805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች
✅ በእኛ ላይ ስላለ ወይም በምናቃቸው ላይ
በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን
📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው
📖 መዝሙር 34: 15:17
የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና። ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።
Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ቅዳሜን ስለፈወስ
✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች
✅በተለይ በዚህ ሰአት ሀገራችን እና በአለም ላይ በብዛት በተሰራጨው covid 19 ስለተያዙ ሰዎች
ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸው ይህም በሽታ ከአገራችን እና ከአለም እንዲጠፋ በህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል 🙏
📖 የያዕቆብ መልእክት 5
14፤ ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። 15፤ የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ መንፈስቅዱስ
✅ በጀመርነው የፍልሰታ ፆም ከፍ ወደ አለ ወደ መንፈሳዊ እድገት መውጣት እንዲሆንል እንዲረዳን መንፈስ ቅዱስን እንለምንለን
📖 የዮሐንስ ወንጌል 14
26፤ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።
ሮሜ 1:17
ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና።
ጻድቅ በእምነት በህይወት ይኖራል በማየት ወይም በሚሰማው ወይም ከሁኔታ ሳይሆን የእግዚአብሔር ቃል እንደሚለው ማመን እንዲሁም ቃሉ እውነት እንደሆነ እርግጠኛ ሆነን በእምነት መናገር ከአንደበታችን ማውጣት በህይወታችን ላይ መናገር
2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 04
13 ነገር ግን፡— አመንሁ ስለዚህም ተናገርሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ያው አንዱ የእምነት መንፈስ ስላለን፥ እኛ ደግሞ እናምናለን ስለዚህም እንናገራለን፤
ያመነ ቃሉን ይናገራል ቃሉን
ያውጃል:: የተጻፈውን እናምናለን እንናገራለን::
እመን እንጂ አትፍራ ይለናል ቃሉ ስለዚህ በችግር ጊዜ እልፈራም ሰው ምን ያደርገኛል ጌታ ይረዳናል አሜን::
በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና አይዞህ አትፍራ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝኩህም ::
ሀሌሉያ የእግዚአብሔርን ያው ነው ለኢያሱ የተናገረው ዛሬም ለእኛ ይናገረናል ሁሌም ከእኛ ጋር ነውና በሚሆነው በሚገጥመን ውጣ ውረድ ሁሉ እግዚአብሄር ከእኔ ጋራ ነው :: እግዚአብሄር ከእኔ ጋር ከሆነ ማን ይቃወመናል ሁል ጊዜ አብሮነቱን ማሰብ ቃሉን ማመን ይሁንልን አሜን::
እንግዲህ እግዚአብሄር በቃሉ ብዙ ተናግሮናል ሁሌም ይናገረናል :: ቃሉ የሚለንን ነን በእምነት እናገር እናውጀው: :
ያለ እምነት እግዚአብሔር ማስደስት አይቻልም ይለናል ቃሉ::
እግዚአብሔር የሚደሰተው ቃሉ እንደሚለን ስናምና ስኖረው ነውና ዛሬ አባታችንን የምናስደስትበት የእምነትን ጸጋ በእጅጉ ያብዛልን: :
እንግዲህ ሁልጊዜ ታምነን፥ በእምነት እንጂ በማየት አንመላለስምና በሥጋ ስናድር ከጌታ ተለይተን በስደት እንዳለን የምናውቅ ከሆንን፥
ጌታ ሆይ ታምነህ ተሰማራ ይላል ቃልህና ቃልህ የሚለንን በማመን ባስቀመጥከን ስፍራ በእምነት እንድንሰማራ በእምነት የምንመላለስ ጸጋ በእምነት የምኖርበት በእምነት ይምናገለልበት በእምነት የምንወጣበት በእምነት ቃልህን የምንመሰክርበት በእምነት ስለአንተ የምናገርበት በህይወታችን እምነትንየምንገልጽበትብ የምንተገብርበት ጸጋ አቅም ብርታት ጉልበት ችሎታ በኢየሱስ ስም አፍስልን አሜን!!
ጌታ ሆይ እናመሰግንሃለን ስላሳለፍነው ቀን እጅግ አድርገን እንባርክሃለን ከምህረትህ እና ከቸርነትህ የተነሳ የሐምሌን ወር በሰላም አስጀምረኸን በብዙ ምስጋና ውስጥ አሳልፈኸን በድል እዚህ አድርሰኸናል እና እናመሰግንሃለን !
በዚህ ምሽት ብዙ ምስጋና ብዙ አምልኮ ብዙ ዝማሬ ይዘን እፊትህ ቀርበናል ምስጋናችን አምልኮአችን ዝማሬአችን ጥያቄዎቻችን ሁሉ በፊትህ ሞገስን አግኝተውልን ባርኮትህ እንዲበዛልን በልጅህ በጌታችን በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንለምንሃለን! መንፈስ ቅዱስ ሆይ አንተ አፅናኛችን ረዳታችን መሪያችን ነህ በዚህ ምሽት በመካከላችን በመገኘት አረስርሰን እያንዳንዱ ድርጊቶቻችን ፀሎታችን ልመናችን አምልኮአችን ምስጋናችን ቅንነት በተሞላ ቅን ልብ እንድናቀርብ ልባችንን እርዳው!!!
በጌታ በኢየሱስ ስም 🙏🏽🙏🏽🙏🏽
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ እምነት
ወደ ዕብራውያን 11
1፤ እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።
እግዚአብሄር ሆይ
መዝሙረ ዳዊት 145
15፤ የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ። 16፤ አንተ እጅህን ትከፍታለህ፥ ሕይወት ላለውም ሁሉ መልካምን ታጠግባለህ። 17፤ እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ ነው በሥራውም ሁሉ ቸር ነው። 18፤ እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፥ በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው። 19፤ ለሚፈሩት ምኞታቸውን ያደርጋል፥ ልመናቸውንም ይሰማል ያድናቸዋልም።
እግዚአብሔር ሆይ በአንተ ተስፋ እናደርጋለን አለማችንን ይዘን የምህረት በር እናንኳኳለን ከበዛው በደል ሀጢያት አለማችንን ለመዳን ምህረትህን እንጠይቃለን:: እግዚአብሔር አባታችን ሆይ የሁሉ የበላይ መታመኛችን ተስፋችን አንተ ነህ በደልን ክፋትን ሁሉ ይቅር ብለህ አለም ካለችበት ጭንቅና መከራ ግራ መጋባት ሞት ጨለማ ሁሉ ነጻ አውጣት ብለን በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እንጸልያለን::
እግዚአብሔር ሆይ ክብር በአለማችን ያድር ዘንድ ማዳንህን ተረድቶ አንተን በማወቅ በመረዳት እንድትኖር በሰማይ ያለው ምህረትህ እንዲሁም በምድር ይሁን:: እውነትህ ይዘራ ይብዛ ፍቅር ይብዛ መልካም አስተሳስብ በምድር ይብቀል መልካም በማድረግ የምትታወቀው አንተ ብቻ ነህና መልካምነትህ በምድራችን ይገለጥ ምህረትህ ምድርን ይሸፍን ፍቅርይ ይግዛ ፍቅርህ ያስተዳድር የክርስቶስ ብርሀን በአለማችን ይብራ የትንሳኤው ብርሀን ሞትን ድል አድርጎ የተነሳው የኢየሱስ ብርሀን በምድራችን ይብራ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ አለማችን
✅ በብዙ አቅጣጫዎች እየቆሰለችል ላለችው ይቺ አለም እኛ የእግዚአብሔር ልጆች በህብረት ሆነን ወደ ፀጋው ዙፋን እናቀርባታለን
🙏
📖 መዝሙረ ዳዊት 85(9-12 )
ነገር ግን ክብር በምድራችን ያድር ዘንድ ማዳኑ ለሚፈሩት ቅርብ ነው፤ ምሕረትና እውነት ተገናኙ፤ ጽድቅና ሰላም ተስማሙ። እውነት ከምድር በቀለች፥ ጽድቅም ከሰማይ ተመለከተች። እግዚአብሔርም በጎ ነገርን ይሰጣል፥ ምድራችንም ፍሬዋን ትሰጣለች።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ስለ እግዚአብሔር ዘላለማዊ ፍቅር
✅ፍቅሩ ከገባን በላይ እንዲገባን
✅ ይህንን ፍቅር ያላወቁት ማወቅ እንዲሆንላቸው
✅በተወደድንበት ልክ መውደድን እንድንችል
በህብረት እንፀልያለን 🙏
ትንቢተ ኤርምያስ 31
3፤ እግዚአብሔርም ከሩቅ ተገለጠልኝ፥ እንዲህም አለኝ፡— በዘላለም ፍቅር ወድጄሻለሁ፤ ስለዚህ በቸርነት ሳብሁሽ።
አሜን አባ እናመሰግንሃለን ከምህረትህ የተነሳ ያለፈውን ሳምንት በሰላም እና በጤና አሳልፈን አዲሱን ሳምንት ጀምረናል ክብር ሁሉ ለአንተ ይሁን!
ዘመኑን ዋጁ እንዳልከን በተሰጠን የልጅነት ስልጣን ሳምንቱን በፍቅር በሰላም በመልካም ፍሬ እንዲሁም በምንፀልይባቸው ርዕሶች ሁሉ ዋጀነው !
ምህረትህን ተደግፈን አንንገዳገድም እንሻገራለን! ወዳየህልን ትንሳኤ እና ብርሃን እንገሰግሳለን ለጠላት ምክር እና ከንቱ ሴራ አንንበረከክም በደሙ የዋጀን ስለእኛ ሞቶልን እኛን ያቆመን የጠላትን ወጥመድ የሰባበረልን ያስመለጠን እድል ፈንታችን ኢየሱስ ነው!!! ክብር ሁሉ ለስምህይሁን!!!
🙏Thanksgiving Mondays 🙏
( ሰኞን በምስጋና)
✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን
✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን
✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው
በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን
📖 መዝሙረ ዳዊት 107: 20-22
ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው። ለሰው ልጆች ስላደረገው ተኣምራት ስለ ምሕረቱም እግዚአብሔርን ያመስግኑ፤ የምስጋና መሥዋዕትንም ይሠውለት፥ በእልልታም ሥራውን ይንገሩ።
2ኛ ነገሥት 20
1፤ በዚያም ወራት ሕዝቅያስ እስከ ሞት ድረስ ታመመ። ነቢዩም የአሞጽ ልጅ ኢሳይያስ ወደ እርሱ መጥቶ፡— እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡— ትሞታለህ እንጂ በሕይወት አትኖርምና ቤትህን አስተካክል፡ አለው። 2፤ ፊቱንም ወደ ግድግዳው መልሶ እንዲህ ሲል ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፡— 3፤ አቤቱ፥ በፊትህ በእውነትና በፍጹም ልብ እንደ ሄድሁ፥ ደስ የሚያሰኝህንም እንዳደረግሁ ታስብ ዘንድ እለምንሃለሁ። ሕዝቅያስም እጅግ አድርጎ አለቀሰ። 4፤ ኢሳይያስም ወደ መካከለኛው ከተማ አደባባይ ሳይደርስ የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ሲል መጣለት፡— 5፤ ተመልሰህ የሕዝቤን አለቃ ሕዝቅያስን እንዲህ በለው፡— የአባትህ የዳዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡— ጸሎትህን ሰምቻለሁ፥ እንባህንም አይቻለሁ፤ እነሆ፥ እፈውስሃለሁ፤ በሦስተኛውም ቀን ወደ እግዚአብሔር ቤት ትወጣለህ። 6፤ በዕድሜህም ላይ አሥራ አምስት ዓመት እጨምራለሁ፤ አንተንና ይህችን ከተማ ከአሦር ንጉሥ እጅ እታደጋለሁ፤ ስለ እኔም ስለ ባሪያዬም ስለ ዳዊት ይህችን ከተማ እጋርዳታለሁ።
አሜን ጌታ ሆይ ተመስገን የህዝቄልን ጸሎት ሰምተህ ሞትን ሽረህ በእድሜው ላይ 15 አመት የጨመርክለት እግዚአብሔር አባታችን ሆይ ዛሬም ለምናውቃቸው ለማናውቃቸው አንተ ግን ለምታውቃቸው ለተጨነቁ ሁሉ ተስፋ ላጡ ሁሉ በኢየሱስም እድሜ እንድትጨምርላቸው ጤናቸው ሙሉ እንዲሆን ታሪካቸው እንዲቀየር አዲስ ምእራፍ እንዲጀምሩ የአንተ ጉብኝት እንዲያገኛቸው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አጥብቀን ጸለይን ስሰማኸን እናመሰግንሀለን!!!
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌ቅዳሜን ስለፈወስ
✅በተለዩ በሽታዎች ስለተያዙ ሰዎች
✅በተለይ በዚህ ሰአት ሀገራችን እና በአለም ላይ በብዛት በተሰራጨው covid 19 ስለተያዙ ሰዎች
ከለይ ከሰማይ ፈውስ እንዲሆንላቸው ይህም በሽታ ከአገራችን እና ከአለም እንዲጠፋ በህብረት አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ይሰማናል 🙏
📖 የያዕቆብ መልእክት 5
14፤ ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። 15፤ የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌የእግዚአብሄርን ዕቃ ጦር ማንሳት እንዲሆን
✅ከጠላት ከሚመጣው ውጊያ ለማምለጥ
✅በሁሉ ስራ እና አገልግሎት ብቁ ለመሆን
✅በእውነት እና በነፃነት ለመኖር
በ ኤፌሶን 6 (13:17) የተዘረሩትን ዕቃ ጦሮችን እድናውቅ እንድናስታውስ እናም እንድንጠቀም ፀጋው እንዲበዛል በህብረት እንፀልያለን
🙏
📖ወደ ኤፌሶን 6
13፤ ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ።
14-15፤ እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤ 16፤ በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤ 17፤ የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው። 18፤ በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ፤
ትንቢተ ኢሳይያስ 62:2-5
ኢትዮጵያዬዬዬዬ
አሕዛብም ጽድቅሽን ነገሥታትም ሁሉ ክብርሽን ያያሉ የእግዚአብሔርም አፍ በሚያወጣልሽ በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ
አንቺ በእግዚአብሔር እጅ እንደተዋበ አክሊልና በአምላክሽም እጅ እንደ ነገሥታት ዘውድ ትሆኛለሽ
ከእንግዲህ ወዲህ ተረስታ የቀረች ነች አትባዪም ፡ ምድርሽም አውድማ ሆና አትቀርም ፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በአንቺ ደስ ብሎታል ምድርሽ ደስተኛ ባል ያላት ተብላ ትጠራለች ፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር በአንቺ ደስ ይለዋል እርሱ ለምድርሽ ባል ይሆንላታል ፡
ጕልማሳ ድንግሊቱን ሙሽራ አድርጎ እንደሚወስድ እንዲሁም ልጆችሽ አንቺን ያገቡሻል ፡ ሙሽራም በሙሽራይቱ ደስ እንደሚለው እንዲሁ አምላክሽ በአንቺ ደስ ይለዋል።
አሜን አሜን ሃሌሉያ
ልዑል እግዚአብሔር በኢትዮጵያ ለዘላለም ይንገሥ!!! መሪዎቿ ባለስልጣናቶቿ ከእግዚአብሔር የተቀቡ ይሁኑ! ለኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም ፍቅር ከፍታ እና ብልፅግና ይትጉ!
ኢትዮጵያዬ ሆይ አምላክሽ በምድርሽ በልጆችሽ ልብ ለዘላለም ይነግሣል!!!
ሃሌሉያ🙏🏽🙏🏽🙏🏽
ጌታ ሆይ ዛሬ ስለ ሕዝባችን እንፀልያለን በአዘኔታ እና በምህረት እኛን ዝቅ ብለህ እንድትመለከተን እንጠይቅሀለን ፡፡ ጀርባችንን በብዙ መንገድ ከአንተ የመለስንበትን ሆኔታዉች ይቅር በለን እና እኛ የፍትህና የሰላም መንገድን ለመከተል እንደፈለግን ሕዝብ መልሰን ፡፡
አገራችንን ከጦርነት እና ሁከት ከዘር ክፍፍል እና ጥላቻ ከፍርሃት እና ግራ ከመጋባት ከበሽታ ከማንኛውም የጠላት ሀሳብና አሰራር ሁሉ ጠብቃት። እኛ እንደ አንድ ህዝብ ወደ አንተ ዘወር ብለን በችግር ቀን ወደ አንተ የምንጮህ ህዝብ አርገን፡፡
ወደ መሪዎቻችን እና ገዥዎቻችን ሁሉ ቀርበህ ይህንን ህዝብ የሚገዙበትን
ጥበብ እና ማስተዋል ስጣቸው ፡፡ የሚያደርጎቸው ውሳኔዎች በጥበብ የተሙሉ እንዲሆኑ እንለምንሀለን። ጌታዬ ሆይ ህዝብህን በማሰተዋል ወደ አንተ እንዲመጣ እንፀልያለን ፡፡
እንደ አዳኛቸው ከማያውቁህ ሁሉ ጋር ተገናኛቸዉ ያላወቁህ ይወቁህ ያልቀመስሁ ይቅመሱህ፡፡ ወንጌል አንድ ቀን በዚህች ምድር ከባህር ዳርቻ እስከ ባህር ዳርቻ ድረስ በግልጽ እና በእውነት እንዲሰበክ እንፀልያለን ፡፡ የእውነት ቃልህን ሰባኪዋች አድርገን ፡፡ ለዚህ ሕዝብ የመዳንን ደስታ እና ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ የመሆኑን የማመን ፀጋን አብዛላቸዉ። በእየሱስ ስም ፀለይን አሜን🙏🏻🙏🏻
🙏ሀሙስ ስለ ኢትዮጵያ 🙏
✅ ስለ ሀገራችን ስለ ህዝቦች ሁሉ
በፀሎት እና በምልጃ ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን እርሱም ምድራችንን ይፈውሳል 🙏
📖 2ኛ ዜና መዋዕል 7
14፤ በስሜ የተጠሩት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ፥ ፊቴንም ቢፈግሉ፥ ከክፉ መንገዳቸውም ቢመለሱ፥ በሰማይ ሆኜ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ።
ገላትያ 5:18
በመንፈስ ብትመሩ ግን ከሕግ በታች አይደላችሁም።
መዝሙር 139:7-10
ከመንፈስህ ወዴት እሄዳለሁ? ከፊትህስ ወዴት እሸሻለሁ?
ወደ ሰማይ ብወጣ፥ አንተ በዚያ አለህ። ወደ ሲኦልም ብወርድ፥ በዚያ አለህ።
እንደ ንስር የንጋትን ክንፍ ብወስድ፥ እስከ ባሕር መጨረሻም ብበርር፥
በዚያ እጅህ ትመራኛለች፥ ቀኝህም ትይዘኛለች።
ሮሜ 8:14
በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።
አሜን አሜን አሜን አባ ተባረክ
ተመስገን መንፈስ ቅዱስ ዛሬን ደግሞ በዚህ መልኩ ልታገኘን ወደድክ ደግመን ደግመን ተመስገን እንላለን ሃሌሉያ አቤቱ አባታችን በመንፈስህና በህግህ መመራት ሆነልን ሃሌሉያ ብርሀንህን አበራህልን ከአንተ ወዴት እንሸሻለን በቀኝ እጅህ ተይዘናል ቸርነትህን አበዛህልን ሃጢያታችንን ይቅር ብለህ መሀሪነትህን በብዙ አሳየኸን ርህራሄህን አሳይተህ እረፍትህን
እየሰጠህ የምታኖረን አባታችን እናመስግንሃለን አሁንም ደግመን ደግመን ለእኛም ለወገኖቻችን ለአገር ለቤተክርስቲያን መሪዎች በጥፋት ላይ ላሉት ሁሉ በህብረት በፊትህ ወድቀን ከጥፋታችን ሁሉ በደምህ እንድታነፃን ምህረትህን ይቅርባይነትህን እንለምንሃለን በጌታ እየሱስ ክርስቶስ ስም አሜን🙏🏾🙏🏾🙏🏾
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ )
📌መንፈስ ቅዱስ ወደ ንስሃ እንድንገባ እንዲረዳን
✅ መርምረኝ
✅ልቤን እወቅ
✅መንገዴንም እወቅ
እንለዋለን ፈቅደን እርሱ በእኛ ውስጥ እንዳይሰራ የሚያርጉ ጨለማዎች ላይ ብርሃን እንዲያበራ በንስሃ ወደ አባታችን እንድንመለስ እንዲረዳን መንፈስ ቅዱስን በህብረት እንጠራለን
እንፀልያለን 🙏
📖 መዝሙረ ዳዊት 139
23፤ አቤቱ፥ መርምረኝ ልቤንም እወቅ፤ ፍተነኝ መንገዴንም እወቅ፤ በደልንም በእኔ ውስጥ ብታገኝ እይ፤ የዘላለምንም መንገድ ምራኝ።
