Yoni Soccer [ ዮኒ ]
Open in Telegram
የተለያዩ እግር ኳስ ነክ መረጃዎች የሚቀርቡበት ➜ ለሀሳብ እና አስያየት በዚህ Link ይጠቀሙ ► @yoni_tade
Show more5 030
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
5 030
🚨አርሰናል ለኤሚል ስሚዝ ሮው የውሰት ዝውውር ጥያቄ ቀርቦለት ውድቅ አድርጓል፤
ለተጨዋቹ የውሰት ዝውውር ጥያቄ ያቀረበው የዳቪድ ሞይሱ ዌስትሃም ነበር፤
ተጨዋቹ የማይክል አርቴታ እቅድ አካል እንደሆነና በመድፈኞቹ ቤት ለመቆየት ፍቃደኛ እንደሆነ ታውቋል።
✍️ [ Fabrizio Romano ]
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ሞሀመድ_ሳላህ
ግብፅ ከጋና ጋር በነበራት ጨዋታ ላይ ጉዳት አስተናግዶ የነበረው ሳላህ ለምን ያህል ጊዜ ከሜዳ እንደሚርቅ ታውቋል፤
የግብፅ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ባወጣው መረጃ ሳላህ ያጋጠመው ጉዳት በታፋው አካባቢ የጡንቻ መሳሳብ እንደሆነ ገልጿል፤
በዚህም ም/ት ሳላህ ቀጣይ ግብፅ የምታደርጋቸው ሁለት መርሀ ግብሮች እንደሚያልፉት ታውቋል፤
የሊቨርፑሉ ኮከብ ግብፅ ከኬፕ ቨርዴ ጋር የምታደርገው የመጨረሻ የምድብ ጨዋታ እና ወደ 16ቱ ዙር የምታልፍ ከሆነ በ16ቱ ዙር የምታደርገው ጨዋታ ያልፉታል።
📲 | @yonj_tade |
5 030
#ኤሚል_ስሚዝ_ሮው
አርሰናል ለእንግሊዛዊው አማካይ ኤማል ስሚዝ ሮው የውሰት ዝውውር ጥያቄ ቀርቦለት ውድቅ አድርጓል፤
ለተጨዋቹ የውሰት ዝውውር ፕሮፖዛሉን አቅርቦ ውድቅ የተደረገበት የዴቪድ ሞይሱ ዌስትሃም ነው፤
መድፈኞቹ የጨዋታ ጊዜው የተገደበውን ወጣቱን አማካይ በውሰት የመልቀቅ ሃሳብ የላቸውም፤
ስሚዝ ሮው የአሰልጣኙ ማይክል አርቴታ ዕቅድ አካል እንደሆነ የተነገረ ሲሆን እርሱም ቢሆን በአርሰናል ለመቆየት ደስተኛ ነው።
📲 | @yoni_tade |
5 030
⌚️ | ተጠናቀቀ |
◉ #ጋና 1-2 #ኬፕ_ቨርዴ
⚽️ጂኩ 56' ⚽️ሞንቲዬሮ 17'
⚽️ሮድሪጌስ 90+2'
✔️ ኬፕ ቨርዴ በጥቋቁር ኮከቦቹ ላይ አስገራሚ ድል ተቀዳጅታ ምድብ ሁለትን መምራት ጀምራለች፤
⚠️ጎሎቹን በComment ላይ⚠️
📲 | @yoni_tade |
5 030
⌚️ | ተጠናቀቀ |
◉ #ኤሲ_ሚላን 3-1 #ሮማ
⚽️አድሊ 11' ⚽️ፓሬዴስ 69'
⚽️ዥሩድ 36'
⚽️ኀርናንዴዝ 84'
✔️ ሚላን Top 4 ውስጥ ለመጨረስ የሚያደርገውን ፍልሚያ አጠናክሮ ቀጥሎበታል፤
⚠️ጎሎቹን በComment ላይ⚠️
📲 | @yoni_tade |
5 030
⌚️ | ተጠናቀቀ |
◉ #ሌንስ 0-2 #ፒ_ኤስ_ጂ
⚽️ባርኮላ 30'
⚽️ምባፔ 89'
✔️ ፒ.ኤስ.ጂ የፈረንሳይን ሊግን በ8 ነጥቦች ልዩነት እየመራ ይገኛል፤
📲 | @yoni_tade |
5 030
⌚️ | ተጠናቀቀ |
◉ #ሪያል_ማድሪድ 4-1 #ባርሴሎና
⚽️ቪኒሰሽ 7' 10' 39' ⚽️ሌዋንዶስኪ 33'
⚽️ሮድሪጎ 64'
🚨⚪️🏆OFFICIAL: ሪያል ማድሪድ የ2022/23 ስፔን ሱፐር ካፕ አሸናፊ ሆኗል
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ግብፅ_አቻ_ወጣች
ግብፅ በኮትዲቯሩ አፍሪካ ዋንጫ መክፈቻ ጨዋታዋ ነጥብ ጥላለች፤
ፈርኦኖቹ ከሞዛምቢክ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 2-2 በሆነ ውጤት ጨርሰዋል፤
የፈርኦኖቹን ጎሎች ሞሀመድ እና ሞሀመድ ሳላህ ሲያስቆጥሩ ለሞዛምቢክ ዊቲ እና ሴሌሲዮ ባኡኬ አስቆጥረዋል፤
ግብፅ በቀጣይ ጋናን የምትገጥም ሲሆን ሞዛምቢክ ደግሞ ኬፕ ቨርዴን ትገጥማለች።
📲 | @yoni_tade |
5 030
#በአቻ_ተጠናቀቀ
በ21ኛው ሳምንት እንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ተጠባቂ ጨዋታ ማን.ዩናይትድ እና ቶተንሃም በአቻ ውጤት ተለያይተዋል፤
በኦልድ ትራፈርድ በተደረገው ይህ መርሀ ግብር ጥሩ ጨዋታ ታይቶበት 2-2 በሆነ ውጤት ተጠናቋል፤
የማን.ዩናይትድን ጎሎች ራስመስ ሆይለንድ እና ማርከስ ራሽፈርድ ሲያስቆጥሩ ለቶተንሃም ሪቻርሊሰን እና ቤንታኩር አስቆጥረዋል።
📲 | @yoni_tade |
5 030
#በአቻ_ጨርሰዋል...
በጉዲሰን ፓርክ የተደረገው የ21ኛው ሳምንት የኤቨርተን እና አስቶን ቪላ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቋል፤
0-0 በተጠናቀቀው ጨዋታ አስቶን ቪላ ከሊቨርፑል ጋር በነጥብ የሚስተካከልበት ዕድል አምልጦታል፤
ኤቨርተን የዘንድሮ ክስተት ከሆነው አስቶን ቪላ 1 ነጥብ አሳክቶ መውጣቱ በጥሩ ጎኑ የሚታይለት ነው፤
የጨዋታውን ውጤት ተከትሎም ኡናይ ኤምሬ በፕሪሚየር ሊግ ቆይታው ከ97 ጨዋታዎች በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ምንም ጎል ያልተቆጠረበት ጨዋታ መርቷል፤
አስቶን ቪላ በ43 ነጥብ 3ኛ ደረጃ የተቀመጠ ሲሆን ኤቨርተን በበኩሉ በ17 ነጥብ ከወራጅ ቀጠና በ1 ነጥብ ርቆ 17ኛ ተቀምጧል።
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ናይጄሪያ_ነጥብ_ጣለች
በ2023ቱ የኮትዲቯር አፍሪካ ዋንጫ ለአሸናፊነት የምትጠበቀው ናይጄሪያ በመጀመሪያ ጨዋታዋ ነጥብ ጥላለች፤
በአውሮፓ ትላልቅ ሊጎች የሚጫወቱ ኮከቦቿን ይዛ ኢኳቶሪያል ጊኒን የገጠመችው ናይጄሪያ 1-1 በሆነ ውጤት ጨዋታዋን ጨርሳለች፤
የናይጄሪያን ጎል ቪክቶር ኦስሚኀን ሲያስቆጥር ለኢኳቶሪያል ጊኒን ደግሞ አይባን ኤዱ አስቆጠጥሯል፤
⚠️የጨዋታውን ጎሎች በComment ላይ⚠️
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ማን_ዩናይትድ_እና_ማርሻል...
ማን.ዩናይትድ የሳሳውን የፊት መስመሩን ለማጠናከር የተለያዩ የአጥቂ መስመር ተጨዋቾችን እንደ አማራጭ እየተመለከተ ይገኛል፤
ከመመልከት ባለፈም የኦልድ ትራፈርዱ ክለብ በስም ካልተጠቀሱት እነዚህ የተለያዩ አጥቂ መስመር ተጨዋቾች ወኪሎች ጋር ንግግር አድርጓል፤
ከንግግር ባለፈ ወደፊት እንዳይገፋበት መሰናክል የሆነበት የአንቶኒ ማርሻል ቆይታ ጉዳይ ነው፤
አንቶኒ ማርሻል በመጪው ክረምት ኮንትራቱ የሚጠናቀቅ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ክለቡ አሁን ክፍት በሆነው የጥር ዝውውር መስኮት ሊሸጠው የተለያዩ ጥረቶችን እያደረገ ይገኛል፤
የዩናይትድ ጥረት እስካሁን ድረስ አልሳካ ያለ ሲሆን ለዚህም ም/ቱ ማርሻል ከፈላጊዎቹ እየቀረቡለት ያሉትን ጥያቄ እየተቀበለ ባለመሆኑ ነው፤
የተለያዩ ምንጮችም ማርሻል በጥሩ የዝውውር መስኮት ዩናይትድን መልቀቅ እንደማይፈልግና እስከ ሰኔ መቆየት ፍላጎቱ እንደሆነ እየገለፁ ይገኛሉ፤
ማን.ዩናይትድ ማርሻልን እስካልሸጠ ድረስ አዲስ አጥቂ ወደ ክለቡ ማምጣት የሚከብደው ሲሆን አሁን ባለው አካሄድም በዚህ ወር አዲስ አጥቂ የማስፈረሙ ነገር አጠራጣሪ ነው፤
ፈረንሳዊው አጥቂ ከቀያይ ሴጣኖቹ ጋር ኮንትራቱን የማደስ እድሉ ጠባብ በመሆኑ እስከ መጪው ክረምት ቆይቶ በነፃ ዝውውር የፈለገውን ክለብ መርጦ የመቀላቀል እድሉ ሰፊ ነው።
✍️ [ FABRIZIO ROMANO ]
📲 | @yoni_tade |
5 030
አዘጋጇ የመክፈቻ ጨዋታዋን አሸነፈች!
የ2023ቱ አፍሪካ ዋንጫ አዘጋጅ ሀገር ኮትዲቯር የመጀመሪያ ጨዋታዋን አሸንፋለች፤
ከጊኒ-ቢሳው ጋር የመክፈቻ ጨዋታዋን ያደረገችው ኮትዲቯር 2-0 በሆነ ውጤት ነው ማሸነፍ የቻለችው፤
ኮትዲቯርን አሸናፊ ያደረጓትን ጎሎች ሴኮ ፎፋና እና ዣን ፊሊፔ ክራሶ አስቆጥሯል፤
ኮትዲቯር በቀጣይ ከናይጄሪያ ጋር የምትገናኝ ሲሆን
⚠️ጎሎቹን በComment ላይ⚠️
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ማን_ዩናይትድ_ወደ_ቀጣዩ_ዙር...
ማን.ዩናይትድ በኤፌ ካፑ ወደ 4ኛው ዙር ማለፉን ዛሬ ምሽት አረጋግጧል፤
በDW ስቴዲየም ዊጋንን የገጠመው ማን.ዩናይትድ 2-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ወደ 4ኛው ዙር አልፏል፤
ማን.ዩናይትድን አሸናፊ ያደረጉትን ጎሎች ዲዮጎ ዳሎት እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ አስቆጥረዋል፤
ቀያይ ሴጣኖቹ በ4ኛው ዙር የኒው ፖርት ካውንቲ እና ኢስቴሌይህ አሸናፊን የሚገጥሙ ይሆናል።
⚠️የጨዋታውን ጎሎች በComment ላይ⚠️
📲 | @yoni_tade |
5 030
#FA_CUP...
የኤፌ ካፕ 4ኛ ዙር ጨዋታዎች ድልድል የተደረገ ሲሆን ተጠባቂ የሆኑት ጨዋታዎች:
#ቶተንሃም ከ #ማን_ሲቲ
#ቼልሲ ከ #አስቶን_ቪላ
#ሊቨርፑል ከ #ኖርዊች/#ብሪስቶል_አሸናፊ
#ኒውፖርት/#ኢስትሌህ ከ #ዊጋን/#ማን_ዩናይትድ
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ጆሹዋ_ኪሚች ወደ #ማን_ሲቲ...?
የ28 አመቱ ጀርመናዊው አማካይ ጆሹዋ ኪሚች በፔፕ ጋርዲዮላ እይታ ውስጥ ስለመግባቱ እየተሰማ ይገኛል፤
ኪሚች ከባየር ሙኒክ ጋር ያለው ኮንትራት ሊጠናቀቅ እየተቃረበ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ይቆያል ወይስ አይቆያም በሚለው ላይ የተለያዩ ሃሳቦች እየተነሱ ይገኛል፤
አሁን ክፍት በሆነው የጥር ዝውውር መስኮት ላይም የተለያዩ ትላልቅ ክለቦች በኪሚች ላይ ፍላጎት እንዳላቸው የሚገልፁ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፤
የፔፕ ጋርዲዮላው ማን.ሲቲም የኪሚች ፈላጊ ናቸው ተብለው ስማቸው ከተነሱ ክለቦች ውስጥ አንዱ ነው፤
እንደ ፋብሪዚዮ ሮማኖ ከሆነ ግን በዚህ የጥር ዝውውር መስኮት ጆሹዋ ኪሚች ወደየትም እንደማይዘዋወር ተናግሯል፤
በተጨማሪም ጆሹዋ ኪሚች ከባየር ሙኒክ ጋር በኮንትራት እድሳት ላይ ያልጀመረው ሙኒክ አሁን ትኩረቱ በዝውውሮች ላይ በመሆኑ እንደሆነ ተናግሯል።
✍️ [ FABRIZIO ROMANO ]
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ካዛሚዬሮ እና #ማን_ዩናይትድ...
የ31 አመቱ ብራዚላዊው አማካይ ካዛሚዬሮ በኦልድ ትራፈርድ ከሚኖረው ቀጣይ ቆይታ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ጭምጭምታዎች እየተነሱ ይገኛሉ፤
ለዚህ ጭምጭምታ መሰረት የሆነው የክለቡ አዲስ ባለሀብቶች INEOS እና ሰር ጂም ራትክሊፍ እድሜያቸው የገፉ እና ከፍተኛ ደሞዝ ላይ ያሉ ተጨዋቾችን በቀጣይ ክረምት እንዲለቁ ሊያደርግ ነው የሚል ወሬ መሰማቱን ተከትሎ ነው፤
ይህ ነገር ታዲያ ከወሬ ደረጃ ባለፈ አሁን ላይ ተጨባጭነት የሌለው ነገር እንደሆነ የዝውውር ኤክስፐርቱ ፋብሪዚዮ ሮማኖ ተናግሯል፤
ሮማኖ በጭምጭምታው ላይ ሲናገር ካዛሚዬሮ አሁን በቀያይ ሴጣኖቹ ቤት ያለበት የከፍተኛ ደሞዝ ኮንትራት ለሰር ጂም ራትክሊፍ መሰናክል እንደሆነ የሚያሳይ ነገር የለም ብሏል፤
ካዛሚዬሮ በ2022 ክረምት ወደ ኦልድ ትራፈርድ ከመጣ በኋላ በመጀመሪያ አመቱ ጥሩ መንቀሳቀስ ችሎ የነበር ቢሆንም ዘንድሮ ግን በጉዳት እና መሰል ነገሮች እንደተጠበቀው እየተንቀሳቀሰ አይገኝም።
✍️ [ FABRIZIO ROMANO ]
📲 | @yoni_tade |
5 030
#ካዛሚዬሮ እና #ማን_ዩናይትድ...
የ31 አመቱ ብራዚላዊው አማካይ ካዛሚዬሮ በኦልድ ትራፈርድ ከሚኖረው ቀጣይ ቆይታ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ጭምጭምታዎች እየተነሱ ይገኛሉ፤
ለዚህ ጭምጭምታ መሰረት የሆነው የክለቡ አዲስ ባለሀብቶች INEOS እና ሰር ጂም ራትክሊፍ እድሜያቸው የገፉ እና ከፍተኛ ደሞዝ ላይ ያሉ ተጨዋቾችን በቀጣይ ክረምት እንዲለቁ ሊያደርግ ነው የሚል ወሬ መሰማቱን ተከትሎ ነው፤
ይህ ነገር ታዲያ ከወሬ ደረጃ ባለፈ አሁን ላይ ተጨባጭነት የሌለው ነገር እንደሆነ
