en
Feedback
Ethiopian Catholic Charismatic

Ethiopian Catholic Charismatic

Open in Telegram
805
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-130 days
Posts Archive
🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 ስለ መስቀሉ ስራ ✅ ጌታችንእየሱስ ክርስቶስን ለኛ የከፈለውን መስዋዕትነት ✅ ለዛም ያደረሰውን ፍቅር እያሰብ በመስቀሉ ስር ሁሉነገራችን እናስቀምጣለን እምነታችንንም እንጨምራለን 📖 ትንቢተ ኢሳይያስ 53 5፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። 6፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።

የተወደዳችሁ ሕዝበ ክርስቲያን፤ ዐርብ ሚያዝያ 9 ቀን 2012 ከረፋዱ 4፡00 - 7፡00 (10:00 a.m. - 01:00 p.m. East African Time) በዋልታ ቲቪ የጠዋቱ የስግደት ጸሎት በቀጥታ እንደሚተላልፍ ስናሳውቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው፡፡ እንደሺሁም ከቀኑ 7:00 - 10፡00 ሰዓት (01፡00 - 04፡00 p.m. E.A.T ) በአዲስ ቲቪ የስግደት ጸሎት በቀጥታ ስርጭት እንዲሁም ከ10:00 - 12:00 (04:00 - 06:00 p.m. E.A.T.) የመስቀል መንገድ በአዲስ ቲቪ (የተቀረፀ) ይተላለፋል፡፡ ለመረጃ ፡ 0912 36 31 89

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 ስለ ትህትና ✅ ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ በፀሎተ ሀሙስ የደቀመዝሙሮቹን እግር በማጠብ ያሳየንን ትህትና እኛ ውስጥ እንዲያድር ✅ ምንም አይነት ትእቢትን ከውስጣቸን እንዲጠፋ መንፈስ ቅዱስ እንዲያግዘን በእየሱስ ስም እንፀልያለን 📖 የዮሐንስ ወንጌል 13(12:17) 12፤ እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፡— ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን? 13፤ እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። 14፤ እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። 15፤ እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። 16፤ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። 17፤ ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌የፍቅር እሳት እንዲነድ ✅ በውስጣችን , በቤተሰቦቻችን , በወዳጆቻችን ✅በ ቤተክርስቲያናችን , በሀገራችን , በአለማችንን 📖 ወደ ሮሜ 5 5፤ በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም።

እግዚአብሔር ታላቅ ነገር አረገልን ደስም አለን!!! “እግዚአብሔር፥ ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ እስከ አሁንም ስለምታገለግሉአቸው፥ ያደረጋችሁትን ሥራ ለስሙም ያሳያችሁትን ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመፀኛ አይደለምና።” — ዕብራውያን 6፥10 የተከበራችሁ ቤተሰቦች እግዚአብሔር ረድቶን ልግስናችን ቀጥሏል ዛሬም ለ18 ቤተሰብ የሚሆን ቁሳቁስ ሰብስበናል እስካሁን 118 ቤተሰብ የሚሆን ቁሳቁስ የሰበሰብን ሲሆን አሁን የቀረን ለ32 ቤተሰብ የሚሆን ብቻ ነው። አሁንም በጌታ ፍቅር እንጠይቃችኋለን የቀረው ላይ እንተባበር እግዚአብሔር ይባርካችሁ!!!

🙏Tonight’s prayer intention ( የፀሎት ርእስ) 📌 በእውነት እና በመንፈስ እግዚአብሔርን የማገልገል ,የመከተል, የማምልክ ዘመን እንዲሆን ✅ ለሁሉም ክርስቲያኖች እና አብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮች ሁሉ እንፀልያለን 📖 የዮሐንስ ወንጌል 4 24፤ እግዚአብሔር መንፈስ ነው፥ የሚሰግዱለትም በመንፈስና በእውነት ሊሰግዱለት ያስፈልጋቸዋል።

Voice 014.m4a2.72 MB

📣የክርስቶስ ቤተሰቦች ሰላማችሁ ይብዛ እያልን ይህን የችግር ግዜ ተባብረን እንለፈው እያልን ጥሪያችንን እናስተላልፈዋለን። ❇️ ከቤተክርስቲያን በተላለፈው ጥሪ መሠረት በፎቶው ላይ እንደምታዩት እስካሁን ጥሩ ጉዞ መጓዝ ችለናል በቀሪው ደግሞ ሁላችንም ተባብረን የቀረውን እንድንሞላ አደራ እንላለን የሰጣችሁም ሰዎች ብትሆኑ ሰጠን ብላችሁ እንዳታቆሞ ዙሪያችሁ ካለው ሰው የመሰብሰብ ኃላፊነት ይጠበቅባችኋል። በዚህ ሳምንት ቀሪውን እንሞላለን ጌታ ይረዳናል። ቆላስይስ 3 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²³ ለሰው ሳይሆን ለጌታ እንደምታደርጉ፥ የምታደርጉትን ሁሉ በትጋት አድርጉት፥ ²⁴ ከጌታ የርስትን ብድራት እንድትቀበሉ ታውቃላችሁና፤ የምታገለግሉት ጌታ ክርስቶስ ነውና።

Thanksgiving Mondays 🙏 ( ሰኞን በምስጋና) ✅ አዲስ ሳምንትን ስላሳየን ✅አብሮነቱ ጥበቃው ባርኮቱ ስላልተለየን ✅ ምስጋና ሁሌ ስለሚገባው በምስጋና ጉዳዮቻችንን ጥያቄአችንን ይዘን በደስታ እንቀርባለን 📖 ወደ ኤፌሶን 5 20፤ ሁልጊዜ ስለ ሁሉ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምላካችንንና አባታችንን ስለ ሁሉ አመስግኑ።

የተከበራችሁ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እስካሁን ባለው የአሰባሰብ እንቅስቃሴ እሰከ ዛሬው ቀን ሰኞ ድረስ እግዚአብሔር ረድቶን ለ100 ቤተሰብ መሰብሰብ ችለናል ቀጣይ በሚኖረን ሳምንት የቀሪውን 50 ቤተሰብ እንደምንሰበስብ አምነን ጉዞአችንን እንቀጥላለን

የኢትዮጵያ ካቶሊክ ካሪዝማቲክ ሪኒዋል ማህበር ስጦታቸውን በማስረከብ ላይ!
የኢትዮጵያ ካቶሊክ ካሪዝማቲክ ሪኒዋል ማህበር ስጦታቸውን በማስረከብ ላይ!

የካቶሊክ ካሪዝማቲክ ሪኒዋል ተወካዮች ስጦታቸውን ለአ.አ ሃገረ ስብከት ካቶሊክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጊዜያዊ የምግብ ማከማቻ ክፍል ሲያስረክቡ። ክቡር አባ ጴጥሮስ በርጋ በሃገረ ስብከቱ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስም
የካቶሊክ ካሪዝማቲክ ሪኒዋል ተወካዮች ስጦታቸውን ለአ.አ ሃገረ ስብከት ካቶሊክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጊዜያዊ የምግብ ማከማቻ ክፍል ሲያስረክቡ። ክቡር አባ ጴጥሮስ በርጋ በሃገረ ስብከቱ ጠቅላይ ጽ/ቤት ስም ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል። ሌሎች መንፈሳውያን ማህበራትና በጎ ፍቃድ ያላቸው ምዕመናን ይህንን የፍቅር ስራ አርዓያ እንዲከተሉ ጥሪ አቅርበዋል።

እግዚአብሔር ይመስገን በጣም ጥሩ የመስጠት የአምልኮ ፕሮግራም ዛሬም አድርገናል በሁለቱ ቀናት ለ 90 ቤተሰብ የሚሆን ቁሳቁስ አግኝተናል ቀጣዩ ቀሪ ጉዞ በቀሪው አንድ ሳምንት እንደምንሰበስብ እናምናለን !!!

ዛሬ ሚያዝያ 4 የሆሳዕና የበዓል ቅዳሴ ጠዋት በቲቪ ስለሚተላለፋ የመሰብሰቢያ ሰዓታችን የሚሆነው ከቀኑ 7:30 እስከ 10:30 ይሆናል።

ዛሬም የመስጠት አምልኮአችን ይቀጥላል ዛሬ ሚያዝያ 4 በሚኖረን የመስጠት የአምልኮ ግዜ ቀሪውን በገንዘብም ይሁን በቁሳቁስ ለመሰብሰብ እቅድ ይዘናል በመድሀኒዓለም ቅጥር ግቢ ውስጥ በዚህም መሰረት ለመርዳት እየፈለጋችሁ ከአቅም በላይ ሆኖባችሁ ከቤት መውጣት ላልቻላችሁ እቤት ድረስ መጥተን የምንሰበስብ ይሆናል ለምታደርጉት ማንኛውም ድጋፍ እግዚአብሔር ይስጥልን ።