en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌እግዚአብሔር ስለ እኛ ስለሚያስበው ሀሳብ ✅ እውነተኛ ሀሳቡን መረዳድ እንዲሆን ✅በብዙ ያራለፉ በዚህ እውቀት እንዲያርፋ በእየሱስ ስም እንፀልያለን 🙏 📖 ትንቢተ ኤርምያስ 29 11፤ ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም።

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 (ሰኞን በምስጋና ) ✅ እግዚአብሔር ታማኝ ስለሆነ ✅አብሮነቱ ጥበቃው ሳይለየን በዚች ቀን በዚህ channel እንድንገናኝ ስለረዳን ✅ አገራችንን ስለጠበቀልን ✅ መልካም ዜናን ስላሰማን በደስታ በብዙ ምስጋን በፊቱ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 95 1፤ ኑ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበለን፤ ለአምላክ ለመድኃኒታችን እልል እንበል። 2፤ በምስጋና ወደ ፊቱ እንድረስ፥ በዝማሬም ለእርሱ እልል እንበል፤ 3፤ እግዚአብሔር ታላቅ አምላክ ነውና፥ በአማልክትም ሁሉ ላይ ታላቅ ንጉሥ ነውና። 4፤ እግዚአብሔር ሕዝቡን አይጥላቸውም፤ የምድር ዳርቻዎችም በእጁ ውስጥ ናቸው፥ የተራሮች ከፍታዎች የእርሱ ናቸው።

ትንቢተ ኢሳይያስ 65 24፤ እንዲህም ይሆናል፤ ሳይጠሩ እመልስላቸዋለሁ፥ ገናም ሲናገሩ እሰማለሁ። አሜን መልሳችን አንተ ነህ ጥያቄን የምትመልስ የምትሰማ አይኖችህ ሁል ጊዜ በእኛ ላይ ናቸው የምታይ ጌታ ሆይ ሳንጠራህ ገና ሳንጠይቅህ የሚያስፈልገንን የምታውቅና የትሰጠን የምትመልስልን የቅርብ አምላካችን ከእስትንፋሳችን ይልቅ ቅርብ የሆንክ ልብንና ኩላሊትን የምትመረምር አምላክ ነህ በሁላችንም ልብ ውስጥ ያለውን ጸሎታችንን ስለተመለከትክ እናመሰግንሀለን ገና ለጌትነትህ እንገዛልሀለን ክቡር ነህ እንሰግድልሀለን የልቤ አምላክ የልቤ ተባርክ የልቤ አምላክ ተባረክ የውስጣችንን የምታውቅ የምትረዳ አባታችን አቅራቢያችን አዘጋጃችን ስጪያችን ሰሚያችን መፍትሄአችን እናከብርሀለን እናወድስሀለን እውቅና ለአንተ እንሰጣለን ስምህ ከዘላለም እስከለዘላለም ከፍ ይበል አሜን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ተለያዩ የግል ጥያቄዎች ✅ በእኛ ላይ ስላለ ወይም በምናቃቸው ላይ በዚህ ሰዐት በህብረት ጥያቄዎቻችንን ይዘን ወደ አባታችን ፊት እንቀርባለን 📌በተለየ ሁኔታ እንዲፀለይለት የሚፈልግ ቦታው ክፍት ነው ኤፌሶን 3:20-21 እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው ለእርሱ በቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን አሜን።

የዮሐንስ ወንጌል 14 6፤ ኢየሱስም፡— እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። ኢየሱስ ሆይ ለህይወታችን መንገድ ያሳየኸን ምሪታችን አንተ ነህ እውነት የሆንክ ኢየሱስ ህይወትን ይሰጠኸን እረኛችንም አንተ ነህ በለመለመ መስክ መሪያችን አንተ ነህ ከፊታችን ቀድመህ የምትወጣ መንገዳችንን ያጸዳህልን ክፉን የጠረክልን እኛ ሳንወጣ አንተ ቀድመህ ሁሉን ያስተካከልክ መሪያችን ኢየሱስ እናመሰግንሀለን እናከብርሀለን እናደናንቅሀለን ታላቅነትህን መሪነትህን አዛዥነትህን ጌትነትህን የበላይነትህን ታላቅነትህን እናገራለን እናወራለን አሁንም በሀገራችን አንተ ቅደም አንተ ውጣ በጠቅላይ ሚንስትራችን ላይ አንተ ቅደም በኢየሱስ ክቡር ደም ሸፈነው ጋረድነው ሕዝብን በጥበብ እንዲመራ ጸጋህን አብዛለት አንተ ውጣ መንፈስ ቅዱስ ምሪትን ያብዛለት አንተ ሳትወጣ እሱ አይውጣ በሚንስትሮቹ ሁሉ በፕሬዘንዳንታችንም በሁሉም በስልጣን ላይ ሆነው ሀአገራችንን የሚመሩትን አንተ የሾምካቸውን አንተ ያስቀመጥካቸውን ሁሉ አንተ ቅደም በሚያስቡት በሚሰሩት ባቀዱት ሁሉ ላይ አንተ ቅደም አንተ ውጣ ጌታ ሆይ ግድ አልንህ አንተ ውጣ አሁንም አንተ ምራ በኢየሱስም ስም አሜን:: ጸሎታችንን ስለሰማኸን እናመሰግንሀለን!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ሰለ እግዚአብሔር ምሪት ✅በህይወታችን ✅ በቤተሰቦቻችን ✅በሀገራችን አንተ ያለየህልን አይሁንብን , ከእኛ ጋር ካልወጣህ አንወጣም የምንልበትን ፀጋ እንዲሰጠን በራሳችን ሳይሆን በእርሱ ብቻ እንድንመራ በህብረት እንፀልያለን Thank 📖 ኦሪት ዘጸአት 33 15፤ እርሱም፡— አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ፥ ከዚህ አታውጣን።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ እግዚአብሔር ብርሃን ✅በእርሱ ዘንድ ከቶ ጨለማ ስለሌለ ✅የትኛውንም ጨለማ በእርሱ ብርሃን ዘንድ መኖር ስለማይችል ከውስጣች ጀምሮ በሁሉም ቦታ የእግዚአብሔር ብርሃን በጨለማው ላይ ሁሉ እንዲያበራ በህብረት እንፀልያለን 📖 1ኛ ዮሐንስ 1 5፤ ከእርሱም የሰማናት ለእናንተም የምናወራላችሁ መልእክት፡— እግዚአብሔር ብርሃን ነው ጨለማም በእርሱ ዘንድ ከቶ የለም፡ የምትል ይህች ናት።

🙏Thanksgiving 🙏 (ምስጋና ) ✅ እግዚአብሔር ታማኝ ስለሆነ ✅አብሮነቱ ጥበቃው ሳይለየን በዚች ቀን በዚህ channel እንድንገናኝ ስለረዳን ✅ አገራችንን ስለጠበቀልን ✅ መልካም ዜናን ስላሰማን በደስታ በብዙ ምስጋን በፊቱ እንቀርባለን መዝሙረ ዳዊት 48 1፤ እግዚአብሔር ትልቅ ነው፤ በአምላካችን ከተማ በተቀደሰ ተራራ ምስጋናው ብዙ ነው።

የዮሐንስ ራእይ 4:8 አራቱም እንስሶች እያንዳንዳቸው ስድስት ክንፎች አሉአቸው፥ በዙሪያቸውና በውስጣቸውም ዓይኖች ሞልተውባቸዋል፤ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም። እናመሰግንሃለን አባ የጎደለብህን ልንሞላ አይደለም ከፍታም ልንጨምርልህ አይደለም አምላክነትህ ከከፍታዎች በላይ ነው ከፍታህን ልናስተውለው አንችልም ከአይምሮአችን በላይ ነው ምስጋና አልጎደለብህም በፊትህ ምስጋና ተቋርጦ አያውቅም ግን በቃ ዝም ብለን እናመሰግንሃለን በፊትህ ሞገስን ስላገኘን እናመሰግንሃለን አንተን በማመስገን ውስጥ ደስታ አለ አንተን በማመስገን ውስጥ ሰላም አለ አንተን በማመስገን ውስጥ እረፍት አለ ብርሃን አለ ጤና አለ በረከት አለ ስኬት አለ መሻገር አለ ከፍ ማለት አለ ሃሌሉያ ዛሬም ተመስገን ነገም ተመስገን ለዘላለም ተመስገን !!! አሜን አሜን አሜን ሃሌሉያ

አንተን ማመስገን ጥበብ ነው አንተን ማመስገን እውቀት ነው አንተን ማመስገን ማስተዋል ነው ስናመሰግንህ እንጠቀማለን ስናመሰግንህ በመንፈስ እንሞላለን ስናመሰግንህ ደስታችን ይበዛል ከፀጋህ አንጎድልም ሁሌም ተመስገን በሽብሸባ በከበሮ በፀናፅል በእልልታ ተመስገን ተመስገን ሃሌሉያ እልልልልልልልልል

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 30 4፤ ቅዱሳን ሆይ፥ ለእግዚአብሔር ዘምሩ፥ ለቅድስናውም መታሰቢያ አመስግኑ። 5፤ ቍጣው ለጥቂት ጊዜ ነው፥ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን፤ ልቅሶ ማታ ይመጣል፥ ጥዋት ግን ደስታ ይሆናል። 6፤ እኔም በደስታዬ፡— ለዘላለም አልታወክም፡ አልሁ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌በፀሎት ለደከሙ ✅ከራሳችን, ከህብረታችን ጀምሮ ለሁሉ ሀይላቸው/ችን እንዲታደስ በውስጣቸው/ችን ያለውን መንፈስ ቅዱስ በብዙ እንዲገለጥ በእየሱስ ስም እንፀልያለን🙏 📖 ትንቢተ ኢሳይያስ 40 29፤ ለደካማ ኃይልን ይሰጣል፥ ጕልበት ለሌለውም ብርታትን ይጨምራል።

የልምላሜ ሕይወት ክፍል 5.m4a13.63 MB

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ክርስቶስ የሰጠንን ትእዛዞች እንድናከብር ✅በፍቅሩ እንድንኖር ✅ በብዙ እንድናፈራ ✅ምሳሌ እንድንሆን ትእዛዞቹን እንድንጠብቅ ከእነርሱም የሚያርቁንን ነገሮች መርምረን እንድንተው ፀጋውን እንዲያበዛልን በእየሱስ ስም እንፀልያለን🙏 📖 የዮሐንስ ወንጌል 15 9፤ አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ። 10፤ እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ። 11፤ ደስታዬም በእናንተ እንዲሆን ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን ነግሬአችኋለሁ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ ክርስቲያኖች አንድነት ✅ከአንዱ መንፈስ ስለጠጣን ✅ ሁሉም በክርስቶስ አንድ ስለሆነ ✅ ለመንግስቱ ስለምንሰራ እግዚአብሄር በመንፈሱ እንደ አዲስ አንድነታችንን እንዲያድስ በልዮነት እና በጥል ውስጥ ላሉት ደግሞ ሰላም እንዲመጣላቸው በእየሱስ ስም እንፀልያለን🙏 📖 1ኛ ቆሮንቶስ 12 13፤ አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል። 📖 1ኛ ቆሮንቶስ 1 10፤ ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ።

#የልምላሜ ሕይወት ክፍል 4 🌾ፍሬ ማፍራት ✅ ፍሬ ማለት ውጤታማነት ማለት ሲሆን ይህ ውጤታማነት በሰዎች ሕይወት ውስጥ የሚያመጣው ደስታ አለ። የመንፈስ ፍሬ ከእግዚአብሔር ጋር ሕብረት ያላቸው በመንፈስ የሚመላለሱ ለቃሉ ትኩረት በመስጠት ቃሉን በማድረግ የሚመላለሱ ሰዎች የሚያገኙት ልዩ የሆነ ከመንፈስ ቅዱስ የሚገኝ ስጦታ ነው። 🌿 የልምላሜ ሕይወት ጉዞ ወደ ፍሬ ነው ፍሬ ማፍራት እንድንችል የሚጠበቅብንን ሁሉ ልናደርግ ይገባል እንዲሁ በአጋጣሚ የሚመጣ ፍሬ የለም። ዘር፣መተከል፣ ማደግ ሲኖር ነው ፍሬ ማፍራት የሚመጣው። አለማደግ ትልቅ የክርስቲያን ችግር ነው ብዙ ዘመን ቤተክርስቲያን እየተመላለሱ የማያድጉ ሰዎች ሀዘንተኛ ናቸው በራሳቸው መንገድ ስለሚሄዱ ደስታ የላቸውም ስለዚህ በክርስትና ማደግ ማለት የሀዘን መድሀኒት ነው የፍቅር የሰላም የደስታ መገኛ ነው። ስለዚህ በየእለቱ ማደግ ይጠበቅብናል። 🙏 ፍሬ ለማፍራት ምን ማድረግ ይጠበቅብናል? 1 በእርሱ መኖር ዮሐንስ 15 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴ በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም። ⁵ እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል። ✅ እንዴት ፍሬ ማፍራት እንደምንችል የነገረን ኢየሱስ ነው ስለዚህ ፍሬ ለማፍራት ከኢየሱስ ጋር መኖር መቻል አለብን ከኢየሱስ ጋር መኖር ማለት ቤተክርስቲያን መመላለስ ማለት ብቻ አይደለም። ቤተከርስቲያን እየተመላለሱ ፍሬ የሌለው ሕይወት ፍቅር፣ደስታ፣ ሰላም የሌለው ሕይወት የሚኖሩ በጣም ብዙ ክርስቲያኖች አሉ። ከእንደዚህ አይነት ሕይወት ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል። ከእርሱ ጋር መኖር ማለት በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ቃሉን በማድረግ ትእዛዙን በመፈጸም ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕብረት በማድረግ መኖር ነው። ይህን ካደረግን ፍሬ የማናፈራበት ምንም ምክንያት የለም። “ከክርስቶስ ጋር ተሰቅዬአለሁ፤ እኔም አሁን ሕያው ሆኜ አልኖርም ክርስቶስ ግን በእኔ ይኖራል፤ አሁንም በሥጋ የምኖርበት ኑሮ በወደደኝና ስለ እኔ ራሱን በሰጠው በእግዚአብሔር ልጅ ላይ ባለ እምነት የምኖረው ነው።” — ገላትያ 2፥20 ✅ ጳውሎስ እርሱ መኖር አቁሞ ክርስቶስ በእርሱ እየኖረ እንደሆነ ይገልፃል ይህ ማለት አስተሳሰብ ፣ አካሄዱ ፣ ተግባሩ ፣ ንግግሩ ሁሉ ነገሩ በክርስቶስ ምሪት እንዳደረገ ይገልፃል። በዚህ ምክንያት ነው ጳውሎስ በብዙ ፍሬ መኖር የቻለው እስር ቤት ሆኖ ደስታ የሰበከው። እንግዲህ እኛም እንዲሁ ክርስቶስ እንዲኖርብን ራሳችሁን ስጡ ይለናል። ሀሳባችንን፣ አካሄዳችን ፣ ተግባራችን አስረክበን እርሱ እንዲኖርብን ልንፈቅድለት ይገባል። በመሰለን እና በተመቸን መንገድ እየሄድን ፍሬ አናፈራም። በክርስቶስ ልንኖር ይገባል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌አገልጋይ ስለመሆን ✅እየሱስ በዚህ ምድር ሲኖር እንዳገለግለው እኛም እራሳችንን ዝቅ አርገን ማገልገል እንዲሆንልን ✅ለእግዚአብሄር አገልግሎት ህይወታቸውን ሰጥተው ለሚኖሩ ሁሉ ደግሞ አዲስ የመንፈስ መታደስ እንዲሆንላቸው እንፀልያለን 🙏 📖 የማርቆስ ወንጌል 10 43፤ በእናንተስ እንዲህ አይደለም፤ ነገር ግን ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፥ 44፤ ከእናንተም ማንም ፊተኛ ሊሆን የሚወድ የሁሉ ባሪያ ይሁን፤

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ ) 📌ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ✅እግዚአብሔር ለኛ ያሳያውን ታላቅ ፍቅር ከተረዳነው በላይ እንድንረዳው ✅ለሌሎችም ይህ መረዳት እንዲመጣ ፀጋው እንዲበዛ በእየሱስ ስም እንፀልያለን 🙏 📖 1ኛ ዮሐንስ 3 1፤ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ልንጠራ አብ እንዴት ያለውን ፍቅር እንደ ሰጠን እዩ፥ እንዲሁም ነን። ስለዚህ ምክንያት ዓለም እርሱን ስላላወቀው እኛን አያውቀንም።

የልምላሜ ሕይወት ክፍል 3.m4a19.47 MB