en
Feedback
Inclusive Education - Afar Region (Channel)

Inclusive Education - Afar Region (Channel)

Open in Telegram

A Channel for inclusive education reference materials

Show more
336
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ድህረ አደጋ ሽብረት (Post-Traumatic Stress Disorder) (በዶ/ር ኢየሩሳሌም ጌቱ) በህክምናው አጠራር Post-Traumatic Stress Disorder በመባል የሚታወቀው በሰዎች አካ
ድህረ አደጋ ሽብረት (Post-Traumatic Stress Disorder) (በዶ/ር ኢየሩሳሌም ጌቱ) በህክምናው አጠራር Post-Traumatic Stress Disorder በመባል የሚታወቀው በሰዎች አካላዊ ጉዳት የሚያደርስ በጣም አሰቃቂ ሁኔታ ስላጋጠማቸው፣ ስለተመለከቱ ወይንም እንዲህ ባለው ሁኔታ ውስጥ ስላለፉ የሚከሰት የስነልቦና መረበሽ አይነት ነው። ይህ ከአንድ መጥፎ አጋጣሚ በኃላ በስሜት ተቀርፆ በሚቀር ጭንቀትና ፍርሃት ወይም ስጋት አማካኝነት የሚመጣ የስሜት መዛባት በማንኛውም የእድሜ ክልል ላይ ሊከሰት ይችላል። የትኛው የማህበረሰብ ክፍል ለድህረ አደጋ ሽብረት ተጋላጭ ነው? - ከፍትኛ ለሆነ አደጋ የተጋለጡ ሰዎች (ጦርነት፣ ግርፊያ፣ የመኪና አደጋ ወይም የእሳት ቃጠሎ) - ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው - የሚዎዱትን ሰው በድንገተኛ ሞት ያጡ - በልጅነታቸው አሰቃቂ ጥቃት የደረሰባቸው (አካላዊ ወይንም መንፈሳዊ) PTSD (ድህረ አደጋ ሽብረት) ያጋጠማቸው ሰዎች ምን አይነት ምልክቶችን ያሳያሉ? - ቅዠት - እንቅልፍ ማጣት - ቀደም ሲል ባጋጠማቸዉ ችግር ምክንያት ስለአዪት ስቃይ በጣም ብዙ ማሰብና መጨነቅ - በቀላሉ ድንግጥ ማለት - የስሜት መደንዘዝ - ይወዱዋቸዉ በነበሩ ነገሮች ላይ ደስታን ማጣት - ራሳቸውን ከአካባቢ፣ ከሰው እና ሁኔታዎችን ከሚያስታውሳቸው ነገሮች ማራቅ የህክምና ባለሙያን ማማከር የሚገባው መቼ ነው? - የህይወት ትርጉም ማጣት እና የተስፋ መቁረጥ ስሜቶችን ማስተናገድ ሲጀምሩ - ምልክቶቹ በአኗኗር ዘይቤ ላይ ተፅእኖ ማስከተል ሲጀምሩ - እራስን ለመጉዳት ወይም ለማጥፋት ማሰብ ሲጀምሩ በ ድህረ አደጋ ሽብረት የተጠቁ ሰዎች በሌላም ዓይነት የስነልቦና መረበሽ ህመም የመጠቃት እድላቸው ከፍ ያለ ስለሆነ በጊዜ የህክምና እርዳታ ቢያገኙ ይመከራል። @melkam_enaseb

ዓይነ ስውርነት ☞  አጋላጭ መንስኤዎች ☞ ሕክምናቸውስ? በአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የዓይን ሕክምና ክፍል ኃላፊ እና የዓይን ሐኪም ዶክተር ሰሎሞን ቡሳ ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ካደረጉት ቆይታ የተወሰደ ☞ የሞራ ግርዶሽ፣ ግላኮማ፣ ትራኮማ፣ አነጣጥሮ የማየት ችግር (ሪ ፋክቲቭ ኢር)፣ የስኳር ሕመም (ዲያቤቲስ) እና ከመደበኛው የመወለጃ ጊዜ ቀድሞ መወለድ ዓይነ ስውርነትን ከሚያስከትሉ በርካታ መንስኤዎች መካከል ይጠቀሳሉ።  1.  የሞራ ግርዶሽ የሞራ ግርዶሽ በተፈጥሮ ከሚመጡ ለዓይነ ስውርነት አጋላጭ መንስኤዎች አንዱ ሲሆን÷ በኢትዮጵያ ከፍተኛው የዓይነ ስውርነት ምክንያት ሆኖ ይጠቀሳል፡፡ ከ15 ዓመታት በፊት የተካሄደ የጥናት ውጤት እንዳመላከተው÷ በኢትዮጵያ ከሚኖረው ሕዝብ ቁጥር 1 ነጥብ 6 በመቶው የዕይታ ችግር አለበት፡፡ አሁን ሊጨምር እንደሚችል ይገመታል፡፡ በጥናቱ ግኝት መሰረት ካለው የዓይነ ስውርነት ምጣኔ 50 በመቶ የዓይነ ስውርነት ምክንያቱ የሞራ ግርዶሽ መሆኑን ጠቁመው÷ ይህም በተፈጥሮ (አብሮ በመወለድ)፣ በአደጋ (ምት) እና በዕድሜ መግፋት ሊመጣ ይችላል። የሞራ ግርዶሽን ቀድሞ መከላከል ባይቻልም ከተከሰተ በኋላ ግን በቀዶ ሕክምና ይስተካከላል። 2.  ግላኮማ ጤናማ የዓይን ግፊት ከ10 እስከ 21 ድረስ ሲሆን÷ ከ21 ሚሊ ሜትር ኦፍ ሜርኩሪ በላይ ከሆነ ግፊቱ ከፍ ማለቱ ብቻ ሳይሆን በተጓዳኝ የዓይን ነርቭን (ኦፕቲካል ነርቭ) በመጉዳት ዕይታን ይቀንሳል፡፡ ቶሎ ሕክምና ካልተደረገለትም እስከ ዓይነ ስውርነት ያደርሳል። ግላኮማ በዘር ይተላለፋል፣ ምክንያታቸው በውል ባልታወቁ ሁኔታዎች ይከሰታል፣ አንዳንዴ የዓይን ውስጥ ሕመሞችም ይህን ሊያመጡት ይችላሉ፡፡ ምንም ዓይነት የሕመም ምልክት ስለሌለው ዕይታ ቀስ በቀስ እየቀነሰ ይሄድና ፊት ለፊት ብቻ እንጂ ወደ ጎን ማየት እስከማይቻልበት ደረጃ ያደርሳል። ግፊቱ ከፍ በሚልበት ጊዜ ደግሞ የራስ ምታት ያስከትላል፣ በመብራት ዙሪያ እንደ ቀስተደመና የሚመስሉ ቀለማትን ያሳያል፣ ብዥታዎችንም ይፈጥራል፡፡ እንደዚህ በሚሆንበት ጊዜ ተመርምሮ ሕክምና መጀመር ይገባል፤ ሕክምናው ለዕድሜ ልክ የሚሰጥ ሲሆን መቋረጥ የለበትም። የተጎዳውን ነርቭ መመለሾ ስለማይቻል ተጨማሪ ጉዳት እንዳይደርስ ግፊቱን ለማውረድ መድኃኒቱ እንደሚሰጥ አስገንዝበው÷ ያለው ዕይታ ባለበት እንዲቆይ (እንዳይጠፋ) ለማስቻል ይህን በማድረግ ዕይታን ማቆየት ይቻላል። 3.  ትራኮማ በኢትዮጵያ ዓይነ ስውርነትን ከሚያስከትሉ መንስኤዎች ትራኮማ ሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኝና በጀርም የሚመጣ ሕመም ነው፡፡ ባብዛኛው የውኃ እጥረት ባለበትና ሞቃታማ አካባቢ፣ ዝንቦች በብዛት በሚፈለፈሉበት፣ ሰዎች ትፍግፍግ ብለው በሚኖሩበትና  በሚተኙበት፣ ፎጣና የትራስ ጨርቆችን በጋራ በመጠቀም ይከሰታል፤ ይተላለፋልም። ይህ ሕመም የዓይንን ቆብ ወደ ውስጥ ቆልምሞ ጸጉሩ የዓይን ብሌንን እየፈገፈገ አቁስሎ ጠባሳ በመፍጠር ብርሃን እንዳይተላለፍ በማድረግ ዓይነ ስውርነትን ያስከትላል፡፡ ስለሆነም የአካባቢ እና የግል ንጽህናን በመጠበቅ ቀድሞ መከላከል እና ሕመሙ ከተከሰተ በኋላም ሕክምና በማድረግ በትራኮማ ምክንያት የሚመጣውን ዓይነ ስውርነት ማስቀረት ይቻላል። 4. አነጣጥሮ የማየት ችግር (ሪ ፋክቲቭ ኢር) ከአነጣጥሮ የማየት ችግር ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ ችግሮች ደረጃቸው የተለያየ ሲሆን በመነጽር የመስተካከል ዕድል እንዳላቸው ይታመናል። በየትኛውም ሰው ላይ ሕመሙ ቢስተዋልም በይበልጥ ልጆች፣ ወጣቶች፣ ተማሪዎች አነጣጥሮ የማየት ችግሮች በከፍተኛ ደረጃ እንደሚታይባቸው መረጃዎች ያመላክታሉ። ቢያንስ ወደ 7 ነጥብ 8 በመቶ የሚሆነው የዕይታ ችግር ከአነጣጥሮ የማየት ችግር ይመጣል። እነዚህ ሰዎች ተመርምረው መነጽር ሊታዘዝላቸው እና ዕይታቸውን ማስተካከል የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር እንደሚገባም ይመከራል። 5. የስኳር ሕመም (ዲያቤቲስ) ሌላኛው የዓይነ ስውርነት መንስኤ በአሁኑ ወቅት  ከከተማ እስከ ገጠር እተስፋፋ የሚገኘው የስኳር ሕመም ነው፡፡ በደም ውስጥ ያለው የስኳር መጠን ሳይስተካከል ሲቀርና ከፍ ብሎ በሚገኝበት ወቅት እንደሚከሰት የሚታመነው የስኳር ሕመም፥ በባህሪው የደም ስሮችን ልፍስፍስ የማድርግ  እና በቀላሉ  እንዲቀደዱና ደም እንዲረጩ የሚያደርግ ነው። በመሆኑም ሕክምና ካልተደረገ በዓይን ውስጥ (ረቲና ላይ) ያሉ ቀጫጭን የደም ስሮች በቀላሉ ደም ሊረጩ ይችላሉ፤ ይህን ተከትሎም ዕይታ ሊጎዳና ሊጠፋ የሚችልበት አጋጣሚ ይከሰታል፡፡ ስለዚህ የስኳር ታማሚዎች ሁልጊዜ የደም ስኳራቸውን እንዲስተካከል ሕክምናቸውን መከታተል ይጠበቅባቸዋል፤ እንዲህ ሲሆን ዕይታቸው ሳይጎዳ ለረጅም ጊዜ ይቆያል ሲሉ። 6. ከመደበኛው የመወለጃ ጊዜ ቀድሞ መወለድ ከመደበኛው የመወለጃ ጊዜ (ዘጠኝ ወር) ቀድሞ መወለድ ለዓይነ ስውርነት ከሚጋልጡ ምክንያቶች አንዱ ሆኖ ይጠቀሳል። ሕጻናት በማህጸን ውስጥ እያሉ  ሙሉ ዕድገቱን ያልጨረሰው ብሌን (ረቲና) በሚወለዱበት ጊዜ፥  ደም መርጨት፣ የብሌን መላቀቅ ችግር ያስከትልና ለዓይነ ስውርነት ሊያደርስ ይችላል። በመሆኑም ያለ ጊዜያቸው የሚወለዱ ሕጻናትን ወደ ሕክምና በመውሰድ ዓይናቸው እንዲመረመርና ተገቢው ክትትል መደረግ ይኖርበታል፡፡ ከ15 ዓመታት በፊት በተካሄደ የጥናት ውጤት እንደተመላከተው÷ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚኖረው ሕዝብ ቁጥር 1 ነጥብ 6 በመቶው ዓይነ ስውር (የዕይታ ችግር ያለባቸው) ናቸው፡፡ አሁን ሊጨምር እንደሚችል ይገመታል፡፡ ለዓይነ ስውርነት በማጋለጥ ሂደታቸው ቅደም ተከተል መሰረትም÷  የሞራ ግርዶሽ፣ ትራኮማ፣ ግላኮማ፣ አነጣጥሮ የማየት ችግሮች፣ የስኳር ሕመምና የተለያዩ ምክንያቶች፣ የሕጻናት የዓይነ ስውርነት ችግሮች ይጠቀሳሉ፡፡ በአብዛኛው የዓይን ሕመም ሕክምና በሀገር ውስጥ ስለሚሰጥ፥ ህብረተሰቡ በዓይኑ ወይም በዕይታው ላይ ዕክል ሳያጋጥመው ቀድሞ ለመከላከሉ ትኩረት እንዲሰጥና ችግሩ ካጋጠመም ጊዜ ሳያባክኑ ወደ ዐይን ሕክምና ተቋም እንዲሔድ ይመከራል ህብረተሰቡ በልማድ ወደ ሕክምና ተቋም የሚሔደው የዕይታ ችግር  ሲደርስበት መሆኑን በመጠቆም፥  አንድ ሰው ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ ቢመረመር የዓይኑን በጤንነት የመቆየት ጊዜ ማራዘም ይቻላል። ምክንያቱም በዘር ሊተላለፉ የሚችሉ የዓይን ችግሮች ስላሉና  ምንም ዓይነት የሕመም ምልክት ሳያሳዩ (ለምሳሌ ግላኮማ) ዓይነ ስውርነትን የሚያስከትሉ ምክንያቶች አሉ። @inclusiveafar

#Amputee_Football_Federation @inclusiveafar

IMG_20221207_210742_628.jpg1.27 KB

"...No Dream is too big and no disability can stop you fron your dreams..." Ghanim Al Muftah #Ghanim #Qhatar #fifa t.me/inclusiveafar

"No Dream is too big and no disability can stop you fron your dreams" Ghanim Al Muftah #Ghanim #Qhatar #fifa t.me/inclusiveafar

2) --- refers   to   an   ongoing   process education/services for all while respecting diversity and the different needs and abilities, characteristics and learning expectations of the students and communities and eliminating all forms of discrimination
Anonymous voting

1) ---------------means a loose/lack/abnormality of an anatomic, physiological or psychological structure or function or deviation on a person.
Anonymous voting

ተደራራቢ የአካል ጉዳት (Multiple disabilities) ምንድን ነው? በ ሰለሞን ግዛቸው ------------ ተደራራቢ የአካል ጉዳት የተለያዩ የአካል ጉዳቶች ጥምረት ላለበት ሰው የተሰጠ ስያሜ ነው ፣ ወይም ተደራራቢ የአካል ጉዳት በትምህርት ቅስሞሽና በሌሎች አስፈላጊ የሕይወት እንቅስቃሴዎች ላይ  ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሁለት እና ከዚያ በላይ የአካል ጉዳት አይነቶች በአንድ ጊዜ መከሰት ነው። ተደራራቢ የአካል ጉዳት አለቸው ከምንላቸው ሰዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ  ከአንድ በላይ ጉልህ/ግልጽ የሆነ የአካል ጉዳት ይታይባቸዋል፡፡ አንድ ጉዳት ተደራራቢ የሚባለው ጉዳቱ ጉልህ/ግልጽ ተጽዕኖ ያሳደረና ህጻኑን  በተለመደው የልዩ ትምህርት መርሃግብር ዝግጅት አንድ አይነት የአካል ጉዳት ላለባቸው ተማሪዎች በተዘጋጀ ቦታ ውስጥ በበቂ ሁኔታ  ለማስተናገድ ሲያስቸግር ነው፡፡ ለምሳሌ፡-     የአዕምሮ ዕድገት ውስንነትና የእይታ ተግዳሮት/አይነስውርነት   የአካልጉዳትና የእይታ ተግዳሮት/አይነስውርነት   የአካል ጉዳትና የመስማት ተግዳሮት/መስማት መሳን   የአዕምሮ ዕድገት ውስንነትና የስሜት ጉዳት   የመስማትና ማየት ችግር (መስማት መሳንና አይነስውርነት) Deaf-blind ወዘተ.  ይሁንና በአንዳንድ አገሮች ለምሳሌ በአንዳንድ የአሜሪካ ግዛቶች ያሉ ህጎች እንደሚያመለክቱት “አንድ ሰው ተደራራቢ የአካል ጉዳት አለበት ለመባል ከታዩበት የአካል ጉዳት አይነቶች መካከል  ቢያንስ አንዱ የአዕምሮ ዕድገት ውስንነትን ማካተት አለበት ” ይላል፡፡  በዚህ እሳቤ መሰረት ደግሞ መስማት መሳንና አይነስውርነት (Deaf blind) በተደራራቢ የአካል ጉዳት ውስጥ ሊካተት አይችልም፡፡ ይሁን አንጂ በሌሎች አለም አገራትና በእኛ ሀገር ይህ የጉዳት አይነት በተደራራቢ የጉዳት አይነት ውስጥ ይመደባል፡፡ እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባን ነገር ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ልጆች አማካይ ወይም ከዚያ በላይ የአዕምሯዊ ብቃት/ችሎታ/ተሰጥኦ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ነገር ግን የበለጠ ጉልህ በሆነው የአካል ጉዳት ምክንያት  ከፍተኛ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ፡፡ለምሳሌ፡- ልዩ ተሰጥኦ ያላቸው ወይም የተለየ ችሎታ ያላቸው ኦቲዝም ያለባቸው ተማሪዎች ሆነው በጉልህ ላለባቸው የአካል ጉዳት ፣  መስማት መሳን ወይም ዓይነ ስውርነት የተለየ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሊያካትት ይችላል ፡፡ ስርጭት/Prevalence፡- ልዩ ትምህርት ፍላጎት አላቸው ተብለው ከሚለዩት ውስጥ  ከ3% ያልበለጡ ናቸው፡፡ መገለጫዎች፡- ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ሰዎች እንደጉዳቱ ክብደት፣ የጉዳት አይነቶች ጥምረት፣  እንዲሁም እንደ ሰውየው ዕድሜ ሰፋ ያሉ የስነ ልቦና፣ የባህሪ እና አካላዊ መገለጫዎች  ሊያሳዩ ይችላሉ ፡፡   ስነልቦናዊ መገለጫ፡- (ከፍተኛ የመገለል ስሜት፣ፍርሀት፣ ቁጠና ብስጭት፣ ራስን የመጉዳት ስሜት ወዘተ )   የባህሪ መገለጫዎች፡- ከዕድሜ ዕኩዮቻቸው አንጻር ያለበሰሉ  መሆን፣ ጓደኝነት መመስረት መቸገር፣ ራስን የመንከባከብ ክህሎት ማነስ፣ ገለልተኛ መሆን ወዘተ   አካላዊ መገለጫ፡- የስሜት ህዋሳት ስሜትን ማጣት፣ አካላዊ መፍዘዝ፣ የዕለት ተለት ዕንቅስቃሴዎችን ለመካናወን መቸገር፣ ጥገኛ መሆን ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያላቸው ልጆች ወላጆች የሚከተሉት እንዲያደርጉ ይመከራል፡-   ስለልጅዎ የአካል ጉዳተኝነት ሁኔታ መማር ማወቅ   የልጅዎ ልዩ ፍላጎቶች ምን እንደሆኑ መገንዘብ ና እነዚህ ፍላጎቶች መሟላታቸውን ማረጋገጥ   ልጅዎን ልክ እንደሌሎች ልጆችዎ መውደድና መንከባከብ   ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለበት ልጅዎ ራሱን/ሷን እንድትችል  በሚቻለው ሁሉ መንገድ ማበረታት   ልጅዎ ሊያከናው በሚችላቸው ማናቸውም የዕለት ተለት ዕንቅስቃሴዎች  ውስጥ በጥንቃቄ ማሳተፍ   ልጅዎን ሊረዱ ከሚችሉ ሐኪሞች እና ሌሎች ባለሙያዎች ጋር በየጊዜው መገናኘት   ልጆቻቸው ተመሳሳይ የአካል ጉዳት ካለባቸው ሌሎች ወላጆች የድጋፍ ቡድን ውስጥ መሳተፍ ሀሳብ መለዋወጥ   ከሁሉም በላይ… ተስፋ ሰጭዎችና ደጋፊዎች  መሆን ፡፡ በእርስዎ ድጋፍ  ልጅዎ ጥሩ እና ትርጉም ያለው ሕይወት መኖር ይችላልና ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸውን ልጆች ማስተናገድ የሚቻልባቸው መንገዶች /Accommodations/strategies አብዛኞቹ አካል ጉዳተኛ  ልጆች በሕይወታቸው ውስጥ በተወሰነ ደረጃ እገዛ እና ድጋፍ ይፈልጋሉ ፡፡ የሚያስፈልጋቸው የድጋፍ አይነት ግን እንደ አለባቸው ጉዳት አይነትና ክብደት ይወሰናል፡፡ ከዚህ አንጻር  መለስተኛ ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ልጆች ለተወሰኑ ተግባራት ብቻ ጥቂት ድጋፍ ይፈልጉ ይሆናል  ነገር ግን ከባድ/ከፍተኛ ተደራራቢ የአካል ጉዳት  ያለባቸው ልጆች እድሜአቸውን በሙሉ ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ሊፈልጉ ይችላሉ ፡፡  በእኛ አገር ሁኔታም ከትምህርት ገበታ ዉጪ ተገልለው ከሚገኙ አካል ጉዳተኛ ህጻናት ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወስዱ ይገመታል፡፡  ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለበትን ልጅ ወላጆች ለመደገፍ ወይም ልጁን ለማስተማር የሚከተሉት ማወቅ አስፈላጊ ነው ።   ምን አይነት የአካል ጉዳቶች እንዳሉበት ማወቅ፤   እያንዳንዱን የአካል ጉዳት ምን ያህል ከባድ ( መካከለኛ ወይም ዝቅተኛ) እንደሆነ መረዳት; እና   እያንዳንዱ የአካል ጉዳት በመማር እና በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴው ላይ ሊያደርስ የሚችለውን መገመትና ቅድሚያ የሚሰጠውን በትኩረት መለየት ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸውን ልጆች በሚከተሉት መንገዶች ማካተትና መደገፍ ይቻላል፡-   የተማሪውን ችግሮች ለመፍታት ወላጆችን ፣ የትምህርት ባለሙያዎችን እና የሕክምና ባለሙያዎችን ያካተተ ቡድን በጋራ መመስረት   እንደ ፊዚዮቴራፒስት/ወጌሻ፣ የንግግር / የቋንቋ ቴራፒስት/ወጌሻ  ወ.ዘ.ተ  ባለሙያዎችን ካሉ ማሳተፍ   የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን፣ የማስተማሪያ ዘዴዎችን፣ የውስጥ ለውስጥ መንገዶችንና የመግባቢያ መንገዶችን  ተደራሽ ማድረግ በአለም ላይም ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ልጆች በተለዩ ት/ቤቶች ይማሩ ነበር ፡፡  ይሁን እንጂ ከቅር ጊዜ  ወዲህ እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች በአካባቢያቸው  በሚገኝ መደበኛ የመማሪያ ትምህርት ቤት ውስጥ  በተሳካና ዉጤታማ በሆነ  ሁኔታ በመማር ላይ ይገኛሉ ፡፡  ይህ የሚሆነው ግን ተገቢ የድጋፍ አገልግሎቶች እና የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች መኖራቸውን በማረጋገጥ በው፡፡  ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸውን ልጆች አካል ጉዳት አልባ ከሆኑ  እኩዮቻቸው ጋር በተመሳሳይ ትምህርት ቤት እንዲማሩና  በተመሳሳይ እንቅስቃሴ እንዲሳተፉ ማስቻል የልጆቹን  ማህበራዊ ክህሎቶች ና ጓደኝነትን ለማዳበር ወሳኝ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ ፡፡ በኢትዮጵያም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ተደራራቢ የአካል ጉዳት ያለባቸው ልጆች ወደ ት/ቤት የመምጣት ዕድል አልነበራቸውም፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በክልሎች በተቋቋሙ የአካተቶ ት/ት የድጋፍ መስጫ ማዕከላት ውስጥ መኖራቸውን ሪፖርቶች ያሳያሉ፡፡ ስለሆነም ይህ አጭር ጽሁፍ የተዘጋጀው ትምህርት ቤቶች ተደራራቢ የአካል ጉዳት ማለት ምን ማለት እንደሆነ እና ለእነዚህ ልጆች ሊደረግ ስለሚገባው ድጋፍ ፍንጭ ለመስጠት ነው፡፡ 

አካታች ስፖርት ውሹ ስፖርትን አይነስውራንን በማካተት የሚያሰለጥነው ወጣት #ኢቢሲ ሼር ማድረግ አይዘንጉ አካታችነትን በተግባር! @inclusiveafar

የሚጥል ህመም ያለባቸውን ሰዎች ለማገዝ መደረግ ስለሚገባው ጥንቃቄ በሰለሞን ግዛቸው

ያለ ሁለት እጆች መኪና መንዳት አጃኢባ ያሲን በተፈጥሮ ሁለት እጅ የሌላት አጃኢባ ያሲን #driving_without_arms @inclusiveafar

አካል ጉዳት መኖር አለመቻል አይደለም። የሰው ልጅ እንዳለው በርካታ ልዩነቶች ፣ ችሎታዎችም በተለያየ መንገድ ይገለፃሉ። የአካል ጉዳት ያላቸውን ወገኖች ከፊት ያሉ በርካታ መሰናክሎችን ካስወገድንላቸው፣ ለአለማችን ጠቃሚ የሆነ በርካታ ነገሮችን ማበርከት ይችላሉ። @inclusiveafar

Inclusive schools mean ordinary (regular) schools open to all children and students regardless of poverty, gender, ethnic backgrounds, language, learning difficulties and impairments. In inclusive schools teachers find ways to know their students, to identify diverse needs of learners, and to provide appropriate support according to the needs.

ሰለ ADHD አጭር ገለፃ #MoH @inclusiveafar
+1
ሰለ ADHD አጭር ገለፃ #MoH @inclusiveafar