.edu.sa
لتصفح دليل القبول 📔
https://bit.ly/IUGuide
#قبول_1444
@abujunaidposts
👌 መውሊድን የተመለከቱ ብዥታዎችና መልሶቻቸው
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
⌚️ የ 72 ደቂቃ ሙሀደራ
(64 kbps = 34.65 mb)
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/267
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን?
⌚️ በነሲሓ ቲቪ የቀረበ አጭር ውይይት
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/411
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
መውሊድ ኢስላማዊ በዓል ነውን?
⌚️ የ 10 ደቂቃ ውይይት
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/411
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🗞 እውነተኛ የነብዩ ውዴታ በተግባር ይገለፃል
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/409
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
🗞 እውነተኛ የነብዩ ውዴታ በተግባር ይገለፃል
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/407
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
የሀሰን ታጁ መውሊድ መፅሀፍ ሲፈተሽ
⌚️ የ 10 ደቂቃ መልዕክት
🎙 አቡጁነይድ ሳላህ አሕመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/117
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
ስለ አል ቁበቱል ኸድራዕ እና አረንጓዴ አለባበስ የፃፍኩትን በተመለከተ
በትናንትናው እለት ስለ አል ቁበቱል ኸድራዕ እና #አረንጓዴ አለባበስ በፃፍኩት ዙርያ አንዳንድ ወንድሞች በኮሜንትና በግል በርካታ አስተያየቶች ደርሰውኛል። በቅድሚያ ስለተሳትፏችሁ እያመሰገንኩ፤ ከደረሱኝ መልዕክቶች በመነሳት ተከታዮቹን ስድስት ነጥቦች ለማስፈር እወዳለው።
1) በግዜ ሂደት አረንጓዴው ቁባ ነብዩ ያሰሩትና ያዘዙት የሚመስላቸው ሊኖሩ ይችላሉ። በአንዳንድ ሀገራት የተወሰኑ የሱፊያ ጦሪቃ ተከታይ ነን የሚሉ ፊርቃዎች (የሞቱ ሷሊሆች ቀብር ያሉባቸው) መስጂዳቸውን ቁባ እና ሚናራ አረንጓዴ በመቀባት ከሙስሊሞች መሳጂድ ለመለየት ይሞክራሉ። ስለዚህም ክስተቱን በአንዳንድ ቀብሮች ላይ ለሚገነቡ ቁባዎች መረጃ ሊያደርጉት ሲሞክሩ ይስተዋላል። ከሰሞኑ ደግሞ ምክንያቱ ምን እንደሆነ ባላውቅም በከተማችን የሚገኙ አንዳንድ የአህሉሱና መስጂዶችን አረንጓዴ በመቀባት ለማመሳሰል ሲጥሩ ተመልክቻለው።
በአረንጓዴ ጥምጣም የሚታወቁ አንዳንድ የቢድዓ ሰዎችም የአረንጓዴውን ቁባ በረካ ከጅለው ስለሆነ የቁባውን አመጣጥና ታሪክ ያሰፈርኩት ይህንን ከማረም አኳያ ጠቃሚ በመሆኑ ነው።
2) አንዳንዶች እንደተረዱት ፅሁፌ አረንጓዴ መልበስ አይቻልም የሚል አይደለም። አረንጓዴ መልበስ እንደሚቻልና ሙባህ መሆኑን ገልጫለው። ነገር ግን ሱና ነው ወይም የተወደደ ሙስተሀብ ነው ለማለት የሚያስችል ግልፅ መረጃ ያስፈልጋል ለማለት ነው። ነጭ መልበስ ሱና ነው የምንለው መልዕክተኛው ከመልበሳቸው በተጨማሪ በላጭና የተወደደ መሆኑን ስለነገሩን ነው። አረንጓዴውን መልበስን በተመለከተ ግን ግልፅ መረጃ አለመኖሩም በተከታዮቹ ነጥቦች ይብራራል ኢን ሻ አላህ።
3) ከኢብኑ ማጀህ በስተቀር በአምስቱ የሀዲስ ድርሳናት በተዘገበና ነብዪ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አረንጓዴ መልበሳቸውን በሚጠቁም ሀዲስ አቢ ሪምሳህ የአላህ መልዕክተኛ ሁለት አረንጓዴ ልብሶችን (ሽርጥና ኩታ) ለብሰው እንዳያቸው ተናግሯል።
እንደ አረንጓዴው ሁሉ ጥቁር ኢማማና ቀይ ቀሚስ ሌላም መልበሳቸው በሰሂህ የቡኻሪና ሙስሊም ዘገባዎች ላይ ሰፍሯል። ሆኖም ቀይ ቀሚስ ወይም ጥቁር ኢማማ መልበስ ሱና ነው ብሎ መገንዘብና በቋሚነት መልበስ ስህተት ይሆናል። አለባበሱን የዘገቡልን ሰሀቦችና የዚህ ኡማ አበው ሰለፎችና የቅን ተተኪዎቻቸው በሱናነት አልተረዱትም አልተገበሩትምም። ስለዚህም አንዳንድ የሱፍያ ጦሪቃ ተከታዮች የታወቁበት ይህ ቋሚ አረንጓዴ አለባበስ ቋሚ ነብያዊ ፈለግ አለመሆኑ የማያጠራጥር እውነታ ነው። የቃጥባሬ ኮፍያና እራስን ለመለየት የሚደረጉ መሰል ቡድናዊ አርማዎችም በተመሳሳይ መልኩ ይታያሉ።
4) የመልእክተኛን የአለባበስ ሁኔታ ስንመለከት ልብስ ልማድ (ዓዳ) እንጂ ዒባዳ አይደለምና ከሀር ውጪ የኖሩበት ማህበረሰብ የለበሰውንና የገራላቸውን ይለብሱ ነበር። በአንድ አይነት ልብስ የታጠሩ አልነበሩም። ከሰዎች ለመለየት መጣርን ወይም የሌላቸውን ለመልበስ መጣጣርን አናስተውልም። ስለዚህም፤ መልእክተኛው የለበሱትን አንዱን የልብስ ቀለም መርጦ ሱና ነው በማለት ቋሚ መለያ ማድረግ ትክክለኛ አካሄድ አይሆንም።
5) አላህ የጀነት ሰዎችን አስመልክቶ አንዲህ ይለናል፦
{وَیَلۡبَسُونَ ثِیَابًا خُضۡرࣰا مِّن سُندُسࣲ وَإِسۡتَبۡرَقࣲ} الكهف 31
(ከቀጭን ሐርና ከወፍራም ሐርም አረንጓዴን ልብሶች ይለብሳሉ) አልከሕፍ 31
ይህ ግን አረንጓዴ መልበስን ከሌሎች ቀለሞች በበለጠ የተወደደ ሱና ወይም (ሙስተሀብ) አያደርገውም። የጀነት ሰዎችን አስመልክቶ በቁርአን የተገለፀ ፀጋ ሁሉ በዱንያ ላይ ብንተገብረው ሱና ነው ማለት አይደለም። ለምሳሌ፦ ለጀነት ሰዎች ከተዘጋጁ ፀጋዎች መካከል የሚከጅሉትን የበራሪ አእዋፋት ስጋ መመገብ ተጠቅሷል።
አላህ እንዳለው፤
{وَلَحۡمِ طَیۡرࣲ مِّمَّا یَشۡتَهُونَ }
(ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ ይዞርላቸዋል) አልዋቂዓህ 21
አንድ ሰው ከዚህ በመነሳት የወፍ ስጋ መብላት ሱና ነው ቢለን ስህተት ይሆናል። በቋሚነት ይህንን ብቻ መመገብ ከጀመረ ደግሞ ደግሞ ሌላ ችግር ነው። ፍራፍሬና ሌሎች ፀጋዎችንም በዚሁ መልኩ መመልከት ይቻላል።
6) ነገሩ እንዲህ ከሆነ፤ ከሰሞኑ አንዳንድ ወንድሞቻችን በአረንጓዴ የተጠቀለሉት ለምን ይሆን የሚል ጥያቄ ተፈጥሮብኛል?
ሱና ነው ከሚል መነሻ ከሆነ ሱና አይደለምና ሊታረሙ ይገባል። አንታረምም ካሉ፤ ቢያንስ የቢድዓ ሰዎችን የአለባበስ ፋሽንና አጠማጠም ይራቁ።
ግዜው ለመውሊድ ቅርብ ስለሆነ እኛም የረሱል ወዳጆች ነን ለማለት ከሆነ ውዴታ በዚህ አይገለፅምና አሁንም ያስተውሉ።
አክራሪ ሱፍዮችና አህባሾች ለመመሳሰልና ለማባበል ከሆነ ግን አካሄዱ በአደጅጉ ያስተዛዝባልና ይመለሱ።
አንዳንዶቹ ቀልድ ወዳድ ስለሆኑ #አረንጓዴ አሻራ ነው ይሉን ይሆናል፤ ከዚህ የተባለው ችግኝ መትከል ነውና ግዜ ሳንገድብ የሁል ግዜ ተግባራችን ብናደርገው እላለው።
ወቢላሂ ተውፊቅ
አቡጁነይድ ጳግሜ 4/2014
@abujunaidposts
አረንጓዴ መልበስ እና ቁበተል ኸድራእ
በነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቤት ላይ የተሰራው አረንጓዴ ቁባ በሳቸው ትዕዛዝ የተፈፀመ ሱና አይደለም። የተሰራው በ7ኛው የሒጅራ ክፍለ ዘመን መካከለኛው ምስራቅን ከአንድ መቶ አመት በላይ በመራው የግብፁ (ደውለት አልመማሊክ) መሪ ሱልጣን መንሱር ሰይፈዲን ሲሆን በ 678 ዓ.ሒ ነበር። ከሌላው የመስጂዱ ጣሪያ እንዲለይ በማለት ትንሽ ከፍ ባለ አራት ማእዘን ቅርፅ ጉብታ ነበር የሰራው።
አረንጓዴ ቀለሙን በተመለከተ በቅድሚያ የእንጨት ከለር ቆይቶም ሰማያዊና ነጭ ቀለሞች ነበሩት። በመጨረሻ ግን በቅርቡ ከ 190 አመታት በፊት አካባቢውን ተቆጣጥሮ በነበረው የኡስማኒያ ኢምፓየር ሱልጣን አብዱልሐሚድ ትእዛዝ ታድሶ አረንጓዴ ተቀብቷል።
(ዓሊ ሐፊዝ፤ ፉሱሉን ሚን ታሪኽ አልመዲናህ አልሙነወራህ ገፅ 128)
ብዙሃኑ ዘንድ የፈጠረውን የተበሩክ ብዥታ እና አሉታዊ ተፅእኖዎች በማስተዋል ብዙ ኡለማዎች የሱልጣኑን ተግባር ቢያወግዙትም ፊትናን ከመራቅ አንፃር ባለበት ተትቷል።
ከዚህ በመነሳት አንዳንድ አንጃዎች ዘንድ አረንጓዴ ልብስ መለያ ሆኗል። አንዳንዴ ሱና ነው ሌላ ግዜም የጀነት ሰዎች ልብስ ነው ይላሉ።
ታላቁ የመዲና ሙሐዲስ አብዱልሙህሲን አልዓባድ ስለዚህ ተጠይቀው፤ ሁለቱም የሚጠቅሱት ምክንያት መረጃ የሌለው መሆናቸውንና በትክክለኛ ሀዲስ ተመራጭነቱ የተጠቀሰው ነጭ ልብስ መሆኑን ከገለፁ በኃላ፤ ምንም እንኳ አረንጓዴ ልብስ የተፈቀደ ሙባህ ቢሆንም የቢድዓ ሰዎች መለያ ካደረጉት ግን ብንተወው የተሻለ መሆኑን መክረዋል።
አላህና መልዕክተኛውን የሚወድ ሱናቸውን ሲተገብርና ከመጤ ቢድዓዎች ሊርቅ፤ የኖሩለትን የተውሒድ ጥሪ ሊያስተጋባ ይገባል እንጂ አረንጓዴ በመልበስ መሐባን መግለፅ አይቻልም።
{ قُلۡ إِن كُنتُمۡ تُحِبُّونَ ٱللَّهَ فَٱتَّبِعُونِی یُحۡبِبۡكُمُ ٱللَّهُ وَیَغۡفِرۡ لَكُمۡ ذُنُوبَكُمۡۚ وَٱللَّهُ غَفُورࣱ رَّحِیمࣱ }
"አላህን የምትወዱ እንደኾናችሁ ተከተሉኝ፤ አላህ ይወዳችኋልና፡፡ ኀጢኣቶቻችሁንም ለናንተ ይምራልና፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው" በላቸው።
[Surah Âl-`Imrân: 31]
አላህ ትክክለኛ ግንዛቤን ይወፍቀን
አቡጁነይድ ጳግሜ 3 /2014
@abujunaidposts
🔊 በትዳር ውስጥ የሚከሰቱ ችግሮችና ሸሪአዊ መፍትሄዎቻቸው
🎙አቡ ጁነይድ ሳላሕ አሕመድ
🔗 Share Link
https://t.me/abujunaidposts/188
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
⛱ የመስጂዶች ሚና
🎙አቡጁነይድ
ሳላህ አሕመድ
🔗 Telegram Link
https://t.me/abujunaidposts/397
----------------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
የሺዓና የአህሉሱና የዓሹራ ውሎ
✍ አቡጁነይድ ሳላህ አህመድ
ሙሀረም 12/ 1436 ዓ.ሒ ተፃፈ
የዓሹራ ቀን፤ የፊዓአውንን ትእቢትና አምባገነነንነት ያከተመበትና ለሌሎችም መቀጣጫ የሆነበት፣ ነብዩላህ ሙሳም የተደሰቱበት ለአህሉሱና ታላቅ ትርጉም ያለው የድል ብስራት ቀን ነው። አህሉሱና ይህንን ቀን በአል አያደርጉትም። የተለየ ድግስም ሆነ አለባበስ የላቸውም። ሆኖም መልእክተኛው ﷺ በደነገጉት መሰረት ይፆሙታል፣ መልካም ተግባራትን ይፈፅሙበታል፣ ከአላህ ልዩ ምንዳን በመከጀልም በዒባዳ ያሳልፉታል።
ሺዓዎች ግን ስለ ዓሹራ ቀን ሲያስቡ ሚታወሳቸው የታላቁ ሰሀቢይ የአሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ልጅ ሁሰይን የተገደሉበት ቀን መሆኑ ብቻ ነው። ሺዓዎች በዚህ ቀን ሀዘናቸውን ለመግለፅ እራሳቸውን የሚጎዱ ብዙ ነገሮችን በስፋት ይፈፅማሉ። ጭንቅላትንና ሌሎች አካሎቻቸውን በስለት መብጣትና ማድማት (ተጥቢር)፣ ፊታቸውን መደብደብ (ለጥም፣) እራስን በሰንሰለት መግረፍና ማንገላታት፣ በእንብርክክ መሄድ፣ ብዙዎችም ዘንድ ጥቁር መልበስና የለቅሶ ሙሾ ማውረድ ብሎም በራስ ላይ ኩነኔን መጥራት የተለመዱ የአሹራ ትእይንቶቻቸው ናቸው።
በእጅጉ ይገርማል፤
ለኛ ለአህሉሱና ደስታን ሲያላብሰን፣ ተስፋን አሰንቆ ድልን ሲያበስረን፤ ለወንጀላችን ማርታን ለማግኘት ሩጫ ውስጥ ሲከተን፤
ለሺአዎች ግና፤
የሀዘን የዋይታ፣ የውድቀት የሽንፈት ማስታወሻ፣ የተስፋ ማጨለሚያ ነው!!
ሁሰይን የነብዩ ﷺ የልጅ ልጅ በኢስላማዊ እውቀት ከመጠቁ ታላላቅ ሰሀቦች አንዱ ናቸው። በኢባዳ ብርቱ የተወዳጇ የመልእክተኛው ﷺ ልጅ የፋጢማ ረዲየላሁ አንሀ ልጅ ናቸው። ሆኖም...
ቀሪውን በዚህ ሊንክ ያንብቡ
http://clearfaith.blogspot.com/2015/10/blog-post.html?m=1
------
📮የአቡጁነይድ መልዕክቶች
@abujunaidposts
አሹራ... ታሪክና እርምት 1–4
በአሹራ፣ የቀብር አምልኮና የሁሰይን መገደል ዙርያ በሺዓዎች የሚነሱ ጉዳዮችን ለመዳሰስ ሞክረናል። ሁላችንንም አላህ በሱና ላይ እስከሞት ከሚፀኑት ያደርገን ዘንድ እለምነዋለው።
Part 1 https://youtu.be/WmK_NzcVYdg
Part 2
https://youtu.be/xxSgqdIk5tQ
Part 3
https://youtu.be/2hmD6EfzNzQ
Part 4
https://youtu.be/YAmqFXfp8rU
@nesihatv
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
