ውብ ታሪኮች®
Open in Telegram
“ማወቅ መልካም ነው ያወቁት ማሳወቅ ይበልጥ መልካምነት ነው።” ውብ ታሪኮች 𝐎𝐅𝐅𝐈𝐂𝐈𝐀𝐋 𝐏𝐀𝐆𝐄® ለሃሳብ አስተያየታችሁ👉 @Jemseidbot
Show more1 092
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
April '24
April '240
in 0 channels
March '24
+13
in 0 channels
Get PRO
February '24
+11
in 0 channels
Get PRO
January '24
+7
in 0 channels
Get PRO
December '23
+19
in 0 channels
Get PRO
November '23
+10
in 0 channels
Get PRO
October '23
+21
in 0 channels
Get PRO
September '23
+15
in 0 channels
Get PRO
August '23
+30
in 0 channels
Get PRO
July '23
+29
in 0 channels
Get PRO
June '23
+26
in 0 channels
Get PRO
May '23
+34
in 0 channels
Get PRO
April '23
+27
in 0 channels
Get PRO
March '23
+35
in 0 channels
Get PRO
February '23
+53
in 0 channels
Get PRO
January '23
+40
in 0 channels
Get PRO
December '22
+133
in 0 channels
Get PRO
November '22
+105
in 0 channels
Get PRO
October '22
+36
in 0 channels
Get PRO
September '22
+36
in 0 channels
Get PRO
August '22
+40
in 0 channels
Get PRO
July '22
+56
in 0 channels
Get PRO
June '22
+51
in 0 channels
Get PRO
May '22
+49
in 0 channels
Get PRO
April '22
+34
in 0 channels
Get PRO
March '22
+66
in 0 channels
Get PRO
February '22
+80
in 0 channels
Get PRO
January '22
+219
in 0 channels
Get PRO
December '21
+23
in 0 channels
Get PRO
November '21
+134
in 0 channels
Get PRO
October '21
+106
in 0 channels
Get PRO
September '21
+617
in 0 channels
Get PRO
August '21
+403
in 0 channels
Get PRO
July '21
+606
in 0 channels
Get PRO
June '21
+288
in 0 channels
Get PRO
May '21
+404
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 April | 0 | |||
| 07 April | 0 | |||
| 06 April | 0 | |||
| 05 April | 0 | |||
| 04 April | 0 | |||
| 03 April | 0 | |||
| 02 April | 0 | |||
| 01 April | 0 |
Channel Posts
ዝሙት የሚያሳድዳት ጉብል‼
====================
አንድ ገና ሃያዎቹን ያልደፈነች ጉብል ወደኔ ስልክ መታች። ሠላምታ አቅርባልኝ ስታበቃ ምን እንደማግዛት ስጠይቃት እንባዋ ማቆሚያ አላገኘም። በጣም እየተንዘፈዘፈች አንብታ እስክትረጋጋ ጠበቅኋት። በልቤም ይህችን ወጣት ታግሼ በማዳመጥ ከቻልኩ ችግሯን በመካፈል ምንዳ ከጌታየ ለማግኘች ከጃይ ሆንኩ።
በነገራችን ላይ እንደ ክረምት ዳመና ልውረድ ልውረድ የሚል እንባቸውን ለማራገፍ የሚሹ ሰዎችን መታገስ ችግራቸውን የመቅረፍ አንዱ አካል እንደሆነ የሥነ ልቡና ጠቢባን ይገልጣሉ።እናም እኔም ያደረግኹት ያንን ነው። እርግጥ ነው ጀሊሉ ፊት ተንበርክኮ ማልቀሱ ከሁሉም በላይ አዋጪና ፍቱን ነው።ግና አንዳንድ ችግሮች መውጪያቸው ሲገድ ደግሞ ሰውን(ወንድምን፣ እህትን) ማማከር ግድ ይሆናል።………
ወጣቷ በመጨረሻ ተረጋግታ ሰዓቴን እየፈጀችብኝ በመሆኑ ይቅርታ ጠየቀችኝ። ለዚህ ምንም እንዳይሰማትና ሃጃዋን ለማዳመጥ መዘጋጀቴን ገልጬ አረጋጋኋት። ጉዳዩዋ ባጭሩ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ መሆኗን፣ ከት/ቤት መልስ የቤተሰብን ሱቅ እየጠበቀች ትምህርቷን እንደምታጠና ነገረችኝ። ሂጃቧን አሳምራ እንደምትለብስ፣ በሶላቷ እንደማትደራደር፣ ሱቋ ውስጥ ሆና ከጥናቷ ጎን ለጎን የተወዳጅ ዑስታዞችን ዳዕዋ በስልኳ እያዳመጠች ኢማኗን እንደምትጠብቅ፣ ሌላው ቀርቶ ያን ያክል የሴት ጓደኞች እንኳን እንደሌሏት አወጋችኝ።
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን አንድ የሌላ ዕምነት ተከታይ ወጣት ሱቋ እየመጣ እቃ በመግዛት ሰላም እንደሚላት፣ እዚያው ቆም እያለ በመጫዎት ልቧን እንዳሸፈተው፣ እየቆየ ሲሄድ ለረዥም ጊዜያት በስልክ እንደሚያወሩ፣ ቀስበቀስም የት/ት ሰዓቷን እየሰዋች ከርሱ ጋር ጭልጥ ወዳለ ዝሙት መግባቷን ተናገረች። በዚሁ መሃል በሳግ የታጀበ እንባዋን በኃይል ታወርደዋለች። ከወጣቱ ጋር ዉላ ስትመለስ ታጥባ ሶላቷን ከሰገደች በኋላ ተውበት አድርጋ ሁለተኛ ከርሱ ጋር እንደማትሆን፣ ስልኩን እንደማታነሳ ትወስንና ግና ወጣቱ ሲደውል፣ ወይም በአካል ሲመጣ ያንን ለማድረግ አቅም እንደሚያንሳት አጫወተችኝ። ባጭሩ ልጁን እንዳፈቀረችው አልደበቀችኝም።
በመጨረሻም "ዑስታዝ አሁን እኔን አላህ ይምረኛል? ያውም ከካፊር ወንድ ጋር እንዲህ እየተጨማለቅሁ? እባክህ መላ ካለህ ንገረኝ" ብላ ምርር ወዳለ ለቅሶዋ ተመለሰች።
* * **
ሰፊ ከሆነው ምክሬ በፊት አላህ እርሷን እንደሚምራት ምንም እንዳትጠራጠር አበክሬ አሳወቅኋት። አንቺንማ በደንብ ነውንጂ የሚምርሽ! ምክኒያቱም ይህ እንባሽኮ የተውበት ምልክት፣ ከጌታሽ ጋር ለመታረቅ የምታቀርቢው ቁርባን ነው በማለት አባሸርኳት። አሉ አይደለም እንዴ በሺህ ሳይሆን በመቶ ሺህ ምናልባትም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዝሙትን ሃላል አድርገው የያዙ ሙስሊም እህቶች! ያሉበት ሁኔታ የማያስደነግጣቸው፣ ገንዘብ በማሳደድ፣ ለፋሽን፣ ለተንቀሳቃሽ ስልክ፣ ለመኪና፣ ብሎም መኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ገንዘብ ሳይቀር ከሃብታም ሹገር ዳዲዎች እየቀፈሉ ዘንጠው ወጣ ገባ እያሉ የሚኖሩ። ዘመድ ጎረቤት ውጭ ሃገር ሳይሄዱ፣ ሳይወጡና ሰይወርዱ ይህን ያህል ገንዘብ ከወዴት እንደሚያመጡ ግራ እስኪገባው ድረስ ያነጠጡ፣ የተገማሸሩ!
አንቺ ግና ተግባርሽ ትክክል ያለመሆኑን፣ የጌታሽን ቁጣ እንደሚያመጣብሽ በማወቅሽ ነው ይህን ያህል ማንባትሽ። ባይሆን ከዚህ በኋላ የምር ተውበት አድርጊ፣ ከልጁ ጋር ተቆራረጭ፣ ስልኩን አታንሺ ብቻ ሳይሆን ስልክሽን ላልተወሰኑ ጊዜያት ዝጊ፣ ሱቅ አትግቢ፣ ቤትሽ መጥቶ ካስጠራሽ አትውጪ፣ ት/ቤት ስትሄጂ መንገድ ላይ እንደይረብሽሽ ኢማን ካላቸው የሰፈር እህቶች ጋር ጓደኝነት አብጂ ወዘተ… ……
አንድ የማልደብቃችሁ ጉዳይ ውጤቱ ምን እንደሆነ ለማወቅ መደወል ሲኖርብኝ ሥራ በዝቶብኝ አልደወልኩላትም፣ እርሷ ግን አንድ ቀን ደውላ ሁኔታዎች ጥሩ እየሆኑ እንደሆነ አጫወተችኝ። በዚሁ መሃል አራት ኪሎ ለታክሲ ስጋፋ ስልኬን ጎበዞቹ ሊያስቀምጡልኝ( ኪኪኪኪ) ስለወሰዱት ግንኙነታችን ተቋረጠ።
ይህን ያወጋሁዋችሁ በዚህ አባዜ የተያዛችሁ እህቶች እንድትጠነቀቁ፣ ከአላህ እዝነት ተስፋ እንዳትቆርጡና ዝሙትን አቅልላችሁ እንዳታዩት ነው።ወጣት ሴቶች ሆይ! ወላሂ ዝሙት ከመሥራት ለአንዱ ጠባየ ሸጋ ሙስሊም 3ኛ ወይም 4ኛ ሚስት መሆን በላጭና ለጀነት የሚያበቃችሁ መሆኑን ልብ በሉ። ልጅቷ ልጁ ካፊር መሆኑ ነበር ይበልጥ ያስጨነቃት። ካፊር ሆነ ሙስሊም ያለችበትን ሁኔታ ከዝሙትነት አያወጣውም።
………እናም የጋብቻን መንገድ አቅልሉ፣ ሠርግ፣ ጂኒ እያላችሁ የሚወዳችሁን አታሽሹ። ሃብት ይመጣል ወላሂ። የወላጆቻችሁን ታሪክ አስተውሉ፣ ብዙዎቹ በአንዲት ጠባብ ክፍል ለሃያና ሰላሳ ዓመት ተቀምጠው እናንተን ወይም ታላላቆቻችሁን ወልደው ነው አሁን ለሚገኙበት ማለፊያ ህይወት የበቁት። አደራ ከዝሙት ባቡር እንዳትሳፈሩ፣ አንዴ ከገባችሁበት ማቆሚያ የለውምና። እንዲያው መቅዘፍ፣ መጃጃል፣ ከአላህና ከሰው ዓይን መውደቅ፣ ሲገፋም ሁስነል ኺታም እስከማጣት አደጋ አለው ጓዶች!
© አቡ ቢላል
#ሼር_በማድረግ_ለሌሎች_ያካፍሉ
Join 👇👇👇👇
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch
| 2 | በቲክቶክ ፎሎው አድርጉ👆
አጫጭር ዳዕዋ ምክሮችና አዝካሮች የቁርአን አንቀፆችን ያገኛሉ | 0 |
| 3 | https://www.tiktok.com/@ferid9191?_t=8iopyK4rupq&_r=1 | 0 |
| 4 | No text... | 0 |
| 5 | No text... | 0 |
| 6 | በጊዜ ለመነሳት ደግሞ በጊዜ ተኙ። ዕድሜያችሁን ለዉድ ነገር አታዉሉ። ቲክቶክ ይቅርባችሁ ። ቻትም እንደው ዝምብሎ መድከም እኮ ነው። እኔ ትናንሽ ንግድ አልሠራም እንደሚለው ኩሩ ነጋዴ ከፍ ከፍ ያሉ በጎ ሥራዎችን መርጣችሁ ሥሩ።
ዉዱእ አድርጉና፣ ሱናችሁን ስገዱና፣ ዚክራችሁን አድርጉና ነፍሳችሁን ለፈጠራችሁ ጌታ አስረክቡና፣ የአላህን ጥበቃ እመኑና ጥቅልል ብላችሁ ተኙ። ያኔ ሌሊታችሁ ያምራል ፤ ህልማችሁም ጥሩ ይሆናል። ኢንሻአላህ ።
ቲስበሑ ወዳጆጄ
#ሼር_ማድረግ_እንዳትረሱ
Join 👇👇👇👇
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch | 0 |
| 7 | No text... | 0 |
| 8 | No text... | 0 |
| 9 | No text... | 0 |
| 10 | አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱላህ
#ሼር_ማድረግ_እንዳትረሱ
Join 👇👇👇👇
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch | 0 |
| 11 | ያ ቢንቲ😢💙
አጭር ሰከንድ ልብን የምትነካ መልእክት አዳምጧት
#ሼር_ማድረግ_እንዳትረሱ ✔
@wub_tarikoch | 0 |
| 12 | No text... | 0 |
| 13 | አሰላሙ ዓለይኩም ወራህመቱላህ
እንዴት ከረማችሁ ያጀመዓ? | 0 |
| 14 | አጣሁት የምትለው ልጅም ሆነ ንብረት ባለቤቱ አላህ ነው፤ ቢኖረኝ ብለህ የምትመኘው ሪዝቅ ካዝናው አላህ ዘንድ ነው፤ በድሎህና ጎድቶህ የሄደ ሰው የአላህ ባርያ ነው፣ ተሸክመህ የምትዞረው ሀሳብ ከአላህ ነው፣ ወደፊትህን ብትፈራው በአላህ እጅ ነው፣ መጨረሻህ ቢያሳስብህ አዋቂው አላህ ነው፣ ቢሰጠን የሱ ነው፣ ቢከለክለንም የራሱን ነው፣ ቢያቆየን መብቱ ነው፣ ቢወስደን ንብረቱ ነን።
ያገኘነው፣ ያጣነው፣ የምንመኘው፣ የምንናፍቀው ሁሉ የሱ ነው፡፡ ከሱ ሆነን ወደርሱም ሆነን አላህ ይጎዳናል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው፡፡ ምድር ላይ አስገኝቶን ያለ ልጅ ያለ አጋር ያለ ወገን ብቻችንንም ይተወናል ብሎ ማሰብ ኢማን ማጣት ነው፡፡
ድንግሏ መርየም ወለደች፣ መሃኗ ሳራ ልጅ አገኘች፣ ዘከርያ ማምሻ ዕድሜው ላይ አላህ ብቻዉን አልተተወም፣ ዒሳ አንቀልባ ዉስጥ ሆነው ተናገሩ፣ መቶ ዓመት በላይ የተኙ ወጣቶች ከእንቅልፍ ነቁ፣ አላህም ለነቢ ሙሳ ባህርን ከፈለ፣ እሣት ነቢዩ ኢብራሂምን አላቃጠለችም፣ ነቢ አዩብ በዓመታት በሽታ ወድቀው አልቀሩም፣ ዓሳ ነባሪ ነቢ ዩኑስን ዉጦ አላስቀረም፣ ነቢ ሙሐመድ ከምንም ተነስተው ዓለምን አበሩ፡፡
በአላህ ላይ ሰፋ አድርገህ አስብ፣ በአምላክህ ላይ ትልቅ የቂን ይኑርህ፣ ባመጣህ ጌታ ላይ መጥፎ አትጠርጥር ፣ ዉስጥህን በጥሩ ሀሳቦች ገንባ፣ ኢማንህንም ከፍ አደርግ፣ እሱ ከሻው የማይሆነው የለም፡፡ አልሙ ተስፋ አትቁረጡ፣ ተጓዙ በጠዋት አትድከሙ፡፡
ከምንም ያስገኘን አላህ በችግሮች መሃል ፈጽሞ አይተወንም።
ሰባሐል ኸይር ዉዶቼ!
ጁምዓ ሙባረክ❤
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch | 0 |
| 15 | ከክፍል 9_11 ተለቋል👆 | 0 |
| 16 | ነበር፡፡ ስለሪያዕና ወንጀልን ስላለማስፋፋት የነገረቻቸውን ምን ያህል በተግባር እንዳወዋሉት ለማረጋገጥ ነበር፡፡ ሁሉም ተማሪወች ኸይር ስራና ወንጀላቸውን የከተበበት ማስተታወሻ ሊያሳዩዋት አለመፍቀዳቸውም አስፈነደቃት፡፡
.
.
ይቀጥላል!......
#ሼር_ማድረግ_እንዳትረሱ
#ቻናላችንን_ይቀላቀሉ👇
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch | 0 |
| 17 | የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል አስራ አንድ
(ረያን እና ሪና ሁዳ)
.
.
*ከዓመታት በፊት*
<<ኻሊድ መጥቷል አህሉ!>> ምን ይሉት ንግግር ነው? አህላም በግርምት ላይ ናት፡፡ ኻሊድ እንደሆነ ያሰባሰበላትን፣ ሰርቶ ያገኘላትን፣ ለምኖ የተቀበለላትን ገንዘብ ሁሉ በሰፈር ማቲዎች ነበር የሚልክላት፡፡ ከቁጥብነቱ የተነሳ ችግሮቿን እንኳ በቴክስት ነበር የሚካፈላት፡፡ ይህ ሁሉ ከኻሊድ የሚጠበቅ ነው፡፡ ከመስጂድ አለመጥፋት፣ በኸይር ስራዎች ላይ ሁሉ መሳተፍ፣ ሴቶችን ቀና ብሎ ለማየት አለመድፈር... እኒህ ነበሩ መገለጫዎቹ፡፡ አህላምን ለብቻዋ ሊያናግር ቤቷ ድረሰ መምጣቱ ግን የእርሱ ባህሪ አልነበረም፡፡ አህላምም በጥልቅ መገረም ውስጥ ሰምጣ ጩንጩን አይኖቿን ብትበለጥጣቸው ትክክል ናት፡፡
<<አሰላሙዓለይኪ አህላም ኻሊድ ነኝ፡፡>> አላት ልክ እንዳያት፡፡
<<ወዓለይከሰላም ኻሊድ! እንዴት ነህ? ምን እግር ጣለህ?>> አለችው፡፡
<<ልጠይቅሽ ነዋ! አሁን እናትሽ እንዴት ናቸው?>> አለ ከአንገቱ እንደተሰበረ፡፡
<<አልሀምዱሊላህ እየተሻላት ነው፡፡>>
<<መታከሚያው ገንዘብ ተሟላልሽ እንዴ?>> በጨረፍታ ተመልክቷት ድጋሚ አቀረቀረ፤ ስሜቷን ሊያነብ፡፡
<<አንተ የምትልክልኝ እኮ ይበቃ ነበር፡፡ እሱን ላጠራቅም ሳስብ ግን ለቤት የሚሆን ወጭ ያስፈልገኛል፡፡ ምን እንደማደርግ ጨንቆኛል፡፡ ወይ ትምህርቱን አቋርጠዋለሁ፡፡>>
<<ያምሻል እንዴ አህሉ... አህላም! በቃ የእስካሁኑን ገንዘብ ለወጭሽ ተጠቀሚ ለእናትሽ የሚሆን ገንዘብ እኔ አመጣለሁ፡፡ እነ ኢልያስ ቃል ገብተውልኛል!>>
<<የሚያምህማ አንተን ነው>> ድምጿን ከኻሊድ ይበልጥ ከፍ ለማድረግ ሞከረች፡፡ <<የእነኢልያስ እጅ ለእንደዚህ አይነት ነገር መች ይፈታና!>>
<<እርሱን በእኔ ጣዪው አህላም>> አለ ኻሊድ ረስቶት የነበረውን አንገት መስበር አስታውሶ እየተጎነበሰ፡፡
<<እሺ... በምትኩ ግን ምን ጠየቁህ!>>
<<ጓደኛቸው እንድሆን ብቻ! እነንዳስጠናቸው ወይም ፈተና እንደዳሰራቸው ይፈልጋሉ፡፡>>
<<ምን ማለት ነው ብቻ? እያወቅካቸዎው፡፡ ይጠጣሉ፣ ይቀቅማሉ፣ ያጨሳሉ፡፡ ማምሺያና ማደሪያዎቻቸው መጠጥ ቤቶች ናቸው፡፡ እነሱ ጋር ጓደኛ መሆን ጓደኛ መሆን ብቻ ነው?>>
<< አብሽሪ አህሉ... አህላም! ራሴን ምን ያህል ጠንካራ እንደሆንኩ አውቃለሁ!>>
*አሁን*
<<ያኔ ነው ሁሉም ነገር የጀመረው፡፡>> አለች አህላም የፊዳን አይኖች እያጤነች <<ጥቀቂት ቆይቶ ከጓደኞቹ የባሰ አጫሽ፣ ጠጪ፣ ሴት አውል ሆኖ አረፈው፡፡ እነርሱ እውቀቱን ተጠቅመው እዚሁ ዩኒቨርሲቲ ገብተውልሽ ነበር፡፡ ሁሉም ተጫሩ እንጅ፡፡ እኔ ደግሞ በእርሱ መበላሸት ተረማምጄ እናቴንም አሳከምኩ፤ እንደተመኘሁት የሜዲሲን ተማሪ ሆንኩ፡፡ እና እዳ የለብኝም?>> ከቀኝ አይኗ የወረደችውን የእምባ ዘለላ ከቁብ ሳትቆጥር ፊዳ ላይ አጉረጠረጠች፡፡ ፊዳ የማጽናኛ ቃላት ሁሉ ተሰለቡባት፡፡
*
የኢምራን ቢሮ ውስጥ ጎንለጎን የተሰለፉት ህጻናት ተደርድረዋል፡፡ ሴቷ ያለወትሮዋ እርሳስማ ጅልባብ በእርሳስማ ሂጃብ ነው ያደረገችው፡፡ ባለመነጽሩ ታዳጊና ከጎኑ የቆመው ሌላ ታዳጊም ልክ እንደልጅቱ ኢምራን ላይ አፍጥጠዋል፡፡
<<ስራሽን ጨረስሽ?>> አለ ኢምራን ወደልጅቱ እየተመለከተ፡፡
<<በሚገባ!>> አለች ሀያት ዳጎስ ያለ ጥራዝ ጠረጴዛው ላይ እያስቀመጠች፡፡
ኢምራን ከጥራዙ አጋማሽ ቦታ ላይ ገልጦ ማንበብ ጀመረ
<<ኢስላምና አለባበስ:
ሴት ልጅ ሂጃብ መልበሷ በኢስላም ውድ ያደርጋታል። ልክ እንደ እንቁ። አይን አዋጅ፤ የህዝብ ሚስት ሳትሆን በአንድ ሰው እጅ ብቻ የምትረጋ ናት። ለምሳሌ ገንዘብን እንውሰድ። ብዙ ሰው ብሩን ይዞ ሲንቀሳቀስ ሁሉም ሰው እንዲያየው አድርጎ አይደለም። ዋሌቱ ውስጥ ደብቆ፤ ኪሲ አጉሮ ከሰው ዕይታ በራቀ መልኩ ተጠብቆ ነው የሚያስቀምጠው። ብሩን መሸፈኑ ግን ብሩ ዋጋ የለለው አያደርገውም። እንደውም ዋጋ እንዳለው ያሳያል ምክንቱም በግልፅ ይዞት ቢሄድ ሊሰረቅ፣ እሱ ብቻ ሳይሆን ገንዘቡን ለመስራቅም ሲሉ እሱ ላይ ጉዳት ሊያደርሱበት ይችላሉ።
.
በኢስላም ሴቶችም ከብሩ በላይ ዋጋ ኣላቸው። ገንዘብን እንደሸፈንን ሁሉ እነሱም ውድ ነገር ስለሆኑ ራሳቸውን መሸፈን ኣለባቸው። ካልሆነ እነርሱም በእይታ ሊሰረቁ፤ ከዚያም ሴትነታቸውን ሊነጠቁ ይችላሉ። ለወንዶች ፊትና ከመሆንም አልፎ ወደ ዚና መጣራትም ነው። ያለ ሂጃብ መንቀሳቀስ ማለት አዳኝ ነብር በተሰበሰበበት ሚዳቆን መላክ ማለት ነው።
.
ኢስላም ለሁሉም ችግር መፍትሄ አለው። ልክ ካዝና ውስጥ ተቆልፎ ሲቀመጥ ዋጋውን እና ደረጃው እንደማይቀንሰው ሁሉ ሴት ልጅም ስትሸፈን እና ስትደበቅ ከጥሩ ሰው ዓይን ውስጥ ማለትም በሀላል ለሚፈልጋት ውስጥ እንጂ አትገባም። የብዙ ሴቶች ችግር ከዚህ ጋ የተያያዘ ነው። አንዲት ወጣ ብላ ልትመጣ ከመስተዋት ፊት የምትሽቀረቀረውን እንስት ለምን? ብለን ብንጠይቅ፤ <ውብ ለመምሰል> አሊያም <የምሄድበት ቦታ አስገድዶኝ> ልትለን ትችላለች። ዋነኛው እና ለኛ የማይነግሩን ሰበብ ግን <ወንድን ለመሳብ> የሚለው ነው። ግን እንደዚያ በውበትሽ፤ በመገላለጥሽ ተማርኮ የመጣ ወንድ ትክክለኛ ምርጫ ነው? መልሱን ለእንስቶች እተወዋለሁ!>> ኢምራን አንብቦ እንደጨረሰ ከልቡ ፈገግ አለ፡፡ የሀያትን ስም ከእቅዶቹ መሀከል ለመሰረዝ የታዳጊዎቹ መሰናበት ሩቅ ሆነበት፡፡
<<ጥሩ! በኋላ በደንብ የምመለከተው ይሆናል፡፡ በቅድሚያ ግን አንቺ ምን እንዳገኘሽ ንገሪን፡፡>>
<<ምን ልበልህ ኡስታዝ! ይሄ ለሁለተኛ ጊዜ የሰራሁት ሪሰርች ነው። የመጀመሪያውን እንኳን መፃፌን... ሀሳቦቹን ማሰቤ ብቻ እየሰቀጠጠኝ ነው። አልሀምዱሊላህ.... ራሴን ለማጋለጥ የወሰንኩበት ቀን በጣም ቅርብ ነበር። አላህ ሲረዳኝ....>> አለች ሀያት፡፡
<<እሰስከዛሬ እከኮ ይህ አመለካከት አልነበረሽም፡፡ እና ሂጃብ መጥቀም የጀመረው ይህንን ሪሰርች ስታጠነናቅቂ ነው ማለት ነው?>>
<<እንዴ ኡስታዝ?>> አፏን ሸፍና በዝግታ ሳቀች፡፡ <<እኔ ማወቅና አለማወቅ ከሂጃብ ጠቃሚነት ጋር ምን ያገናኘዋል? ከእኔ መጠቀም ጋር እንጅ>>
<<እናም... አላህ አያድርግብንና በድሮ አቋምሽ ብትፀኝ ኖሮ የሂጃብ ጠቃሚነት አይጠፋም ነበር እያለልሽኝ ነው?>>
<<ኧረ ምን አገናኙት ኡስታዝ?>> አሁንም ሳቅ ተናነቃት፡፡
ሱደየይስና አማን የሀያትና የኡስታዝ ኢምራን ንግግር ለጥያቄያቸው የሚሆን መልስ መሆኑ ገብቷቸዋል፡፡ የኢምራንን የሰሞኑን አካሄድ በደንብ እየተረዱት መጥተዋል፡፡
*
<<ሪያዕ ስራን ለአላህ ብቻ አጥርቶ የመስራት ወይም የኢኽላስ ተቃራኒ ነው፡፡>> ነባት በተማሪዎቹ መሀከል ትንጎራደዳለች፡፡ << ኸይር ስራዎቼ ከአላህ ዘንድ ደርሰው አጅርን ያስገኙልኛል ብዬ ሳይን ሰዎች አይተው ያደንቀቁኘኝ ዘንድ አሊያም የእነርሱን ኩነነና ፍራቻ ከሰራሁ ሪያዕ ውስጥ ገብቻለሁ ማለት ነው፡፡ እናም ልጆቼ ሪያዕ ትልቅ በሽታ ነው ልናስወግደው ይገባል፡፡ አላህ ብሀነሁ ወተዓላ ኸይር ስራዎቻቸውን ከሰዎቸች ከሚደብቁት መሀከል ያድርገን፡፡ ሌላው ነገር አዋቂዎች ሁነን ወንጀልን አንዳፈር እንጅ ባለማወቅ ለሰራናቸው ሀጢያቶች ኢንሻአላህ አዛኙ ጌታችን ይቅር ይለናል፡፡ የሰራነውን ወንጀል ለሌሎች መናገር ወንጀሉን ማስፋፋት ስለሆነ እርሱም ተገቢ አይደለም፡፡>> ነባት ዙሪያ ገባዋን ቃኘች፡፡ << አሁን ሰሞኑን ስናደርግ እንደነበረው ማስታወሻዎቻችሁን ታስረክቡኛላችሁ>> ብላ ማስታወሻዎቹን መሰብሰብ ያዘች፡፡ ፍቀደኛ ሆኖ የሰጣት ግን አንድም ተማሪ አልነበረም፡፡ ከከልቧ ተደሰተች፡፡ ሁሉን ያደረገችው ሆን ብላ | 0 |
| 18 | *
<<እርግጠኛ ነሽ ግን ነቡ ሀሩን እዚህ ነው የሚያመሸው የሚያድረው>> ራውዳ በቁመት የምትበልጣትን ነባትን ሽቅብ እየተመለከተች ጠየቀቻት፡፡
<<አዎ ቪዲዮዎችንና ጽሑፎችን ሲያዘጋጅ፣ ሲያርም፣ ሲያስተምር እቅድ ሲያወጣ ነው እኮ የቆየው፡፡>>
<<ያ አላህ! እኔ እኮ ይህን ሁሉ አላውቅም፡፡ ሀሩኔ ግን ምን አይነት ፍጥረት ነኽ ኸይር ስራውን ከእኔ ከሚስቱ እንኳ ይደብቃል? የአላህ ይቅር በለኝ፡፡ ሁሉን አላውቅ ሆኜ ነው፡፡>> አቀረቀረች፡፡ <<ታውቂያለሽ? እኔ እኮ ማስተማሩ ጊዜ ያሳጣው ይመስለኝ ነበር ፡፡ ይኽማ እኔም የቤቱን ስራ አግዤው ለሀሩኔ ጊዜ ከሰጠሁት አጅር አገኘሁ ማለት አይደል?>> አለች ራውዳ፡፡
<<እንዴ ለእናንተማ ጊዜ ሊኖረው ይገባል፡፡ እኔም እኮ ባለትዳር ነኝ፡፡ ኢምሩና ፊርዲም እንደዛው እኛ ግን እንደርሱ አይደለንም።>>
<<እንዴ እርሱማ ግዴታው ነው፡፡ ለእኔም ለልጃችንም ጊዜ ሊነኖረው ይገበባል፡፡ እኔም ግን እዚህ ለሚሰራው ኸይር ስራ ጊዜ ሊኖረኝ ይገባል፡፡>>
.
.
.
ይቀጥላል
#ሼር_ማድረግ_እንዳትረሱ
#ቻናላችንን_ይቀላቀሉ👇
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch | 0 |
| 19 | የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል አስር
(በረያን እና ሪና ሁዳ)
"አየሽ ፊዱ እዚህች ምድር ላይ እንዲሳካልኝ የምፈልገው ነገር ቢኖር ኻሊድን ወደቀድሞ ህይወቱ መመለስ ነው፡፡ መዋያና ማደሪያው መስጂድ ሲሆን፣ ሀያዕ የተሞላበት ዓይኑ ከሴት ልጅ ፊት ሲሰበር... ያንን ማየት ነው የምመኘው፡፡ ከዚያ የእናቷን አይነት ደስታ በሌሎች ላይም ማየት የምትሻ ጎበዝ ዶክተር መሆን፡፡ እኒህ ብቻ ናቸው የእኔ ፍላጎቶች>>
<<ለምን ግን ስለህይወትሽም ስለአንቺና ኻሊድ ግንኙነትም በደንብ አትነግሪኝም? ሁልጊዜ ትጀምሪልኝና ትተይዋለሽ፡፡>> ፊዳ አቋረጠቻት፡፡
<<መጀመሪያ ግን ሁለቱንም ምኞቶቼን ጀሊሉ እንዲያሳካልኝ ዱዓ አድርጊልኝ፡፡>>
<<ኢንሻአላህ! አሁን በደንብ አውሪኝ>> ፊዳ ጆሮዎቿን ቀስራ ተመቻቸች፡፡
*ከዓመታት በፊት*
"አህሉ! አንቺ አህሉ!" የነጃት ድምፅ ነበር፡፡ ነጃት የአህላም ጓደኛ ናት ጎረቤቷም ጭምር፡፡ እናቷ <<ከዚህች ችጋር የማይፋታት ልጅ ራቂ፤ ተጨንቃ አታስጨንቅሽ፤ ለእርሷ የመጣ መቅሰፍት አንቺን መንካቱም አይቀርም!>> ሲሉ ሰርክ ይነዘንዟታል፡፡ <<ከአንቺና ከዚያ ጥቁር ልጅ በቀር እኮ የሚጠጋትም አጥታለች፡፡ ተይ እንጅ ልጄ ለራስሽም እወቂበት እንጅ! ሁሌም የእርሷን ቀዳዳ ደፋኝ ሁነሽ እንዴት ትዘልቂዋለሽ፡፡ የእርሷ ችግር እንደሆን የሚደፍኑት ሽንቁር ሳይሆን ትልቅ ቡትርፍ ነው>> እናቷ ያክሉበታል፡፡ ነጃት እቴ መስሚያዋ ጥጥ ነው፡፡ "አንቺ ሞኝ ልጅ ስሚ ይሻልሻል! ይኸው አባቷን የገደለ ክፉ እጣዋ እሷኑ አንከባልሎ እናቷን ደም ያስተፋ ይዞልሻል፡፡ ያ የምትመጻደቅበት ቀይ ፊትዋ ወብ ቁመናዋአሁን የት አለ? ማዲያት ወርሷት የለም እንዴ? ጉብዝናዋስ ብትይ ይኸው እናቷን ልታስታምም ትምህርቷን ስታቋርጠው ርባናው ጠፋም አይደል? አዱኛቸውን ነስቶ በርሀብ ይቆላቸውስ ይዞም የለ? አባትሽ በየጊዜው የሚሰጣቸው ገንዘብ ምን ጠቅሟቸዋል? ምንም! ክፉ እጣ ነዋ የሚከተላቸው፡፡ እንደዚህ አይነቱን አዛኙ ጌታ ይደርስላቸው ዘንድ መለመን ካልሆነ ሌላ ምን ማድረግ ይቻላል፡፡ እንደአንቺ አብሮ ረሀብ ይግደለኝ ማለት ግን እውነት እልሻለሁ ሞኝነት ነው፡፡>>
ነጃት ግን የማንንም ሀሜት አትሰማም፡፡ ጆሮዬ ሆይ እነሆ ትለብሰው ዘንድ ዳባ መጥቶልሀል ትላለች፡፡ ድሮ ግን እንደሁሉም ጎረቤቶች እንደ ሁሉም ጓደኞቿ አይነት ነበር ለአህላም የነበራት አመለካከት፡፡ ቤተሰቦቿ ገንዘብ ከሰጧት፤ እንደማንኛውም ሰው ስሟ ሲጠራ ከንፈር ከመጠጠችላት ሌላ ምን አግብቷት፡፡ ይህንን ኃሳቧን ከስሩ የነቀለው 'አንድ ጥቁር ልጅ ነው' ይኽ ልጅ በመምጣቱ ነበር አሁንም ላንቃዋ እስኪበጠስ መጣራቷ፡፡
<<አቤት ነጁ>> አለች አህላም፡፡
<<ኻሊድ መጥቷል አህሉ፡፡>> አለቻት ነጃት፡፡
* አሁን *
ሀያት በሶስተኛው ርዕሷ ላይ ሰፋፊ መረጃዎችን ማሰባሰብ ልትጀምር ነው፡፡ ከዚያ በፊት ግን የቀደሙትን አርዕስት መገርመም ይዛለች፡፡ የባህል አልባሳትና የግለሰብ ፍላጎት የሚለው ርዕሷ ላይ ከዩቱዩብ አግኝታ ቃልበቃል ያሰፈረችው ጽሁፍ የተኮረኮረች ያህል አሳቃት፡፡
<< ሙስሊሞች ሴቶቻቸውን እንዲሸፈኑ ያስገድዳሉ ይሄ በጣም ኃላቀር አስተሳሰብ ነው።ከአካልህኮ ምትሸፍነው የምታፍርበትን ነገር ነው። እነሱ ሰዉነታቸው ላይ የሚያፍሩበት ነገር አለ ማለት ነው፣ ባይሆንማ አይሸፍኑትም ነበር። ካለፈሩበት ደሞ ምንም የሚሸፍኑበት ምክንያት የላቸውም።የኔን አለባበስ እንደምትመለከተው ነው 'ወደ አጭር ቀይ ቀሚሷ እየጠቆመች' ምንም የማፍርበት ሰውነት ስለለለኝ ዘና ብዬ አምሮብኝ ተቀምጫለሁ። አሁንኮ ሁሉም ነገር ሰልጥኗል ፋሽኑ በየጊዜው ይለዋወጣል አንተም አብረህ ስልጣኔው ጋር ታድጋለህ። ይህ ባ'ጠቃላይ ዘመናዊነት ነው። መሸፋፈንኮ በድሮ ዘመን የነበሩ ሴቶች የሚለብሱት አለባበስ ነው። አሁን 21ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ነን ወደኋላ የምንመለስበት ምክንያት የለንም።>>
ጥቀቂት ገጾችን ገልጣም ከሁለተኛው ርዕሰሷ ጋር ተፋጠጠች፡፡ "የኢስላምን አልባሳት እንዴተት ማዘመን ይቻላል?" የጻፈቻቸውን ነጥቦች በጉልህ ማጤን ያዘች፡፡
- አዳዲስ የሂጃብ አስተሳሰሮች
- ጅልባቦችን ጠበብ በማድረግ ቅርፅን ማጉላት
ውበት ያለችውን ሁሉ በኢስላማዊ አልባሳት ላይ ጨማምራ ጠቁማለች፡፡ ሶስተኛው ርዕሷ ግን ጊዜያትን ፈጅቶባታል፡፡ "ኢስላምና አለባበስ" ለመንደርደሪያ ይሆነኗት ዘንድ የዩቲዩብ ቪዲየዮዎችን፣ መጽሀፍትና ሳይንሳዊ ጥናቶችን አገላብጣለች፡፡ ከዩቲዩብ ያገኘችውን አንድ ቪዲዮ ድጋመሚ ትመለከታለች፡፡ በቪዲዮው ላይ ኒቃብ ያደረገች ሴት ቃለመጠይቅ ይደረግላታል፡፡ ስለአለባበሷ ስትጠየቅ የሰጠችው ምላሽ ግን ሀያትን ራሷን እንድትቃኝ ረዳት፡፡
<< በፊት የሰው ልጅ ሲፈጠር ራቁቱን ነው። ከዛ ቅጠል መልበስ ጀመረ ፣ ከዛ ላባ፣ እያለ እያለ… መሸፈን ጀመረ። ስለዚህ ስልጣኔ የምንለው መሸፈን እንጂ ወደ ድሮው መራቆት መመለስ አይደለም። እንዴት መራቆት ዘመናዊነት መልበስ ደሞ ኋላቀርነት ሊሆን ይችላል! እኛ ሳንሆን እነሱ ናቸው ወደ ድሮው እየተመለሱ ያሉት >>
አስተሳሰቧን ሙሉበሙሉ የሚቀይሩ መአት ቪዲዮዎችና ጽሑፎችንም አገኘች፡፡
በአዲሷ ርዕስ ስር ብዙ ንዑስ አርዕስቶችን አካተተች፡፡ የመጀመሪያዎቹን ሁለት አርዕስት በድጋመሚ ለማንበብ እንኳ ሰቀጠጧት፤ ከሪሰርቿ አወጣቻቸው፡፡
*
<<የአላህ እስከዛሬ እዚህ ነበር የምተሰራው? እኔ እኮ ሚፍታህ አል ቀልብን ብቻ ነበር የማውቀው>> አለች ራውዳ ዓይኖቿ እንደፈጠጡ፡፡
"አጂ....ብ! ምን አይነት ጉድ ነው" ልጄ አሉ ሸህ አህመድም አስከትለው፡፡
ሀሩን ራውዳን ከነባት ጋር አገናኝቷት ሸህ አህመድን ወደኢምራን ቢሮ ወሰዳቸው፡፡
<< አሰላሙዓለይኩም አኺ! ከራውዲ አባት ጋር መጥቻለሁ!>> ሀሩን ሸህ አህመድን ወደወንበር መራቸው፡፡
"ወዓለይኩም አስሠላም አኺ! የራውዲ አባት ስላገኘሁዎት ደስ ብሎኛል፡፡ ወላሂ ከተገናኘን እኮ ስንት ጊዜያችን! ጤናዎን እንዴት ነዎት? ኧረ ተቀመጡ እንጅ፡፡>> አለ ኢምራን ሸህ አህመድን ከጨበጣቸው በኋላ፡፡
<< እንዴት እንደናፈቃችሁኝ እኮ ልጆቼ! አልሀምዱሊላህ እኔ ደህና ነኝ!>> አሉ እየተቀመጡ፡፡
ኢምራን፡ <<እንዴት አገኙት ቦታውን>>
ሸህ አህመድ፡ <<ማሻአላህ ወላሂ አስደናቂ ነው በዚያ ላይ ለኸይር ነገር መጠቀሚያ ነው፡፡ ማሻአላህ አላህ ስራዎቻችሁን ይውደድላችሁ፡፡>>
<<አሚን የራውዲ አባት ግን ምን እንከን አገኙበት፤ የሚስተካከል?" ጠየቀ ሀሩን፡፡
<<ከጠየቅከኝማ አይቀር ልጄ ሀሩን አንድ የከነከነኝን ነገር ልንገርህ!>>
<<ምንድን የራውዲ አባት?>> ጠየቀ ኢምራን፡፡
"ለምን ብቻችሁን ልጄ? እውነት ነው ሚስጢራዊነቱ ከሪያዕ ይጠብቃቹኃል፡፡ ቡድኑን ግን የሁሉም አድርጉት፡፡ ወጣቶች ናችሁ ወጣት ሙስሊሞችን ሁሉ የኢስላም አርበኞች ማድረግ ትችላላችሁ፡፡ መተሳሰሩ እንደእኛ ዘመን አይከብድባችሁም፡፡ ምነው አጠበባችሁት ሰፋ አድርጋቸው አስቡ እንጅ፡፡ አብሽሩ!" ብለው ከወንበሩ ብድግ አሉ ሸህ አህመድ፡፡
<< እሺ የራውዲ አባት!>> ኢምራንና ሀሩንም ተከታትለው ተነሱ፡፡ | 0 |
| 20 | የኢስላም አርበኞች
ምዕራፍ ሁለት
ክፍል ዘጠኝ
<<' ከኒውተን በፊት ነገሮች ሁሉ በምድር ላይ ይንሳፈፉ ኑሯል? '>> ሱደይስ አዲሱን ጥያቄ እንዳነበበ በሳቅ ተንፈራፈረ፡፡
<<ምን ያስቅሀል?>> አለው አማን፡፡
<<ይህንን ጥያቄ አዳምጥማ...>> ሳቅ እየተናነቀው ሱደይስ ጥያቄውን አነበበለት፡፡ አማንም በተራው እስኪያነባ ሲስቅ ቆይቶ <<ቆይ ቆይ... ይኽ ነገር እንደባለፈው ሌላ መልዕክት ይኖረዋል፡፡ ካልሆነ መቼም እነኡስታዝ ኒውተን ስላገኘው ነው የመሬት ስበት የተፈጠረው ብለው አያስቡም>> አለ ሳቁ ያመነጫት ዕምባውን እየጠረገ፡፡
*
ሀሩን አዲሱን ስራውን ተላምዶታል፡፡ ቤቱ ተቀምጦ የቪዲዮ አርትኦት ስራ ይከውናል፡፡ በቅርቡ ለዘመድ ጥየቃ እግሯ እንደወጣ ያልተመለሰችው የቤት ሰራተኛቸው ሁሉንም የቤት ውስጥ ስራ ጥላበት ነው የሄደችው፡፡ ምግብ ለማብሰል ሲንደፋደፍ ሳሊም እንዲያስጠናው ይጠይቀዋል፡፡ የምግብ ሳሆኖችን ሲያጥብ የቆሸሹ ልብሶቻቸው ለውቅያ የቀረበ እህል መስለው ይከመራሉ፡፡ አሁንም ፓስታ ሊቀቅል የለኮሰው ምድጃ ላይ እንዳፈጠጠ ነው፡፡ ድንገት ብሶት ፈንቅሎት ተንሰቀሰቀ፡፡ ራውዳ ናፈቀችው፡፡ የቤት ስራው መደራረብ ሳይሆን ለብዙ ዘመናት ይህንን ሁሉ ስታደርግ ከእርሱ ጊዜውን እንኳ ማግኘት አለመቻሏ ሚስቱን አስናፈቀው፡፡ ድንገት የቤቱ መጥሪያ ሲጮህ በድንጋጤ እጁን ከምድጃው ላይ ጨመረው፡፡
'ባባ በር እየተንኳኳ ልከፍት ነው>> የሳሊም ድምፅ ከሳሎን ተነስቶ በኩሽናው አድርጎ ሀሩን ጆሮ አረፈ፡፡
<<ባባ አያቴ ነው፡፡ አልሀምዱሊላህ ኡሚም አለች፡፡>>
ሀሩን የተቃጠለ እጁን ረስቶ እንደህጻን ሮጠ፡፡
*
ፊዳ ከአህላም ጋር ተቀምጣለች፡፡ የደራው ጨዋታቸው ቀጥሏል፡፡ ነብስ ለነብስ ተገናኝተው አብረው መክነፍ ይዘዋል፡፡ ኡፍፍፍፍ!
"ቆይ ግን አንድ ባች ወደኋላ የቀረሽው ምን ሆነሽ ነው? ያውም ይህን የመሰለ እውቀት ይዘሽ?" አለች ፊዳ በጨዋታቸው መሀከል፡፡
አህላም በትካዜ ስታሰላስል ቆይታ ብሶቷን መተንፈስ ያዘች፡፡
<<ህይወት ግን ላንቺ ምንድን ናት?" ብላ ጀመረች፡፡
*
"ህይወት ለኔ?" ኢምራን አሚር የጠየቀውን ሀሳብ በአዕምሮው ሲያላምጥ ቆየና "የትኛውን ህይወት? አሁን ያለንበት? እሱኮ ገና በወንፊት ውስጥ የመንገዋለልን ያህል ነው፡፡ ህይወታችን እኮ የሚጀምረው ወይ እህል ሆነን ወፍጮ ቤት ወይ ገለባ ሆነን መኖ ቤት ስንገባ ነው፡፡ የዚህች ዱኒያ ህይወትማ ገና ቅድመ-ህይወት እንጂ ህይወት አይደለም" አለው በሳይኮሎጂስት አይኖቹ እየተመለከተው፡፡
*
አህላም ንግግሯን ቀጠለች "አየሽ እኔ ማለት እኮ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሆኜ ራሴን ለማጥፋት የሞከርኩ ሰው ነኝ፡፡ ችግር ሲደራረብብኝ፣ ቤተሰቦቼን ሳጣ፣ ስታመም፣ የታመመች እናቴን ለማስታመም ተስፋ ያደረግኩትን ትምህርቴን ለማቋረጥ ስገደድ በቃ ምን ልበልሽ ፊዱ? ጥንካሬዬ ሁሉ ተሟጥጦ ሰነፍ ሆንኩኝ፡፡ ከሰነፍም የሰነፎች ቁንጮ ችግርን ከመጋፈጥ ራሷን ማጥፋትን የመረጠች ሰነፍ! እና ያኔ ነው ኻሊድን ያገኘሁት፡፡ እና ራሴን አጥፍቼ ዱኒያዬንም አኼራዬንም ከአላህ በታች ሰበብ ሆኖ ያተረፈልኝን ሰው እሱ ነው ህይወቴ ብልሽ ትፈርጂብኛለሽ? ከራስ በላይ ንፋስ እያለ በተረተ አፋቸው እኔ ለገዛ ህይወቴ ያለኝን ሁሉ በመስጠቴ የሚዘልፉኝስ ትክክል ናቸው ትያለሽ?" በሚንቀለቀሉ አይኖቿ ፊዳ ላይ አፈጠጠች፡፡
"ትክክል እኮ ነሽ እና እሰሱን ለማስተካከል ብለሽ አኼራሽን ማበላሸት ነበረብሽ?" አለች ፊዳ፡፡
"እሱስ አድርጎት የለ?" አለቻት አህላም፡፡
ፊዳ የንግግራቸው መቋጫ ጥሩነት ስላልታያት ወሬ ቀየረች፡፡
"አሁን ግን ጠንካራ ሆነሻል አይደል? ወደፊት ምንድነው ማሳካተት የምትፈልጊው?"
*
በሱደይስና አማን ክፍል ውስጥ ሲሰማ የነበረው ሳቅ ባስፈሪ ጸጥታ ተተክቷል፡፡ ሁለተቱም በጥያቄ መልክ ለቀረበባቸው ቅኔ ወርቁን በመፈለግ ላይ ናቸው፡፡
"አሙ! እኛ ግን ለምንድነው በሳይንስ ያልተረጋገጠን ነገር ሁሉ የማናምነው?" አለ ሱደይስ መነጽሩን ከአይኖቹ አለያይቶ በጠረጴዛው ላይ እያስቀመጠ፡፡
"ምን አይነት ጥያቄ ነው ሱዲ? ያለልተረጋገጠ ነገር ምኑ ይታመናል?"
"ተው እንጅ አሙ! እስኪ አረጋጋጩ ማነው? የሰው ልጅ አይደል እንዴ? ሰዎች ደግሞ ገደሎ ነን፡፡ ሁለሉን ነገር መርምረን ልንደርስበት አንችልም፡፡ መሬት ሞላላ ከመሆኗ በፊት ጠፍጣፋ ነበረች እንዴ? የዳልተን፣ የአሪስቶትል፣ ዘመናዊው እያልን የተማርናቸው የአተም ህገጎች ሁለሉ ሳየይንሳዊ አይደሉም? ነበሩ እውነት ግን አንድ ነች፡፡ ሳየይንሱ ግን ብዙ ብሏል፡፡ እስከ ኒውተን ድረሰ በሰዎች ያልታወቀው የመሬት ስበት ያኔ አልነበረም ማለት ነው እንዴ አሙ? ፈጽሞ! ይልቀቅ የመሬት ስበት ኒውተን አገኘውም አላገኘውም ጥንት ጀምሮ የነበረ ነው፡፡"
"ሱዲ ይህ ማለት እከኮ..." አማን አቋረጠው፡፡ "ፈጣሪን ካለላዬን አናምንም ለምንለው እኛ ጥሩ መልሰ እነንጅ ጥያቄ አይደለም የላኩልን፡፡"
*
"ምን እያሰብኩ ነው ልጄ?" ከሸመገለ ሰውነታቸው እየተንቀጠቀጠ በሚወጣ ድምጻቸው የራውዳ አባት ሸህ አህመድ ሐሩንን ከሀሳቡ አናጠቡት፡፡
"ኧረ ምንም ጋሼ የሰሞኑን ኑሮዬን እያሰብኩ ነበር፡፡"
ሸህ አህመድ "እና ብቻህን ኑሮ ከበደህ?" ብለው በጥምጣማቸው አፋቸውን ሸፍነው ተንከተከቱ፤ ራውዳመም ተከተለቻቸው፡፡ ሳሊም ምክንያቱ እንኳ ሳየይገባው አብሯቸው ሳቀ፡፡
"አየህ ልጄ?" አሉ ሸህ አህመድ ሳቀቃቸውን ገትተው <<ሁሉን ያደረግነው አውቀን ነው ኑሮ ለብቻ ይከብዳል፣ የሚያማክሩት ማጣተት ይከብዳል፡፡ ይህ ሁሉ ሀላፊነት ተከምሮባት እንኳ ልጄ ራውዲ እህ ብለህ እንድትሰማት፣ የሚገባትን ሀቋን የሆነውን ጊዜሀህን ነበር የጠየቀችህ አንተ ግን መስጠት አልቻልኩም፡፡ ያነኔ ነው ብቸኝነትን ትቀምሰወው ዘንድ ጥላህ ከእኔ ጋር እነንድትመጣ የመከርነው፡፡ እነኔ መቼም ማቀቃናቴ እንጅ ማጠጥፋቴ አልታየኝም፡፡>> አሉ፡፡
ሀሩን በእምባ የወረዛ ፊተቱን አብሶ እመር ብሎ ተነሳና 'አውፍ በይኝ ራወውዲ!>> ተጠመጠመባት፡፡
<<አብሽር ሀሩኔ! እኔ እከኮ አንተን መቀየም አይሆንልኝም፡፡>> አለች ራውዳ፡፡
<<ኤደዲያ የምን መጃጃል ነው ይለልቅ ለጥፋቱ ይቀጣ!>> አሉ ሸህ አህመድ
<<ምነን ልቀጣ?>> አለ ሀሩን እንደፈገገ፡፡
<<በል የምትሰራውን አስጎብኘን>> አሉት ሸህ አህመድ ከኮስማና ፊተታቸው በልጦ የተንዠረገገ ጢመማቸውን እየያሻሹ፡፡
.
.
.
ይቀጥላል
#ሼር_ማድረግ_እንዳትረሱ
#ቻናላችንን_ይቀላቀሉ👇
@wub_Tarikoch
@wub_Tarikoch | 0 |
