en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 ለተለያዩ የግል ጥያቄዎቻችን ✅ የኛን እና የወገኖቻችን ልመናዎች በ ምስጋና እና በምልጃ በአባታችን ፊት እናቀርባለን 📖 ወደ ፊልጵስዩስ 4 6፤ ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።

ስለመንፈስ ቅዱስ ምሪት ✅በእኛ እና በቤታችን ✅ በየቤተክርስቲያን አገልጋዮች እና መሪዎች ✅ በየሀገር መሪዎች መንፈስ ቅዱስ ብቻ እንዲመራ በእየሱስ ስም እንፀልያለን! 📖ወደ ሮሜ 8 14፤ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ ሁሉ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ናቸውና።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በእግዚአብሔር ቃል ላይ ስለመተከል ✅ በእርሱ እውነት ላይ ብቻ ቆመን ሙቀቱም ድርቁንም እንድናልፍ ✅ የምናፈራ እንድንሆን ፀጋውን እንዲሰጠን እንለምናለን 📖 ትንቢተ ኤርምያስ 17 8፤ በውኃ አጠገብ እንደ ተተከለ፥ በወንዝም ዳር ሥሩን እንደሚዘረጋ ሙቀትም ሲመጣ እንደማይፈራ ቅጠሉም እንደሚለመልም፥ በድርቅ ዓመትም እንደማይሠጋ ፍሬውንም እንደማያቋርጥ ዛፍ ይሆናል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 የእየሱስ ብርሃን ቦግ ብሎ በጨለማ ሁሉ ላይ እንዲበራ ✅ ከእኛ ውስጥ ጀምሮ እስከ አለም ጫፍ ድረስ 📖 የዮሐንስ ወንጌል 8 12፤ ደግሞም ኢየሱስ፡— እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም፡ ብሎ ተናገራቸው።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በዚህ ወቅት ከስራቸው ለተፈናቅሉ ✅ወደፊት ሲያዩ ለጨለመባቸው ✅የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ ለገቡ እግዚአብሄር አባት ያላችውን እንዲባርክ ከጭንቀታቸው ነፃ እንዲአወጣቸው በጎደለው ነገር እንዲሞላላቸው ሁሉ በእምነት እንፀልያን 📖 ወደ ፊልጵስዩስ 4 19፤ አምላኬም እንደ ባለ ጠግነቱ መጠን በክብር በክርስቶስ ኢየሱስ የሚያስፈልጋችሁን ሁሉ ይሞላባችኋል።

🙏Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 መዝሙረ ዳዊት 118 28፤ አንተ አምላኬ ነህ አመሰግንህማለሁ። አንተ አምላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ሰምተኸኛልና፥ መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 ስለ ህፃናት እና ታዳጊዎች ✅ በእግዚአብሔር እውቀት እንዲያድጉ ✅ በእግዚአብሔር ቤት ህይወታቸውን እንዲጨርሱ ✅በመንፈስ ቅዱስ ፍሬዎች እና ስጦታዎች እንዲሞሉ በጌታ ፊት እናቀርባቸዋለን ትንቢተ ኢሳይያስ 54 13፤ ልጆችሽም ሁሉ ከእግዚአብሔር የተማሩ ይሆናሉ፥ የልጆችሽም ሰላም ብዙ ይሆናል።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌በሁሉ ጊዜያት እና ሁኔታ ውስጥ ሆነን የማንበገርበት መንፈስ እንድንሞላ ✅በውርደት ✅ በመብዛት ✅በመጉደልም ✅ በመጥገብ ✅በመራም በእየሱስ ሀይል ሁሉን እችላለሁ የሚያስብል መንፈስን በእየሱስ ስም እንለምናለን 📖 ወደ ፊልጵስዩስ 4 11፤ ይህን ስል ስለ ጉድለት አልልም፤ የምኖርበት ኑሮ ይበቃኛል ማለትን ተምሬአለሁና። 12፤ መዋረድንም አውቃለሁ መብዛትንም አውቃለሁ፤ በእያንዳንዱ ነገር በነገርም ሁሉ መጥገብንና መራብንም መብዛትንና መጉደልን ተምሬአለሁ። 13፤ ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ።

🩸 Mothers 🩸Cancer patients 🩸People with immunity deficiencies and blood diseases 🩸People who need surgery or have suffered trauma . ✅Still need blood to survive ! There is a serious shortage at this time because of the COVID19. All who are eligible to donate please ,lets go and do so. Location - Stadium Blood Bank Time - Sunday ,9 pm afternoon local time One unit of blood saves three lives !

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ስለይቅር ባይ ልብ ✅ ከእግዚያብሔር ፊት በድፍረት ለመቅረብ ✅ የጌታችን የእየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ለመከተል ይቅር ማለት ያለብን እና ይቅርታ መጠየቅ የሚያስፈልገንን ሰዎች ይዘን በፊቱ እንቀርባለን ለሰዎች ሁሉ ደግሞ ይህ ሀሳብ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት እንዲነካቸው እንፀልያለን 📖 የማርቆስ ወንጌል 11 25፤ ለጸሎትም በቆማችሁ ጊዜ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ፥ በማንም ላይ አንዳች ቢኖርባችሁ ይቅር በሉት። 26፤ እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ሰዎች ሁሉ በአምላክ ላይ ብቻ እረፍት እንዲያገኙ 📖 መዝሙረ ዳዊት 46 10፤ ዕረፉ፥ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ፤ በአሕዛብ ዘንድ ከፍ ከፍ እላለሁ፥ በምድርም ላይ ከፍ ከፍ እላለሁ።

Today also we have received additional donation from Catholic Charismatic Movements. We are very very greatful for their kind
Today also we have received additional donation from Catholic Charismatic Movements. We are very very greatful for their kind heart. Their contributions in general could help approximately 130 to 150 families. May God bless each and every member of thier movement!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌ስለ የእግዚአብሔር መልካምነትን ✅ አመቱን በዚህ ሀስብ ስለጀመርነው ዛሬም እያንዳንዱ ነገር ላይ መልካምነትን በእምነት እንናገራለን 📖 ትንቢተ ናሆም 1:7 ፤ እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል።

የጽድቅ ኑሮ.m4a9.03 MB

“እንዲህ አይሁን፤ በቃልህ ትጸድቅ ዘንድ ወደ ፍርድ በገባህም ጊዜ ትረታ ዘንድ ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ሰው ሁሉ ውሸተኛ ከሆነ እግዚአብሔር እውነተኛ ይሁን።” — ሮሜ 3፥4 በጽድቅ መኖር የማይቻል ህይወት አይደለም የእግዚአብሔር ቃል እንደሚቻል ነው እንጂ እንደማይቻል አልነገረንም ስለዚህ በጽድቅ ለመኖር ምን ማድረግ እንዳለብን ከቃሉ መማር አለብን። አብዛኛው ሰው እንዴት በፅድቅ መኖር እንችላለን እኛ እኮ ሰዎች ነን ይላል በእርግጥ ሰው በኃይሉ አይበረታም ነገር ግን ከእግዚአብሔር ባህሪ ተካፍዮች ሆነናል ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል የነገረን እውነት ነው። ስለዚህ በፅድቅ መኖር ይቻላል የኢየሱስ ሞት እና ትንሳኤ ይህን ሕይወት አመጣልን። 2ኛ ጴጥሮስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²-³ የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። ⁴ ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን። ሙሉ ሀሳቡን ከታች ባለው አጭር ስብከት መከታተል ይቻልላ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 የእግዚአብሔርን ፅድቅ እና መንግስትን ስለመፈለግ ✅ በእርሱ መንግስት ሁሉ መልካም ስለሆነ ✅ በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ሰላም እን ደስታ እንጂ መብልና መጠጥ ስላልሆነ( ሮሜ 14:17) መንፈስ ቅዱስን የእርሱን ፅድቅ እና መንግስትን የምንፈልግበትን ፀጋ ለሁሉ እንዲሰጥ በእየሱስ ስም እንጠይቃለን 📖. የሉቃስ ወንጌል 12 31፤ ዳሩ ግን መንግሥቱን ፈልጉ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።

የትንሳኤው ኃይል ካስገኘልን እውነቶች አንዱ #ጽድቅ የትንሳኤው ኃይል በሕይወታችን ካመጣልን አስደናቂ ነገር ውስጥ ቀዳሚው አዲስ ፍጥረት በመሆን ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ማድረግ መቻላችን ነው ። ሰው በአዳም ኃጢአት ምክንያት አጥቶት ከነበረው ትልቁ ቁምነገር ከእግዚአብሔር ጋር ህብረት ማድረግ አለመቻል ነበር አሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ሞት እና #ትንሳኤ ዳግም ወደዚህ ሕብረት መግባት ችለናል ። እግዚአብሔር ከሀጢአት ጋር ሕብረት ማድረግ አይችልም ባህሪውም አይደለም። (መዝ 34:15 ) የእግዚአብሔር ዓይኖች ወደ ጻድቃን ጆሮዎቹም ወደ ጩኸታቸው ናቸውና። ስለዚህ እኛ እስካልጸደቅን ድረስ እግዚአብሔር ፊቱን ወደእኛ ማድረግ አይችልም እኛም በእርሱ ፊት መሆን አንችልም ነበር በክርስቶስ የተሰራው የትንሳኤ ኃይል እኛን አጽድቆ በእግዚአብሔር ፊት መሆን ፥ መታየት ፥ መሰማት እንድንችል በክርስቶስ በኩል ይህን እድል አስገኘልን ። 2ኛ ቆሮ 5 ¯¯¯¯¯¯ ²¹ እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው። የትንሳኤ ትልቁ ኃይል እኛን ማጽደቁ ነው። “ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24 ሰው ባለው ነገር ነው መኖር የሚችለው። እኛ ደግሞ በፊት ጽድቅ አልነበረንም አሁን በክርስቶስ በኩል ጽድቅ አግኝተናል። ስለዚህ የጽድቅ ኑሮ መኖር እንችላለን። ግን ለምን በጽድቅ መኖር አልቻልንም ? የብዙዎች ጥያቄ ትንሽ ምክንያቶቹን እንጥቀስ 1 ለእግዚአብሔር ቃል የሚገባውን ትኩረት አለመስጠት 2 በዓለም ፍቅር መያዝ ሁሉን መፈለግ 3 በስጋ መመላለስ (ገላ 5:21) የስጋ ስራ 4 ስለ ሕይወት ያለን የተዛባ አመለካከት (አለመርካት) 5 ራስ ወዳድነት

የተንሳኤ ውጤት መጽደቅ.m4a9.39 MB

Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ የትንሳኤው ብርሃን ስለበራልን ✅ህያው ተስፋ ስላለን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 1ኛ ጴጥሮስ 1 3-5፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ!

ውድ የፀሎት ቤተሰቦች በትንሳኤ በአል ምክንያት ዛሬ እና ነገ ማታ chain prayer አይኖረንም. ሰኞ 3 ሰአት ላይ እንገናኝ ! ☀️የትንሳኤው ብርሃን በልባቹ በቤታችሁ ...በሀገራችን እንዲህም በአለም ያብራ !☀️ “Do not abandon yourselves to despair. We are the Easter people and hallelujah is our song.” Pope John Paul the second. 🎉🎉Hallelujah!!!! 🎉🎉 ❤️❤️❤️