en
Feedback
Bisrat pre-primary; primary and middle school in Ethiopia.

Bisrat pre-primary; primary and middle school in Ethiopia.

Open in Telegram
1 290
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
1-. አልበርት አንስታይን አንስታይን ከ1879-1955 የኖረ ታላቅ የሳይንስ ሊቅ ነበር። በተለይ ሁለት ግኝቶቹ የሳይንስ እይታችንን በእጅጉ የቀየሩ ሲሆን አንስታይን ምድራችን ካፈራቻቸው የሳይንስ ሊቆች ውስጥም ሆነ ወደፊት ከሚወለዱት ውስጥ ተወዳዳሪ አይገኝለትም የሚባል ብርቅዬ ሳይንቲስት ነው። አንስታይን በልጅነቱ ዳይስሌክሊስ (ሲያነቡ ወደ ግራ የሚያነቡ) የነበረ ሲሆን በትምህርቱ ደካማ በመሆኑ አስተማሪዎቹ ደደብ አድርገው ይገምቱት ነበር። በ15 ዓመቱ ትምህርቱን አቁሞ ከዓመት በኋላ ዙሪክ የሚገኝ አንድ ፖሊ ቴክኒክ ለመግባት አመልክቶ የመግቢያ ፈተናውን ወድቋል። ይህ ሰው ግን በፊዚክስ ንድፈ ሃሳብ ዓለምን በመቀየሩ የኖቬል ሽልማት ለመሸለም የበቃ ድንቅ ሳይንቲስት ነው። 2- ቤንጃሚን ፍራንክሊን ይህ ሰው የሂሳብ ትምህርት አይሆነውም ነበር። እናም አባቱ ከትምህርት ቤት አስወጥቶ ሻማና ጧፍ ሲያሰራው አደገ። ነገር ግን ይህ ሰው አሜሪካ ካፈራቻቸው ታላላቅ ሰዎች አንዱ በመሆን ታዋቂ ፖለቲከኛ፣ ሳይንቲስት፣ ጸሐፊ እና የፔንሲልቫኒያ ፕሬዚዳንትና የአሜሪካ መስራች አባት ለመባል የበቃ ሰው ነው። 3- ቻርለስ ዳርዊን ወጣቱ ዳርዊን በትምህርቱ በመድከሙ አባቱ "አንተ ከአደን እና ውሻ በስተቀር የምትወደው ነገር የለም፤ ስለዚህ ለራስህም ሆነ ለቤተሰብ ውርደት እንዳትሆን" ብሎ ከትምህርት ቤት አስወጣው። የህክምና ትምህርት ሞከረ አስጠላው። የሃይማኖት ትምህርትም ሞክሮ ነበር አልሆነለትም። ብዙውን ግዜውን ግን ከስፖርተኞች ጋር ነበር የሚያጠፋው። ይህ ሰው ግን በመጨረሻ አጠቃላይ የስነ-ህይወት ሳይንስን ለመቀየር ችሏል። 4- ሴናተር ኤድዋርድ ኤም ኬኔዲ ይህ የማሳቹሴትስ ሴናተር በአንድ ወቅት ለአሜሪካ ፕሬዚዳንትነት ሁሉ ተወዳድሯል። ግን ፈተናውን ጓደኛው ሲፈተንለት ተይዞ ከሚማርበት ሃርቫርድ ዩኒቨርስቲ ተባርሮ ነበር። 5- ሰር ዊንስተር ቸርችል ይህ ሰው ታላቅ እንግሊዛዊ ፖለቲከኛ፣ ገጣሚ፣ ደራሲና ሰዓሊ ሲሆን እንግሊዝን በአንደኛ እና ሁለተኛ የዓለም ጦርነት በተለያየ የመንግስት ስልጣን ደረጃ የመራ ታላቅ የፖለቲካ ሰው ነው። (በአገራችን መዲና አዲስአበባ ጎዳና በስሙ ተሰይሞለታል) ቸርችል ይህቺ ምድር ካፈራቻቸው ድንቅ የፖለቲካ ሰዎች አንዱ ቢሆንም በትምህቱ ደካማ ስለነበር ሮያል የውትድርና ኮሌጅ ለመግባት ከአንዴም ሁለት ግዜ ተፈትኖ በመውደቁ መግባት አልቻለም ነበር። 6- ቶማስ ኤድሰን ይህ ታላቅ ፈላስፋ ትምህርት ቤት የሄደው ለሶስት ወራት ብቻ ነበር። ምክንያቱም በስምንት ዓመቱ አስተማሪው "ደደብ" ብሎ ስለሰደበው እናቱ ከትምህርት ቤት አውጥታ ቤት ውስጥ አስተማረችው። በዘጠኝ ዓመቱ ይሞክራቸው የነበሩት ነገሮች ከእናቱ አቅም በላይ ሆኖ ተገኝቷል። ቶማስ ኤድሰን በህይወት ዘመኑ አንድ ሺህ አዳዲስ ግኝቶችን የፈለሰፈ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ የኤሌክትሪክ ብርሃን እና ሸክላ ማዘፈኛ ሲኖሩበት ያሻሻላቸው ነገሮች ደግሞ ፊልም ማሳያ፣ ቴሌፎን ይገኙበታል። 7- አይዛክ ኒውተን ይህ ሰው ደካማ ውጤቶች ስለነበሩት ከትሪንቲ ኮሌጅ ሆነ ከካምብሪጅ ዩኒቨርስቲ ሲመረቅ የክብር ወይም የማዕረግ ተመራቂ አልነበረም። ነገር ግን በታሪክ ከታወቁት ታላላቅ የሳይንስ ፈጣሪዎች አንዱ በመሆን የዘመኑ ሳይንስ በእርሱ ስራዎች ላይ ለመመርኮዝ በቅተዋል። (በመለሰ አበበ ተሊላ)        

የትምህርት ክፍሎች ተግባርና ኃላፊነት 1. የትምህርት ክፍሉን አመታዊ እቅድ ያዘጋጃል ። 2.በስሩ ያሉ መምህራንን የእቅድ ዝግጅት ይገመግማል 3.በስሩ ያሉ መ/ራንን የማስታወሻ አዘገጃጀትይገመግማል 4.መ/ራን ያዘጋጁት የት/ት ዕቅድና ማስታወሻ የት/ቱን አላማና ግብ የሚያሳካ መሆኑን ይገመግማል። 5.የተዘጋጀው ዕቅድ ከት/ቱ አላማ ጋር የተጣጣመ መሆኑን ያረጋግጣል 6.በት/ት ክፍሉ ስር ያሉ መምህራን የእርስ በእርስ የክፍል ምልከታ እንድያደርጉ ያስተባብራል፡፡ 7.በት/ት ክፍሉ ስር ያሉ መምህራን በ table of specification  መሰረት ጥራት ያለው ሙከራዎችንና ፈተናዎችን ማዘጋጀታቸውንና ፈተናውን በአግባቡ እርማት መሰጠቱን ይከታተላል 8.በት/ት ክፍሉ ስር ያሉ መምህራን የውጤት ትንተና እንድሰሩ በማድረግና በትንተናው መሰረት ዝቅተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ወላጆችን በማነጋገር የማጠናከሪያ ት/ት እንድያዘጋጁ ያደርጋል፡፡ 9.በሰልፍ ስነ-ስርዓት ላይ በመገኝት ያስተባብራል 10.የጥያቄና መልስ ውድድሮች በወጣላቸው መርሃ ግብር መሰረት እንድከናወን ያደርጋል 11.የዲፓርትመንት እና የአቻ ፎረም ውይይቶች ሳይቆራረጡ እንድካሄዱና በወቅቱ ሪፖርት እንድደረግ ያደርጋል፡፡ በት/ት ክፍሉ ተግባራዊ ጥናትና ምርምር እንድሰራና እንድተገበር ያደርጋል የተማሪዎችን ካውንስልና ፓርላማ ያስተባብራል 12.የክ/ጊዜ ብክነትን ይቆጣጠራል ት/ቤቱ በሚጠራቸው ስብሰባዎች ላይ በግምባር ቀደምትነት ይገኛል፡፡ በወጣው ሣምንታዊ ፕሮግራም መሰረት በስሩ ያሉ መምህራን ሁሉን አቀፍ የተማሪዎች ደህንነት እንድጠበቅ ክትትል ያደርጋል፡፡ 13.ከት/ቤቱ አመራሮች ጋር ተቀራርቦ ይሰራል እና የተማሪዎችን ባህሪና የመማር ሁኔታ ይከታተላል 14.ወርሃዊ ሪፖርቶችን ያዘጋጃል በወቅቱ ሪፖርት ያደርጋል 15.በወላጆች ስብሰባ/ጉባኤ ላይ ይገኛል የተማረፊዎች ደብተር እርማት ይከታተላል 16.በስሩ ያሉ መ/ራን በፈጠራ ስራ ላይ እንድሳተፉ ያደርጋል 17.የት/ክፍሉ አባላት መርጃ መሳሪያዎችን እንድያመርቱና እንድጠቀሙ ያደርጋል 18.በት/ቤቱ የሚሰጠውን የተማሪዎች ምገባ ያስተባብራል።

የክፍል ኃላፊ መምህራን ተግባር እና ኃላፊነት በመማር ማስተማር ምክትል ርዕሰ መምህር ተመርጦ  ለአንድ ክፍል ኃላፊ በመሆን የሚከተሉትን ተግባራት ያከናዉናል፡፡ ክፍሉ ለመማር ማስተማር ምቹ እንድሆን ያደራጃል፡፡የክፍል አለቃ ተማሪዎችን ያስመርጣል፡፡ ጠዋት አንደኛዉ ክፍለ ጊዜ ከመጀመሩ በፊት እና ከሰዓ ትስድስተኛዉ ከመጀመሩ በፊት ተማሪዎችን ስም ይጠራል፡፡ ተማሪዎች የክፍል መተዳደሪያ ደንብ እንድያወጡ ድጋፍ ያደርጋል፡፡ የተማሪዎችን ስነ-ምግባር በተማሪዎች የክፍል መተዳደሪያ መሰረት ክትትል በማድረግ አስፈላጊዉን እርምት ይሰጣል፡፡ የክፍል ተጠሪ መምህር ሳያወቀዉ ምንም አይነት የተማሪ ጉዳይ ወደ አስተዳደርም ሆነ ወላጅ መላክ እንደሌለበት ለመምህራን ተገቢዉን የአሰራር ሂደት ያሳዉቃል፡፡ የክፍሉን ንጽህና በመቆጣጠር ተገቢዉን ክትትል በማድረግ ንጹህና ጽዱ እንድሆን ያደርጋል፡፡ በስሩ የሚተዳደሩ ተማሪዎች የሰልፍ ስነ-ስርዓት አክብረዉ በተገቢዉ ሰዓት ጸጥታ አክብረዉ እንዳከናወኑ በክፍል ውስጥ ፉክክር ለመፍጠር በቡድን በቡድን በመመደብ እርስበርሳቸው እንዲወዳደሩ በማድረግ ያስተባብራል፡፡ በየሳምንቱ መጨረሻ የቀሪ ተማሪዎች ስም ዝርዝር እና ቁጥር ለስርዓተ ት/ት ም/ር/መ/ር ወይም ለተማሪዎች ሪከርድ ገቢ ያደርጋል፡፡ በየመንፈቅ ዓመቱ በታቀደው ዕቅድ መሰረት የተማሪዎች ሮስተር እና ሰርተፊኬት ይሰራሉ፡። የተሰራውን የተማሪዎች ሮስተርና ሰርተፍኬት ለት/ቤቱ በወቅቱ ገቢ ማድረግ፡፡ በየመንፈቅ አመቱ እና በየአመቱ የት/ቤት መዝጊያ ቀን በመገኘት ለየተማሪዎች ውጤታቸው ይሰጣሉ፡። የተማሪዎችን ውጤትና ስነ-ምግባር በተመለከተ በፕሮፋይል ይይዛሉ፡፡ የክፍል ወተመህ ያደራጃሉ፣ ይመራሉ ይሰበስባል፣ በየወሩ ያወያያሉ፡፡ የትምህርት ጊዜን በሚያባክኑ እና በጊዜ ወደ ትምህርት በማይመጡ ተማሪዎች ላይ ክትትል በማድረግ አስፈላጊውን የማስተካከያ እርምት እንዲያደርጉ ያደርጋል፡፡ የስነምግባር ችግር ያለባቸውን መረጃ በፅሁፍ በመያዝ ወላጅ ወይም  አሳዳጊ በማስጠራት በወቅቱ ማሰፈረም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ለትምህርት ቤቱ አስተዳደር እስከ መጨረሻ እንዲከታተል ማስደረግ። ስም የሚጠራቸው ተማሪዎች የትምህርት ቤቱን የደንብ ልብስ በተገቢው አኳኋን ለብሶ መምጣቱን መቆጣጠር፡፡ ከክፍል ተማሪዎች ጋር  በወር አንድ  ጊዜ በትምህርት ቤቱ መማር ማስተማር እንዲሁም አስፈላጊ በሚባሉ ዕርሶች ላይ ውይይት ማካሄድ፣ መፍትሄ ማፈላለግ፣አስፈላጊም ከሆነ የሚመለከተውን አካል ጋብዞ ውይይት ማድረግ እንዲቻል ምቹ ሁኔታ መፍጠር፡፡

ለርዕሰ መምህርነት ለመወዳደር ያመለከታችሁ መምህራን ዛሬ 10:00 ሰዓት ኦሬንቴሽን ለመውሰድ ርዕሰ መምህር ቢሮ ተገኙ።

ዛሬ ባይሽ ኮልፌ የተባለ በጎ አድራጊ የወጣቶች ስብስብ ግምቱ 16,000 ብር የሚያወጣ የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ ለሴት ተማሪዎቻችን ለግሰውልናልና ክብረት ይስጥልን።
ዛሬ ባይሽ ኮልፌ የተባለ በጎ አድራጊ የወጣቶች ስብስብ ግምቱ 16,000 ብር የሚያወጣ የሴቶች ንፅህና መጠበቂያ ለሴት ተማሪዎቻችን ለግሰውልናልና ክብረት ይስጥልን።

ግርማዊነታቸው! —— "በፎቶግራፍ ላይ እንደሚታዩት ሳይሆን ጠጋ ብሎ ለተመለከታቸው ሰው ጃንሆይ በጣም ረቂቅ ሆነው ይታያሉ።" የንጉሱ የእረፍትም ሆነ የስራ ሰዓቶች በፕሮግራም የተጠበቁ ነበሩ። ማለዳቸው በፀሎት ስነስርዓት ከተጀመረ በኋላ የሰውነት ማጠንከሪያ እንቅስቃሴ ያ፣ደርጋሉ፣ የፃም እለት ካልሆነ በቀር ቁርስ ይመገባሉ፤ የአለም ዜናዎችን ይከታተላሉ። ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ወደ ፅህፈት ቤታቸው ያመራሉ። በስድስት ሰዓት ከፅ/ቤታቸው ወጥተው ለአንድ ሰዓት ያህል ቆመው የህዝብ አቤቱታ በመስማት ይግባኝ የሌለው ፍርድ ይሰጣሉ። ወደ መኖሪያቸው ኢዮቤልዩ ቤተመንግስት በማምራት ምሳ ይመገባሉ፣በዚያም ለአንድ ሰዓት ረፍት አድርገው በዘጠኝ ሰዓት ይመለሳሉ። አብዛኛውን ጊዜ መሸት ሲል በአውቶሞቢላቸው ሆነው ት/ቤቶችን፣ ሃኪም ቤቶቹን፣ ወታደራዊ ሰፈሮችንና የስራ እቅድና ጅምሮችን ይጎበኛሉ። ማታ ላይ በቤተ መንግስት የሚጠበቁትን እንስሳት ራሳቸው ቀርበው የመመገብ ልምድ ነበራቸው። እራት ላይ እጅግ ቀለል ያለ ነገር የመመገብ ልምድ ሲኖራቸው በንባብ ቤታቸው የመቆየትና ንባብና ልዩ ልዩ የፅህፈት ስራ ሲከውኑ ያመሻሉ። ጃንሆይ በቀን ከ5 ሰዓት የዘለለ እንቅልፍ የላቸውም። ከልጅነት ጀምሮም ምንም አይነት ሱስ (ሲጋራ፣አልኮል)አልነበረባቸውም። የሚመገቡትም በመጠኑ በመሆኑ ሰውነታቸው የቀጨጨ ነው። ሰዎች "እንደወፍ የቀለሉ" በሚል ይገልፇቸው ነበር። ------------- ቴሌስታር ፖርሌም ጋዜጣ The Life Style of HIM ንባብ:— "ንጉሰ ነገስቱ" በጌታቸው ሃሰን ( 1984)