EOTC BOOK PDF FREE/(የኢ/ኦ/ተ-መጽሐፍት )
Open in Telegram
ይኽን መጽሐፍ ብላ! ሕዝ.3:1 ꧁-------------------------꧂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ክርስትናን የሚሰብኩ የቅዱሳት መጽሐፍት ማሕደር!! በ #PDF Free "መጽሐፍትንና የእግዚአብሔርን ኃይል አታውቁምና ትስታላችሁ።" ማቴ 22፥29 የመጽሐፍ ቅዱስ አርዕስቶችና አንድምታዎች ፣ የአባቶች የሊቃውንት መጽሐፍት ይገኙበታል። ኑ ༒
Show more655
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#መጽሐፈ_ወግሪሰስ በአባ ገብረ ኪዳን ግርማ (የብሉይና የሐዲሳት መምርህር)
#መጽሀፍትን_የመመልከት_ጥቅም
አምላክ ወዶ የጻፋቸውን መጻሕፍት መመልከትን አታቋርጥ። እነርሱ በጠበበችው ጎዳና ትጓዝ ዘንድ ይመሩሀል፤ መርተውም ወደ ዘለዓለም ሕይወት ወደ መንግስተ ሰማያት ያደርሱሀል። ጥሪት ቁሪትን ሁሉ ጥላ፤ በአንተና በሞት መሀል ያለው የጊዜ ቀጠሮ መቼ እንደሚደርስ አታውቅምና። ልብ በማያበላሸው ነቀዝ በማይበላው ሌባ በማይሰርቀው ሰማያዊ መዝገብን አድርግ እንጅ። ውዳሴ ከንቱ አትውደድ፣ መነቀፍንም አትጥላ፤ ዓለምን ስለሚጠላ መመስገን ክፉ መነቀፍ መልካም ይሆንለታልና። ድልድል ቅምጥልነትህ ወደ ሐዘንና ትካዜ እንዳይለወጥ ሕሊናህን ከዚህ ዓለም ሐሳብ ወደ ሰማይ አምጥቀው፤ የዚህ ዓለም ፍቅር ከንቱ ነውና።
ከመጽሐፉ የተወሰደ.....ዳሕላክ
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ኃጢአትን ከመሥራት ለመቆጠብ ዓይነተኛ መንገድ ነው። መጻሕፍትን አለማወቅ ግን ጥልቅ ጉድጓድና ታላቅ ገደል ነው። ስለመለኰታዊው ሕግ አለማወቅ ታላቅ ክህደት ነው። እንዲህ ያለው ነገር ደግሞ ለኑፋቄ መወለድ፣ ለምግባረ ብልሹነት፣ ለኢክርስቲያናዊ ሕይወት መምጣትና የላይኛውን ዋጋ ዝቅ አድርጎ ለመመልከት ምክንያት ይሆናል።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
የቤተክርስቲያን ድምፅ!!
በሚገባ ይነበብ
ገዳማውያን አበው የበረሃ አባቶች ተናግረዋል ንጉሥ ቴዎድሮስ ይመጣል ስለሚባለው፣ ስለሲኖዶሳዊ አንድነት፣ በወቅቱ ስላለው ሰላም ማጣት የመሳሰሉትን ጉዳዮች ከ10 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ገዳማት በጋራ መልእክት አጥርተው ገልጸውታል።በጸሎት እንድንበረታም አሳስበዋል::
በተለይ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ተከታዮች እውነቱን እወቁት በአባቶቻችን ስም አታጭበርብሩ!
በሚገባ ይነበብ
ገዳማውያን አበው የበረሃ አባቶች ተናግረዋል ንጉሥ ቴዎድሮስ ይመጣል ስለሚባለው፣ ስለሲኖዶሳዊ አንድነት፣ በወቅቱ ስላለው ሰላም ማጣት የመሳሰሉትን ጉዳዮች ከ10 በላይ የሚሆኑ ታላላቅ ገዳማት በጋራ መልእክት አጥርተው ገልጸውታል።
በጸሎት እንድንበረታም አሳስበዋል
በተለይ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ተከታዮች እውነቱን እወቁት በአባቶቻችን ስም አታጭበርብሩ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan
